ar
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

الذهاب إلى القناة على Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

إظهار المزيد
3 321
المشتركون
+324 ساعات
+247 أيام
+9630 أيام
أرشيف المشاركات
የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ የሮቦት ሲኖዶስ በገረሴ ዙርያ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው አርሶ አደሮች ድጋፍ አደረገ። ** የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ የሮቦት ስኖዶስ ፕረዝዳንት ቄስ ከተማ ካምሌ እና ዋና ፀሐፊ ቄስ ደመቀ ጩራቀ በገረሴ ዙርያ ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ተገኝተው ለገረሴ ዙርያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሳሁን ካማ በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው 28 አባወራ አርሶ አደሮች ድጋፍ አደርጓል። አቶ ካሳሁን ካማ ስረከቡ እንደተናገሩት ስኖዶሱ ገና የተመሠረተ ለጋ ስኖዶስ እንደመሆኑ ድጋፍ አልጠየቅንም። ነገር ግን ፈጣሪ አሳስቦአቸው ይህንን በጎ ተግባር ድጋፍ ስላደረጉ በፈጣሪና በወረዳው ህዝብ ስም አመሰግናለሁ ብለዋል። ለድሃ የሰጠ ለእግዚአብሔር ያበድራል እንደሚባለው የስኖዶሱ መልካም ተግባር እኛ እርስ በርሳችን እንድንረዳዳና እንድንደጋገፍ መልካም ተሞክሮ ነው ብሏል። ስኖዶሱ በዚህ ብቻ ሳይሆን ለበርካታ መታከም ለማይችሉ የማህበረሰብ ጤና መድህን ፈንድ በመግዛት እንደዚሁም ለተቸገሩት በመርዳት ከማህበረሰቡ ጎን የቆመ ስለሆነ ለቀጣይ በማናቸውም ሁኔታ ከስኖዶሱ ጎን በመቆም የወረዳው መንግስት ተደጋግፈው እንደሚሠሩ ተናግሯል። ዶ/ር ቦርሴ ቦታ የገረሴ ዙርያ ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ በበኩላቸው የገረሴ ዙርያ ወረዳ የመሬት አቀማመጥ ወጣ ገባ በመሆኑ ለተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭ በመሆኑ በርካታ አርሶ አደሮችን ለጉዳት እየተዳረጉ መሆኑን ተናግሯል። ባለፈው ወቅቱን ባልጠበቀ ዝናብ አኳያ በተፈጥሮ ናዳ አደጋ የደረሰባቸው ከጋርባንሳ ሦሮጌ፣ ከጋርባንሳ ካርቼ፣ ከመሌ ጋጉሌ እና ካምኣለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ ለመጡ 28 አባወራ አርሶ አደር ቤተሰቦች 14 ኩንታል የምግብ እህል ስኖዶሱ ድጋፍ ማድረጋቸውን በመግለጽ አመስግኗል። በወረዳው በተፈጥሮ አደጋ እና አየር መዛባት ምክንያት ለችግር የተጋለጡ በርካታ አርሶ አደሮች መኖራቸውን ኃላፊው ተናግረው ስኖዶሱ ከወንጌል ሥራ ጎን ለጎን በመንግሥት ልሸፈኑ ያልቻሉ በርካታ የልማት ሥራዎችን ከጎናችን ሆነው እንዲደግፉ ስሉ ጥሪ አቅርቧል። የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ የሮቦት ስኖዶስ ፕረዚዳንት ቄስ ከተማ ካምሌ በበኩላቸው ስኖዶሱ አድስ ነው፣ ቀጣይ ከወረዳ፣ ከዞንና ከክልሉ መንግሰት ጋር አብረን ለመሥራት ዕቅድ አለን ብሏል። እስከአሁን ባለን ሂደት ከወረዳም ይሁን ከቀበሌ መንግስት ለእኛ ሥራ እንቅፋት የሆነ ነገር የለም በማለት ቀጣይ አብረን ተባብረን ለመሥራት እግዚአብሔር እንዲረዳን እንለምናለን ስሉ አስታወቋል። ገረሴ፣ ጥር 8/2016 ዓ.ም(የገረሴ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት) መረጃውን ከየገረሴ ዙርያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን የፌስቡክ ገፅ አገኘነው።

በማዕከላዊ ስምጥ ሸለቆ፣ ኮንሶ ሰበካ፣ አዲስ ከተማ ማህበረ ምዕመናን ከጥር 3-5/ 2016 ዓ.ም ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፍራን ተካሄደ። ለሶስት ቀናት በቆየው ኮንፍራንስ የእግዚአብሔር ቃል በኋይልና በሙ
+9
በማዕከላዊ ስምጥ ሸለቆ፣ ኮንሶ ሰበካ፣ አዲስ ከተማ ማህበረ ምዕመናን ከጥር 3-5/ 2016 ዓ.ም ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፍራን ተካሄደ። ለሶስት ቀናት በቆየው ኮንፍራንስ የእግዚአብሔር ቃል በኋይልና በሙላት ተሰብኳል እንዲሁም ልዮ የአምልኮ እና የፀሎት ጊዜ እንደነበረ ከማህበረ ምዕመኗ ማህበራዊ ድህረ ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል። 📸 - አዲስ ከተማ ማህበረ ምዕመናን የሚድያና ኮሚኒኬሽን አገልግሎት

የኖርዌጂያን ሉተራን ሚሲዮን መሪዎች የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት ጎበኙ። በቆይታቸውም የቤተክርስቲያኒቱን ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ተሾመ አመኑ እና የልጆችና ወጣቶች
+7
የኖርዌጂያን ሉተራን ሚሲዮን መሪዎች የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት ጎበኙ። በቆይታቸውም የቤተክርስቲያኒቱን ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ተሾመ አመኑ እና የልጆችና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳን አግኝተው አነጋግረዋል። ** ** ** Norwegian Lutheran Mission (NLM) leaders visited the Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus, central office. During their time at the office, the leaders met with the general secretary, Rev Teshome Amenu, and children and youth department director, Wondmagegn Udessa.

“አስተምህሮ እና የምዕመናን ጥበቃ” በሚል አርዕስት ለማኅበራነ ምዕመናን መሪዎችና አገልጋዮች ስልጠና በመሠጠት ላይ ይገኛል * * * * * * በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ ለሚገኙ የማህበራነ ምዕ
+9
“አስተምህሮ እና የምዕመናን ጥበቃ” በሚል አርዕስት ለማኅበራነ ምዕመናን መሪዎችና አገልጋዮች ስልጠና በመሠጠት ላይ ይገኛል * * * * * * በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ ለሚገኙ የማህበራነ ምዕመናን ቄሶች፣ ወንጌላዊያን እና ሽማግሌዎች በአዲስ አበባ ማህበረ ምዕመናን ለሁለት ቀናት የተዘጋጀው ስልጠና ዛሬ ጥር 7/ 2016 ተከፍቷል። ስልጠናው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ በማለዳው የፀሎት ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረው ስልጠናውን ከፍተዋል። በወቅታዊነት በወንጌላዊያን አማኞች ዙሪያ እየተነሱ ያሉ ሀሰተኛ አስተምህሮና ልምምዶችን በእግዚአብሔር ቃል መሠረት መከላከል እና ምዕመናንን መጠበቅ የሚቻልበትን ሰፊ ግንዛቤ ለአገልጋዮች የሚያስጨብጥ ስልጠና መሆኑ በስልጠናው የተመላከተ ሲሆን የስልጠናው ተሳታፊ አገልጋዮችም በአገልግሎት ስፍራዎቻቸው ያሉ ተግዳሮቶችን በማንሳ ተወያይተውባቸዋል። ስልጠናውም ነገ ቀጥሎ የሚውል ሲሆን በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ ለሚገኙ አፋን ኦሮሞ ተናጋሪ ማህበራነ ምዕመናን ተመሳሳይ ይዘት ያለው ስልጠና ጉለሌ በሚገኘው ፊንፊኔ ኦሮሞ ማህበረ ምዕመናን በቀጣይ ሳምንት እንደሚሰጥ አገልግሎቱን ከሚመራው የቤተክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮ እና ቲኦሎጂ ዲፓርትመንት መረዳት ተችሏል።

"ልጆች ወደ ኢየሱስ ይምጡ" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማኅበራነ ምዕመናን የልጆች ቀን በህፃናት አገልግሎት፣ በግጥም፣ በድራማ፣ በስነ ጽሑፍ እና ለልጆች በመ
+9
"ልጆች ወደ ኢየሱስ ይምጡ" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማኅበራነ ምዕመናን የልጆች ቀን በህፃናት አገልግሎት፣ በግጥም፣ በድራማ፣ በስነ ጽሑፍ እና ለልጆች በመፀለይ ዛሬ ተከብሮ ውሏል። ከማ/ምዕመናን አስከ ዋናው የቤተክርስቲያኒቱ ጽሕፈት ቤት ያለውን የልጆች አገልግሎት ለማጠናከር ያስችል ዘንድ ገቢ የማሰባሰብ ስራዎች ተሰርተዋል። _ _ _ “ ...ሕፃናትን ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉ አትከልክሉአቸው፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደነዚህ ላሉት ናትና።" ማርቆስ 10:14 * * * * Today, Under the theme "Let Children come to Jesus", congratulations of The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus celebrated Children's day with the services given by children, poetry, drama, literature and prayer for children. In order to enhance children ministry from congregation level to the central office, fundraising was also held. _ _ _ “Let the little children come to me, and do not hinder them, for the kingdom of God belongs to such as these." Mark 10:14 #የልጆች_በዓል #guyyaa_ayyaana_ijoollee MY Sunday School EECMY Youth Ministry

!ነገ! #Tomorrow!
+1
!ነገ! #Tomorrow!

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምስራች ድምጽ የመገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት ፥ የንዋየ ቅዱሳት ማከፋፈያ ** ** ** ** EECMY Yemisrach Dimth Communications Servicer, Vestment Distribution Center

The Mekane Yesus Seminary community celebrated Christmas. The community celebrated Jesus’ birthday with a prayer, songs, a pr
+8
The Mekane Yesus Seminary community celebrated Christmas. The community celebrated Jesus’ birthday with a prayer, songs, a proclamation of the word of God, and the Lord's Supper. The event took place at Ammanuel G/Selase Hall.

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት አገልጋዮችና ሰራተኞች የ2016 የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓልን ዛሬ በጽሕፈት ቤቱ አዳራሽ
+9
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት አገልጋዮችና ሰራተኞች የ2016 የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓልን ዛሬ በጽሕፈት ቤቱ አዳራሽ በፀሎት፣ በአምልኮ እና የእግዚአብሔርን ቃል በመከፋፈል በጋራ አክብረዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱም መሪዎች ለሰራተኞቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus head office ministers and staffs celebrated the 2024th birth of our Lord and Savior Jesus Christ, today in the office hall with prayer, worship, and sharing the word of God. Leaders of the church also conveyed holiday greetings for the workers.

Upcoming_Day! መጪ የቤተክርስቲያኒቱ ቀን! #የኢትዮጲያ_ወንጌላዊት_ቤተ_ክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_የሚስዮን_ቀን ጥር 12/2016 - በመላው የቤተክርስቲያኒቱ ማህበራነ ምዕመናን ይከበራል። Th
Upcoming_Day! መጪ የቤተክርስቲያኒቱ ቀን! #የኢትዮጲያ_ወንጌላዊት_ቤተ_ክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_የሚስዮን_ቀን ጥር 12/2016 - በመላው የቤተክርስቲያኒቱ ማህበራነ ምዕመናን ይከበራል። The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus Mission Day! January 21/2024 - it will be celebrated at every congregations.