ወንጌሉ አገልግሎት | Wongelu Ministries
رفتن به کانال در Telegram
ጤናማ አብያተክርስቲያናትን ለክርስቶስ ክብር መፍጠር | Healthy Churches for the Glory of Christ Follow us on Instagram, Facebook, Tiktok, and Youtube @wongeluministries http://wongelu.com
نمایش بیشتر4 202
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
+17030 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژانویه '25
ژانویه '25
+6
در 1 کانالها
دسامبر '24
+279
در 2 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+221
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+178
در 1 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+335
در 1 کانالها
Get PRO
اوت '24
+477
در 2 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+312
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+273
در 3 کانالها
Get PRO
مه '24
+346
در 3 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+315
در 1 کانالها
Get PRO
مارس '24
+256
در 1 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+316
در 2 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+291
در 2 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+231
در 2 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+551
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '230
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '230
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '230
در 0 کانالها
Get PRO
مه '230
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '230
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '230
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '230
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '230
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '220
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '220
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '220
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '22
+2
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '220
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '220
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '220
در 0 کانالها
Get PRO
مه '22
+2
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '22
+1
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '22
+6
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '22
+6
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '22
+15
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '21
+260
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 ژانویه | +6 |
پستهای کانال
ታሕሳስ 24 | በገና የሚገኘው አንድነት
የእግዚአብሔር ልጅ የተገለጠውም የዲያቢሎስን ሥራ ያፈርስ ዘንድ ነው። (1ኛ ዮሐንስ 3፥8)
ሰይጣን በየቀኑ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ኀጢአቶችን እያሰለፈ ይፈበርካል። በትልልቅ የጭነት አውሮፕላኖች እየጫነ ወደ መንግሥተ ሰማይ በመላክ በእግዚአብሔር ፊት ዘርግፎ ይስቃል፤ ያሽካካል።
አንዳንድ ሰዎች የዚህ ፋብሪካ ሰልፍ ቋሚ ቅጥረኞች ሲሆኑ ሌሎች ደግሞ ሥራ መልቀቂያ አስገብተው አልፎ አልፎ ግን ይሠራሉ።
በዚህ ፋብሪካ በየደቂቃው የሚመረተው ምርት፣ እግዚአብሔርን የሰይጣን መሳለቂያ ያደርገዋል። የእግዚአብሔርን ብርሃን፣ ውበት፣ ንጽሕና እና ክብር አክርሮ የሚጠላው ሰይጣን፣ ኀጢአትን ዋነኛ ቢዝነሱ አድርጎ ይንቀሳቀሳል። ፍጥረታት ፈጣሪያቸውን ሲንቁ፣ ሳይታዘዙ እና ሲጠራጠሩ እንደሚደሰተው በምንም አይደሰትም።
በዚህም ምክንያት ገና ለሰው ልጅ እና ለእግዚአብሔር መልካም ዜና ነው። “ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው” (1 ጢሞቲዎስ 1፥15)። ይህ ለእኛ መልካም ዜና ነው። “የእግዚአብሔር ልጅ የተገለጠውም የዲያቢሎስን ሥራ ያፈርስ ዘንድ ነው” (1ኛ ዮሐንስ 3፥8)። ይህ ደግሞ ለእግዚአብሔርም መልካም ዜና ነው።
ገና ለእግዚአብሔር መልካም ዜና የሆነበት ምክንያት፣ ኢየሱስ የመጣው የሰይጣን ፋብሪካ ላይ የሠራተኞች አድማ ለመምራት ስለሆነ ነው። ፋብሪካ ውስጥ ገብቶ፣ ታማኝ ለሆኑት የአንድነት ጥሪ አቅርቦ፣ ከፍተኛ የሆነ የሰው ፍልሰት አስጀምሯል።
ገና የኀጢአት ፋብሪካ የሠራተኞች ሰልፍ ላይ የታወጀ የአድማ ጥሪ ነው። ከአመራሮች ጋር የሚደረግ ድርድር ወይም ስምምነት የለም። ሠራተኞች በግላቸው ወስነው፣ እዚህ እዛ ሳይሉ ለሚመረተው ምርት ያላቸውን ቀጥተኛ ተቃውሞ የሚገልጹበት አድማ ነው። ከእንግዲህ ይህንን ምርት አናመርትም።
የገና አንድነት የፋብሪካውን የጭነት አውሮፕላኖች በረራ ያሰርዛል። ያለ አንዳች ኀይል እና ሁከት ለእውነት ባለው የጸና ትጋት የሰይጣን ፋብሪካ ሕይወትን የሚያጠፋ መሆኑን ያጋልጣል።
የገና አንድነት ፋብሪካው ሙሉ በሙሉ እስኪዘጋ ድረስ አያርፍም፤ ተስፋም አይቆርጥም።
ኀጢአት ድባቅ ተመትቶ ከምድረ ገጽ ሲጠፋ፣ ያኔ የእግዚአብሔር ስም ሙሉ በሙሉ ነጻ ይወጣል። ከእንግዲህ የሚስቅ፣ የሚሳለቅ አይኖርም። በዚህ የገና በዓል ለእግዚአብሔር ስጦታ ልትሰጡ ከፈለጋችሁ፣ ኀጢአት ከሚገጣጠምበት ሰልፍ ለቃችሁ ውጡና ድጋሚ አትመለሱ። በዚያ ምትክ የፍቅር መገጣጠሚያ ሰልፍ ላይ ተሰለፉ። የንጉሡ የእግዚአብሔር ስም ሙሉ በሙሉ ነጻ ወጥቶ በጻድቃን ምስጋና እና ክብር መካከል ቆሞ የሚደነቅበት ጊዜ እስኪመጣ ድረስ በዚህ የገና አንድነት ላይ ግብረ ዐበሮች ሁኑ።
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | X (Twitter) | Website
#ለዛሬ
| 2 | Tahesas_24_በገና_የሚገኘው_አንድነት_Wongelu_Ministries.mp3 | 1 |
| 3 | ታሕሳስ 23 | ገና ለነፃነት ነው
እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሀት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። (ዕብራውያን 2፥14-15)
ኢየሱስ ሰው ሆኖ ወደ ምድር የመጣበት ምክንያት ከሰው በላይ የሆነ ሰው መሞቱ አስፈላጊ ስለነበር ነው። ኢየሱስ ሰው ሆነ ማለት አምላክ ራሱን የሞት ፍርደኞች እስር ቤት ውስጥ ቆለፈ እንደማለት ነው።
ሞት ክርስቶስ ላይ የተጋረደ አደጋ አልነበረም። ሞትን መርጦ እና ተቀብሎት ነው የመጣው። እንዲያውም የመጣበት ዋነኛው ምክንያት ያ ነው፤ “እንዲሁ የሰው ልጅም ሊያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም” (ማርቆስ 10፥45)።
ሰይጣን በምድረ በዳ (ማቴዎስ 4፥1-11) እና በጴጥሮስ አንደበት (ማቴዎስ 16፥21-23) ኢየሱስን ከመስቀሉ ዓላማ ሊያስተው የሞከረውም ለዚህ ነበር! መስቀሉ የሰይጣን መጥፊያ ነበር። እንዴት ኢየሱስ ሰይጣንን አጠፋው?
ሰይጣን “በሞት ላይ ሥልጣን” እንዳለው ዕብራውያን 2፥14 ይነግረናል። ይህ ማለት ሰይጣን ሞትን አስፈሪ የማድረግ አቅም አለው ማለት ነው። ሰይጣን “በሞት ላይ ሥልጣን” ስላለው ሰዎች በሞት ፍርሀት ተጠፍረው እንዲኖሩ ያደርጋል። ሰዎችን በኀጢአታቸው ጠፍሮ በመያዝ ሞት አስጨናቂ እንዲሆንባቸው የማድረግ ሥልጣን ነው።
ነገር ግን ኢየሱስ ይህንን ሥልጣን ከሰይጣን ነጠቀው። ትጥቅ አስፈታው። ከሰይጣን ኩነኔ የሚከላከልልንን የጽድቅ ጥሩር አለበሰን። ይህንን እንዴት አደረገ? በሞቱ፣ ኢየሱስ ኀጢአታችንን ሁሉ አጠበ። ኀጢአት የሌለበት ሰው ደግሞ በሰይጣን ሊኮነን አይችልም። ካገኘነው ምሕረት የተነሣ ከእንግዲህ ማንም ሊያጠፋን እና ሊያወድመን አይችልም። የሰይጣን ዕቅድ የነበረው የእግዚአብሔርን ተከታዮች በራሱ በእግዚአብሔር ችሎት ውስጥ የእግዚአብሔርን አገዛዝ ማፍረስ ነበር። ነገር ግን አሁን በክርስቶስ ምክንያት ኩነኔ የለብንም። የሰይጣን ክህደት ተገልብጧል። ዓለምን ሁሉ ያወከበት ተንኮሉ እንክትክቱ ወጥቷል። “ቁጣውን ለጥቂት ጊዜ እንሸከማለን፤ ምክንያቱም መጥፋቱ አይቀሬ ነው።” መስቀሉ ሰይጣንን ደርምሶታል፤ የመጨረሻውን እስትንፋሱን የሚስብበት ጊዜም ተቃርቧል።
ገና ለነፃነታችን ነው፤ ከሞት ፍርሀት ነፃ የወጣንበት።
ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ሞታችንን ሊሞት በቤተ ልሔም የእኛን መልክ ይዞ ተወለደ። ይህንን ሁሉ ያደረገው ደግሞ ዛሬ በከተማችን ውስጥ ያለ ፍርሀት እንድንመላለስ ነው። አዎን፣ ፍርሀት አልባ! ለደስታችን ሥጋት የነበረው ትልቁ ፍርሀት ከተወገደልን፣ በጥቃቅኖቹ ምድራዊ ፍርሃቶች ለምን እንታወካለን? እስቲ አስቡት፤ እንዴት ብለን ነው፣ “ሞትን አልፈራም፤ ግን ከሥራ መባረርን እፈራለሁ” የምንለው? አስቡት! አይሆንም!
ሞት (ሞት ስል፣ የልብ ምታችን አቁሞ የምንቀዘቅዝበት ሞት ማለቴ ነው!) ከእንግዲህ ከተወገደ፣ በርግጥም ከጥግ እስከ ጥግ ነፃ ነን ማለት ነው። ስለ ክርስቶስ እና ስለ ፍቅር ስንል ከፀሓይ በታች የትኛውንም አደጋ በድፍረት ልንጋፈጥ ነፃ ነን። ከእንግዲህ የፍርሀት ባሮች አይደለንም።
እንግዲህ ልጁ ነፃ ካወጣችሁ፣ በእውነት ነፃ ትሆናላችሁ!
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | X (Twitter) | Website
#ለዛሬ | 309 |
| 4 | Tahesas_23_ገና_ለነፃነት_ነው_Wongelu_Ministries.mp3 | 282 |
| 5 | መጋቢዎች ለሕዝባቸው እንዲጸልዩ የቀረበ ጥሪ
ጌታችን የራሱን ሰዎች ደቀ መዛሙርቱን፣ “በዚህ ተቀመጡ ከእኔም ጋር ትጉ” ብሎ በጠየቀ ጊዜ ከሚወዱት ሰው ጋር በታማኝነት ለመትጋት እና ለመጸለይ ፍላጎት እንደ ነበራቸው ርግጠኛ ነኝ። እንዳለመታደል ሆኖ፣ ያ ፍላጎት ብቻ በቂ አልነበረም። ይልቁንም፣ እያንዳንዱ መጋቢ ወደ ጸሎት ሲመጣ “መንፈስ ዝግጁ ነው ሥጋ ግን ደካማ ነው” ለሚለው እውነት የማይረሱ ምሳሌዎች ሆነዋል (ማቴዎስ 26፥41)። እንቅልፍ አጥተህ ለሕዝብህ ለመጸለይ ምን ያህል ጊዜ አዲስ ቁርጥ ውሳኔ አድርገሃል? ግን ልክ “ዐይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበር” እንደሚል ምን ያህሉን ጊዜ በዐይኖችህ መድከም የተነሣ ዕቅድህ ሳይሳካ ቀርቷል (ማቴዎስ 26፥43)?
የዚህ ጽሑፍ ዐላማ ጸሎትን በሚያበረታቱ የእግዚአብሔር ቃል እውነቶች፣ የዛሉትን ዐይኖቻችንን ማበርታት ነው። እነዚህ ማሰላሰሎች ነፍሳችሁ “እኛ ግን በጸሎት… እንተጋለን” በሚለው ሐዋርያዊ ጩኸት እንድትነሣ ያደርጋታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ (የሐዋርያት ሥራ 6፥4)።
ለዚህም፣ ከጸሎት አልባ እንቅልፋችን ያስወጡናል ብዬ ተስፋ የማደርጋቸውን ስድስት መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነቶችን አቀርባለሁ።
ተጨማሪ ለማንበብ...
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website
#Articles | 453 |
| 6 | መጋቢዎች_ለሕዝባቸው_እንዲጸልዩ_የቀረበ_ጥሪ_the_call_for_pastors_to_pray_for_their.mp3 | 403 |
| 7 | ታሕሳስ 22 | ለሚሲዮናዊነት ሥራ የሚውለው የገና ሞዴል
ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው። (የዮሐንስ ወንጌል 17፥18)
ገና ለሚሲዮን (ወይም ለሚሽነሪነት) ሥራ የሚጠቅም ሞዴል ነው። ሚሲዮናዊነት የገና ነጸብራቅ ነው። “ልክ እንደ እኔ፣ እናንተም” የሚል ሐሳብ እናገኝበታለን።
አደጋዎቹን እንደ ምሳሌ ልንወስድ እንችላለን። ክርስቶስ ወደገዛ ወገኖቹ መጣ፤ የገዛ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም። እናንተንም እንዲያው። በእርሱ ላይ ሴራ አሢረውበት ነበር፤ እናንተንም ላይ እንዲያው። እርሱ ዘላቂ ቤት አልነበረውም፤ እናንተም እንዲያው። የሐሰት ክስ ከምረውበት ነበር፤ እናንተም ላይ እንዲያው። ገርፈውት እና አፊዘውበት ነበር፤ እናንተም ላይ እንዲያው። ከሦስት ዓመት አገልግሎት በኋላ ሞተ። እናንተም እንዲያው።
ነገር ግን ከእነዚህ አደጋዎች ሁሉ የባሰውን አደጋ ክርስቶስ አምልጧል። እናንተም እንዲያው!
በ16ተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ፍራንሲስ ኤግዜቪየር (1506-1522 እ.ኤ.አ.) የተባለ ሚሲዮናዊ አባ ፔሬዝ ለተባሉ የማላካ (የዛሬ ማሌዢያ አካባቢ) አባት ወደ ቻይና ባደረገው ሚሲዮናዊ ጉዞ ያጋጠመውን መከራ ሊገልጽላቸው እንዲህ ሲል ጻፈ፦ “ከአደጋዎቹ ሁሉ የከፋው አደጋ የሚከሰተው በእግዚአብሔር ምሕረት ላይ ያለን እምነት እና እርግጠኝነት የጠፋ ዕለት ነው… የእግዚአብሔር ጠላቶች ሁሉ ተሰብስበው ሊያደርሱብን ከሚችሉት ከየትኛውም አካላዊ ክፋት ሁሉ የሚብሰው በእርሱ ላይ ያለን እምነት መሸርሸር ነው፤ ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ አጋንንትም ሆኑ የእነርሱ መጠቀሚያ ሰዎች አንድም እርምጃ ወደ ኋላ ሊይዙን አይችሉምና።”
አንድ ሚሲዮናዊ ሊያጋጥመው የሚችለው ከፍተኛው አደጋ ሞት ሳይሆን በእግዚአብሔር ምሕረት ላይ ሊያድርበት የሚችል ጥርጣሬ ነው። ያንን አደጋ ሊያመልጥ ከቻለ፣ ሊያጋጥሙት የሚችሉት ሌሎች አደጋዎች ሁሉ መውጊያ አይኖራቸውም። በመጨረሻም እግዚአብሔር ሁሉንም ጩቤ እና ስለት ለመንግሥቱ በትር ያደርገዋል። ጄ.ደብልዩ. አሌክሳንደር እንዲህ ብሏል፤ “አሁን ላይ ያለው እያንዳንዱ ድካም፣ በሚሊዮን ዓመታት ክብር በተትረፈረፈ መንገድ ይካሳል።” ክርስቶስ በእግዚአብሔር ካለመታመን አደጋ አምልጧል። በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው። እናንተንም እንዲሁ!
በዚህ የገና ሰሞን ስለ ክርስቶስ መወለድ ስታስቡ፣ ገና ለወንጌል ተልዕኮ እንደ ሞዴል ወይም እንደ ምሳሌ እንደሚያገለግል አስታውሱ። እኔ እንደሆንኩት፣ እናንተም እንዲሁ። ያ ተልዕኮ ደግሞ አደጋ ያለበት ነው። ከአደጋዎች ሁሉ ደግሞ የከፋው አደጋ የእግዚአብሔርን ምሕረት አለመታመን ነው። ለዚህ አደጋ እጃችሁን ከሰጣችሁ ሁሉም ነገር አከተመ ማለት ነው። እዚህ ጦርነት ላይ ካሸነፋችሁ ደግሞ፣ ለሚሊዮን ዓመታት የሚጎዳችሁ አንዳች አይኖርም።
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website
#ለዛሬ | 511 |
| 8 | Tahesas_22_ለሚስዮናዊነት_የሚውለው_የገና_ሞዴል_Wongelu_Ministries.mp3 | 453 |
| 9 | በወንጌሉ አገልግሎት ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ለንባብ የበቃው፣ "ኢየሱስ ማን ነው?" የተሰኘው የግሬግ ጊልበርት መጽሐፍ በኢትሮንስ መተግበሪያ ላይ ለንባብ ቀርቧል።
መጽሐፉን የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ተከትለው በቴሌብር መግዛት ይችላሉ።
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.aquila.ethrons | 533 |
| 10 | ታሕሳስ 21 | ሊታሰብ የሚችለው ታላቁ መዳን
እነሆ፥ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት ወራት ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር። (ትንቢተ ኤርሚያስ 31፥31)
እግዚአብሔር ቅዱስ እና ፍትሐዊ አምላክ ሲሆን፣ ከእንደኛ ዐይነት ኀጢአተኞች ፍጹም የተለየ ነው። በገናም ጊዜ ሆነ በዓመቱ የትኛውም ወቅት ዋና ችግር የሚሆንብን ነገር ይህ ነው። እጅግ ቅዱስ እና ፍጹም ፍትሐዊ ከሆነ አምላክ ጋር እንዴት እንታረቅ? ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ እግዚአብሔር በምሕረት የተሞላ አምላክ ሲሆን፣ ክርስቶስ ከመወለዱ አምስት መቶ ዓመት በፊት፣ በትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 31 አንድ ቀን አዲስን ነገር እንደሚያደርግ ይናገራል። ጥላዎቹን ሁሉ ዋነኛው በሆነው መሲሕ እንደሚተካ ቃል ይገባል። በታላቅ ኀይል በሕይወታችን ውስጥ እየሠራ ከውጭ የሚከለክለን ነገር ሳይኖር ከውስጣችን ፈቅደን እንድንወደው፣ እንድንታመነው እና እንድንከተለው ፈቃዱን በልባችን ይጽፋል።
ሊታሰብ የሚችለው ታላቁ መዳን ይህ ነው። እግዚአብሔር በአጽናፈ ዓለሙ ሁሉ ውስጥ ሊገኝ የሚችለውን ታላቁን እውነታ ሐሴት እንድናደርግበት በነፃ ሰጥቶናል። ከዚህም አልፎ፣ ይህንን እውነታ በታላቅ ነፃነት እና እርካታ እያጣጣምን እንድናውቀው ማድረጉ እጅግ ታላቅ ነገር ነው። ይህ እውነት ሊዘመርለት የሚገባ እጅግ ውድ የገና ስጦታ ነው። ይህንንም ነው በአዲሱ ኪዳን ቃል የገባው። ሆኖም ግን አንድ ታላቅ ዕንቅፋት ነበር። ያም ዕንቅፋት በኀጢአታችን እና በዐመፃችን ምክንያት ከእግዚአብሔር መነጠላችን ነው።
ቅዱስ እና ፍትሐዊ የሆነው ይህ አምላክ እኛን ኀጢአተኞችን እንዲህ ባለ ርኅራኄ ተመልክቶ፣ በአጽናፈ ዓለሙ ውስጥ ያለው ታላቁን እውነታ (ልጁን) ሐሴት እንድናደርግበት ሊሰጠን እንዴት ይችላል? መልሱ ደግሞ ይህ ነው። እግዚአብሔር ኀጢአታችንን ኢየሱስ ላይ በመጫን ፍርዱን ልጁ ላይ አደረገ፤ ቅድስናው እና ፍትሐዊነቱ ሳይዛባ በደላችንን ሊተውልን እና በምሕረቱ ሊገናኘን ስለፈለገ፣ በእኛ ምትክ ልጁ ላይ ፈረደበት። “ክርስቶስ የብዙ ሰዎችን ኀጢአት ለመሸከም፣ እንዲሁ አንድ ጊዜ መሥዋዕት ሆኖአል፤ ሁለተኛ ጊዜም ይገለጣል፤ ይህም ለሚጠባበቁት ድነትን ለማምጣት እንጂ ኀጢአትን ለመሸከም አይደለም” (ዕብራውያን 9፥28)።
ክርስቶስ በመስቀል ሲሞት በገዛ ሰውነቱ ውስጥ ኀጢአታችንን ተሸክሞ ነበር (1ኛ ጴጥሮስ 2፥24)። ለእኛ የተገባውን ፍርድ ወሰደልን (ሮሜ 8፥3)። በደላችንን ሰረዘልን (ሮሜ 8፥1)። ይህም ማለት ከእንግዲህ ኀጢአታችን ተወግዷል ማለት ነው (ሐዋርያት ሥራ 10፥43)። እግዚአብሔር ኀጢአታችንን በልቡ ቋጥሮ ሊከሰን ቀን እየጠበቀ አይደለም። ይህ ማለት በአንድ መልኩ ኀጢአታችንን ይረሳል ወይም አያስብብንም ማለት ነው (ኤርሚያስ 31፥34)። ኀጢአታችን ሁሉ በክርስቶስ ሞት ተቃጥሎ ከስሟል።
ይህ ማለት እግዚአብሔር አሁን ቃላት ሊገልጹት የማይችሉትን ታላቁን የአዲስ ኪዳን ተስፋ ቃል አትረፍርፎ ሊሰጠን ፍትሐዊ የሆነው ባሕርይው ይፈቅድለታል ማለት ነው። በአጽናፈ ዓለማችን ካሉት ተጨባጭ እውነታዎች ሁሉ የሚልቀውን ታላቁን እውነታ ኢየሱስ ክርስቶስን ደስታችን ይሆን ዘንድ ሰጠን። በሙሉ ልባችን፣ በነፃነት እና ያለ አንዳች መከልከል ክርስቶስን እንድንወድ እና እንድንገዛለት የገዛ ፈቃዱን፣ የልቡን መሻት በልባችን ላይ ጻፈልን።
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website
#ለዛሬ | 587 |
| 11 | Tahesas_21_ሊታሰብ_የሚችለው_ትልቁ_መዳን_Wongelu_Ministries.mp3 | 514 |
| 12 | በወንጌሉ አገልግሎት ወደ አማርኛ የተተረጎመው፣ "ወንጌል ምንድን ነው?" በሚል ርዕስ በግሬግ ጊልበርት የተጻፈው መጽሐፍ በኢትሮንስ መተግበሪያ ላይ በ ዲጂታል አማራጭ ቀርቧል።
መጽሐፉን በሚከተለው ማስፈንጠሪያ ያገኙታል።
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.aquila.ethrons | 592 |
| 13 | ታሕሳስ 20 | ስኬታማው የእግዚአብሔር ውድቀት
ስለዚህ እግዚአብሔር እጅግ ከፍ አደረገው፤ ከስምም ሁሉ በላይ የሆነውን ስም ሰጠው፤ ይኸውም በሰማይና በምድር፣ ከምድርም በታች፣ ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ስም ይንበረከክ ዘንድ፣ ምላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው። ፊልጵስዩስ 2፥9-11 (አ.መ.ት)
የእግዚአብሔር ስኬታማ ውድቀት መጀመሩ የተበሰረው በገና ነው። ኀይሉን ማሳየት የሚወደው ሽንፈት በሚመስል መንገድ ነው። ስትራቴጂያዊ ድሎችን ለመጎናጸፍ ስልታዊ ማፈግፈግን ይተገብራል።
ከዐሥራ ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች መካከል አንዱ የሆው ዮሴፍ በሕልሙ ብዙ ክብር እና ሥልጣን ቃል ሲገባለት በብሉይ ኪዳን እናነባለን (ዘፍጥረት 37፥5-11)። ነገር ግን ያንን ድል ለመጎናጸፍ በግብፅ ባሪያ መሆን ነበረበት። ያ ብቻ ደግሞ በቂ አልነበረም፤ በሐቀኝነቱ ምክንያት የነበረበት አስከፊ ሁኔታ ትንሽ መሻሻል ሲያሳይ ከባርነትም ወርዶ እስረኛ ሆነ።
ነገር ግን ይህ ሁሉ ለራሱ፣ ለቤተሰቡ፣ ከዚያም አልፎ ለዓለም ሁሉ የሚተርፍ መልካምን ነገር እንዲያመጣ በእግዚአብሔር የታቀደ ነበር። ምክንያቱም የፈርዖንን ጠጅ አሳላፊ ሊተዋወቅ የቻለው በእስር ሳለ ነበር። በኋላም ይህ ሰው ነው ዮሴፍን ወደ ፈርዖን የሚያቀርበው። ፈርዖንም በግብፅ ሁሉ ላይ ሾመው። በስተመጨረሻም ሕልሙ ተፈጸመ። ወንድሞቹ ሰገዱለት፣ እርሱም ከረሃብ ታደጋቸው። ዮሴፍ የክብርን ማማ የተቆናጠጠው ባልተለመደ መንገድ ነበር።
ይህ መንገድ ግን የእግዚአብሔር መንገድ ነው፤ ለልጁም ጭምር። ራሱን ባዶ አድርጎ የባርያን መልክ ያዘ። ከባርያም የባሰ እስረኛ ነበር። አልፎም በሞት ተቀጣ። እንደ ዮሴፍም ታማኝ ሕይወት ኖረ። “ስለዚህ እግዚአብሔር እጅግ ከፍ አደረገው፤ ከስምም ሁሉ በላይ የሆነውን ስም ሰጠው፤ ይኸውም በሰማይና በምድር፣ ከምድርም በታች፣ ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ስም ይንበረከክ ዘንድ” (ፊልጵስዩስ 2፥9-10)።
እግዚአብሔር ለእኛም ያስቀመጠው ይህንኑ መንገድ ነው። ክብር ቃል ተገብቶልናል፤ ነገር ግን ያ የሚሆነው በሮሜ 8፥17 በግልጽ እንደሚነግረን አብረነው መከራን ከተቀበልን ብቻ ነው። ወደ ላይ መንገዱ በሥር በኩል ነው። ወደ ፊት የምንሄደው በኋላ በኩል ነው። ስኬት ላይ የሚደረሰው መለኮታዊ ዕቅድ ውስጥ ባለው የውድቀት መንገድ ነው። እነዚህ መንገዶች ሁልጊዜ ሲታዩ የውድቀት መንገድ ይመስላሉ።
ነገር ግን በዚህ የገና በዓል ከዮሴፍ እና ኢየሱስ የምንማረው አንድ ነገር ካለ ይህ ነው። ሰይጣን እና ኀጢአተኛ ሰዎች ለክፋት ያቀዱትን እና ያሰቡትን፣ “እግዚአብሔር ግን ዛሬ እንደ ሆነው ብዙ ሕዝብ እንዲድን ለማድረግ ለመልካም አሰበው” (ዘፍጥረት 50፥20)።
እናንተ ፈሪ ቅዱሳኖች በርቱ
የምትፈሯቸው ደመናዎች ሁሉ
በምሕረት ተሞልተው በቅርቡ ይፈስሳሉ
ብዙ በረከትን ከላይ ያወርዳሉ
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website
#ዛሬ | 656 |
| 14 | Tahesas_20_ስኬታማው_የእግዚአብሔር_ውድቀት_Wongelu_Ministries.mp3 | 547 |
| 15 | እውነተኛ ደስታ ከወሲብ ኀጢአት ነፃ አወጣው
የርካሽ ፍቅሮች መፍያ አፍላል
አውግስጢኖስ የተወለደው እ.ኤ.አ. ሕዳር 13፣ 354 አሁን ላይ አልጄሪያ በመባል በምትታወቀው ታጋስቴ በምትባል ስፍራ ነበር። ታጋስቴ ሂፖ በምትባለው ከተማ አቅራቢያ ያለች ከተማ ነች። መካከለኛ ገቢ የነበረውና በግብርና ሥራ ይተዳደር የነበረው አባቱ ፓትሪሺየስ፣ ልጃቸው አውግስጢኖስ በንግግር ጥበብ ሊያገኝ የሚችለውን የላቀ ትምህርት ሁሉ እንዲያገኝ ጠንክረው ይሠሩ ነበር። ዕድሜው ከዐሥራ አንድ እስከ ዐሥራ አምስት አመት ሳለ ከሚኖርበት ስፍራ ሠላሳ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚያክል ርቃ በምትገኝ ማዳውራ በተባለች ከተማ ተማረ። በመቀጠልም አንድ ዓመት ቤት ወስጥ ከቆየ በኋላ ከዐሥራ ሰባት ዓመቱ አንሥቶ ሃያ ዓመት እስኪሞላው በካርቴጅ ትምህርቱን ተከታተለ።
አውግስጢኖስ ለሦስት ዓመት ትምህርት ወደ ካርቴጅ ከመሄዱ በፊት እናቱ ዝሙት እንዳይፈጽም ከምንም በላይ ደግሞ የማንንም ሚስት እንዳያማልል አበክራ አስጠንቅቃው ነበር። ይሁን እንጂ አውግስጢኖስ ከጊዜ በኋላ ኑዛዜ በተሰኘ መጽሐፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ “የርካሽ ፍቅሮች መፍለቅለቂያና መፍያ አፍላል ወደ ሆነው ካርቴጅ መጣሁ… በውስጤ ውስጣዊ ምግብ የሆንከው የአንተ የአምላኬ የማያቋርጥ ራብ ነበር።”[1] በካርቴጅ አንድ ቁባት ይዞ ለዐሥራ አምስት ዓመት አብሯት የኖረ ሲሆን አዲዎዳቱሰ የተባለ አንድ ወንድ ልጅ ከእርሷ ወልዷል።
አውግስጢኖስ ከዐሥራ ዘጠኝ ዓመቱ አንሥቶ እስከ ሠላሳ ዓመቱ ድረስ ለሚቀጥሉት ዐሥራ አንድ ዓመታት የንግግር ጥበብ መምህር በመሆን ያስተምር ነበር።
ተጨማሪ ለማንበብ...
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website
#Articles | 966 |
| 16 | እውነተኛ_ደስታ_ከወሲብ_ኀጢአት_ነፃ_አወጣው_true_joy_delivers_him_from_the_sin_of.mp3 | 633 |
| 17 | ታሕሳስ 19 | ሕይወት እና ሞት በገና በዓል
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። (የዮሐንስ ወንጌል 10፥10)
ይህንን የጥሞና ማጥኛ መጻፍ ልጀምር ስል ማሪዮን ኒውስትረም የተባለች ሴት መሞቷ ተነገረኝ። ማሪዮን እና ባሏ ኤልመር በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ በአባልነት የቆዩባቸው ዓመታት በጊዜው የነበሩ ሌሎች አባሎቻችን በሕይወት ከቆዩት ዓመታት ይረዝም ነበር። 87 ዓመቷ ነበር። ከባለቤቷ ለ64 ዓመታት በትዳር አብረው ቆይተዋል። ከኤልመር ጋር ባወራሁ ጊዜ በሕይወቱ ተስፋ እንዳይቆርጥ እና በጌታ እንዲበረታ ስነግረው፣ “እርሱ እውነተኛ ጓደኛ ሆኖልኛል” ብሎ መለሰልኝ። ክርስቲያኖች ሁሉ ወደ ሕይወታቸው መገባደጃ ሲደርሱ ልክ እንዲሁ “ክርስቶስ እውነተኛ ጓደኛ ሆኖልኛል” ማለት እንዲችሉ ጸሎቴ ነው። የገና በዓል በደረሰ ጊዜ ሁሉ የእናቴን ሞት በማስታወስ ዓመታቱን እቆጥራለሁ። በ56 ዓመቷ በአውቶቡስ አደጋ በእስራኤል አገር ነበር የሞተችው። ቀኑ ታኅሳስ 7 ቀን 1967 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. ዲሴምበር 16 ቀን 1974 ዓ.ም) ነበር። የዚያን ቀን አስከፊ ክስተት እስከ አሁን ድረስ በሚገርመኝ መንገድ በልቤ እውን ነው። ራሴን ካልከለከልኩት፣ በጣም በቀላሉ ዕንባዬ ይመጣል፤ ለምሳሌ፥ ልጆቼ ሳያውቋት መሞቷን ሳስብ። የገና በዓል ማግስት ቀበርናት። እንዴት ያለ ውድ የገና ቀን ነበር!
ብዙዎቻችሁ በዚህ ገና ያጣችሁትን ሰው በማስታወስ ከሌላው ጊዜ በተለየ መልኩ ታዝናላችሁ። ስሜታችሁን አትዝጉበት። ይምጣ። ይሰማችሁ። አለዚያ ፍቅር ትርጉሙ ምን ሊሆን ነው? ለምንወዳቸው ሰዎች ያለን ፍቅር በሕይወትም ሆኑ በሞት ሊጋጋል ይገባል። ነገር ግን መራራ አትሁኑ። መራርነት እጅግ በጣም አስከፊ በሆነ መንገድ ራስን ያጎሳቁላል። ኢየሱስ በገና ወደ እኛ የመጣው የዘለዓለም ሕይወት ይኖረን ዘንድ ነው። “እኔ ግን ሕይወት እንዲኖራቸውና እንዲትረፈረፍላቸው መጥቻለሁ” (ዮሐንስ 10፥10 አ.መ.ት)። ኤልመር እና ማሪዮን የዕድሜያቸውን የመጨረሻ ዓመታት የት እንደሚያሳልፉ ተነጋግረው ነበር። “ማርዮን እና እኔ የመጨረሻ ቤታችን ከጌታ ጋር እንደሚሆን ተስማምተን ነበር” ይላል ኤልመር።
የቤታችሁ ናፍቆት ዕረፍት ይነሣችኋል? በቤተሰባችን ውስጥ ለበዓላት የቤተ ዘመድ መገናኘት አለ። የበዓል ሰሞን ሲሆን ጠቅላላ ቤተሰባችን ከያለበት ተሰብስቦ ወደ ቤት ይመጣል። መሰባሰባችን በጣም ደስ የሚል ስሜት አለው። ደስ የሚለን ዋነኛው ምክንያት ደግሞ በማንነታችን ውስጥ የተቀበረ ለመጨረሻው የቤተ ዘመድ መገናኘት የታቀድን ሰዎች ስለሆንን ይመስለኛል። ሌሎች የቤተ ዘመድ መገናኘቶች ሁሉ ቅምሻዎች ናቸው። ቅምሻዎች ሁሉ ደግሞ መልካም ናቸው። መልካምነታቸው ግን ዋናውን እስካካተተ ድረስ ብቻ ነው።
በዚህ ወቅት የምናገኛቸው ጣፋጭ ነገሮች የመጨረሻ እና ዘለዓለማዊ የሆነውን እና ሁሉን የሚያረካውን ዋነኛ ጣፋጭ የሚተኩ አይደሉም። አደራችሁን እንደ ምትክ እንዳትቆጥሯቸው። እያንዳንዱ ማጣት እና እያንዳንዱ ደስታ በመንግሥተ ሰማይ ለሚኖረው ዘለዓለማዊው የቤተ ዘመድ መገናኘት ልባችሁን ይምራ። ገና ይህ ካልሆነ ታዲያ ምንድን ነው? እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። ማሪዮን ኒውስትረም፣ ሩት ፓይፐር፣ እናንተ እና እኔ ዛሬም ለዘለዓለምም ሕይወት እንዲኖረን መጥቶልናል! በዚህ የገና ሰሞን ከዘለዓለማዊው ምንጭ በመጠጣት ዛሬያችሁ የበለጸገ እና ጥልቅ የሆነ ትርጉም እንዲኖረው አድርጉ። ደርሷል፤ እጅግ ቅርብ ነው።
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website
#ለዛሬ | 737 |
| 18 | Tahesas_19_ሕይወት_እና_ሞት_በገና_በዓል_Wongelu_Ministries.mp3 | 597 |
| 19 | እውነተኛ ደስታ ከወሲብ ኀጢአት ነፃ አወጣው
የርካሽ ፍቅሮች መፍያ አፍላል
አውግስጢኖስ የተወለደው እ.ኤ.አ. ሕዳር 13፣ 354 አሁን ላይ አልጄሪያ በመባል በምትታወቀው ታጋስቴ በምትባል ስፍራ ነበር። ታጋስቴ ሂፖ በምትባለው ከተማ አቅራቢያ ያለች ከተማ ነች። መካከለኛ ገቢ የነበረውና በግብርና ሥራ ይተዳደር የነበረው አባቱ ፓትሪሺየስ፣ ልጃቸው አውግስጢኖስ በንግግር ጥበብ ሊያገኝ የሚችለውን የላቀ ትምህርት ሁሉ እንዲያገኝ ጠንክረው ይሠሩ ነበር። ዕድሜው ከዐሥራ አንድ እስከ ዐሥራ አምስት አመት ሳለ ከሚኖርበት ስፍራ ሠላሳ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚያክል ርቃ በምትገኝ ማዳውራ በተባለች ከተማ ተማረ። በመቀጠልም አንድ ዓመት ቤት ወስጥ ከቆየ በኋላ ከዐሥራ ሰባት ዓመቱ አንሥቶ ሃያ ዓመት እስኪሞላው በካርቴጅ ትምህርቱን ተከታተለ።
አውግስጢኖስ ለሦስት ዓመት ትምህርት ወደ ካርቴጅ ከመሄዱ በፊት እናቱ ዝሙት እንዳይፈጽም ከምንም በላይ ደግሞ የማንንም ሚስት እንዳያማልል አበክራ አስጠንቅቃው ነበር። ይሁን እንጂ አውግስጢኖስ ከጊዜ በኋላ ኑዛዜ በተሰኘ መጽሐፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ “የርካሽ ፍቅሮች መፍለቅለቂያና መፍያ አፍላል ወደ ሆነው ካርቴጅ መጣሁ… በውስጤ ውስጣዊ ምግብ የሆንከው የአንተ የአምላኬ የማያቋርጥ ራብ ነበር።”[1] በካርቴጅ አንድ ቁባት ይዞ ለዐሥራ አምስት ዓመት አብሯት የኖረ ሲሆን አዲዎዳቱሰ የተባለ አንድ ወንድ ልጅ ከእርሷ ወልዷል።
አውግስጢኖስ ከዐሥራ ዘጠኝ ዓመቱ አንሥቶ እስከ ሠላሳ ዓመቱ ድረስ ለሚቀጥሉት ዐሥራ አንድ ዓመታት የንግግር ጥበብ መምህር በመሆን ያስተምር ነበር።
ተጨማሪ ለማንበብ...
Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website
#Articles | 1 |
| 20 | እውነተኛ_ደስታ_ከወሲብ_ኀጢአት_ነፃ_አወጣው_true_joy_delivers_him_from_the_sin_of.mp3 | 1 |
