fa
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

رفتن به کانال در Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

نمایش بیشتر
3 315
مشترکین
+724 ساعت
+267 روز
+11030 روز
آرشیو پست ها
The Mekane Yesus Seminary community celebrated Christmas. The community celebrated Jesus’ birthday with a prayer, songs, a pr
+8
The Mekane Yesus Seminary community celebrated Christmas. The community celebrated Jesus’ birthday with a prayer, songs, a proclamation of the word of God, and the Lord's Supper. The event took place at Ammanuel G/Selase Hall.

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት አገልጋዮችና ሰራተኞች የ2016 የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓልን ዛሬ በጽሕፈት ቤቱ አዳራሽ
+9
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት አገልጋዮችና ሰራተኞች የ2016 የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓልን ዛሬ በጽሕፈት ቤቱ አዳራሽ በፀሎት፣ በአምልኮ እና የእግዚአብሔርን ቃል በመከፋፈል በጋራ አክብረዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱም መሪዎች ለሰራተኞቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus head office ministers and staffs celebrated the 2024th birth of our Lord and Savior Jesus Christ, today in the office hall with prayer, worship, and sharing the word of God. Leaders of the church also conveyed holiday greetings for the workers.

Upcoming_Day! መጪ የቤተክርስቲያኒቱ ቀን! #የኢትዮጲያ_ወንጌላዊት_ቤተ_ክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_የሚስዮን_ቀን ጥር 12/2016 - በመላው የቤተክርስቲያኒቱ ማህበራነ ምዕመናን ይከበራል። Th
Upcoming_Day! መጪ የቤተክርስቲያኒቱ ቀን! #የኢትዮጲያ_ወንጌላዊት_ቤተ_ክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_የሚስዮን_ቀን ጥር 12/2016 - በመላው የቤተክርስቲያኒቱ ማህበራነ ምዕመናን ይከበራል። The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus Mission Day! January 21/2024 - it will be celebrated at every congregations.

Balaawwan akkasii kuni rakkina nageenyaatiin akka walii galaatti biyyattiin keessa jirtuun kan wal-qabatee gatii ta’eef nageenya karaa nagaatiin mirkaneessuuf jecha qamoliin qabsoo hidhannaatiin socho’aa jiran hundumtuu gara maree fi araaraatti akka deebi’an ammas irra deebinee waamicha goona. Waaqayyos haala biyya keenyaa keessa seenee nagaa isaa akka buusuuf kadhataa fi waammataan fuula araara isaa barbaaduun amantoota irraa ni eegama. Inni mootii nagaati! Egaan, Ayyaana Dhaloota Kiristoos yeroo ayyaaneffannu kana dhoksaan isaa maal akka ta’e hubataa ayyaaneffachuun ga’ee amantootaati. Ayyaanni namni ofii isaa duwwaaf utuu hin ta’in Waliifis jiiraachuun akka maluu nu yaadachiisuu qaba. Kanaafis, namoota haala adda addaa irraa kan ka’e rakkina keessa jiran hundumaaf, walumaa galatti warra jireenyi itti hir’ate ammas ta’u yeroo hundumaatti birmadhaafii; arjummaanis wal yaadadhaa, gaarummaa duwwaa waliif hawwa’a; nagaas waliif fedhaa. Waaqayyo waaqni nagaa gaarummaa isaatiin yeroo hundaa isin haa yaadatau. Ayyaanichi ayyaana gammachuu fi eebbifamaa hunduma keessaniif haa ta’u; waaqayyo biyya keenyaaf nagaa haa buusu! Waaqayyo isin haa eebbisu; isin haa eegus; Waaqayyo fuula isaa isiniif haa ibsu; isinitti haa araaramus; Waaqayyo fuula isaa gara keessanitti haa deebisu, nagaa isaas isiniif haa kennu. Luba Dr. Yonas Yigezu, Prezidaantii WKWW Makane Yesus Itiyoophiyaa.

#Waldaa_Kiristiyaanaa_Warra_Wangeelaa_Makane_Yesus_Itiyophiyaa. Ayyaana Dhaloota Gooftaa Keenya Yesuus Kiristoos kan bara 2016 ilaalchisee Ergaa Uummata biyyattii maraaf darbe. Maqaa Abbaatti, kan Ilmaatti, kan Hafuura Qulqulluuttis Waaqayyo tokko, Ameen! “Mucaan nuuf dhalateera, ilmis nuuf kennameera; humni mootummaa isaa gatiittii isaa irra jira; maqaan isaa, “Gorsaa, dinqii, waaqayyo-jaba’a, abbaa bara baraa, angafa nagaa” in jedhama.” (Raj. Isa. 9:6) Waaqayyotti kan jaallatamtan, kabajamtoota uummata Biyya keenyaa, biyya keessaa fi biyya ambaa kan jiraattan, bakka adda addaatti, haala adda addaa keessa taatanii, Ayyaana Dhalachuu Gooftaa Keenyaa Yesuus Kiristoos kan bara 2016 ayyaaneffachaa kan jirtan Kiristiyaanotaa! Ayyaanaa fi Araara isaatiin hunduma keenya nagaatti eegee Ayyaana dhalachuu Gooftaa keenya Yesuus Kiristoosiin kan bara 2016tiin isa nuga’ee Waaqayyoof galanni haa ta’u. Baga Waaqayyo Ayyaana Ifa dhaloota isaatiitiin isin ga’e jechuudhaan Maqaa Waldaa Kiristiyaana Warra Wangeelaa Makane Yesuus Itiyoophiyaatii fi maqaa kootiin hawwii garrii isiniif ibsuun jaalladha. Baga ittiin isin ga’e!. Waggaa waggaan guyyaa dhaloota Gooftaa keenya yesus Kiristoos kan kabajnu Waqayyo uumaan keenya tokkicha ilma isaa gara biyya lafaatti ergudhaan ilmaan namaa ofittii ararsuufi goocha gudda inii raawwate yadachuudhan isaa galateeffachuudhaf. Waqayyoo gooftaan keegnaa Ilman namaa gara ulfina isaa isa duraaniitti deebisuuf hojii isaa isa dinqisiisaa hubannaa namaa ol ta’een, tookkichi ilmii isaa foon uffatte namoota gidduu dedeebi’uu dhaan nagaa akka labsu fi gatii cubbuu ilmaan namootaa baasuu dhaan nama ofii isaatti araarse. Kuniis waqayyo biyya lafaa tiif nagaa keenudhaf gatiin inni base ammam guuddaa akka ta’ee muliisaa. Nagaan guutumaa biyya lafaa booqoochiisuu danda’uus kara kana duwwaadhan argama. Goftan keegna Yesus Kristoos ; “ Nagookoo isiniif nan kenna, ani akka biyyi lafaa kennuttan isiniif kenna miti (Yoh. 14:27)” jedhee dubachuun isaas waqaayyoo nagaa isa dhugaa biyya lafaatiff kan ergee kara yesus duwwaa akka ta’ee ibsa. Kennaa, gaarummaa fi jalala isaa isa daangaa hinqabneef galannii isaaf hata’uu. Kabajamtoota uummata Biyya keenyaa; Waaqayyotti kan jaallatamtan amantootaa! Wa’een nageegna biyya keenyaa daran yaddessa ta’ee yemmu jiru kan keessatti ayyaana dhalachuchuu gooftaa keegna yesus kristoos yeroo kabajnu, waqayyo nagaa busuudhaf kara gooftaa keynaa Yesus Kristoos waan nuuf raawwate yaadachaa isa galateeffachuunii fi, nagaa buusuudhaaf fakkeenya kiristos hordofuun ni mala. Inni nagaan haa ta’u akkuma jedhe, nuti warri isatti amannu nagaan akka bu’uuf gama hundumaan dhama’uutu mala. Waldaan Kiristyanaa Warra Wangeelaa Makane Yesus Itiyoophiyaa, wal-dhabdeen biyya keynaa keessa jiruu kam iyyuu, furmaata argachuu kan danda’uu maree, wal-dhaggeeffachuu fi araaraan duwwaan akka ta’e yeroo adda addaatti irra deddebitee hubachiisaa turte. Waldaan Kiristiayaanaa Ilmaan namaa nagaa fi jaalalaan akka waliin jiraataniif wangeela nagaa lallabdii; kuniis itti gafatama ishe isa guddaa dha. Wal-ajjeechaa fi miidhaa bifa kamiin iyyuu uummata irra ga’uun ni mormiti. Waaqayyo namni akka badu hin jaallatu; kanaafis karaa kiristoos araara buuse du’a jireenyatti jijjire. Kanaafis namni hundinu mirga jireenyaan jiraachuu qaba; kuni immoo bifa hundumaan mirkanaa’uu mala. Waldaan Keenyaa rakkolee nageenyaa yeroo dhaa gara yerootti bakka adda addaatti uumamani irraa kan ka’e yeroo yerootti midhamaa akka jirtuu bekamadha. Kanafis ji’a Sadaasa darbee keessaa Zoonii Qellem Wallaggaa, aanaa Gidaamii keessatti amantoota nama sagal mana sagadaa keessa kadhata irra turani irratti ajjeechaan haala suukanneessaadhaan raawwatame fakkeenya tokko. Haala kana ilaalchise Waldaan keenya gadda guddaadhaan balaleffachuu ishee irra iyyuu gama mootummaatiinis hordoffiin godhamee uummataaf ifa akka ta’uu gaafachuun ishee ni yaadatama.

#የኢትዮጵያ_ወንጌላዊት_ቤተ_ክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ የ2016 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የመልካም ምኞት መግለጫ አዲስ አበባ በአብ፣ በወልድ ፣በመንፈስ ቅዱስ ስም አንድ አምላክ፣ አሜን! ‹‹ ሕጸን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣  የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል፡፡››   በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ እና የተከበራችሁ፤ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን፤ የክርስትና እምነት ተከታዮች፤ ህዝበ ምዕመን፤ መላው የአገራችን ህዝቦች፤   ከሁሉ በማስቀደም አምላካችን እግዚአብሔር ምሕረቱንና ቸርነቱን አብዝቶልን በሰላምና በጤና ጠብቆ ለ2016 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ስለ አደረሰን ለእርሱ ምስጋና፤ ክብርና ውዳሴ ይሁን እያልኩ በራሴና በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ስም እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቴንና የተሰማኝን ደስታ ልገልጽላችሁ እወዳለሁ፡   የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል በየዓመቱ የምናከብረው ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለውን ታላቅ ፍቅር የገለጸበትና  ቅዱስ ትዕዛዙን በመተላለፍ በኃጢአት የወደቀውን የሰው ልጅ ከራሱ ጋር ያስታረቀበትን መለኮታዊ የማዳን ሥራ ለማሰብና እርሱን ለማመስገን ነው፡፡ እግዚብሔር አምላካችን የሰውን ልጅ ወደ ቀደመው ክብሩ ለመመለስ ከሰው አዕምሮ በላይ በሆነው ድንቅ አሰራሩ መለኮት ሥጋ ለብሶ በሰው መካከል በመመላለስ ስለ ሰላም እንዲያውጅና የሰላም እንቅፋት የሆነውን የኃጢአትን ዋጋ በመክፈል ለሰው ሁሉ የሚሆን እውነተኛ ሰላምን ሊያረጋግጥ፤ የሄደበት መንገድ እና ለዚህም የከፈለው ዋጋ መገመት ከሚቻለው በላይ እጅግ ታላቅ እንደሆነ ያረጋግጣል፡፡  ለዓለም ሁሉ የሚሆን እውነተኛ ሰላም የሚገኘው በዚሁ መንገድ ብቻ ነው፡፡ ጌታችንና መዲኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደበት በዚያች ሌሎት መላዕክትና የሰማይ አእላፋት “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን፤ ሰላምም በምድር፤ ለሰውም በጎ ፈቃድ (ሉቃ 2:14)” ብለው ያሰሙት ዝማሬ በእርሱ መገለጥ በሰማይና በምድር መካከል ፍጹም የሆነ ሰላም መውረዱን ያበሰረ የምስራች ዜማ ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም…›› (ዮሐ. 14፡27) በማለት ለተከታዮቹ ዳግም ሲያረጋግጥ እግዚአብሔር በእርሱ በኩል ለዓለም የላከው ሰላም ፍጹም መሆኑን ያስታውሰናል፡፡ ለዚህ ለማይነገረው ስጦታው፣ ለፍቅሩና ለቸርነቱ ክብርና ምሥጋና ይድረሰው፡፡ የተከበራችሁ የአገራችን ሕዝቦች፤ በጌታ የተወደዳችሁ ሕዝበ ምዕመን! በዓለማችን የሰላም ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ በሆነበት በአሁኑ ጊዜ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ስናከብር እግዚአብሔር በራሱና በሰው ልጆች መካከል፤ እንዲሁም በሰው ልጆች መካከል የነበረውን ጥል አስወግዶ ሰላምን ለማውረድ ያደረገውን ማሰብ ብቻ ሳይሆን የክርስቶስን ምሳሌነት ለመከተል መወሰንን ይጨምራል፡፡  በተለይም በአሁኑ ጊዜ  በአገራችን የሚታዩት ግጭቶችና አለመረጋጋቶች ተወግደው ሰላም እንዲሰፍንና አገራዊ አንድነት እንዲረጋገጥ መላው የአገራችን ሕዝቦችና ሕዝበ ምዕመኑ እንደወትሮው የእግዚአብሔር አምላካችንን ጣልቃ ገብነት ተግተው መለመንና አቅም የፈቀደውን ሁሉ ለማድረግ መዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል፡፡   የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በአገራችን በተለያዩ ቦታዎች ለሚነሱ  አዳዲስ ግጭቶችም ሆነ ለሰነበቱት አለመግባባቶች ዋነኛ መፍትሔ ሊሆን የሚችለው በሰላማዊ መንገድ  ተቀራርቦ መመካከርና መነጋገር ብቻ እንደሆነና የትጥቅ ፍልሚያ ሰላም ሊያመጣ እንደማይችል ታምናለች፡፡ የሰው ልጆች አብረው በሰላምና በፍቅር እንዲኖሩ የሰላም ወንጌልን ትሰብካለች፡፡ ከሰላም እጦት የተነሳ የሚፈጠረውን ሞትና እንግልት ትቃወማለች፤ በበኩልዋም ችግሮች ሲፈጠሩ ለእርቅና ለሰላም ጥረቶች የምትጠየቀውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆንዋንም በየጊዜው ስትገልጽ  ቆይታለች፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱም ራስዋ በየጊዜው በተለያዩ ታጣቂ ኃይላት መካከል በሚከሰቱ ግጭቶች ቀጥታ ተጠቂ የሆነችባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው፡፡ ለዚህም በቅርብ ጊዜ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቄለም ወለጋ ዞን በጊዳሚ ወረዳ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በጸሎት ላይ በነበሩ ንጹሐን ምዕመናኖቻችን ላይ  የደረሰው የጅምላ ግድያ በማሳያነት ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ በጊዜው ድርጊቱን ከመቃወምና ከማውገዝ ባሻገር ሁኔታውን አስመልክቶ ክትትል እንዲደረግና ለህዝብ ይፋ እንዲሆን ጥሪ ማድረግዋ የሚታወስ ነው፡፡ አያይዛም እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት ላንዴና ለመጨረሻ ለማስወገድ የትጥቅ ፊልሚያዎችን አቁሞ ለሰላማዊ ምክክር ዕድል መስጠት ብቸኛ አማራጭ እንደሆነም አስታውሳለች፡፡ አሁንም ይህንኑ ጥሪ ደግማ ደጋግማ ማሰማትዋን ትቀጥላለች፤ ምዕመናንዋንም በዚሁ መስመር በጸሎት በማትጋት ላይ ትገኛለች፡፡ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥም፤ እርሱ የምህረት ፊቱን ይመልስልናል፤ ሰላሙንም በእርግጥ ይሰጠናል፡፡ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ይህንን ዕድል በመጠቀም ጤና ነክ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያም የተለየ ጥሪ ማድረግ ትወዳለች፡፡ በተለይም የኤች አይ ቪ ስርጭትን ለመግታት እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ዜጎች ሁሉ የየበኩላቸውን ብርቱ ተሳትፎ እንዲያደርጉ፤ ምርመራ ማድረግን እንዲያበረታቱ፤ መዲኃኒት መውሰድ የጀመሩት በምንም ምክንያት ሳያዛንፉ እንዲወስዱ፤ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ወገኖች እንዳይገለሉ አስፈላጊው ጥረት እንዲያደርጉ አበክረን እናሳስባለን፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በአገራችን በአሁኑ ወቅት የወባ ወረርሽኝ ከፍተኛ ጥቃት እያደረሰ ስለሆነ በዚህም ረገድ መንግሰትና ህብረተሰቡ በጋራ እንዲንቀሳቀሱና የወባ ታማሚዎችም በቂ የህክምና አገለግሎት እንዲያገኙ የሚመለከታቸው ሁሉ ጥረት ያደርጉ ዘንድ አደራ ለማለት እንወዳለን፡፡ በጌታ የተወደዳችሁ ምዕመናን፤ ይህንን በዓል ስታከብሩ እግዚአብሔር በልጁ በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያሳየንን ፍቅርና ወደር የሌለውን ቸር ሥጦታውን እያሰባችሁ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ከቤት ከንብረታቸው ለተፈናቀሉትና ምንም መተዳደሪያ ለሌላቸው ወገኖች እንድትራሩ፣ ህመምተኞችን፤ ድሆችን፤ አባትና እናት የሌላቸውን ሕጻናትን  በቸርነት እንድታስቡ፤ ለእርስ በርሳችሁ ቸርነት እንድታደርጉ፤ ለሰላምና ለመልካም አብሮነት እንድትፈላለጉ፤ በሆነ ሰበብ የተጋጫችሁም እንድትታረቁ በእግዚአብሔር ስም በአባታዊ ፍቅር እለምናችኋለሁ፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በዓሉን የሰላምና የደስታ ያድርግላችሁ፤ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ይጠብቃችሁ እግዚአብሔር ፊቱን ያብራላችሁ ጸጋውንም ይስጣችሁ እግዚአብሔር ፊቱን ይመልስላችሁ በረከቱን  ሰላሙንም ምሕረቱንም ያብዛላችሁ አሜን ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዚደንት

#Guyyaa_Ayyaana_Ijoollee WWWMYI #Baga_Ittiin_Isin_Gahe! 👉Guyyaa: Amajjii 05, 2016ALI 👉Luqqisii:- Maariqoos 10:14  "...Lakkisaa ijoolleen gara koo haa dhufan, hin dhowwinaa! Mootummaan Waaqayyoo warra akkasiitiif ta'a. …" 👉Mata Duree: ‘Ijoolleen Gara Yesuus Haa Dhufan’ 👉Guyyichatti:- Mata duree kenname irratti barumsi bal’aan nikennama, tajaajilli faarfannaa, walaloo, gaaffii fi deebii…garagaraa nidhiyaata. Maatiin ijoolleedhaaf kan kennamu badhaasa garagaraa qabatanii dhufu. Waliin immoo Waaqayyo waaqessu. 👉Tajaajila Ijoollee Deeggaruu:- Waldaa Amantootaa (Congregations) irraa kaasee hamma Waajjira Olaanaatti kan jiru tajaajila ijoollee deeggaruuf galiin walitta niqabama. Waaqayyo ijoollee keenyaa fi tajaajila isaanii dachaan eebbisuu!               *  *   *   * EECMY Children’s Day 👉Date: 05 January 2015 EC/14Jan.2023 👉Leading Verse: Mark 10:14 “Let the little children come to me, and do not hinder them, for the kingdom of God belongs to such as these." 👉Theme of the Day: "Let the Children Come to Jesus" 👉Main Activities of the Day: There will be teaching from the Bible on the selected theme, as well as various songs, plays, dramas, poems, question-and-answer sessions, etc. Parents will come up with gifts for the children, and Worship God together  👉Supporting the Children's Ministry: To support the church's children's ministry at all levels—from the congregation to the central office—fundraising will be done that day. May God bless our children and their ministry!!! EECMY Children Ministry https://t.me/MYSundaySchool

ለኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢ #የልጆች_በዓል_እንኳን_አደረሳችሁ! 👉ቀን፡- ጥር 05፤ 2016 ዓ.ም 👉መሪ ጥቅስ፡- ማርቆስ 10:14 “ ...ሕፃናትን ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉ አትከልክሉአቸው፤ የእግዚአ
+2
ለኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢ #የልጆች_በዓል_እንኳን_አደረሳችሁ! 👉ቀን፡- ጥር 05፤ 2016 ዓ.ም 👉መሪ ጥቅስ፡-  ማርቆስ 10:14 “ ...ሕፃናትን ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉ አትከልክሉአቸው፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደነዚህ ላሉት ናትና።" 👉መሪ ሃሳብ (ርዕስ)፡- “ልጆች ወደ ኢየሱስ ይምጡ” 👉በዕለቱ፡- በርዕሱ ዙርያ ሰፊ ትምህርት ይሰጣል፡ የተለያዩ የዝማሬ፡ የድራማ፡ የግጥም፡ የጥያቄና መልስ ውድድሮች…ወዘተ  ይቀርባሉ፡፡ ወላጆች ለልጆች የሚሰጥ ስጦታ ያመጣሉ: አብረው እግዚአብሔርን ያመልካሉ፡፡ 👉የልጆችን አገልግሎት መደገፍ፡- ከማ/ምዕመናን ጀምሮ እስከ ዋናው ጽ/ቤት ያለውን የልጆች አገልግሎት ለማጠናከር የገቢ ማሰባሰብ ሥራ ይሰራል፡፡ እግዚአብሔር ልጆቻችንን እና አገልግሎታቸውን አብዝቶ ይባርክ!!!                *  *   *   *

የኢ/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ የልጆች ቀን: ጥር 05/2016 ዓ.ም ××× Kabaja Guyyaa Ijoollee WWWMakaana Yesuus Itoophiyaa :- Amajjii 05, 2016ALI ×××
+1
የኢ/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ የልጆች ቀን: ጥር 05/2016 ዓ.ም ××× Kabaja Guyyaa Ijoollee WWWMakaana Yesuus Itoophiyaa :- Amajjii 05, 2016ALI ××× EECMY Children's Day :- January 14/2024 The department media accounts below 👇 https://t.me/MYSundaySchool EECMY Youth Ministry

ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን × × × ልጆች የነገ ፍሬዎች ናቸው: ወጣቶች ደግሞ የሀገር ተረካቢዎች ናቸው፡፡ ልጆች እና ወጣቶች ላይ ትኩረት ሰጥታ የማትሰራ ቤተክርስቲያን በአንድ እና
+8
ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን × × × ልጆች የነገ ፍሬዎች ናቸው: ወጣቶች ደግሞ የሀገር ተረካቢዎች ናቸው፡፡ ልጆች እና ወጣቶች ላይ ትኩረት ሰጥታ የማትሰራ ቤተክርስቲያን በአንድ እና በሁለት ትውልድ ጊዜ ውስጥ መጥፋቷ አይቀርም፡፡ ይሄ በምዕራባውያን አንዳንድ ቤተክርስቲያናት ሲሆን ታይቷል፡ ይሄ ውድቀት ወደ እኛም እንዳይመጣ ከእነርሱ ስህተት ተምረን ልጆች እና ወጣቶች ላይ ትኩረት ሰጥተን መስራት ይጠበቅብናል፡- ልጆች እና ወጣቶችን በእግዚአብሔር ቃል ማስታጠቅ፤ ወደ አገልግሎት እና መሪነት ማሳደግ ፤ በትምህርት እና በምክር ከክፉ የጠላት ወጥመዶች እና የስህተት ትምህርቶች መጠበቅ ይጠበቅብናል፤ ልጆች እና ወጣቶቻችን በሁለንተናዊ መልኩ እንዲያድጉ ማስተማር፤ አቅጣጫ ማሳየት እና ማበረታታት ይጠበቅብናል፡፡ በነገር ሁሉ እግዚአብሔር ጥበብን እና ማስተዋልን ያብዛልን: አሜን:: "በቃልና በኑሮ በፍቅርም በእምነትም በንጽሕናም ለሚያምኑቱ ምሳሌ ሁን እንጂ፥ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው።...ለማንበብና ለመምከር ለማስተማርም ተጠንቀቅ።...የተሰጠህን፥ በአንተ ያለውን የጸጋ ስጦታ ቸል አትበል። ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር። ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፥ በእነዚህም ጽና፤ ይህን ብታደርግ፥ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና።" 1ጢሞ. 4:12-16 ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን! EECMY Youth Ministry

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus Development and Social Services Commission (EECMY-DASSC) 102th Regular Board me
+7
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus Development and Social Services Commission (EECMY-DASSC) 102th Regular Board meeting has taken place at Skylight International Hotel, Addis Ababa. - - - - የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ-ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማትና መህበራዊ አገልግሎቶች ኮምሽን 102ኛ መደበኛ የቦርድ ስብሰባ በአዲስ አበባ Skylight ሆቴል አካሂዷል። Mekane Yesus Church Development Commission. EECMY DASSC

Tajaajiltootni 42 tajaajila Dubbii Waaqayyoo fi Dhoksaa Qulqulluu geggeessuuf muudamaniiru.                                   Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuusitti Sinoodosiin Giddu Galeessa Itiyoophiyaa tajaajila Dubbii Waaqayyoo fi Dhoksaa Qulqulluu adeemsisuuf namoota 42f Waldaa Amantoota Addis Ababaatti gaafa Muddee 14, bara 2016 itti gaafatamni Lubummaa Kenneeraaf. Guyyaa kanattis Pirezedaantiin Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Lubni Dr. Yoonaas Yiggazuu tajaajiltoota Muudaman kanaa fi Amantoota guutummaaf ergaa dabarsanii Muudama kanas kennaniiru. Tajaajiltootni Lubummaadhaan Muudamanis gara Waldaa Amantootaa keessaa dhufanitti derbi'anii tajaajila isaanii kan itti fufan yammuu ta'u;  hir'ina Sinoodosichi tajaajiltoota Lubummaadhaan muudaman qabuuf  muudamni kun kan fooyyessu ta'uun isaa ibsameera. Sinoodosiin Giddu Galeessa Itiyoophiyaa Amantoota Kuma Dhubba Torba (700,000) ol qabaachuudhaan Waldaa Makaana Yesuus keesatti tajaajila kennaa jira. Seenaa Sinoodosichaa keessattis si'a tokkicha tajaajiltoota baayyina akkasii qabaniif wal duukaa muudama kennuun kun isa jalqabaa ta'ee galmaa'eera. Itti Aanaa Pirezedaantii Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Lubni Dr. Taarikuu Tolosaa,  keessumootni Afeeramanii fi Maatiin tajaajiltoota Lubummaatti muudamanis sirnicha irratti argamaniiru.

ለቃሉና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ፥ 42 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ተሰጠ ** ** ** ** የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ መአከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለቃሉና ቅዱሳት ሚስጥ
+9
ለቃሉና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ፥ 42 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ተሰጠ ** ** ** ** የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ መአከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለቃሉና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ለ42 አገልጋዮችን በአዲስ አበባ ማህበረ ምዕመናን ታህሳስ 14/2016 ዓ.ም የቅስና ሀላፊነት ሰጥቷል። በእለቱም የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ለጉባኤውና ለአገልጋዮቹ መልዕክት አስተላልፈው የቅስና ሀላፊነት ሰጥተዋል። የቅስና ሀላፊነት የተቀበሉት አገልጋዮች ወደ የመጡበት ማህበረ ምዕመናን በመመለስ አገልግሎታቸው የሚቀጥሉ ሲሆን በሲኖዶሱ ካለው የቅዱሳት ሚስጥራት የአገልግሎቱ ፍላጎት የተነሳ የቄሶቹ ሹመትና ምደባ አገልግሎቱን እንደሚያሻሽል ይታመናል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያኒቱ ከ700 ሺህ በላይ ምዕመናን ያቀፈ እና ከፍተኛ የቆዳ ስፋት ይዞ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲኖዶስ ነው። በሲኖዶሱም ታሪክ እለቱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አገልጋዮች በአንድ ቀን የቀሰሱበት ቀን ሆኖ ተመዝግቧል። የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የእጩ ቄሶቹ ቤተሰቦች በዕለቱ ተገኝተዋል። - - - - - - - - -