fa
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

رفتن به کانال در Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

نمایش بیشتر
3 306
مشترکین
-224 ساعت
-107 روز
-3830 روز
آرشیو پست ها
#ራእየ ዮሐንስ « በዮሐንስ ራእይ የሚገኙ ምስጢራት እንደ ቃላቱ የበዙ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ቃል ጥልቅ የሆነ ምስጢር በውስጡ አዝሏል፡፡ ይህም ስለ መጽሐፉ ልንሰጠው ከሚገባው የከበሬታ ስፍራ ትንሹ ነ
#ራእየ ዮሐንስ « በዮሐንስ ራእይ የሚገኙ ምስጢራት እንደ ቃላቱ የበዙ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ቃል ጥልቅ የሆነ ምስጢር በውስጡ አዝሏል፡፡ ይህም ስለ መጽሐፉ ልንሰጠው ከሚገባው የከበሬታ ስፍራ ትንሹ ነው፡፡ እያንዳንዱ ቃል የያዘው ምስጢር እጅግ ብዙ በመሆኑ ለእርሱ የሚኖረን ምስጋና ከሚገባው በታች ነው፡፡ እኔ ለምረዳውም ሆነ ለማልረዳው ለእያንዳንዱ ቃል ምስጋና አቀርባለሁ፡፡›› #ቅዱስ ሄሮኒመስ ‹‹ እኔ ከማስበው በላይ ብዙ ሐሳቦችን አምቆ የያዘ ቢሆንም በብዙ መልኩ ታላላቅ ምስጢሮችን መያዙን ተረድቻለሁ፡፡ ለመረዳት ያለኝ አቅም ትንሽ ቢሆንም ከቃላቱ ባሻገር ጥልቅ ምስጢር መያዙን ግን አምናለሁ። እኔ በምረዳው ያህል ዐረፍተ ነገሮችን ለመተርጎም ወይንም ይህ ነው ብዬ ለመናገር አልችልም፤ በየዋሕነት እና በእምነት እንዲሁ እቀበለዋለሁ እንጂ፡፡ ለአእምሮ የተደላደለ እና ተስማሚ ሆኖልኛል፤ እናም ያልተረዳሁትን ነገር አልቃወመውም፤ አደንቃለሁ እንጂ።›› #የእስክንድርያ ፓትርያርክ ዲዮናስዮስ ◍ይኽ እጅግ ተፈላጊ መጽሐፍ ሀርድ ከቨር ሲኾን የተወሰኑ ቅጂዎች ብቻ የቀሩት በመኾኑ እንዳያመልጥዎ እነኾ ጋብዘንዎታል።   ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥ #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳምና_ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ ፨ ታቦቱ_ሥላሴ፥ ፨ ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ፥ ፨ የገዳሙ ስም ማኅበረ ሥላሴ፡፡ ፨ በየቀኑ በሁሉም ቤክ በቅዳሴ ላይ ስሙ የሚነሳው ገናናው ገዳም (ብዙዎች ግን የማያውቁት)፡፡ ፨ እንኳን ሰዉ ከብቱ ሥርዐት ያለው ድንቅናዕፁብ ገዳም፡፡ ፨ ገዳሙን ያጠፉ አውሮፕላኖችን በጸሎት የከሰከሱ አባቶች የሚገኙበት የበርካታ ትምህቶችና የጥበብ ማዕክል፤ …. ኢትዮጵያውያን ሁሉ ቢያንስ አንዴ ሊያዩት የሚገባ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ገዳም!!!፡፡ ፨ በዚህች በየካቲት 27 እለት ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወመነኰሳት (ለአቡነ ክፍለ ማርያም፥ ለአቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘቋራ፥ ለ፯ቱ ዘሥላሴ በመባል ለሚጠሩ ቅዱሳን፣ ለዐርከ ሥሉስ /የአርኬና የመልክአ ቊርባን ደራሲ/፤ ….) የኾኑትና ፤ ጽድቃቸውና ቃልኪዳናቸው እንደ ምድር አሸዋ የበዛው፥ እንደ ሰማይ ከዋክብት ለመቊጠር የሚያስቸግረው ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ዘማኅበረ ሥላሴ ልደታቸውም እረፍታቸውም ነው፡፡ - እኒህ ጻድቅ የተወለዱት በጎጃም(ሸዋም የሚሉ አሉ) ሲኾን፤ የተወለዱትም ሆነ 104ዓመታት ከኖሩ በኋላ ያረፉበት ቀን በመድኀኔ ዓለም ወርኀዊ በዓል በየካቲት 27 ነው፡፡ - ጻድቁ በተለያዩ ገዳማት በአርድእትነትና ሥርዐተ አበው በማጥናትና በመተግበር ከቆዩ በኋላ፤ ምንኩስናን ከአቡነ ተንሥአ ክርስቶስ ዘትግራይ ተቀብለዋል፤ ኋላም ወደ ታላቁ ገዳም ገዳመ ዋሊ (ገዳመ ዋልድባ) ገብተው ከቆዩ በኋላ ወደ ገዳመ አስቄጥስ በመሄድ ለ18 ዓመታት ከቆዩ በኋላ በስተመጨረሻ ምናኔያቸውን በማኅበረ ሥላሴ አድርገዋል፡፡ * በ1616ዓ.ም. ሱስንዮስ 8,000 ክርስቲያኖችን የካቶሊክን ካልተቀበላችሁ ብሎ ጠዳ ላይ በሰየፈ ጊዜ ሳይፈሩና ሳይፍሩ ለሃይማኖታቸው ከተከራከሩና ጠበቃ ከኾኑት መካከል ግንባር ቀደሙ ናቸው፡፡ (ሌሎችም ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ፣ እኅተ ጴጥሮስ፣ ፍቅርተ ጴጥሮስ፣ ሐራ ድንግል ምዕመነ ድንግል አብረው ይጠቀሳሉ)፡፡ እነዚህም ቅዱሳን ሐዘናቸውን ወደ ፈጣሪያቸው በማድረሳቸው ሱስንዮስ ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ (ተቀሰፈ)፡፡ -  የሱስንዮስ ልጅ ፋሲልም አባቴን ይፈውሱልኝ ብሎ መልእክትን ላከ፤ ጻድቁ ዐምደ ሥላሴና አባ ምዕመነ ድንግል ዘጩጊ ማርያም ተገኝተው ካቶሊክነቱን ከተወ እሺ ብለው 3ት ሱባኤ ጸልየው ፈወሱት፤ ሱስንዮስም ንሥሐ ገብቶ ቅዱስ ቊርባንን ተቀበለ፡፡ በሰኔ 21 1624ዓ.ም. ‹‹የእስክንድርያ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ይመለስ፥ የሮም ካቶሊክ ሃይማኖት ይፍለስ፥ ልጄ ፋሲል ይንገሥ›› ብለው አዋጅ ነገሩ፤ ልጃቸው ፋሲልንም ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ቅብዓ መንግሥት (አፈዋተ መንግሥት) ቀብተው አነገሡት፤ ንጉሡም ለገዳሙ የእርሻ መሬት የሚሆን ጣቁሳ ላይ 44ት ጉልት ጐለተ፥ የገዳሙንም ስም ‹‹ማኅበረ ሥላሴ›› ብሎ ሰየመው፡፡ - ታላቁ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ቀድሞም ከእርሳቸው በፊት የነበረ ቢኾንም፤ በተለያዩ ዘመናት በጠላት የጠፋ ስለነበረ ዳግመኛ ያስፋፉትና እንደ መሶብ ያስባረኩት ናቸው፤ - ከወለዷቸው አንዱ ዐርከ ሥሉስ ከደረሳቸው አንዱ በኾነው በመልክአ ቊርባን ላይ፤ ‹‹ሰላም ለክሙ ጻድቃነ ዛቲ ዕለት ኵልክሙ፤ ዕድ ወአንስት በበአስማቲክሙ፡፡ ቅዱሳነ ሰማይ ወምድር ማኅበረ ሥላሴ አንትሙ፤ ዝክሩነ በጸሎትክሙ በእንተ ማርያም እሙ፤ ተማኅጸነ ለክርስቶስ ሥጋሁ ወደሙ፡፡ በማለት የደረሱለት ሲኾን፤ በዚህም በየቀኑ በቅዳሴ ላይ ከቊርባን በፊት የማኅበሩን ስም የማይጠራ ቤተ ክርስቲያን የለም፡፡ ፨ ብፁዕ አባ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ንብረቱ ገዳም ውስተ ሀቌሁ ቅንአቱ ዘአዲም ያስተጋብእ ጽድቀ ዘእምኵሎሙ ቅዱሳን በጾም ወበጸሎት ሀለወ በክብር ወበሰላም፡፡ /መሐረነ አብ/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ (#የሺዎች_ማኅበር)፤ ፨ ምቅዋመ ሥላሴ፡፡ ፨ስለ ገዳሙ አጠቃላይ ሁኔታ፤ *ገዳሙ የሚገኘው በሀገራችን በመተማ በረሃ ደቡባዊ ክፍል፥ ከጎንደር በስተምዕራብ አቅጣጫ (132 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ) ሲሆን፤ ከአ.አ. 901ኪ.ሜ. ርቀት ላይ፤ ከደረቅ ዐባይ ቀበሌ በ4ት ሰዓት የእግር ጕዞ ይገኛል፡፡ የጣቁሳ የቋራና የሱዳን በረሓማው አከባቢዎችም ያዋስኑታል፡፡ *ከፀሐዩ ሐሩር ማየልና ከቆላነቱ የተነሣ ‹‹በደንጊያው ላይ ተልባ ያስቆላል›› እየተባለ የሚነገርለት ነው፡፡ የተለያዩ ዕፅዋትና አራዊት የሚገኙበትም ሲሆን ቦታው በብሔራዊ ደረጃ ጥብቅ ደን ነው፡፡ * የገዳሙ ይዞታ ከ19ሺህ 186 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሲሆን፤ በቦታ ስፋት የሚመስለው ዋልድባ (ዋሊ) ብቻ ነው፡፡ በዚህም ከሃገራችን ገዳማት 2ቱ ታላላቅ ገዳማት እጅግ በጣም ሰፋፊ ይዞታ ያላቸው ገዳማት ናቸው፡፡ * ገዳሙ በ፪ት ትላልቅ ወንዞች (በገንዳ ውኃና ሸንፋ ወንዝ) የተከበበ ነው፡፡ *ገዳሙ በሚገኝበት በረሃ ውስጥ 4ት ተራሮች(አምባዎች) ይገኛሉ፡፡ እነርሱም፤ ድባ(የማኅበረ ሥላሴ ገዳም ያለበት)፣ ከርከመች፣ ኩክቢና ጎርማስ ይባላሉ፡፡ *ገዳሙን በርቀት ሆነው የሚያዋስኑት ታላላቅ ገዳማትም፤ በሰሜን አቅጣጫ ደምጫ፥ በደቡብ ጋንጫ(ዋታሆ አቦ) ናቸው፡፡ *በገዳሙና በአካባቢው ከሚገኙት የተለያዩ ዕጽዋት መካከል (ሰርኪን፥ ሲና፥ የዕጣን ዛፍ/ዋልያ/፥ መቀር፥ ወርካ፥ ክርክራ፥ ሽመል) እና ሌሎችም ልዩ ልዩ ዕጽዋት የሚገኙበት ሲኾን፤ ከዱር አራዊት መካከልም (አንበሳ፥ ነብር፥ አጋዘን፥ ቶራ/ሚዳቋ/፥ ድኩላ፥ አሳማ፥ ጉሬዛ፥ ዝንጀሮ፥ ቀይ ጦጣ፥ የተለያዩ የእባብና የዘንዶ ዝርያዎች) ይገኙበታል፡፡

📖ፍትሐ ነገሥት ምን አለ? ፍትሐ ነገሥት በኢትዮጵያ በሕገ መንግሥትነት ጭምር ለዘመናት ያገለገለ ትልቅ ዋጋ ያለው መጽሐፍ ነው:: ፍትሕ መንፈሳዊና ፍትሕ ሥጋዊ በሚል የተከፈለው ይህ የቤተ ክርስቲያ
📖ፍትሐ ነገሥት ምን አለ? ፍትሐ ነገሥት በኢትዮጵያ በሕገ መንግሥትነት ጭምር ለዘመናት ያገለገለ ትልቅ ዋጋ ያለው መጽሐፍ ነው:: ፍትሕ መንፈሳዊና ፍትሕ ሥጋዊ በሚል የተከፈለው ይህ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጥንታዊ ሀብት በሀገራችን ለሕግ ሙያ ፈር ቀዳጅ ሲሆን ዘመናዊው የሕግ ሙያ የሚፈለገውን የሕግ ትንታኔም ጭምር ቀድሞ በመረዳት የራሱ ትርጓሜ ቤት ያለው ጥልቅ የትምህርት ዘርፍ ነው:: በታሪክም የፍትሐ ነገሥት ሊቃውንት ነገሥታቱን በማማከርና በፍርድ ሒደትም ላይ በንቃት በመሳተፍ ሀገር ሲያስተዳድሩ ኑረዋል:: በዚህ የትርጓሜ ትምህርት ቤት ያለፉ ሊቃውንት ወደ ዘመናዊው የሕግ ትምህርት ዘርፍ ሲገቡም መምህራኖቻቸውን የሚቀድሙና የሕጉን አቅጣጫ ቀድመው የሚያስቡ እንደ እሳት የማይጨበጡ ተማሪዎች የሚሆኑት በትርጓሜ ቤቱ ሞረድነት የተሳለ ብሩሕ ሕሊና ስላላቸው ነው:: ◍ የፍትሐ ነገሥትን መንፈሳውያት አናቅጽ የተረጎሙበት ይህ መጽሐፋቸው ለማንኛውም አንባቢ በሚገባ አገላለጽ ከትርጓሜ ቤቱ ጥልቅ ትምህርት በተጨማሪ የራሳቸውን ብሩሕ አተያይና ማስተዋል የሚያሳዩ አስደናቂ ምሥጢራትንና ዘመንን የሚዋጁ መፍትሔዎችን በውብ ብርዕ አስቀምጠውልናል:: ረቂቁን በተመለከትሁ ጊዜ እንዲህ ዘመኑን የዋጀ ሥራ ከሊቃውንት ጎራ መፍለቁን አይቼ "ዘልብየ በጽሐ" (የልቤ ደረሰ) ብዬ ፈጣሪን እያመሰገንሁቀጣዩን ሥራቸውን በናፍቆት እየጠበቅን ፍትሐ ነገሥትን ከጥሩ ምንጭ እንጠጣ እላለኹ። ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት  በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

በቀደምት ጀግኖች አያቶቻችን ታላቅ ተጋድሎ እና መስዋዕትነት እንዲሁም በታላቁ ታሪክ የማይረሳው ንጉሳችን ዳግማዊ አጤ ምንሊክ እና በእቴጌ ጣይቱ ብጡል ብልህ አመራር እና አስተባባሪነት ለተቀዳጀነው አ
በቀደምት ጀግኖች አያቶቻችን ታላቅ ተጋድሎ እና መስዋዕትነት እንዲሁም በታላቁ ታሪክ የማይረሳው ንጉሳችን ዳግማዊ አጤ ምንሊክ እና በእቴጌ ጣይቱ ብጡል ብልህ አመራር እና አስተባባሪነት ለተቀዳጀነው አንፀባራቂው የ፻፳ ወ፱ኛው የአድዋ ድል በዓል እንኳን አደረሳችሁ የሚል መልዕክቴን ሳስተላልፍ በታላቅ ብሔራዊ ኩራት ነው:: ይህ በታሪክ ተመዝግቦ በየአመቱ የምንዘክረው አድዋ ላይ የተቀዳጀነው ድል የኢትዮጵያን ነፃነት ያስከበረ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ የቅኝ ግዛት ቀንበር ተጭኗቸው ሲሰቃዩ ለነበሩ አፍሪካዊያን ወንድም እና እህቶቻችን እንዲሁም በመላው አለም በጭቆና ውስጥ የነበሩትን ጥቁር ህዝቦች ቀና ብለው እንዲሄዱ እና ነፃ እንዲወጡ በወቅቱ ታላቅ መነቃቃትን የፈጠረ ገናና የጥቁር ህዝቦች ድል ነው። የዘንድሮውን የ፻፳ ወ፱ ኛው የአድዋ ድል በአል ስናከብር ሀገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ቀላል ለማይባሉ አመታት አንድነቷን አስጠብቃ ወደ ፊት እንዳትራመድ ሰቅዞ የያዛትን ተከታታይ የብሔር ፖለቲካ አዙሪት እንደ ሀገር እና እንደ ህዝብ ያስከፈለንን እና እያስከፈለን ያለውን ዋጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ካለንበት ውስብስብ እና እጅግ ኋላቀር የዘር ፖለቲካ ለመውጣት ከመቼውም ጊዜ በላቀ አንድነታችንን አስተባብረን የህልውናችን መሰረት የሆነችው እናት ሀገራችንን ለማዳን በንቃት መቆም ይጠበቅብናል። ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ግዮን መጻሕፍት

📖ኰኲሐ ሃይማኖት 【ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】 ✍️...በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተ
📖ኰኲሐ ሃይማኖትወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】 ✍️...በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተኛ ለማስመሰል በጻፍከው ስሕተት የምእመናንን ልቡና ይሆንን? አይሆንን? ከሚል ጥርጥር ላይ ስለጣልከው እኔም “ይነግረው ያጣ ያሙኝ አይመስለውም” እንደሚባለው ተረት ዝም ብንልህ ጥፋትህ እየቀጠልክ ስለሔድክ ለምእመናን ነገርህ እውነት ይመስላቸዋል በማለት “ገሥጽ ወተዛለፍ” ያለው ቃል እያጽናናኝ (፪ጢሞ. ፬÷፪) መልሱን ስጽፍልህ ያመላለሱ ዘዴ እያስገደደኝ በማደርገው ንግግር አንዳንድ ላይ “ባርክዎሙ ለእለ ይረግሙክሙ” የተባለው ትእዛዝ ሳይፈርስብኝ የቀረ አይመስለኝምና የሰውን መዳኑን እንጂ መጎዳቱን የማይወድ ቸሩ አምላክ ኹላችንንም ይቅር ብሎ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያገናኝን፡፡ አሜን፡፡ [ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰደ] 🫧መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ሊቅ ረቂቅ የሃይማኖት አርበኛ መኾናቸው ዛሬም በመጻሕፍቶቻቸው፤ ሲወሳ፤ ሲመሰከር ፤ትውልድ ሲሻገር ይኖራል። በእቅበተ እምነት ዙሪያም ይኽ ነው የማይባል አሻራ አኑረውልናል ።ከድንቅና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቻቸው መካከል ለኘሮቴስታንቱ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ  ምላሽ የሰጡበት ኰኲሐ ሃይማኖት የተሰኘው መጽሐፋቸው በትህትና የተለበጠ በእውቀት የተጠረዘ መጽሐፍ መኾኑ መስካሪ የማያሻው እንዲኹም በዚኽ ዘመን ላለው የኑፋቄ ትምህርት እና ግርታ ውስጥ እየወደቀ ላለው ወጣት አይነተኛ መፍትሔ ይኽ መጽሐፍ እንደኾነ መገንዘብ አይከብድም። ©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት  በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖ኰኲሐ ሃይማኖት 【ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】 ✍️....በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነ
📖ኰኲሐ ሃይማኖትወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】 ✍️....በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተኛ ለማስመሰል በጻፍከው ስሕተት የምእመናንን ልቡና ይሆንን? አይሆንን? ከሚል ጥርጥር ላይ ስለጣልከው እኔም “ይነግረው ያጣ ያሙኝ አይመስለውም” እንደሚባለው ተረት ዝም ብንልህ ጥፋትህ እየቀጠልክ ስለሔድክ ለምእመናን ነገርህ እውነት ይመስላቸዋል በማለት “ገሥጽ ወተዛለፍ” ያለው ቃል እያጽናናኝ (፪ጢሞ. ፬÷፪) መልሱን ስጽፍልህ ያመላለሱ ዘዴ እያስገደደኝ በማደርገው ንግግር አንዳንድ ላይ “ባርክዎሙ ለእለ ይረግሙክሙ” የተባለው ትእዛዝ ሳይፈርስብኝ የቀረ አይመስለኝምና የሰውን መዳኑን እንጂ መጎዳቱን የማይወድ ቸሩ አምላክ ኹላችንንም ይቅር ብሎ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያገናኝን፡፡ አሜን፡፡ [ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰደ] 🫧መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ሊቅ ረቂቅ የሃይማኖት አርበኛ መኾናቸው ዛሬም በመጻሕፍቶቻቸው፤ ሲወሳ፤ ሲመሰከር ፤ትውልድ ሲሻገር ይኖራል። በእቅበተ እምነት ዙሪያም ይኽ ነው የማይባል አሻራ ያስቀመጡ መኾናቸው የአደደባባይ ምስርጢር መኾኑ አይረሴ ነው  ።ከድንቅና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቻቸው መካከል ለኘሮቴስታንቱ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ  ምላሽ የሰጡበት ኰኲሐ ሃይማኖት የተሰኘው መጽሐፋቸው በትህትና የተለበጠ በእውቀት የተጠረዘ መጽሐፍ መኾኑ መስካሪ አያሻውም ። ©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት  በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። #📚 ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

💧ዜና መጽሐፍ 【አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ】 📖ነገረ መላዕክት ቅዱሳን መላእክት በነገረ ድኅነት (በክርስትና) ከፍተኛ ሱታፌ ያላቸው የእግዚአብሔር ናቸው፡፡ ሰማያውያን ፍጥረቱ ስለተፈጥሮአቸው፧ አገል
💧ዜና መጽሐፍ 【አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ】 📖ነገረ መላዕክት   ቅዱሳን መላእክት በነገረ ድኅነት (በክርስትና) ከፍተኛ ሱታፌ ያላቸው የእግዚአብሔር ናቸው፡፡ ሰማያውያን ፍጥረቱ ስለተፈጥሮአቸው፧ አገልግሎታቸው፧ _ ኃይላቸው፧ _ ቅድስናቸው፧ ምስጋናቸው፧ አማላጅነታቸው፥ ረዳትነታቸው፥ ወዘተ. . . በብሉይ ኪዳን፥ በሐዲስ ኪዳንም ሆነ በአዋልድ መጻሕፍት በብዙ ተጽፎ ይገኛል። ነገር ግን በዘመናችን ብዙ ትኩረት ካልተሰጣቸው ርዕሶች አንዱ "ነገረ መላእክት" ነው እላለሁ፡፡ ይህም ክፍተት ቁጥሩ ጥቂት የማይባል ሰው ስለጉዳዩ የመሰለውን እንዲያስተምር በር ሳይከፍት አልቀረም። ፈቃደ እግዚአብሔር ሁኖ እነሆ ይህንን ክፍተት ይሞላል ብዬ የማምንበት መጽሐፍ ተዘጋጅቷል። መጽሐፉ ስለ ንጹሐን መላእክት እና ተያያዥ ጉዳዮች በከፍተኛ ጥንቃቄና ማስተዋል ከመዘጋጀቱ ባሻገር፥ በየዘመናቱ እየተነሱ ለአማኞች ፈተና ለሆኑ ርዕሶች ኦርቶዶክሳዊ መልስን ይዟል። ከዚህ በፊት ባዘጋጇቸው መጻሕፍት ያልተዳሰሱ ይዘቶች ላይ ትኩረት እንደሚያደርጉ የተመለከትናቸው መምህር ዲበ ኵሉ ሰንደቄ፤ ንባብ ከሐተታ፡ ትርጓሜ ከምስጢር፧ ትምህርትንም ከእዝናት (ሞክር) አሰናስለው ይህንን የመሰለ መጽሐፍ ስለጻፉልን እያመሰገንኹ፧ አንብበን እንጠቀምበት ዘንድ በአክብሮት እጋብዛለሁ። መልካም ንባብ! [ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ] ታላቁን ጾም በንባብ ለማሳለፍ አይነተኛ ምርጫ እነኾ ፦በጣም በሚገርም ይዘት በልዩ አጻጻፍ በጥልቅ መረዳት እንዲኹም  ለማንበብ በሚያጓጓ ኹኔታ #መምህር ዲበኩሉ ሰንደቄ  ያዘጋጁልንን #ይኽን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል ። #📚 ግዮን መጻሕፍት ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ዜና መጻሕፍት 【ከውስጥ ገጽ የተቀነጨበ 】 ❝.....አንደ እባብ ልባሞ መሆን ማለት ምን ማለት ነው? አባብ ሲጠቃ ጭንቅላቱን እስካዳነ ድረስ፣ አካሉ ቢቆረጥም አይሞትም። ስለዚህ እንደ እባብ ጠቢብ መ
ዜና መጻሕፍት ከውስጥ ገጽ የተቀነጨበ ❝.....አንደ እባብ ልባሞ መሆን ማለት ምን ማለት ነው? አባብ ሲጠቃ ጭንቅላቱን እስካዳነ ድረስ፣ አካሉ ቢቆረጥም አይሞትም። ስለዚህ እንደ እባብ ጠቢብ መሆን ማለት አምነትህን እስካዳንክ ድረስ ሁሉንም ነገር ለማጣት ፈቃደኛ መሆን ማለት ነው። ሀብትህን፣ ስምህን፣ ጓደኞችህን ማጣት ማለት ነው። እውነትን ሁሉ የምትማርበት አምነትህ፣ራስህ ነው። በዚህም አውነት ነፍስህ ነፃ ትወጣለች።❞ ⩩ታላቁን ጾም መዝለቂያ ይኾኑ ዘንድ እኚኽ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት ደስ በሚል አዘገጃጀት ቀርበውልናል በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል ። #📚 ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ኪዳነ ምሕረት በድንቅ ጥበቡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ያደነው እጅጉን መሐሪ ስለሆነ ነው፡፡ የቀደሙት የብሉይ ኪዳን ኪዳናት ሕዝቡን ከሲኦል መታደግ አልቻሉም ነበር፡፡ ፍጹም የሆነው ኪዳን የተደረገው በሰባተኛው ኪዳን ይህም ለሰው ዘር ምሕረትን ባስገኝች በንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ነው፡፡     የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠችውን እናታችንንም ‹‹ኪዳነ ምሕረት›› እያልን የምንማጸናት ለዚህ ነው፡፡ ለአዳም የተገባለት የምሕረት ቃል በእርሷ ተፈጽሟልና፡፡ እመቤታችን አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ወልዳዋለችና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራን ተቀብሎ እንዲሁም በመስቀል ተሰቅሎ ዓለምን ያዳነው ከእርሷ በነሣው ሥጋና ነፍስ ነውና፡፡     በነገረ ማርያም ተጽፎ እንደምናገኘው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት በኋላ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ልጇ መቃብር ቦታ ጎልጎታ እየሄደች ትጸልይ ስለ ነበር  በየካቲት ፲፮ ቀን በጸለየችው ጸሎት ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ ጸሎቷም እንዲህ የሚል ነበር፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ፥ ከሥጋዬ ሥጋ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በቻለችህ ማኅፀኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡››   ጌታችንም ምን ሊያደርግላት እንደምትሻ ሲጠይቃት በስሟ ለሚማጸኑ፣ መታሰቢያዋን ለሚያደርጉ፣ ለችግረኛ ለሚራሩ፣ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ለሚያንጹ፣ ዕጣን፣ ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን ለሚሰጡ ምሕረትን እንዲያደርግላቸው ጨምራ ጠየቀችው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በየካቲት ፲፮ ዕለት የገባላትን ቃል ኪዳን እንዲህ በማለት በመሐላ አጽንቶታል፡፡  ‹‹መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበአቡየ ወበመንፈስ ቅዱስ ሕያው፤ በራሴ፣ በአባቴ እና በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ፡፡››  የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠበት ይህ ዕለት ታላቅ ነውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቅት ታከብረዋለች፡፡ ቀድሞ ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነውና፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡   በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ የሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና ችግረኛ መርዳት ይገባናል፡፡   የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት፣ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን! 

✨💥አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ 📖የጽድቅ መንገድ [....ሰዎች በዚህ ዓለማዊ ሕይወት ላይ ኾነው ዘላቂ ያልሆነ ነገር ላይ ጊዜያቸውን ሲያጠፋ ማየት አጅግ ያሳዝናል፡፡ “ለሰውነቱ ስሚደክም ሰው ትርፉ
✨💥አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ 📖የጽድቅ መንገድ [....ሰዎች በዚህ ዓለማዊ ሕይወት ላይ ኾነው ዘላቂ ያልሆነ ነገር ላይ ጊዜያቸውን ሲያጠፋ ማየት አጅግ ያሳዝናል፡፡ “ለሰውነቱ ስሚደክም ሰው ትርፉ ምንድነው?" (መክ. 5፥16) የዓለም ነፋስ _ ለአንድ ሰው ሙላትን ሊያመጣ ይቻለዋልን? ነፋስ ከአቧራ በቀር ወርቅን ይዞ ሊመጣ ይችላልን? የዓለሞ ጥጋብ በስተመጨረሻ ሆዳችን ተነርቶ አንዲፈነዳ እነጂ ጠግበን አንድንረካ አያደርግም፡፡ ዓለም በሚሰጠን ጥጋብ ውስጥ ብስጭት እና እርካታ ማጣት ተሸሽገው እንደሚኖሩበት መርሳት የለብንም፡፡ ዓለማዊ ደስታዎች በጀረት ላይ አንደሚንሳፈፍ አረፋ ጊዜያዊ ናቸው። ጻድቅ ሰው ግን የማይለዋወጥ እና የጸና እንክብካቤን እንዴት ማግኘት እንደሚችል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ይህም ከአግዚአብሔር ዘንድ እንደሚገኝ ያውቃል!!!] ©ከመጽሐፉ የተወሰደ "ታላቁ መምህር አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ከክርስቲያን ቤተሰብ ተወልደው፣ በሐቀኛ ክርስቲያናዊ መንገድ ተምረውና አስተምረው ከዚያም ወደ በረሃ ወርደው መንፈሳዊ ተጋድሎን በእውነት የኖሩት እኒህ አባት፣ የጵጵስና ሹመታቸው ለግብፅ ቤተክርስቲያን ብቻ ይሁን እነጂ የመንፈስ ፍሬያቸው ግን ለመላው ዓለም ነበር። .. ከዚህ ቀደም ጠይቁ ይመልስላችኋል፣ ሰይጣንን አስርቡት፣ ትምህርተ ሺኖዳ፣ አቡነ ሺኖዳ _ መልስ _ አላቸው የተሰኘ ተወዳጅ መጻሕፍቶቻቸውን በጥንቃቄ ተርጉመውና በጥራት አትመው አቅርበውልን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ይህን «የጽድቅ መንገድ» የተሰኘ መጽሐፍ እነሆ ብለውናል ።መጽሐፉን #📚በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል ። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖ኦሪት ዘፍጥረት ✍..ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ ፍጥረት፣ ...መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተርጉማን ትኩ
📖ኦሪት ዘፍጥረት ✍..ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ ፍጥረት፣ ...መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተርጉማን ትኩረት ሰጥተው በስፋትና በጥልቀት ካብራሯቸውና ከተረጎሟቸው ቅዱሳት መጻሕፍት አንዱ ነው፡፡ እኔ ያደረግሁት ከእነዚህ የተለያዩ አባቶች፣ ሊቃውንት እና መተርጉማን ሐሳቦች መካከል የተወሰኑትን አሰባስቦ ማቅረብ ነው፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር በተከታታይ ከቀረበው የኦሪት ዘፍጥረት ማብራሪያ ትምህርት የመጀመሪያዎቹ ዐሥር ምዕራፎች ትምህርት (ከምዕራፍ 1 -10) በዚህ መጽሐፍ ቀርቧል፡፡ #መምህረ ቤተ ክርስቲያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ...በእርግጥ የግሩምነቱን ያኽል ብዙዎቻችን እጅ እንዳልገባ ግልጽ ነው።እንግዲያስ  ምን እንጠብቃለን  ይኽን የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ ፍጥረት፣ ...መሠረት ላይ ትንተና በማድረግ በጥልቅ መረዳት የተጻፈውን ይኽን ግሩም መጽሐፍ አንብበን እንጠቀምበት ዘንድ... #"በመምህረ ቤተ ክርስቲያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ "ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲኾን  መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል#📚 ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖ኦሪት ዘፍጥረት ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ ፍጥረት፣ ...መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተርጉማን ትኩረት
📖ኦሪት ዘፍጥረት ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ ፍጥረት፣ ...መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተርጉማን ትኩረት ሰጥተው በስፋትና በጥልቀት ካብራሯቸውና ከተረጎሟቸው ቅዱሳት መጻሕፍት አንዱ ነው፡፡ እኔ ያደረግሁት ከእነዚህ የተለያዩ አባቶች፣ ሊቃውንት እና መተርጉማን ሐሳቦች መካከል የተወሰኑትን አሰባስቦ ማቅረብ ነው፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር በተከታታይ ከቀረበው የኦሪት ዘፍጥረት ማብራሪያ ትምህርት የመጀመሪያዎቹ ዐሥር ምዕራፎች ትምህርት (ከምዕራፍ 1 -10) በዚህ መጽሐፍ ቀርቧል፡፡ በእርግጥ የግሩምነቱን ያኽል ብዙዎቻችን እጅ እንዳልገባ ግልጽ ነው።እንግዲያስ  ምን እንጠብቃለን  ይኽን የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ ፍጥረት፣ ...መሠረት ላይ ትንተና በማድረግ በጥልቅ መረዳት የተጻፈውን ይኽን ግሩም መጽሐፍ አንብበን እንጠቀምበት ዘንድ... #"በመምህረ ቤተ ክርስቲያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ "ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲኾን  መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል#📚 ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖ዐይነ ልቡና ✍️...❝እኔ በዘመኔ ትውልድ እንድኮራ ከሚያደርጉኝ ወጣት አገልጋዮች አንዱ መምህር ዮሐንስ ነው። በትምህርተ ጽድቅ መጽሐፉ ብዙ ነፍሳትን ወደ እውነተኛው ትምህርት እጃቸውን ይዞ መር
📖ዐይነ ልቡና ✍️...❝እኔ በዘመኔ ትውልድ እንድኮራ ከሚያደርጉኝ ወጣት አገልጋዮች አንዱ መምህር ዮሐንስ ነው። በትምህርተ ጽድቅ መጽሐፉ ብዙ ነፍሳትን ወደ እውነተኛው ትምህርት እጃቸውን ይዞ መር ቷል ዛሬ ደግሞ ዓይነ ልቡናችንን የሚያበራ በኦርቶዶክሳዊ የአበው አስተምህሮ የተቃኘ ትምህርት ያለበት መጽሐፍ ይዞልን በመምጣቱ ለገበሬ ዘርን ለእነስሳ ሳርን የሚሰጥ አምላክ ለመምህራንም በየጊዜው የሚጽፉትን የሚያስተምሩትን አይከለክልምና ሞገስ እንዲሆኑን በንጥረ መባርቅት አምሳል በቤተ ክርስቲያን ሰማይ ላይ ሲገልጣቸው ሳይ ደስ ይለኛል። ከሰማይ በታች ያሉ ምዕመናንን የሚያስደነግጥ ሳይሆን የሚያንፅ ሆኖ ስላገኘሁት እሳት መስሎ ቢታያችሁ እነደ ኢሳይያስ ከንፈራችሁን የሚ ያነጻ እንጅ የሚያቃጥል እሳት ስላልሆነ ከናፍረ ምዕመናንን ያነጻ ዘንድ የተገለጠ መጽሐፍ መሆኑን ባነበብሁት ወቅት ተረድቻለሁና እነሆ በሃይማኖቱ ኦርቶዶክሳዊ፣ በትውልዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ በነገዱ ቄርሎሳዊ፣ በግብሩ ዐቃቤ ልቡና መሆኑን ለማስረዳት ምስክር ሆኜ መጥቻለሁ ምስክርነቴን ከተቀበላችሁኝ ከአበው ትምህርት የተወለደ ለመሆኑ እናንተም ሩቅ ሳትሄዱ የአነጋገሩን ለዛ ስታዩት ብሔረ ሙላዱ መጻሕፍት፣ አባቶቹ ሊቃውንት መሆናቸውን እንደምታረጋግጡ ያለኝን እምነት እየገለጽሁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ብቻ ሳይሆኑ በኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ላይ ያልጠራ አመለካከት ያለው ሁሉ ቢያነበው ምኞቴ መሆኑንእገልጻለኹ❞።በማለት#ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ፤የጋበዙንን እንዲኹም የትምሕርተ ጽድቅ ቅጽ ኹለት በመኾኑ በትምሕርተ ጽድቅ የተደመምን አኹንም ይኽን መጽሐፍ በማንበብ እንታነፅ ዘንድ በጥልቀት የተዘጋጀ ሲኾን 📚መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል📚ግዮን መጻሕፍት መደብር ይደውሉልን !📞፦0913083816

📖ዐይነ ልቡና ✍️...❝እኔ በዘመኔ ትውልድ እንድኮራ ከሚያደርጉኝ ወጣት አገልጋዮች አንዱ መምህር ዮሐንስ ነው። በትምህርተ ጽድቅ መጽሐፉ ብዙ ነፍሳትን ወደ እውነተኛው ትምህርት እጃቸውን ይዞ መር
📖ዐይነ ልቡና ✍️...❝እኔ በዘመኔ ትውልድ እንድኮራ ከሚያደርጉኝ ወጣት አገልጋዮች አንዱ መምህር ዮሐንስ ነው። በትምህርተ ጽድቅ መጽሐፉ ብዙ ነፍሳትን ወደ እውነተኛው ትምህርት እጃቸውን ይዞ መር ቷል ዛሬ ደግሞ ዓይነ ልቡናችንን የሚያበራ በኦርቶዶክሳዊ የአበው አስተምህሮ የተቃኘ ትምህርት ያለበት መጽሐፍ ይዞልን በመምጣቱ ለገበሬ ዘርን ለእነስሳ ሳርን የሚሰጥ አምላክ ለመምህራንም በየጊዜው የሚጽፉትን የሚያስተምሩትን አይከለክልምና ሞገስ እንዲሆኑን በንጥረ መባርቅት አምሳል በቤተ ክርስቲያን ሰማይ ላይ ሲገልጣቸው ሳይ ደስ ይለኛል። ከሰማይ በታች ያሉ ምዕመናንን የሚያስደነግጥ ሳይሆን የሚያንፅ ሆኖ ስላገኘሁት እሳት መስሎ ቢታያችሁ እነደ ኢሳይያስ ከንፈራችሁን የሚ ያነጻ እንጅ የሚያቃጥል እሳት ስላልሆነ ከናፍረ ምዕመናንን ያነጻ ዘንድ የተገለጠ መጽሐፍ መሆኑን ባነበብሁት ወቅት ተረድቻለሁና እነሆ በሃይማኖቱ ኦርቶዶክሳዊ፣ በትውልዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ በነገዱ ቄርሎሳዊ፣ በግብሩ ዐቃቤ ልቡና መሆኑን ለማስረዳት ምስክር ሆኜ መጥቻለሁ ምስክርነቴን ከተቀበላችሁኝ ከአበው ትምህርት የተወለደ ለመሆኑ እናንተም ሩቅ ሳትሄዱ የአነጋገሩን ለዛ ስታዩት ብሔረ ሙላዱ መጻሕፍት፣ አባቶቹ ሊቃውንት መሆናቸውን እንደምታረጋግጡ ያለኝን እምነት እየገለጽሁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ብቻ ሳይሆኑ በኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ላይ ያልጠራ አመለካከት ያለው ሁሉ ቢያነበው ምኞቴ መሆኑንእገልጻለኹ❞።በማለት#ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ፤የጋበዙንን እንዲኹም የትምሕርተ ጽድቅ ቅጽ ኹለት በመኾኑ በትምሕርተ ጽድቅ የተደመምን አኹንም ይኽን መጽሐፍ በማንበብ እንታነፅ ዘንድ በጥልቀት የተዘጋጀ ሲኾን 📚መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል📚ግዮን መጻሕፍት መደብር ይደውሉልን !📞፦0913083816

📖ዐይነ ልቡና ✍️...❝እኔ በዘመኔ ትውልድ እንድኮራ ከሚያደርጉኝ ወጣት አገልጋዮች አንዱ መምህር ዮሐንስ ነው። በትምህርተ ጽድቅ መጽሐፉ ብዙ ነፍሳትን ወደ እውነተኛው ትምህርት እጃቸውን ይዞ መር
📖ዐይነ ልቡና ✍️...❝እኔ በዘመኔ ትውልድ እንድኮራ ከሚያደርጉኝ ወጣት አገልጋዮች አንዱ መምህር ዮሐንስ ነው። በትምህርተ ጽድቅ መጽሐፉ ብዙ ነፍሳትን ወደ እውነተኛው ትምህርት እጃቸውን ይዞ መር ቷል ዛሬ ደግሞ ዓይነ ልቡናችንን የሚያበራ በኦርቶዶክሳዊ የአበው አስተምህሮ የተቃኘ ትምህርት ያለበት መጽሐፍ ይዞልን በመምጣቱ ለገበሬ ዘርን ለእነስሳ ሳርን የሚሰጥ አምላክ ለመምህራንም በየጊዜው የሚጽፉትን የሚያስተምሩትን አይከለክልምና ሞገስ እንዲሆኑን በንጥረ መባርቅት አምሳል በቤተ ክርስቲያን ሰማይ ላይ ሲገልጣቸው ሳይ ደስ ይለኛል። ከሰማይ በታች ያሉ ምዕመናንን የሚያስደነግጥ ሳይሆን የሚያንፅ ሆኖ ስላገኘሁት እሳት መስሎ ቢታያችሁ እነደ ኢሳይያስ ከንፈራችሁን የሚ ያነጻ እንጅ የሚያቃጥል እሳት ስላልሆነ ከናፍረ ምዕመናንን ያነጻ ዘንድ የተገለጠ መጽሐፍ መሆኑን ባነበብሁት ወቅት ተረድቻለሁና እነሆ በሃይማኖቱ ኦርቶዶክሳዊ፣ በትውልዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ በነገዱ ቄርሎሳዊ፣ በግብሩ ዐቃቤ ልቡና መሆኑን ለማስረዳት ምስክር ሆኜ መጥቻለሁ ምስክርነቴን ከተቀበላችሁኝ ከአበው ትምህርት የተወለደ ለመሆኑ እናንተም ሩቅ ሳትሄዱ የአነጋገሩን ለዛ ስታዩት ብሔረ ሙላዱ መጻሕፍት፣ አባቶቹ ሊቃውንት መሆናቸውን እንደምታረጋግጡ ያለኝን እምነት እየገለጽሁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ብቻ ሳይሆኑ በኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ላይ ያልጠራ አመለካከት ያለው ሁሉ ቢያነበው ምኞቴ መሆኑንእገልጻለኹ❞።በማለት#ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ፤የጋበዙንን እንዲኹም የትምሕርተ ጽድቅ ቅጽ ኹለት በመኾኑ በትምሕርተ ጽድቅ የተደመምን አኹንም ይኽን መጽሐፍ በማንበብ እንታተፅ ዘንድ በጥልቀት የተዘጋጀ ሲኾን 📚መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል📚ግዮን መጻሕፍት መደብር ይደውሉልን !📞፦0913083816

# ከ መምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተገኙ እንቁ መጻሕፍት ©አነዚኽን ጣፋጭ ምግቦች ተመግበዋቸው ይኾን...? 📚#ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ እና # ቅዱስ ዮሐ
# ከ መምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተገኙ እንቁ መጻሕፍት ©አነዚኽን ጣፋጭ ምግቦች  ተመግበዋቸው ይኾን...? 📚#ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ እና # ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ #ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ ከሕይወቱ ቅምሻ [....አባ እለእስክንድሮስም አትናቴዎስን በመንበረ ፓትርያርኩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ሥርዓት እያስተማረ አሳደገው፤ እርሱም ተወዳጅ ልጅ ሆነው፡፡ ከዚሁም ጋር ሰዋስው፣ ፍልስፍና፣ ክሂሎተ ነቢብና ሌሎች በዘመኑ የነበሩ ትምህርቶችንም በሚገባ ተማረ፡፡ ቆይቶም ለመዓርገ ምንኵስና በቃ᎓᎓ በቅድስናው፣ በሞያውና በግብረ ገብነቱ እንከን የሌለው ወጣቱ አትናቴዎስ በ23 ዓመቱ ....] #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ ከሕይወቱ ቅምሻ [....ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ራሱን ከዚህ ዓለም የበለጠ ለመሰወርና ብቻውን ዘግቶ ለመኖር በመፈለጉ ወደ ዋሻ ውስጥ ገብቶ በብሕትውናና በጽኑ ትኅርምት ለሁለት ዓመት ሲጋደል ኖረ። በዚያም በትጋሃ ሌሊት፣ ለራሱ ዕንቅልፍ በመከልከል፣ በቀዊም፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቃል በማጥናት፣ በጸሎትና በተዘክሮ ኖረ በመቀጠልም ....] 【#ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ】 [..ሁሉም የሌሊት ቅዠቶች ኖረዋል፡፡ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ በመምጣቱ ከጨለማው ጋር አብረው የጠፉ ህልሞች ብቻ ነበሩ፡፡ ያለ መስሎ ታይቶ እንደጠፋ ጥላ፣ ወደ አየር ተኖ እንደጠፋ ጢስ፣ ሟሙቶ እንዳለቀ አረፋ፣ እንደተበጣጠሰ የሸረሪት ድር ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሁል ጊዜ ይህንን መንፈሳዊ መዝሙር እንዘምራለን፡- “ሁሉ ከንቱ፣ የከንቱ ከንቱ ነው” የሚለውን፡፡]›› 👉መጻሕፍቱን በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል ! ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖 " ማስያስ " ❝...ማስያስ የመጻሕፍት ሁሉ ማዕከላዊ የመጽሐፍ ራስ ሆኖ ቀርቦልናል። ስለዚህም በዲያቆን ሚክያስ አስረስ የተዘጋጀልንንና ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በዘመናት ሁሉ ለ
📖 " ማስያስ " ❝...ማስያስ የመጻሕፍት ሁሉ ማዕከላዊ የመጽሐፍ ራስ ሆኖ ቀርቦልናል። ስለዚህም በዲያቆን ሚክያስ አስረስ የተዘጋጀልንንና ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በዘመናት ሁሉ ለነበሩ አማኞቿ ስትመግበው የነበረውን ይህንን ምሥጢራዊ ትምህርት በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በጥሩ መንገድ ተዘጋጅቶ እናገኘዋለን። ዲያቆን ሚክያስ ከቤተ ክርስቲያን መምህራን ፍጻሜ፣ የሐዋርያት ስብከት ራስ፣ የሰማዕታት የሰማዕትነት አክሊል፣ ከተማረውና ሰፊ ሽፋን ካለው ንባቡ አዋሕዶ የነቢያት ትንቢት የጻድቃንም የምናኔያቸው ምሥጢርና የምድረ በዳ ተጋድሏቸው የምእመናንም እረኛቸው የካህናትም አለቃቸው፣ የአምልኮታቸው መዳረሻ፣ የቅዳሴያቸው ሊቀ ካህናት የመሥዋዕታቸውም ቊርባን የሆነውን ጌታ “ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ማስያስ ናይን ኪርያላይሶን” እያልን በሰሙነ ሕማማት ስግደታችንን በምናቀርብለት ስሙ ይዞልን መምጣቱ እጅግ ደስ ያሰኛል። መጽሐፉ ለኦርቶዶክሳዊ የዶክትሪን አስተምህሮ እንደ መነሻ ወይም መግቢያ በሚመስል አቀራረብ ለሁሉም አንባብያን እንዲሆኑ በተዘጋጁ መጻሕፍት ላይ እስካሁን ያላነበብኳቸውን አዳዲስ ምሥጢራት አካትቶ ቀርቦልናል። ስለዚህም ይህን ግሩም መጽሐፍ በማንበብ ጌታችን እንደመለሳቸው ደቀ መዛሙርት ልቡናችንን በሚያቃጥሉ የትርጓሜ ምሥጢራት መግበን ምዕራብ ወደተባለ ዐለምና ኃጢአት ከምናደርገው ጉዞ እንድንመለስና እንደ እንድርያስም ማስያስን/መሲሑን አግኝተናል ብለን ሌሎችን ወደ እውነተኛው መሲሕ ልንጠራበት ይገባናል።❞ ✍#ብርሃኑ አድማስ መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል ። 📦 ለውድ   አንባብያን ደግሞ ግዮን በአዲስ መልክ የስጦታ ፓኬጅ  ይዞ እየመጣ ነው   በቅርብ ቀን ይጠብቁ! ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖“ቃልኪዳን በነገረ ድኅነት” (በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ) ✍ቆየት ካሉ ነገር ግን እንደ መጽሐፉ ብስለት ብዙዎች እጅ ካልገቡ፣ በጥልቅ ትንታኔ ከተዘጋጁ መጻሕፍት አንዱ የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “ቃል
      📖“ቃልኪዳን በነገረ ድኅነት” (በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ) ✍ቆየት ካሉ ነገር ግን እንደ መጽሐፉ ብስለት ብዙዎች እጅ ካልገቡ፣ በጥልቅ ትንታኔ ከተዘጋጁ መጻሕፍት አንዱ የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “ቃል ኪዳን በነገረ ድኅነት” በሚል ርእስ የተዘጋጀው መጽሐፍ ነው፡፡  መጽሐፉን አንባቢያን ትልቅ መንፈሳዊ መረዳትን ስለሚጠይቀው ስለ ቃል ኪዳንና ነገረ ድኀነት  በቂ ግንዛቤ አግኝተን እምነታችንን በማጽናት ከክርስቶስና ከቅዱሳን ጋር ተጣብቀን በምድር ሰማያውያንን መላእክትን መስለን ተዋሕዶዊ አኗኗርን ገንዘብ እንድናደርግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው ብንል ማጋነን አይኾንም። ❞ ይህ መጽሐፍ ቅዱሳን ከአምላካቸው ጋር ያደረጉትን ቃልኪዳንና በተሰጣቸው ቃል ኪዳን እኛ እንዴት መጠቀም እንዳለብን የሚተነትን ብቻ ሳይሆን፣ ነገረ ድኅነትን ተተርሰው ለሚነሡ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ፣ ተግባራዊ ምልልሳችን በክርስትና ሕይወታችን ውስጥ ያለውን ፋይዳ፣ ስለንስሐና ሒደቶቹም በቂ ግንዛቤ በጥልቀት ያስገነዝበናል፡፡ መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል ። 📦 ለውድ   አንባብያን ደግሞ ግዮን በአዲስ መልክ የስጦታ ፓኬጅ  ይዞ እየመጣ ነው   በቅርብ ቀን ይጠብቁ! # ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖“ቃልኪዳን በነገረ ድኅነት” (በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ) ✍ቆየት ካሉ ነገር ግን እንደ መጽሐፉ ብስለት ብዙዎች እጅ ካልገቡ፣ በጥልቅ ትንታኔ ከተዘጋጁ መጻሕፍት አንዱ የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “ቃል
      📖“ቃልኪዳን በነገረ ድኅነት” (በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ) ✍ቆየት ካሉ ነገር ግን እንደ መጽሐፉ ብስለት ብዙዎች እጅ ካልገቡ፣ በጥልቅ ትንታኔ ከተዘጋጁ መጻሕፍት አንዱ የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “ቃል ኪዳን በነገረ ድኅነት” በሚል ርእስ የተዘጋጀው መጽሐፍ ነው፡፡  ይህን መጽሐፍ ያነበቡ አንባቢያን ትልቅ መንፈሳዊ መረዳትን ስለሚጠይቀው ስለ ቃል ኪዳንና ነገረ ድኀነት  በቂ ግንዛቤ አግኝተውበት እምነታቸውን በማጽናት ከክርስቶስና ከቅዱሳን ጋር ተጣብቀው በምድር ሰማያውያንን መላእክትን መስለው ተዋሕዶዊ አኗኗርን ገንዘብ አድርገው ተመላልሰውበታል፡፡ ❞ ይህ መጽሐፍ ቅዱሳን ከአምላካቸው ጋር ያደረጉትን ቃልኪዳንና በተሰጣቸው ቃል ኪዳን እኛ እንዴት መጠቀም እንዳለብን የሚተነትን ብቻ ሳይሆን፣ ነገረ ድኅነትን ተተርሰው ለሚነሡ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ፣ ተግባራዊ ምልልሳችን በክርስትና ሕይወታችን ውስጥ ያለውን ፋይዳ፣ ስለንስሐና ሒደቶቹም በቂ ግንዛቤ እንዲኖረን ያበቃናል፡፡ መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል ። 📦 ለውድ   አንባብያን ደግሞ ግዮን በአዲስ መልክ የስጦታ ፓኬጅ  ይዞ እየመጣ ነው   በቅርብ ቀን ይጠብቁ! # ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623