ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
رفتن به کانال در Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
نمایش بیشتر3 317
مشترکین
-124 ساعت
-107 روز
-3430 روز
آرشیو پست ها
💧ዜና መጽሐፍ
📚#ምናሴ
ወድቆ መነሳት
ከ ጸሐፊው የጉዳት ማስረሻ የኾነኝ ማስረሻ!በማለት የተዘጋጀልን ለእኛም ማስረሻ እንደሚኾነን ጥርጥር የለውም እንድንጠቀምበት እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን!
ስለ መጽሐፉ...👇
#ምናሴ (ማስረሻ) “አግዚአብሔር መከራዬን ኹሉ አስረሳኝ” ሲል ዮሴፍ በወንድ ልጁ ያወጣው ስም ነበረ። “ጸሎተ ምናሴ” በተሰኘው የንሰሐ ጸሎቱ በቤተ ክርስቲያን የሚታወቀው የይሁዳ ንጉሥ ምናሴ ታሪክ ደግሞ በግል ሕይወታችን ላይ፣ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ፣ አንዲሁም በሀገራችን ላይ የፈጸምናቸውን በደሎች ወለል አድርጎ የሚያሳይና በጸጸት ባሕር አስጥሞ በኀዘናችን ማስረሻ የሚኾን ታሪክ የነበረው ሰው ነው፡፡
#መምህር_ቃኘው_ወልዴ ይኽን የመጽሐፍ ቅዱስ ባለ ታሪክ የአበውን የሥነ ጽሑፍ ዘዴ ተጠቅመው የራሱን ታሪክ በአንደበቱ በማናገር በልብ ወለዳዊ ግለ ታሪክ (Fictional Autobiography) መልክ ውብ መጽሐፍ አበርክተዋል፡፡ መጽሐፈ ሃይማኖት ቀመስ ልብ ወለዳዊ የትረካ አጻጻፍን ሰሚቶሎጂያዋ ቅዠቶችና ያልተረጋገጡ አወዛጋቢ ታሪኮችን በመፍጠር ከመዋል ይልቅ አንዲህ ለአገራዊ፣ ለግላዊና ለመንፈሳዊ ቊስሎች መድኃኒት መኾን የሚችል የአጻጻፍ ስልት አንደ ኾነ የሚያሳይ ድንቅ ሥራ ነው፡፡ መጽሐፉ የአንድን ንጉሥ ድቀትና የአግዚአብሔር ምሕረት ብዛት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይና በንሰሐ የሚጠራ በምናሴ አገላለጽ “ቸርነቱን አየለመንን በልባችን ጉልበት አንድንሰግድ” የሚጣራ መጽሐፍ ነው፡፡
✍️ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
📚ፍኖተ መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
💧ዜና መጽሐፍ
📚#ምናሴ
ወድቆ መነሳት
ከ ጸሐፊው የጉዳት ማስረሻ የኾነኝ ማስረሻ!በማለት የተዘጋጀልን ለእኛም ማስረሻ እንደሚኾነን ጥርጥር የለውም እንድንጠቀምበት እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን!
ስለ መጽሐፉ...👇
#ምናሴ (ማስረሻ) “አግዚአብሔር መከራዬን ኹሉ አስረሳኝ” ሲል ዮሴፍ በወንድ ልጁ ያወጣው ስም ነበረ። “ጸሎተ ምናሴ” በተሰኘው የንሰሐ ጸሎቱ በቤተ ክርስቲያን የሚታወቀው የይሁዳ ንጉሥ ምናሴ ታሪክ ደግሞ በግል ሕይወታችን ላይ፣ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ፣ አንዲሁም በሀገራችን ላይ የፈጸምናቸውን በደሎች ወለል አድርጎ የሚያሳይና በጸጸት ባሕር አስጥሞ በኀዘናችን ማስረሻ የሚኾን ታሪክ የነበረው ሰው ነው፡፡
#መምህር_ቃኘው_ወልዴ ይኽን የመጽሐፍ ቅዱስ ባለ ታሪክ የአበውን የሥነ ጽሑፍ ዘዴ ተጠቅመው የራሱን ታሪክ በአንደበቱ በማናገር በልብ ወለዳዊ ግለ ታሪክ (Fictional Autobiography) መልክ ውብ መጽሐፍ አበርክተዋል፡፡ መጽሐፈ ሃይማኖት ቀመስ ልብ ወለዳዊ የትረካ አጻጻፍን ሰሚቶሎጂያዋ ቅዠቶችና ያልተረጋገጡ አወዛጋቢ ታሪኮችን በመፍጠር ከመዋል ይልቅ አንዲህ ለአገራዊ፣ ለግላዊና ለመንፈሳዊ ቊስሎች መድኃኒት መኾን የሚችል የአጻጻፍ ስልት አንደ ኾነ የሚያሳይ ድንቅ ሥራ ነው፡፡ መጽሐፉ የአንድን ንጉሥ ድቀትና የአግዚአብሔር ምሕረት ብዛት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይና በንሰሐ የሚጠራ በምናሴ አገላለጽ “ቸርነቱን አየለመንን በልባችን ጉልበት አንድንሰግድ” የሚጣራ መጽሐፍ ነው፡፡
✍️ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
📚ፍኖተ መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◈ርቱዓዊ ልምምድ፦
◈ርቱዓዊነት በሕይወት በር እየተመላለሱ የተስፋ ፍጻሜን ለማግኘት በጸናች በቀናች ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ የተዋሕዶት ልምምድ ማድረግ ነው።
◈ወይም በዚህች ርትዕት ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ እስከ ፍጻሜ ድረስ የእውነት በሩን ሳይለቁ በግብርም በነገርም የጸና የቀና ክርስቲያን የመሆን ልምምድ ነው።
◈ወይም በሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ ሁኖ ርቱዓዊነትን በማወቅ እና በመረዳት ላይ ተመሥርቶ የመሆን ልምምድን እያስቀደሙ እስከ ህቅታ ድረስ የመዳን መንገድን ለመጨረስ ሳያቋርጡ ወደ ምድረ ርሥት መጓዝ ነው።
◈ቅዱስ ፍጹም ሐዋርያዊ ተስፋን መውረስ የሚቻለው በዚህ ሕያው መንገድ ነውና።"አመንኩ በዘነበብኩ-የተናገርሁትን አመንሁ።"መዝ.፻፲፭፥፩እን. የአፍ ሌላ የልብ ሌላ ሳይሉ ያመኑትን በሕይወት ልምምድ እየኖሩ ማሳየት የሚቻለው በርቱዓዊነት ልምምድ ውስጥ ነው።
◈የርቱዕነት መነሻው ከእግዚአብሔር ለቅዱሳን የተሰጠው፦ርቱዕ ክሡት ፍጹም የሆነው አስተሳስብ ነው።
◈በዚህ መንገድ፦ረቂቁን ከግዙፉ፣ቋሚውን ከሀላፊው፣እውነቱን ከሀሰቱ፣ጽኑዑን ከወጪ ወራጁ በመለየት የሀሳባትን ቅደም ተከተል በመረዳት ጥርት ያለ ርቱዕ ሐዋርያዊ ህሊናን መፈለግ ነው።
◈ሀሳበ እግዚአብሔር፣ሀሳበ መላእክት፣ሀሳበ ሰብእ፣ሀሳበ ደማውያን፣ሀሳበ ዕፅዋት፣ሀሳበ ፍጥረታት አለ፤
◈ከዚህ ሁሉ ሀሳብ መካከል ለድኅነተ ነፍስ ለርቱዓዊነት የሚበጀንን መለየት እና ሁሉንም በየመልኩ ተረድቶ በርቱዓዊነት መሠረት ላይ ጸንቶ በጠራ ህሊና መገለጽ ያስፈልጋል።
◈ደግሞም ከአቅማችን ድካም የተነሣ ወደ ጽሩይ ህሊና ገብቶ ልቡናን አስፍቶ አእምሮን አቅንቶ መለማመድ እና ከፍ ያለውን ጣዕመ ምሥጢር ማየት ቢያቅተን ወደ ባለቤቱ እንለምናለን፦
"ወንስአል አንቃዲወነ ላዕለ ወሶቤሃ ይሠርቅ ለነ ብርሃን እምነ መጻሕፍተ መለኮት ወእምኔሆሙ ንበርህ በአስማተ ቅድስት ሥላሴ ዘውእቱ እምነትነ-
ወደላይ አቅንተን እንለምን ያንጊዜ የመለኮተን ነገር ከማናገሩ መጻሕፍት ዕውቀት የገልጽለናል ከእነርሱም የሦስቱን ስም በመጥራት አዋቆች እንሆናለን ይሄውም ማመናችን ነው።"ሃይ.አበ.፲፥፪እን.
የኔታ ገብረ መድኅን እንየው
#ኢቮሊዩሺን
የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ እምነት?
ይህ “ኢቮሊዮሺን - የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ ሃይማኖት?” የሚለው ድንቅ መጽሐፍ፣ ሳይንስ መስለው የሚነገሩትንና እንደ ዶግማ የሚታዩትን የኢቮሊዩሺን ቲዎሪ እሳቤዎችን ከመሠረታቸው በመመርመርና በቂ ሳይንሳዊ ማስረጃዎችን በማቅረብ፣ እነዚህ መላ-ምቶች ሳይንስ እንዳልሆኑ ግልጽ አድርጎ አቅርቦልናል።
ይህ የመምህራችን የመምህር ያረጋል አበጋዝ ለትውልድ የሚተላለፍ ድንቅ ሥራቸው፣ በተለይ ትንሽ አስኳላ ትምህርት ለዘለቀው ማኅበረሰብ ሕሊናውን የሚያነቃበትና ራሱን የሚፈትሽበት ጠቃሚ መጽሐፍ እንደሆነ አምናለሁ። መምህራችን ከዚህ በፊት “ሳይንሰ እና ሃይማኖት” በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ያቀረቧቸውን ግሩም ሐሳቦች አጣጥመን ሳንጨርስ ይህን ጥልቅና የብዙዎቻችንን ጥያቄ የመለሱበትን ጠቃሚ መጽሐፍ በማበርከታቸው እግዚአብሔር ይስጥልን፣ በዕድሜ በጸጋ ይጠብቅልን፣ በቀጣዩስ ምን እንጠብቅ? እያልኩ ለአንባብያን መልካም ንባብ እላለሁ።
ዲ/ን ዶ/ር ዮሴፍ አጥላው - የሥነ-ኬሚካል ተመራማሪ፣ በአስትራዜኒካ ፋርማሲቲካል የመድኃኒት ምርምርና ማጎልበቻ ድርጅት
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
Repost from የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ቤት
+. እግዚአብሔር መንፈስ ነው .+
የመንፈስ ቀላል ትርጕሙ «በአካላዊነት ጎልቶ ለዐይን የማይታይ» ፣ «ከመታየት በላይ» ማለት ነው። ቃሉ ወደ አካለ እግዚአብሔር ተጠግቶ ሲነገር የበለጠ ሐሳቡን ከፍ አድርጎ ይገልጣል። እግዚአብሔር የር’ቀ’ቶች ኹሉ መነሻ ስለኾነ - አእምሮአችን ከሚያሰበው ር’ቀ’ት በላይ ረቂቅ ነው። መንፈስ የሚለውም ራሱ የእኛን አስተውሎት/መረዳት ታሳቢ ተደርጎ የተነገረ እንጂ እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው ኾኖ አይደለም። እግዚአብሔር ከምንም - ስለ እሱ ከምናስበውም ከምንናገረውምም በላይ ነው!! እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው እግዚአብሔር ብቻ ነው ፤ እግዚአብሔር በእግዚአብሔርነቱ የሚገለጥለትም አካል የተገለጠውን ለመረዳት እግዚአብሔር መኾን አለበት ፤ እግዚአብሔር የሚገልጠውን እግዚአብሔርነት ማወቅ ለማንም አልተሰጠም። ለማንም አይቻልምና።
ስለ እግዚአብሔር ያለን ዕውቀት እኛ ስለ እሱ ማወቅ የቻልነው መጠን ነው ፤ ይኽም ቢኾን በራሳችን የመጣ ሳይኾን ተገልጦልን ያወቅነው ነው። ያወቅነውም እግዚአብሔርን የማወቃችን ድንበር አይደለም። ከእግዚአብሔር መልካምነት ጋር - ነፍስ በንጽሕና ወደ እሱ በመቅረብ ስትተባበር ፥ ፈቃደ ግብረ ባሕርያቱን ስትሳተፍ እየተገለጠላት የሚኼደው ዕውቀቷ የነበራትን ዕውቀት የሚበልጥ ይኾናል። የዕውቀቷ ፍጻሜም የነበሯት ዕውቀቶች ተቋጭተው ከእነሱ በበለጠ አለማወቅ በ’መ’ያ’ዝ ይኾናል!! የነፍስ ዕውቀት ስለ እግዚአብሔር ምንም አለማወቅ ውስጥ በመግባት ይፈጸማል!! ከእሱ ጋር መኖሯ በቂዋ ስለሚኾን የማወቅ ጥማቷም ይቆረጣል!!
«እግዚአብሔር መንፈስ ነው» የዚኽ ሐሳብ ተሸካሚ ቃል ነው። መንፈስ ምንድነው!? እንደ እውነታው የዚኽን ቃል ደረቅ መዝገበ ቃላዊ ፍቺን ከማስቀመጥ ውጪ ፥ ሐሳቡን በኾነው ልክ ለልብ ማስረዳት አይቻለም ፤ መንፈስ የሚለው ሐሳብ ላይ በሰው ዘንድ ያ’ለ አለመረዳት አ’ለ - «ያ አለመረዳት እግዚአብሔር በነፍሳችን ውስጥ ያለው ቦታ ነው» ለማለት «እግዚአብሔር መንፈስ ነው» ተብሏል።
❝.. ወአልቦ ዘየአምሮ ለወልድ ዘእንበለ አብ ፤ ወለአብኒ አልቦ ዘየአምሮ ዘእንበለ ወልድ - ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር አብን የሚያውቅ የለም❞ [ማቴዎስ ፲፩፥፳፯]። ማወቅ ከተነገረስ የአብ ዕውቀት/መታወቅ ወልድ ላይ ፥ የወልድ ዕውቀትም/መታወቅ አብ ላይ ታውቆ ይቀራል። «ወለዘፈቀደ ወልድ ይከሥት ሎቱ - ወልድ ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር / ወልድ ሊገልጽለት ለወደደው ይገልጥለታል» የሚለው ቀጣይ ንባብ - በአሚን አኹን ለእኛ የተገለጠው ፥ እኛነታችን ስለ እግዚአብሔር ማወቅ የቻለው የዕውቀት መጠን ነው እንጂ አብ ወልድን ፥ ወልድም አብን የሚያውቅበት ማወቅ ለእኛ ተሰጥቷል ማለት አይደለም። አብ አብነቱ ወልድ ላይ ፥ ወልድም ወልድነቱ አብ ላይ የቀረ ነው!!
አካል ከሕሊናት ኹሉ ለራቀ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ሲነገር ፥ እኒኹ ኹሉ ታሳቢ ተደርገው ነው። የእግዚአብሔር አካል ሲባል ወደ ሕሊናችን የሚመጣው ሥዕል የእኛ መሰሉ ቅርጽ ከኾነ የእግዚአብሔርን እግዚአብሔርነት መዘንጋት ነው የሚኾነው። እንደሚታወቀው መገለጦች ኹሉ የተሰጡት ለሰዎች ነው ፤ እነዚያ መገለጦች ደግሞ በሰው መረዳት ልክ የኾኑ ናቸው ፤ ለእኛ ተመጥነው የተሰጡ መገለጦችን ያለቀላቸው የእግዚአብሔር ውክያ አድርጎ መውሰድ ይኽን የምሥጢር ድንበር መዝለል ነው።
አንድ እና ኹለት የለውም እግዚአብሔር አካላዊ ነው። በኹኔታዎች [በተፈጣሪያኑ ውስጥ ያለ ፥ እነሱም ጸንተው ያሉበት] ውጥረት እና ጽምረት የሚመላለስ/ተገላጭ ኀይልም [በእሱ የሚኾን ቢኾኖም] አይደለም ፤ አማን በአማን እግዚአብሔር አካላዊ ነው። ሰው ኹነን አካላዊነትን ከእኛ አካልነት ውጪ መረዳት አይቻለንምና ፥ የእግዚአብሔር አካል በእኛ አካል አንጻር ተገልጿል። ይኽ ማለት ቀጥታ የእኛ አካል የእግዚአብሔር አካል ተመስያ ነው ማለት አይደለም። አካለ እግዚአብሔር በእኛ ሕሊና ከሚሣለው አካል የወጣ ፥ በማንም የማይመረመር የአካሎች ኹሉ ፍጻሜ የኾነ ፍጹም አካል ነው።
በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እግዚአብሔር አካል የተነገሩ ምንባባት በዚኽ አግባብ የምንረዳቸው ናቸው። እግዚአብሔር ከተጻፈው ከሚጻፈው ፥ ከታሰበው ከሚታሰበው ፥ ከተነገረው ከሚነገረው ኹሉ በላይ ነው። እንደ እግዚአብሔርነቱ ማንም ምንም ማለት አይችልም ነበር ፤ ግን ከቸርነቱ የተነሣ ለኹለቱ [መላእክት እና ሰዎች] ፍጡራን ስለ እሱ ሊሉ በሚችሉበት መጠን ፣ ሊረዱት በሚችሉበት መጠን ማንነቱን ገልጦላቸዋል። አኹን ያለን መገለጥ/መረዳት ስለ እግዚአብሔር እኛ ልናውቀው የቻልነው መጠን ነው።
-------------------------------
📜ያገምሩ ኵሎ ወአልቦ መኑሂ ዘያገምሮሙ ብርሃናት ቀዳማውያት ፤ ዘኢየአምር መኑሂ ዘከመ እፎ ውእቱ ክዋኔሁ ፤ ወኢያገምሮሙ ልቡና ፤ ወኢያስተጋብኦሙ ሕሊና ፤ ይሬእዩ ኵሎ ፥ ወኢያስተርእዩ ፤ ወአልቦ ዘይትማሰሎሙ ፤ ወይትዔረዮሙ ሕያዋን እሙንቱ እለ ኢይመውቱ ፤ ወኢይትዌለጡ ፤ ርኁቃን እምነ ኵሉ ወቅሩባን ለኵሉ ለባውያን ፤ ወማእምራን ፈድፋደ እምነ ኵሉ ፤ ኢፍጡራን ፤ ወኢይትረከቡ በሐልዮ ወበለብዎ ፤ ርኁቃን ወልዑላን እሙንቱ ፤ አምጻእያኒሆሙ ለኵሉሙ ፍጡራን እም ኀበ ኢሀልዎ ኀበ ሀልዎ፨
☞ኹሉን ይወስናሉ እንጂ የሚወስናቸው ምንም ምን የለም ፤ ኹኔታቸው እንዴት እንደኾነ ማንም የማያውቅ በቅድምና የነበሩ ብርሃናት ናቸው። ልቡና አይመረምራቸውም ፤ ሕሊና አይወስናቸውም ፤ ኹሉን ያያሉ እነርሱ ግን አይታዩም ፤ የሚመስላቸው የሚተካከላቸው የለም ፤ የማይሞቱ የማይለወጡ ሕያዋን ናቸው። ከኹሉ [መረዳህ] የራቁ ለኹሉ [በመግቦት/በሃይማኖት] የቀረቡ ናቸው ፤ ከኹሉ ይልቅ ዕውቀት የባሕርያቸው ነው። ያልተፈጠሩ ናቸው ፤ በማሰብ በመመርመር አይገኙም ፤ ከ’መ’መ’ርመር የራቁ የረቀቁ ናቸውና። ፍጥረታትን ኹሉ ካለመኖር ወደ መኖርያመጡ እነርሱ ናቸው፨
📜➬ ሃይማኖተ አበው ዘሱንትዩ ፻፱ ፥ ፫
ምሥጢሬ አይታወቅም ፤ ነገር ግን የአንተ አእምሮ ሊቀበለው የሚችለውን ምሥጢር አነግርሃለኹ።
➬ መጽሐፈ ቀሌምንጦስ
“ #እግዚአብሔር_መንፈስ_ነው ” — የዮሐንስ ወንጌል ፬፥፳፬ / 4፥24▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬ ©️ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ
📚#ተንከተም📚
👉ይህ መጽሐፍ፥ ጸሎተ ሃይማኖትን እየጸለዩ የይዘቱን ጥልቀት የማያወቁትን ሁሉ ከአምስት ደቂቃ ላልበለጠ ጊዜ የሚጸልዩት ጸሎት ምን ያህል ሰፊ እንደሆነ የሚያመላክት ግሩም መጽሐፍ ነው። እንግዲያውስ ከ፲፪ቱ አበው የተቀበሉትን፣ ሊቃውንት በ፲፪ አንቀጾች የቀመሙትንና ፲፪ በሮች ወዳሏት መንግሥተ ስማያት የሚያስገባንን ጸሎተ ሃይማኖት በ፲፪ ምዕራፎች ላቀረቡልን ሊቀ ሊቃውንት፥ ዕድሜ፣ ጤና እንዲሰጥልኝ እየተመኘሁ፡ ባለ፲፪ የሆናችሁት እንድታነቡት በ፲፪ቱ ሐዋርያት ስም እጋብዛለሁ፡፡ ሊቀ ሊቃውንትን ስምዐኮነን እና ሌሎች ሊቃውንትንም ልክ እንደዚህ የተቋጠሩትን እንድታፍታቱልን በዚሁ አጋጣሚ አሳስባለሁ፡፡
✍️ከዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
📚#አምስቱ_የንስሐ_መንገዶች
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“ጠላቶቼ ኹሉ ይፈሩ፥ እጅግም ይጐስቁሉ” (መዝ.6፥10)
ይህ ጸሎት ታላቅ የኾነ ጥቅም አለው - ጠላቶች ሲያፍሩና ወደ ኋላ ሲሉ! ምን ማለት ነው? በክፉዎች መንገድ የሚኼዱ ሰዎች ሲያፍሩና ወደ ኋላቸው ሲያፈገፍጉ ከክፋታቸው ይመለሳሉና፡፡
አንድ ሰው በፊቱ ወዳለው ገደል ለመውደቅ እየተንደረደረ እንደ ኾነ ስናየው፡- “ወንድሜ ሆይ! የምትሮጠው ወዴት ነው? በፊትህ ያለው’ኮ ገደል ነው” እንደምንለው ኹሉ፥ ክቡር ዳዊትም “ጠላቶቼ ኹሉ ይፈሩ፥ እጅግም ይጐስቁሉ” ሲልም እነዚህ ሰዎች ከክፉና እነርሱን ከሚያጠፋቸው መንገዳቸው እንዲመለሱ እየጸለየ ነው፡፡
📚 ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
📚#በእንተ_ክህነት
➮ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው
📚 ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
📚 #ፍና_ቅዱሳን
‹‹እግዚአብሔር በአንድም መንገድ በሌላም ይናገራል››
ደቀመዝሙር ለመምህር፤ ምዕመንም ለካህን መመለስ ምክንያት ቢሆን አይደንቅም፡፡ ለበለዓም መመለስ አህያን፣ #ለቅዱስ_ጴጥሮስ ንስሐም ዶሮን እግዚአብሔር ተጠቅሟል፡፡ መስማት መቻል የእኛ ፋንታ ነውእውነተኛ ማንነታችን በስም፣ በማዕረግ፣ በእውቀት፣ በዕድሜ ወዘተ... ተሸፍኖ ሊኖር ይችላል፡፡ ዛሬ ብዙዎቻችን ጋር ያለው ከልብ ያልሆነ የማስመሰል ክርስትና ነው፡፡ መማር፣ መቀደስ ማስቀደስ፣ መዘመር፣ መስበክ ወዘተ... ብቻ ክርስትና መስሎን የምንኖር ብዙዎች ነን፡፡ ይኸውም እንኳ የልማድ እንጂ ከውስጥ ያልሆነ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሥርዓተ አምልኮ ክፍል እንጂ በራሱ ብቻውን የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫ አይደለም፡፡ ስለዚህ ቤተክርስቲያን ሔደን ስለተማርን፣ ስላስቀደስን፣ ስለዘመርን ወይም አገልጋዮችም ስላስተማርን፣ ስለቀደስን፣ ስላስተዳደርን ብቻ ክርስትናን እየኖርን ከመሰለን ተሳስተናል፡፡ ተክል ፍሬ እንዲያፈራ ውሃ፣ ማዕድን፣ የፀሐይ ብርሃን ወዘተ... እንደሚያስፈልገው እኒህም መንፈሳዊ ፍሬ እንድናፈራ የሚያደርጉን ናቸው፡፡ አብዛኞቻችን ግን በእነዚህ ብቻ ታጥረን ቆመናል፡፡👉🏿 የክርስትና ሕይወት መገለጫ ፍቅር፣ ቅድስና፣ ንጽሕና፣ ትኅትና፣ ትዕግሥት፣ ቅንነት፣ ይቅር ባይነት፣ በሌላ አለመፍረድ.... እኒህንም የመሳሰሉት ናቸው፡፡ በመመላለሳችን ሁሉ እኒህ ከሌሉ የክርስትናን ጭምብል አጥልቀን እየተወንን እንጂ ክርስትናን አይደለም፡፡ ብርሃን ከጨለማ በቀላሉ እንደሚለይ ክርስቲያንም በግብሩ ከአሕዛብ በቀላሉ ይለያል፡፡ መለያው ደግሞ ሕይወቱ እንጂ የአገልግሎት ተሳትፎው አይደለም፡፡
📚ፍኖተ መጻሕፍት
t.me/FinoteBooks1623
📚#ሰማዕትነት_አያምልጣችኹ
በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
«የኅሊና ዳኛ»
#እግዚአብሔር በእያንዳንዳችን ኅሊና ውስጥ፣ ኹል ጊዜ ንቁና ትጉ የኾነ ዳኛ ያስቀመጠው ስለ ምንድን ነው ብለኅ ብትጠይቀኝ፣ ከሰው ወገን ይኽን የ'ኅሊና ዳኛ'ን የመሰለ፣ እንቅልፍ የለሽ ዳኛ ስለሌለ ነው ብዬ እመልስልሃለኹ፤ ዳግመኛም፣ የውጪ ዳኞች በገንዘብ፣ በውሸት በመደለል፣ የሐሰት ፍርድ እንዲሰጡ በማስፈራራት፣ እንዲኹም በሌሎች መጠነ ብዙ ምክንያቶች፣ ርቱዕ የኾነ (ያልተዛባ) ውሳኔአቸውን ሊያጣምሙ ይችላሉ፤ የ'ኅሊና ዳኛ'ን ግን በእነዚኽ በገለጽናቸው ምክንያቶች በምንም መንገድ የሚደለል አይደለም፤ ጉቦ ብንሰጠው፣ ልንዋሸው ብንሞክር፣ ብናስፈራራው፣ ሌላ ሌላም ብናደርግ እንኳ፣ ይኽ የ'ኅሊና ዳኛ' ለምናስበውና ለምንሠራው ኀጢአት ምንም ሳይጠመዝዝ እውነተኛ ፍርድን ይሰጣል፤ ኀጢአት የሠራ ሰው፣ ሌላ ሰው ባይወቅሰውም እንኳ፣ ርሱ ራሱ ራሱን ይወቅሳል፤ አንዴ ወይም ኹለቴ ብቻ አይደለም፣ መላ ዘመኑን እየደጋገመ ኅሊናው ይወቅሰዋል፤ ኅጢአት የሠራነው ከረዥም ዘመናት በፊት ሊኾን ይችላል፤ የኅሊናችን ዳኛ ግን ያን የሠራነው ጥፋት ፈጽሞ አይረሳውም።
📚ፍኖተ መጻሕፍት
t.me/FinoteBooks1623
📚#ግሩም_ምክሩ
፲፫ቱ ሕማማተ መስቀልና የሕማሙ ቅኔ ከሊቃውንት
Ⓒበእማኾይ ወለተ-ማርያም መንግሥት መርጡለ ማርያም የሴቶች የቅኔ ጉባኤ ቤት የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜና የቅኔ መምህርት
📚 ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
📚#አንቀጸ_ብርሃን
አንድምታ ትርጓሜ
#አንቀጸ_ብርሃን ፦ የብርሃን ደጃፍ ፤ የብርሃን መስኮት፤ የብርሃን በር፤ አለ፦ ከሌሎች አናቅጽ ሲለያት አንቀጸ ብርሃን አላት። መስታዎት ሲላት ነው። በሌሎቹ አናቅጽ ግዙፋኑ ግሡሳኑ ፍጥረታት ይገቡባቸዋል ይወጡባቸዋል። በዚህ መስታዋት ግን ከብርሃን በቀር ሌላ ነገር አይገባባትም አይወጣባት። እመቤታችንም ብርሃን ዘበአማን ከሚባል ከጌታ በቀር ሌላ ልጅ የላትምና።አንድም ሌሎቹ አናቅጽ ካልተከፈቱ አያስገቡም ካልተዘጉ አይከለክሉም። መስታዋት ግን በዝግነት ሳላ ብርሃንን ያሳልፋል ብርሃንን ሲያስገባ ግዙፋኑን ፍጥረታት ነፋሳትን ማያትን ሳይቀር ይከለክላል። አንድም..
***ይነበብ...
📚 ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
🌹 ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ :
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ ::
" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን(አስገኘችልን) "
◉እርሱም ራሱ ልዑል መሠረታት:: +"+ (መዝ. 86:5)
‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌዉ በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል።#ይህ_መቅደሱን_የሰራበት_ዕለት_ነዉ፡፡ ይህዕለት ትልቅ ህንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነዉ፡፡››
[የቀርጤሱ ቅ/እንድርያስ]
#ማርያም ማርያም ይላል ምጥም እንዳያቄም
#በማን_ስም? ወለዱሽ ሐና እና ኢያቄም
✨ዮም ፍስሐ ኮነ
በእንተ ልደታ ለማርያም!
…... ለጠቅላይ ቤተ ክህነት የተጻፈላቸውን ደብዳቤ ይዘው ቤተ ክህነት ሲደርሱ፤ የቤተክህነቱ ባለሥልጣናት ‘እንዴት ለአንድ መምህር ደመወዝ አንድ መቶ ብር ይከፈላል? ለእርስዎ ሃያ ብር ይበቃዎታል’ ብለው ቀነሱት፡፡
ሆኖም በሁኔታው ያዘኑ የእርሳቸው የሆኑ ሰዎች ‘ንጉሡ የፈቀዱትን እዚህ ያሉት ሠራተኞች ሊቀንሱ ስለማይችሉ አሁንም ሄደው ያመልክቱ’ ይሏቸዋል፡፡
እሳቸውም ‘ሄጄ የማመለክተው እዳ ለምን ተቀነሰልኝ ብዬ ነው? ይኼውም ሲበዛብኝ ነው’ ብለው ያንን ሃያ ብር ደመወዝ ተቀበሉ፡፡
ታዲያ አዲስ አበባ ሄደው በነበሩበት ጊዜ ….. ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን ይሄዳሉ፡፡ ቀደም ሲል ጎንደር አብረዋቸው ይማሩ የነበሩት አለቃ የማነብርሃን የሚባሉ ዳር ሀገር እየተባለ ከሚጠራው ቦታ የሚኖሩ በአጋጣሚ ለጉዳያቸው አዲስ አበባ መጥተው ኖሮ እዚሁ አራዳ ቅዱሰ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን ድንገት ይገናኛሉ፡፡
መንፈሳዊ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ስለኑሯቸው ሲወያዩ፡-
‘አዬ ጥበቡ! ለእኛ ትበጃለህ ብለን የምናምንብህ እዚያ ከገጠር ተሸጉጠህ ቀረህ፡፡ እኔን እንኳ እስኪ ተመልከተኝ’ ብለው በኑሯቸው የደላቸው መሆናቸውን ለማስረዳት ሲሞክሩ፡-
‘አዬ የማነብርሃን! እኔም እኮ የጠላሁት እንዳንተ መሆኑን ነው’ አሏቸው…..”
ከውስጥ ገጽ
«#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ»»
📚ፍኖተ መጻሕፍት
t.me/FinoteBooks1623
📚#ዝክረ ቅዱሳን አንስት ዘተዋሕዶ ፩
...#የጣማፍ_ኄራኒ አኗኗር ገዳማዊነትን በትክክል ላየ ሰማያዊ ሰው ወይም ምድራዊ መልአክ የሚያሰኝ ነው። በዚህ የተቀደሰ ኑርዋ ውስጥ የጥንታውያኑን ገዳማውያን አበውና እማት አኗኗር እንድናይ አድርጋናለች። ሥርዓቱን ከሕይወቷ ጋር እያናበበች ወይም እየኖረች በማሳየት አዲሱ ትውልዳችን የጥንታውያኑን ክርስ ቲያኖች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሕይወትና ፍቅረ እግዚአብሔርን ገንዘብ ያደርግ ዘንድ፥ እንደ መጽሐፍ የሚነበብ አገልግሎቷንና ተጋድሎዋን ማቅረብ የቤተ ክርስቲያን ቀዳሚ ተግባሯ ነው᎓᎓ ከባሕር የወጣ ዐሣና ከገዳሙ የወጣ መነኰስ አንድ ናቸው እንደሚባለው ሁሉ፡ ከወንጌል የራቀ ክርስቲያንም የነፍስ ድኅነት የለውምና፥ ወንጌል ከሆነው የቅዱሳን አበውና እማት ሕይወት እንማር።በአጠቃላይ የመጽሐፉ ዐላማ ሴቶች በመንፈሳዊ ጉዞአቸው ከወንዶቹ በምንም እንደማይተናነሱና ይህንንም በተለያዩ ዘመናት የነበሩ አንስት በገድል እየኖሩ ያሳዩ መሆ ናቸውን ማሳወቅና መልካም አርአያነታቸውንም መግለጽ ነው።
Ⓒለረዥም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረው ይህ መጽሐፍ በጥሩ ኅትመት በድጋሚ ወደ ገበያ መጥቷል።
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
💧በድጋሚ ታትሟል
📚#ኢትዮጵያዊው_በማንነቱ_ፍለጋ📚
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
#ተወዳጆች....
➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በጉምቱ መምህራችን በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተቀመመው ድንቁ መጽሐፋችን #መድሎተ ጽድቅ ቅጽ-፩ #ለ20ኛ_ጊዜ_ታትሟል!!
''ለሰው ልጆች መዳኛ ትሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠችው አንዲቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ክርስትና በሰዎች ግለሰባዊ አስተሳሰብና 'መሰለኝ' በሚል ግምትና መላ ምት የተገኘች ሳትሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠች ናት፡፡''
[ከውስጥ ገጽ....]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
#ተወዳጆች....
➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በጉምቱ መምህራችን በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተቀመመው ድንቁ መጽሐፋችን #መድሎተ ጽድቅ ቅጽ-፩ #ለ20ኛ_ጊዜ_ታትሟል!!
''ለሰው ልጆች መዳኛ ትሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠችው አንዲቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ክርስትና በሰዎች ግለሰባዊ አስተሳሰብና 'መሰለኝ' በሚል ግምትና መላ ምት የተገኘች ሳትሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠች ናት፡፡''
[ከውስጥ ገጽ....]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
