fa
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

رفتن به کانال در Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

نمایش بیشتر
3 306
مشترکین
-224 ساعت
-107 روز
-3830 روز
آرشیو پست ها
Repost from N/a
ምዕላደ ጥበብ ቊጥር ፩ እና ፪ ✍️በ"መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ" ቍጥር ፩፦ በ'ምዕላደ ጥበብ' በመጀመሪያው ክፍል ፥ በእንሳስት ተፈጥሮ ፣ ጸባይ ፣ ግብር ፣ እያንዳንዱ እንስሳ ያለውን የሕይወት
+1
ምዕላደ ጥበብ ቊጥር ፩ እና ፪ ✍️በ"መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ" ቍጥር ፩፦ በ'ምዕላደ ጥበብ' በመጀመሪያው ክፍል ፥ በእንሳስት ተፈጥሮ ፣ ጸባይ ፣ ግብር ፣ እያንዳንዱ እንስሳ ያለውን የሕይወት ዘይቤ - አይተን በድንቂያ ነፍስ አልቀረልንም ነበር፤ ደግሞ ወደ ሰዋዊ የሕይወት ፍካሬ ወርደው ከእኛነታችን ጋር ተሰናስለው የተተነተኑበት መንገድ እና ከእነሱ ልናገኝ የምንችለውን ጥበብ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ አይተን በአንክሮ አፋችንን እንደከፈትን የመጽሐፉ ገጾች ይገባደዳሉ። በ'ኹለተኛ ክፍል' ጠብቁን ተስፋ ስለነበር ክፍል አንዱ የተሰናበተን - በተስፋ ስንጠብቀው ዘገየብን ኾኖም 'ጊዜው ሲደርስ አንባ ይፈርስ' እንዲሉ😊👇 ─━━━━⊱✿⊰━━━━─ ቊጥር ፪፦ ቁጥር ኹለት "ምዕላደ ጥበብ" ከቁጥር አንዱ "ምዕላደ ጥበብ" ድንቂያችንን ተ'ረ'ክ'ቦ ዕፁብ ወመንክር እያስባለን ይዞን እየከነፈ ነው። የገጾች መፈጣጠን ግን የጤና አይመስልም ፤ 'የመጽሐፍ ገጽ አይበርክትልኽ' የተባላችኹ ኹላ ሊመስላችኹ ይችላል😊 ዓይናችኹን ገና ከገጹ ሰፍታችኹ ከማዋደዳችኹ ወዲያው በቀኝ እጃችኹ በኩል ያሉት ገጾች መሟሸሽ ይጀምራሉ። በመኻል በመኻል ድንቂው ሲበረታባችኹ ከንባብ እየተገታች "ወቸው ጉድ የአንተ ሥራ" ትሉ ዘንድ ትገደዳላችኹ... አለቀ🤔 አኹንም በሌላ ተስፋ ጥሎን ኼደ "ምዕላደ ጥበብ በቍጥር ፫* ትቀጥላለች ተብለናል..😊 ─━━━━⊱✿⊰━━━━─ የበለጠ በትጋት በድርሰቶቻቸው ያገለግሉን ዘንድ የ'ጸሐፍያን'ን ሥራዎች ገዝቶ በማንበብ እናበ'ረ'ታ'ታ፨ «ጸሐፊን ከክታብ [ከጽሑፍ] ፣ አንባቢን ከንባብ አያናውጽብን»... እያልን በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል ። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖ላሓ_ማርያም📖 【የማርያም ለቅሶ】 ❝የሰሙነ ሕማማቱ ምንባብ በዕለተ ስቅለት #እመቤታችን ላይ የደረሰውን ሰቈቃ የሚተርክ “ላሐ ማርያም” የተሰኘ ምንባብ ሠርቷል። ይኽ ምንባብ በዕለተ ዐርብ ሲነበብ
📖ላሓ_ማርያም📖 【የማርያም ለቅሶ】 ❝የሰሙነ ሕማማቱ ምንባብ በዕለተ ስቅለት #እመቤታችን ላይ የደረሰውን ሰቈቃ የሚተርክ “ላሐ ማርያም” የተሰኘ ምንባብ ሠርቷል። ይኽ ምንባብ በዕለተ ዐርብ ሲነበብ አንባቢነቱ አንደበቱ ለረታ አረጋዊ ሰው ወይም በደብሩ ገዳሙ ላለ በመዓርግ ከፍ ላለ ሰው ይሰጥና ድምፁን ጐላ አድርጎ ያነበዋል። ታዲያ ንባቡ ረዘም ስለሚል ብዙ ጊዜ በግእዝ ያውም ምድጋም በሚመስል ፍጥነት እየተነበበ ስለሚታለፍ መሳጩና አራኂራኂው ምንባብ መዘከር የሚገባው ልክ ሳይዘከር ያልፋል፡፡ ንባቡ የዓመት ቀለም (ንባብ) ነውና ያለዚያ ቀን መልሰን ለመስማትም ዕድል ስለማይኖረን እመቤታችን በአንድ ልጇ ሕማምና መከራ የደረሰባትን ሰቈቃ ደጋግሞ ለመገንዘብ አጋጣሚ ሳናገኝ እንቀራለን፡፡ እንዲኸ ያለው ዕድል ከሚደርሳቸው የሰሙነ ሕማማት ምንባባት ውስጥ “ድርሳነ ፈያታይ”፣ “መጽሐፈ ዶርሆና “ጸሎተ ስምዖን ዘዐምደ የመሳሰሉ ምንባባትም ይገኙበታል። እነዚኸ ምንባባት በይዘታቸውና በምስጢራቸው ነገረ ስቅለቱ በሚወሳበት ኹሉ ሊወሱና እንደ “ላሐ ማርያም" ያለው ደገሞ ቢቻል ዘወትር፤ ባይቻል እንኳ በዓለ ማርያምንና ወርኃ ጽጌን ጠበቆ ከአቡነ ዘበሰማያትና በሰላመ ገብርኤል ጸሎት ጋር ቢጸልዩት ከእመቤታችን በረከት ረድኤትን የሚያስገኘ ነው፡፡❞ #በአማን_ነጸረ /ደብተራና የሕግ ባለሞያ/ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ሕይወተ_ማርያም_ድንግል📖 ❝ሕይወተ ማርያም ድንግል በሚል ርዕስ የተጠቀሰው መጽሐፍ እመቤታችን ከፅንሰቷ ወራት ጀምሮ እስከ ዕስተ እረፍቷ የተጓዘችበትን የሕደወት መስመር በምሥጢራዊ አገላለጥ ፍን
📖#ሕይወተ_ማርያም_ድንግል📖 ❝ሕይወተ ማርያም ድንግል በሚል ርዕስ የተጠቀሰው መጽሐፍ እመቤታችን ከፅንሰቷ ወራት ጀምሮ እስከ ዕስተ እረፍቷ የተጓዘችበትን የሕደወት መስመር በምሥጢራዊ አገላለጥ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሔተ ብርሃን ሆና አግኝቼዋለሁ፣ አቀራረቡም ትምህርተ አበውን የተከተለ፣በትርጓሜ የበሰለ፤ ትውፊት አበውን አጉልቶ የሚያሳይ ቅዱስ መጽሐፍን መሠረት ያደረገ በመሆኑ እውነተኛ የቤተ ከርስቲያኒቱን ልጆች ያስተምራል ብየ አምናለሁ፤ በጸሐፊውም መንፈሳዊ ኩራት ይሰማናል፣ ብዙዎች ስለ እመቤታችን መስበክና መጻፍ አንደ ነውር ተቆጥሮባቸው በተፈተኑበት ዘመናችን በቋንቋ አጠቃቀሙ በአቀራረቡ የተዋሕዶ ልጆችን የሚያበረታታ ጽሐፍ በመጻሩቸው አደንቃቸዋለሁ: ለወደፊቱም ብዙ እጠብቃለሁ አነሣስቶ ላስጀመራቸው፤ አስጀምሮም ላስፈጸማቸው ለልዑል እገዚአብሔር ከብርና ምስጋና ይሁን፡፡❞ #አባ_አብርሃም ⨳የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ❝እንደው እለት እለት አዲስ ኹል ጊዜ ልዩ እንደያውም ወይን ነው ብል ትክክል ነኝ !ምክንያቱም እያደር አዲስ ነው እለት እለት ሲነበብም ልዩ ለዩ ጣፋጭ እውቀትን ያስይዛልና። ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስቷ ሕይወት ከጽንሰቷ -እርገቷ ድንቅ በሚባል አጻጻፍ ሲያትትማ ወይ ጉድ ሳያሰኝ አይቀርም! #ውድ_አፍቃርያነ_ንባብ ብቻ ደስ በሚል ኹኔታ የተጻፈ ብሎም ውስጣችን ያለውን #የድንግሏ ፍቅሯን ይበልጥ እንዲቀጣጠል ያደርጋልና አያምልጠን እያልን መጽሐፉን #በግዮን_መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ነገረ_ማርያም_በአዲስ_ኪዳን #ስለ መጽሐፉ የሊቃውንት አስተያየት ደራስያንን አኽለኽ መስለኽ፡ ኹነኽ በመተርጉም ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተቸረኽ ወንድማችን መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ይኽነን መጽሐፍኽን
📖#ነገረ_ማርያም_በአዲስ_ኪዳን #ስለ መጽሐፉ የሊቃውንት አስተያየት ደራስያንን አኽለኽ መስለኽ፡ ኹነኽ በመተርጉም ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተቸረኽ ወንድማችን መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ይኽነን መጽሐፍኽን በሰከነ፣ በተሰበሰበ አእምሮ ተመልክቼዋለኍ። በእውነት ያለምንም ማጋነን እንደነ ቅዱስ ቄርሎስ፣ ቅዱስ ኤፍሬም፡ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ፡ አባ ሕርያቆስ _ወዘተርፈ መንፈስ ቅዱስ ስዉር ለኾነ ምስጢረ ሥጋዌ የጥበብ መሣሪያ አድርጉኻል እላለኍ። የመጻሕፍተ ብሉያት ወሐዲሳት መድኀኒቱ ምስጢር ለጠፋባቸው ሕሙማን መናፍቃን ስፔሻል ዶክተር(ሐኪም) ወይም የዘመናችን ሉቃስ ኾነኻቸዋል፡፡ ወንድማችን ሰይጣናዊ ቅናት ካሰከራቸው ፈተና ይጠብቅኽ፡፡ ድንቅ ነው! #መጋቤ ሐዲስ ደጉ ዓለም ካሳ [የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን መምህር] 💦#ውድ_አንባብያን፦ ለተወሰነ ጊዜ ከአይናችን ቢሰወር በናፍቆቱ ተቃጥለን መድረሻ አጥተን የባዘንን እንዳለን አይዘነጌ ነው።ለምን ጉዳዩ፦ #የንግስቷ_የእናታችን_የእመቤታችን ነገር ስለኾነ ሊያውም እንዲህ የተመረመረ ብሎም እመቤታችን ላይ ለሚነሱ ለበዙ ጥያቄዎች አሳማኝ ምላሾችን ያጨቀ መኾኑ የማያከራክር መጽሐፍ መኾኑን አለመመስከር ስለማይቻል። እኛም ድጋሚ መታተሙን እያበሰርን በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተንላችኋል ። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

🔗📖#ትምህርተ_ሃይማኖት_ክርስቲያናዊ_ሕይወት #እግዚአብሔር በረድኤት ከሰው ልጆች ተለይቶ እንደማያውቅ ከሚያስረዱ ነገሮች አንዱ በየዘመኑ ለሚነሣው ትውልድና በትውልዱ ላይለሚነሡ ችግሮች በዚያው ዘመ
🔗📖#ትምህርተ_ሃይማኖት_ክርስቲያናዊ_ሕይወት #እግዚአብሔር በረድኤት ከሰው ልጆች ተለይቶ እንደማያውቅ ከሚያስረዱ ነገሮች አንዱ በየዘመኑ ለሚነሣው ትውልድና በትውልዱ ላይለሚነሡ ችግሮች በዚያው ዘመን ተስማሚ የሆነ መፍትሔ መስጠቱ ነው፡፡ ኑፋቄና መናፍቃን በበዙበት ፣ ክርክርና ተጠየቅ በሠለጠነበት ፤ ሰው ሃይማኖቱን በሚገባ ማወቅና መረዳት በሚሻበት በዚህ ዘመን ፣ሊገባው በሚችል መልኩ የአበውን ሃይማኖት የሚያስረዳ _ መምህርም መጽሐፍም ያስፈልገዋል፡፡ ይህ መጽሐፍ ለዚህ ዘመን ትውልድ የአባቶቹን ርቱዕ ሃይማኖት በጥልቀትና በስፋት ለመረዳት በእጅጉ ተስማሚ የሆነ ፣ብዙ የተደከመበትና ዝግጅቱም ከ10 ዓመታት በላይ የፈጀ ፣በብዙ የቤተክርስቲያን ሊቃውንትና አበውም የታረመ ዝግጅት ነው ፡፡ በተለይም ነገረ ሃይማኖትንና ክርስቲያናዊ ሥና-ምግባርን አጣምሮ በመያዝ፣ የሠለስቱ ምእትን ጸሎተ ሃይማኖት መሠረት አድርጎ በመተንተን የሚያቀርብ በዘመናችን ብቸኛ መጽሐፍ ነው ብዬ እገምታለሁ ፡፡ መጽሐፉ በየቀኑ እየተቀዳ የሚጠጣ እንጂ በአንዴ ተጨልጦ የሚያልቅ አለመሆኑን የመጀመሪያዎቹን ሦስት ገጾች ስናነብ ማወቅ ይቻላል ፡፡ ምናልባትም ዕድሜ ያልቅ እንደሆነ እንጂ ተነብቦ ያልቃል የሚል እምነት የለኝም፡፡ እያንዳንዱ ገጽ በተመስጦ ልብን አረጋግቶና ጊዜ ወስዶ በልቡና ሊያነቡት የሚገባ ነውና፡፡ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

🔗የመጽሐፍ ጥቆማ ለዐብይ ጾም ፩፦ ሕማማት ሕማማት፦ አንድ ጊዜ አንብበው የሚያስቀምጡት አይደለም ፤ ሕማማት ሕይወት ነው፡፡ ሕይወት ዕለት ዕለት ሚኖር እንጂ አንዴ ተከናውኖ ሚቆም ነገር አይደለም፡፡
🔗የመጽሐፍ ጥቆማ ለዐብይ ጾም ፩፦ ሕማማት ሕማማት፦ አንድ ጊዜ አንብበው የሚያስቀምጡት አይደለም ፤ ሕማማት ሕይወት ነው፡፡ ሕይወት ዕለት ዕለት ሚኖር እንጂ አንዴ ተከናውኖ ሚቆም ነገር አይደለም፡፡ ለዚህ ደግሞ መጽሐፉም አጋዥ ነው፡፡ በስድስት ምዕራፍና ሃምሳ ስድስት ንዑስ ርዕሶች የተዘጋጀው መጽሐፍ ደስ ያለንን ምዕራፍ ወይም ንዑስ ርእስ ገልጠን ብናነብ ራሱን ችሎ የሚቆም እና የራሱ መልእክት ያለው ስብከት ሲሆን ከቀደሙት ምዕራፎች ጋር አናበን ስንመለከተው ደሞ ከስብከት ወደ ትምህርትነት የሚያድግ ኃይል ያለው መጽሐፍ ነው፡፡ ፪፦ ድርሳነ ማሕየዊ ልክ እንደ ሌሎች የጸሎት መጻሕፍት በዕለታት የተከፋፈለ ሆኖ የጌታን ከጽንሰቱ ጀምሮ በመስቀል ለሰው ልጅ ያለውን ፍቅር የገለጠበትን የሚያሳይ ጸሎትና ትምህርት የያዘ መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ የተጻፈው በቅዱሳን ሐዋርያት ሲሆን ከቅዱሳት አንስት መካከል የሆኑት ቤርዜዛ ሜልቴዳና ኤልሳቤጥ የሚባሉ እንዲሁም ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጌታን ጠይቀውት አጽፏቸዋል። ፫፦ የብርሃን እናት ስለ ብርሃን ክርስቶስ እናት እመቤታችን ቃላት ሊገልጸው በማይችል ግሩምና ጥልቅ በሚባል አገላለጽ ከቀደመት አባቶች ትምህርት ጋር ተሰናስሎ የተዘጋጀ ድንቅ መጽሐፍ ነው። ፬፦ ላሓ ማርያም አምላክ ለሰው ልጅ ሲል የተቀበላቸውን ጽዋትወመከራ ባየች ጊዜ የአምላክ እናቱን ጥልቅ ሐዘናትና አንጀት የሚያላውስ ለቅሶዋን በማውሳት ይጀምርና የሐዋርያትን ኹናቴ እያስረዳ በዚያው ድርሳነ ፊያታዊን አስዳስሶ በምናብ እለተ አርብ ወስዶ ያሳትፋል ። 👉ውድ አፍቃርያነ ንባብ ፦ታድያ እነዚህን መጻሕፍት #ግዮን_መጻሕፍት በልዩ ቅናሽአቅርቧል። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። https://t.me/GhionBookStore1623

#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት 24ኛ ኅትም! ሕማማት በመድኃኔዓለም ክርስቶስ የምድር ላይ የመጨረሻ 20 ሰዓታት ቆይታ ላይ የሚያተኩር መጽሐፍ ነው:: መጽሐፉ 19 ጊዜ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የታተመና ከ8
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት 24ኛ ኅትም! ሕማማት በመድኃኔዓለም ክርስቶስ የምድር ላይ የመጨረሻ 20 ሰዓታት ቆይታ ላይ የሚያተኩር መጽሐፍ ነው:: መጽሐፉ 19 ጊዜ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የታተመና ከ80 ሺህ ኮፒ በላይ የተሠራጨ ሲሆን በትግርኛ እና በኦሮሚኛ ተተርጉሞ ታትሞአል:: ደራሲው ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ በአጠቃላይ 14 መጻሕፍትን ለአንባቢያን ያደረሰ ሲሆን ክብረ ክህነት ፣ቅዱስ ገብርኤል ፣ ታቦት በሐዲስ ኪዳን ፣ ተግባራዊ ክርስትና ፣ ቃና ዘገሊላ፣ሀቢበ ጊዮርጊስ፣ ከሞት በሻገር፣ አበረታች መድኃኒት፣ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ፣የኤፍራጥስ ወንዝ ፣ የብርሃን እናት እና የግዮን ወንዝ የሚሉት መጻሕፍት ከሕማማት ውጪ ያሉት መጻሕፍት ናቸው:: ሁሉንም በግዮን መጻሕፍት መደብር በልዩ ቅናሽ ያገኟችዋል። ይደውሉ፦ 0913083816 #ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። https://t.me/GhionBookStore1623

#በብዙዎች_እጅ_ዘንድ_ስላልገባው፥ #ግን_ደግሞ_እጅግ ግሩም የሆነ መጽሐፉ እንጠቁምዎት! የዮሐንስ ዘሰዋስው እና የነገረ ሃይማኖት መጻሕፍት አዘጋጅ የኾነው የመምህር ሳሙኤል ፍቃዱ ነው። ምጽአተ ክርስ
#በብዙዎች_እጅ_ዘንድ_ስላልገባው፥ #ግን_ደግሞ_እጅግ ግሩም የሆነ መጽሐፉ እንጠቁምዎት! የዮሐንስ ዘሰዋስው እና የነገረ ሃይማኖት መጻሕፍት አዘጋጅ የኾነው የመምህር ሳሙኤል ፍቃዱ ነው። ምጽአተ ክርስቶስ ይሰኛል። ይህ በ445+10 (455) ገጾችና በ11 ምዕራፎች የተዘጋጀው መጽሐፍ በውስጡ፦ ፩. ምጽአትን ስለ መረዳት ፪. ስለ ምጽአት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌዎች ፫. ስለ ምጽአት ቀን ምንነት ፬. ስለ ምጽአት ምልክቶች ፭. ምጽአትን አስመልክቶ ስለሚነገሩ አንዳንድ አስተምሮዎችና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ፮. በምጽአት ዋዜማ ስለሚታዩ ምልክቶች ፯. በምጽአት ጊዜ ስለሚኖር ታላቁ መከራና ስለ ሰባቱ ጽዋዎች ፰. በምጽአት ጊዜ ስለሚከናወኑ ሦስቱ ዐበይት ክስተቶች ፱. የሚመጣው ማን እንደ ኾነና ስለሚደረገው ፍርድ ፲. ስለ ምረረ ገሃነም ፲፩. ስለ መንግሥተ ሰማያት  ብዙ ዝርዝርና ርቱዕ የኾነውን ትምህርት የያዘ ነው። እርስዎም ይህን ብስል መጽሐፍ በማግኘት ስለ ኦርቶዶክሳዊ ምጽአት ያለዎትን ግንዛቤ ያዳብሩ። ከስሕተት ትምህርቶች ይጠበቁ፤ ሌሎችንም ይጠብቁ። ------------------------- በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። https://t.me/GhionBookStore1623

#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት ምሥጢረ ምሥጢራትን እንደ ጎበኘኋት፡፡ ዘመኑ በመጻሕፍት አቅርቦት በኩል ምቹ ነውና ብዙ መጻሕፍትን የማንበብ እድል ገጥሞኛል። ምሥጢረ ምሥጢራት ግን እንደ ሥያሜዋ ከሌሎች ለየት ብ
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት ምሥጢረ ምሥጢራትን እንደ ጎበኘኋት፡፡ ዘመኑ በመጻሕፍት አቅርቦት በኩል ምቹ ነውና ብዙ መጻሕፍትን የማንበብ እድል ገጥሞኛል። ምሥጢረ ምሥጢራት ግን እንደ ሥያሜዋ ከሌሎች ለየት ብላ አግኝቻታለሁ፡ በምሥጢረ ሥላሴ ላይ ብቻ ትኩረት ማድረጓ አንድ ልዩ ነገር ሁኖ፣ ከዚያውም ዘንድ ወደ ባሕረ ምሥጢሩ ስባ ጎትታ የምታስገባና በጥሩ የሊቃውንት መቅዘፍያ እየቀዘፈች ብዙ ሰዎች ወደ አላዩት የምሥጢር ወደብ የምታደርስ፤ ከይዘት አንጻር ከተመዘነች በምጥቀትና በጥልቀት ለዘመናችን የመጀመሪያ የምትባል መጽሐፍ ናት፡፡ መጽሐፏን የምትመለከቱ ሁሉ፦ በትሐት ሰብእና፣ በንጹሕ ልቡና፤ በቅጥነተ ኅሊና ሁናችሁ እንድትመለከቷት ወንድማዊ ምክሬ ነው። መልካም ንባብ መምህር ኃይለ ማርያም ዘውዱ ዘቦሩ ሜዳ 👉ውድ አንባብያን ይኽን በመ/ር ገብረ መድኅን እንየው እና በመ/ር መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት ተዘጋጅቶ በሊቃውንት ሳይቀር ግሩምነቱ የተመሰከረለትን መጽሐፍ አንብበን ተጠቃሚ ለመኾን ጊዜ ባንሰጥ መልካም ነው እያልን መጽሐፉን #በግዮን_መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ዜና_መጽሐፍ አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ …በአድሜ ዘመኑ ሌላው ቀርቶ የዚህን ጫካ ወለል ምን እንደሌለው፣ ምን እንዳለው እንኳን አይቶት የማያውቅ፤ ጨርሶ ስለኛ የማወቅ ፍላጎት የሌለው እኮ ነው፡፡ ንሥ
ዜና_መጽሐፍ አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ …በአድሜ ዘመኑ ሌላው ቀርቶ የዚህን ጫካ ወለል ምን እንደሌለው፣ ምን እንዳለው እንኳን አይቶት የማያውቅ፤ ጨርሶ ስለኛ የማወቅ ፍላጎት የሌለው እኮ ነው፡፡ ንሥር እኮ በእኛ ላይ የሚኖር፣ ከእኛ ጋር ግን የሌለ፤ ለእኛ ቅርብ የሆነ፡ ከእኛ ግን ሩቅ የሆነ ፍጥረት መሆኑን አታውቅምን?…..! “…..እንደምታውቁት ተፈጥሯችን ከአንድ ቦታ ተተክለን እንድንኖር ያስገድደናል፡፡ ይህ ውብ ተፈጥሯችን ግን የተለየ ጸጋ ነበር፡፡ ፈጣሪ ከአንድ ቦታ ተተክለን እንድንኖር አድርጎ ሲፈጥረን ትልቁ ምሥጢር ችግር መፍታት እንጅ ችግርን መሸሽ ተፈጥሯችን እንዳልሆነ ሲያጠይቅ ነበር…. እኛ እንደ እንስሳት ችግር በመጣ ጊዜ እየፈረጠጥን ከአንዱ ወደ አንዱ ልንሄድ አይገባንም፤ አያስፈልገንምም…….' “መቸም እኛ ዕፅዋት … ነፋስ በነፈሰ ቁጥር መወዛወዛችን የነበረና ያለ ነው፣ ወደፊትም የሚኖር ነው…. ዕፅዋት ልብ በሉ! የምንወዛወዘው ከነፋስ ጋር አላስፈላጊ ግብግብ ላለመግጠም እና ትንሽ አወዛውዞን አልፎ እንዲሄድ እንጅ ከሥራችን እንዲነቅለን አይደለም፡፡' '…..ታምሚያለሁ ብሎ ያላመነ መድኃኒት አይሻም፤ በህመም ያልተሰቃየም በፈውስ አይደሰትም! ጤነኛ ነኝ ብሎ የሚያስብ ባለ መድኃኒት ይፈልጋልን? አዋቂ ነኝ የሚልስ መካሪ ይሻል?.......' በግዮን መጻሕፍት መደብር የተለያዩ መጽሐፎችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኛሉ። ይደውሉ ፦በ0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#ምርጡን_ከተመረጡት_ተማር ከነህሚያ 👉 ጸሎትን ከማርያም 👉 አክብሮትን ከማርታ 👉 ዝቅ ማለትን ከጳውሎስ 👉 ማስተማርን ከዳንኤል 👉 መታዘዝን ተማር የተሸለሙትን ትሸለማለህ!!! #የጽድቅ_መንገ
#ምርጡን_ከተመረጡት_ተማር ከነህሚያ 👉 ጸሎትን ከማርያም 👉 አክብሮትን ከማርታ 👉 ዝቅ ማለትን ከጳውሎስ 👉 ማስተማርን ከዳንኤል 👉 መታዘዝን ተማር የተሸለሙትን ትሸለማለህ!!! #የጽድቅ_መንገድ መጽሐፍ #ሕይወት_እና_ክርስትና መጽሐፍ ሁለቱም የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ አዲስ መጽሐፍት በግዮን መጻሐፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ይገኛሉ። ለበለጠ መረጃ፦ በ0913083816ይደውሉ። https://t.me/GhionBookStore1623

#ፈጣሪ ለዳንኤል የአንበሶችን አፍ ከዘጋ ለሙሴ ቀይ ባህርን ከከፈለ ለኢያሱ ጸሐይን ካቆመ ለጴጥሮስ እስር ቤትን ከከፈተ ለሳራ ልጅን ከሰጠ አላዛርን ከሞት ካስነሳ ላንተም የማያስብበት ምክንያት የለም
#ፈጣሪ ለዳንኤል የአንበሶችን አፍ ከዘጋ ለሙሴ ቀይ ባህርን ከከፈለ ለኢያሱ ጸሐይን ካቆመ ለጴጥሮስ እስር ቤትን ከከፈተ ለሳራ ልጅን ከሰጠ አላዛርን ከሞት ካስነሳ ላንተም የማያስብበት ምክንያት የለም!! ብቻ አንተ በእሱ እመንበት!!? #ወንድሜ_ሆይ_ለነፍስህ_ቤት_ስራላት https://t.me/GhionBookStore1623

#ለነፍስ_አይጠቅምም! ስለ እሳት ማሰብ ገላን እንደማያሞቀው ሁሉ፣ ተግባራዊ ፍቅር የሌለበት እምነትም ለነፍስ አይጠቅምም! የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት
#ለነፍስ_አይጠቅምም! ስለ እሳት ማሰብ ገላን እንደማያሞቀው ሁሉ፣ ተግባራዊ ፍቅር የሌለበት እምነትም ለነፍስ አይጠቅምም! የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ ፦ 👇🎀👇 👉 #ጠይቁ_ይመለስላችኋል 4ተኛ ዕትም 👉 #ሰይጣንን_አስርቡት 2ተኛ ዕትም 👉 #የነፍስ_ምግብ 2ተኛ ዕትም 👉 #እስከማዕዜኑ 3ተኛ ዕትም ሁሉም መጽሐፍት በመጻሐፍት መደብራችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ይገኛሉ። https://t.me/GhionBookStore1623

አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እመጓ፣ ዝጎራ፣ መርበብት፣ ሚተራሊዮን፣ ሰበዝ እና ችቦ በተሰኙ ተወዳጅ መጻሕፍት የሚታወቅ ደራሲ ነው። አኹን ደግሞ ሰባተኛ መጽሐፋቸውን ፍካሬ በሚል እ
አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እመጓ፣ ዝጎራ፣ መርበብት፣ ሚተራሊዮን፣ ሰበዝ እና ችቦ በተሰኙ ተወዳጅ መጻሕፍት የሚታወቅ ደራሲ ነው። አኹን ደግሞ ሰባተኛ መጽሐፋቸውን ፍካሬ በሚል እነሆ ብለውናል በመደብራችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። ይደውሉልን ፦በ0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እመጓ፣ ዝጎራ፣ መርበብት፣ ሚተራሊዮን፣ ሰበዝ እና ችቦ በተሰኙ ተወዳጅ መጻሕፍት የሚታወቅ ደራሲ ነው። አኹን ደግሞ ሰባተኛ መጽሐፋቸውን ፍካሬ በሚል እ
አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እመጓ፣ ዝጎራ፣ መርበብት፣ ሚተራሊዮን፣ ሰበዝ እና ችቦ በተሰኙ ተወዳጅ መጻሕፍት የሚታወቅ ደራሲ ነው። አኹን ደግሞ ሰባተኛ መጽሐፋቸውን ፍካሬ በሚል እነሆ ብለውና በመደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። ለበለጠ መረጃ መደወል በ0913083816

💧ዜና_መጽሐፍ 【አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ】 📖ትምህርተ እግዚአብሔር ➮ይህ “ትምህርተ እግዚአብሔር ዘኦርቶዶክስ"በሚል ርእስ በመ/ር_ምስጢሩ_ታየ የተዘጋጀው መጽሐፍ፣ ስለ #እግዚአብሔር አምላክነትና
💧ዜና_መጽሐፍ  【አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ】 📖ትምህርተ እግዚአብሔር ይህ “ትምህርተ እግዚአብሔር ዘኦርቶዶክስ"በሚል ርእስ በመ/ር_ምስጢሩ_ታየ የተዘጋጀው መጽሐፍ፣ ስለ #እግዚአብሔር አምላክነትና እሠራር እንዲሁም ስለ ሌሎች መሰል ጉዳዮች ልናውቃቻው የሚገቡ መሠረታዊ ሐሳቦችን የያዘ መጽሐፍ ነው። የሚያነሣቸውን ሐሳቦችም ኦርቶዶክሳዊ በሆነ ይዘትና ውበት ባለው የሥነ-ጽሑፍ ለዛ የሚያብራራ ጥሩ መጽሐፍ ነው። መ/ር_ምስጢሩ_ታየ ይህን መጽሐፍ ጽፈው ስላበረከቱልን ከልብ እያመሰገንኩ፣ ይህን መጽሐፍ ብታነቡ ትጠቀሙበታላችሁና ጊዜ ሰጥታችሁ ታነቡት ዘንድ በአክብሮት እጋብዛለሁ።   #ዲ/ን_ያረጋል_አበጋዝ 👉ውድ አንባብያን ይኽን በመ/ር ምስጢሩ ታየ ተዘጋጅቶ በሊቃውንት ሳይቀር ግሩምነቱ የተመሰከረለትን መጽሐፍ አንብበን ተጠቃሚ ለመኾን ጊዜ ባንሰጥ መልካም ነው እያልን መጽሐፉን #በግዮን_መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ቁጣ ድል አይንሣህ ወንድምህን ከሚገባው ይልቅ ለማክበር ሰውነትህን አትጋት። ባገኘህውም ጊዜ እጁን እግሩን ሳመው፤ በጎ አድርግለት አክብረህ ወደህ እየው፡፡ ሥራው ባይደለ ሥራ አመስግነው፣ ከአንተም በ
ቁጣ ድል አይንሣህ ወንድምህን ከሚገባው ይልቅ ለማክበር ሰውነትህን አትጋት። ባገኘህውም ጊዜ እጁን እግሩን ሳመው፤ በጎ አድርግለት አክብረህ ወደህ እየው፡፡ ሥራው ባይደለ ሥራ አመስግነው፣ ከአንተም በተለየ ጊዜ የእሱን ነገር ተናገር፡፡ ከበጎ ሥራው ወገን መናገር በሚቻልህ ገንዘብ በጎ በጎ አድርግለት፡፡ በጎ ነገር በመናገርህ ወደ በጎ ሥራ ትስበዋለህ ታነቃቀዋለህ፡፡ አንተ ባመሰገንከው ምስጋና፣ አንተ ባከበርከው ክብር የተነሣ ያፍር ዘንድ እንዳመሰገንከው ያልሆነ እንደሆነ ያፍራል፤ እንዲህ የሆነ እንደሆነ ዘርአ ትሩፋትን ትዘራበታለህ፡፡ ነፍስህ ከለመደችው ባልንጀራህን ከማክበር የተነሣ በጎ ነገርን መውደድ በልቡናህ ይቀርጻል፡፡ ፍጹም ትሕትናን ገንዘብ ታደርጋለህ ሳትጥር ብዙ ሥራ ትሠራልህ፡፡ የምታከብረው በጎውን ሰው ብቻ አይደለም ነውር ያለበትም ቢሆን አክብረው እንጂ፡፡ እንዲህ የሆነ እንደሆነ አንተ ካከበርከው ክብር የተነሣ አፍሮ ካንተ ድኅነትን ያገኛል። ገንዘብህ የምትሆን ይህችን ጥበብ ለሁሉ አድርጋት፤ ጥበብም የተባለች ሰውን ማክበር ለሰው ማዘን መራራት ናት። አንዱንስ እንኳን አትቈጣ፣ ተቈጥተህ አታሳዝነው፣ ቍጣ ድል አይንሳህ፡፡ ስለ ሃይማኖትም ቢሆን፣ ሥራው ክፉ ስለሆነም ቢሆን ሰው እንዳታማ ተጠበቅ እንጂ አትፍረድበት፡፡ በልዕልና ፊት አይቶ ሳያዳላ የሚፈርድ ዳኛ ክርስቶስ አለንና፡፡ ወደ በጎ ሥራም ልትመልሰውም ብትወድ እዘንለት፤ እያለቀስህ የለዘበ ነገር ንገረው፤ በቍጣ አትናደድበት፤ ጸብ ያለህ ይመስለዋል ፍቅር ውስጣዊ ቍጣን አይሻምና። #ማር_ይስሀቅ