fa
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

رفتن به کانال در Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

نمایش بیشتر
1 160
مشترکین
-124 ساعت
+27 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
በቲክቶክ ከ600,000 በላይ ተከታዮች ያሉት ኢብኑል ጀራህ ድምፃችንን አሰምቷል። እኛም በዚሁ የቲክቶክ ቻለንጃችንን አንድ ብለን ጀምረናል። ሀላችሁም ወደ ቲክቶክ ግቡ! የኢብኑል ጀራህ ፖስት ኮሜንት ላይ በመግባት የደረሰውን በዝርዝር አስረዱ። Here is the link https://vt.tiktok.com/ZSH6LC7JT/ . We are just starting ! ! ! ጠንከር በሉ። ለነቢ ኡማ ይህ ምንም አይደል። አባቶቻችን ስንቱን አልፈዋል። ለስንቱስ ታግለው የል እንዴ? @aaumsu

"የትውልድ ድምፅ!" - አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የእኛም ጥያቄ ይኼው ነው። ከሚዲያዎች ደጅ የተሰባሰቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሴቶች ጥያቄም ይኼው ነው። እያልን ያለነው በትውልዱ ሀብት የትውልድ ድም
"የትውልድ ድምፅ!" - አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ    የእኛም ጥያቄ ይኼው ነው። ከሚዲያዎች ደጅ የተሰባሰቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሴቶች ጥያቄም ይኼው ነው። እያልን ያለነው በትውልዱ ሀብት የትውልድ ድምፅ ይሆኑ ዘንድ የተቋቋሙ ሚዲያዎች የትውልዱን ጥያቄ ለፍትሕ በመወገን ያቅርቡ ነው። ውጤቱን አብረን የምናይ ይሆናል። ከውጤቱም ሚዲያዎቻችንን በትክክል ምን አይነት አቋም እንዳላቸው የምናውቅ ይሆናል። በዚያም መሠረት ከሚዲያዎቻችን ማግኘት የሚገባንን ሁሉ በሁሉም ሰላማዊ መንገድ እየጠየቅን ስለ ፍትሕ እንጮኻለን። ጨቋኙን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መመሪያ አጋልጠው መመሪያው ተሻሽሎ ፍትሕ እስኪረጋገጥ ድረስ ለሁሉም በሁሉም ጥያቄ አለን እንላለን። መልስም እንፈልጋለን ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ ለአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ቅሬታ አቀረቡ ! ! ! --------------
+3
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ ለአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ቅሬታ አቀረቡ ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 23 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- በዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፕሬዚዳንትነት የሚመራው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ል አዲስ መመሪያ አውጥቶ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት እየጣሰ እንደሆነ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ ከተማሪዎች ከፍተኛ ቅሬታ እና አቤቱታ ቢቀርብም ዩኒቨርስቲው ለውይይት በሩን ዘግቶ መመሪያውን ሳያሻሽል በደሉን በመቀጠል ላይ ነው። የተማሪዎችን ድምፅ በማስተጋባት ድምፅ ይሆን ዘንድ ለአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ በማህበራዊ ሚዲያ ቻሌንጅ ቢነገራቸውም ምላሽ አለመስጠታቸውን ተከትሎ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዛሬው እለት ከዋና ጽ/ቤታቸው በመገኘት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ ጠይቀዋል። ጨቋኙ መመሪያ ተሻሽሎ ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ ጥያቄያችን ይቀጥላል። ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! @aaumsu

የፍትሐዊው ንጉስ አባጅፋር ልጆች የቀጠለ ቻሌንጅ ለአራዳ ክ/ከተማ ብልፅግና ጽ/ቤት ፍትሕን የሚደፈጥጥ፣ ሕገ-መንግስቱን የሚንድ፣ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መመሪያን አውጥተው ስለመብት መጠየ
+1
የፍትሐዊው ንጉስ አባጅፋር ልጆች የቀጠለ ቻሌንጅ ለአራዳ ክ/ከተማ ብልፅግና ጽ/ቤት ፍትሕን የሚደፈጥጥ፣ ሕገ-መንግስቱን የሚንድ፣ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መመሪያን አውጥተው ስለመብት መጠየቅን ለተማሪዎቻቸው ተጨማሪ የቤት ስራ በማድረግ የዩኒቨርሲቲውን አመራር እና ተማሪዎችን በማራራቅ የሚታወቁትን የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአራዳ ክ/ከተማ ብልፅግና ጽ/ቤት ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት እጩነት ማቅረቡ ይታወሳል። የፈፀሙትን በደል በመዘርዘርም ይህንን ባስቀመጡበት ገፅ ላይ ተቃውሟችንን አሰምተናል። ሆኖም እስካሁን ድረስ የተሰጠ ምላሽም ሆነ በእርሳቸው ላይ የተወሰደ እርምጃ የለም። የአራዳ ክ/ከተማ ፓርቲ ጽ/ቤት ዛሬ በፖሰተው ፖስት ላይ ፓርቲው ለዜጎች ነፃነት እንደሚሰራ፤ ለፍትሕ እንደሚቆም ፤ በዚህም የሕዝብ አመኔታን እንዳተረፈ ገልጿል። በዚህ ላይ ተቃውሞ ባይኖረንም አሁን ላይ ላስቀመጥነው ቅሬታ እርምጃ አለመውሰዱ ግን ጥያቄ እንድናነሳ ያስገድደናል። ፓርቲው የቆመለትን የዜጎች ነፃነት የፓርቲው እጩ ዶክተር ሳሙኤል መመሪያ አውጥተው ጥሰውታል። ፓርቲው እየተጋለት ያለውን ፍትሐዊነት የፓርቲው እጩ ዶክተር ሳሙኤል እያፈረሱት ነው። ስለሆንም በዚህ ላይ ጥያቄ አለን። ጥያቄያችሁንም https://www.facebook.com/61558631456246/posts/122222497034287715/?app=fbl አሳውቋቸው። የጻፋችሁትን አስተያየት ስክሪንሾት (Screenshot) በማንሳት በቦታችን @Niqab_issueBot በኩል ላኩልን። ድል ለፍትህ! ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! ፍትሐዊት ኢትዮጵያ ለሁሉም !!! ©aaumsu @fivekjemaa

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በነጃሺ ቲቪ ዋና ጽ/ቤት በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ----------
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በነጃሺ ቲቪ ዋና ጽ/ቤት በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ------------------------------------------- መጋቢት 23 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- ብልፅግና ፓርቲ በአራዳ ክ/ከተማ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ አድርጎ ያቀረባቸው ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ከሆኑ ቡሃላ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መመሪያ አውጥተው መጠነሰፊ የመብት ጥሰት እየተፈፀመ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ ሙስሊም ተማሪዎች ያሉ ቅሬታዎችን በማቅረብ በውይይት ይፈታ ዘንድ አቤቱታ ያቀረቡ ቢሆንም የእርሳቸው አመራር የውይይት በሮችን በመዝጋት የተማሪዎችን ድምፅ ችላ ብለዋል።   ሙስሊም ሴት ተማሪዎችም በዛሬው እለት ከነጃሺ ቲቪ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት እየደረሰ ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ማብራሪያ በመስጠት ድምፅ በመሆኑ ከፍትሕ ጎን ይቆሙ ዘንድ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።   የሚፈፀሙት በደሎች ቆመው ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ ድምፃችንን ማሰማታችንን የምንቀጥል ይሆናል። ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! ©aaumsu @fivekjemaa

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በመገኘት እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ ያቀረቡ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የፀጥታ አካላት መዋከብ ደረሰባቸው ! ! ! ---
+1
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በመገኘት እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ ያቀረቡ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የፀጥታ አካላት መዋከብ ደረሰባቸው ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 22 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዛሬው እለት ከ5:00 ጀምሮ FBE ካምፓስ በሚገኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል (AAU Center for Human Rights) በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስለሚገኘው የሰብዓዊ መብት ጥሰት የገለፁ ሲሆን ማዕከሉ በሕግ አግባብ ዩኒቨርስቲውን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ሆኖም ግን ይህ ሆኖ ሊጠናቀቅ ባለበት ሰዓት የዩኒቨርስቲው የጥበቃ ሀላፊዎች እና አካላት ተማሪዎቹ ማዕከሉን መጠየቃቸው ስህተት መሆኑን በመግለፅ በተማሪዎቹ ላይ ማዋከብን ፈፅመዋል። የአንዲት ተማሪንም የመታዎቂያ ካርድ የነጠቁ ሲሆን የሌሎቹንም ፎቶ በማንሳት ሄደዋል። እስከ አሁኑ ሰዓት ድረስም ልጆቹን ወደ ፀጥታ ቢሮ በመጥራት በማናገር ላይ ይገኛሉ። ስለ ሰብዓዊ መብቱ በሰላማዊ መንገድ ሊጠይቅ የተሰባሰበ ተማሪ ላይ አግባብነት የሌላቸው ማዋከቦችን መፈፀም ትክክል እንዳልሆነ እናምናለን። ሙስሊም ተማሪዎች እየጠየቁ ያየው ጥያቄ ግልፅ እና ግልፅ ነው። የሰብዓዊ መብታችንን የሚጥሰው ኢሕገ- መንግስታዊ መመሪያ ይሻር ጥያቄያችን ነው። ከዚህ ውጪ ያለግብር ስም እየሰጡ ተማሪን በማንላታት የሚቀር ጥያቄ እና የሚዳፈን ጥያቄ የለም። የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ሁሉ ትኩረት በመስጠት ችግሩን ይፈቱ ዘንድ ጥሪያችን ነው። ©aaumsu

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በመገኘት እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ ያቀረቡ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የፀጥታ አካላት መዋከብ ደረሰባቸው ! ! ! ------------------------------------------- መጋቢት 22 / 2018 ዓ.ል ------------------------------------------- የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በዛሬው እለት ከ5:00 ጀምሮ FBE ካምፓስ በሚገኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል (AAU Center for Human Rights) በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስለሚገኘው የሰብዓዊ መብት ጥሰት የገለፁ ሲሆን ማዕከሉ በሕግ አግባብ ዩኒቨርስቲውን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ሆኖም ግን ይህ ሆኖ ሊጠናቀቅ ባለበት ሰዓት የዩኒቨርስቲው የጥበቃ ሀላፊዎች እና አካላት ተማሪዎቹ ማዕከሉን መጠየቃቸው ስህተት መሆኑን በመግለፅ በተማሪዎቹ ላይ ማዋከብን ፈፅመዋል። የአንዲት ተማሪንም የመታዎቂያ ካርድ የነጠቁ ሲሆን የሌሎቹንም ፎቶ በማንሳት ሄደዋል። እስከ አሁኑ ሰዓት ድረስም ልጆቹን ወደ ፀጥታ ቢሮ በመጥራት በማናገር ላይ ይገኛሉ። ስለ ሰብዓዊ መብቱ በሰላማዊ መንገድ ሊጠይቅ የተሰባሰበ ተማሪ ላይ አግባብነት የሌላቸው ማዋከቦችን መፈፀም ትክክል እንዳልሆነ እናምናለን። ሙስሊም ተማሪዎች እየጠየቁ ያየው ጥያቄ ግልፅ እና ግልፅ ነው። የሰብዓዊ መብታችንን የሚጥሰው ኢሕገ- መንግስታዊ መመሪያ ይሻር ጥያቄያችን ነው። ከዚህ ውጪ ያለግብር ስም እየሰጡ ተማሪን በማንላታት የሚቀር ጥያቄ እና የሚዳፈን ጥያቄ የለም። የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ሁሉ ትኩረት በመስጠት ችግሩን ይፈቱ ዘንድ ጥሪያችን ነው። @aaumsu

💥 የደርስ ማስታወሻ!!!!!!!!!!!!!!! 🗣🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋 አስደሳች ዜና ✅ ከዚህ በፊት በ አቅሳ መስጅድ ስንከታተል የነበረው በጉጉት ስንጠብቀው የነበ
💥 የደርስ ማስታወሻ!!!!!!!!!!!!!!! 🗣🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋 አስደሳች ዜና ✅ ከዚህ በፊት በ አቅሳ መስጅድ ስንከታተል የነበረው በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ደርሳችን የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ኪታብ እነሆ ከዛሬ ጀምሮ በሸይኻችን ሸይኽ አብዱረሂም ሙሳ ለተማሪዎች በልዩ ሁኔታ ዳግም የሚጀመር ስለሆነ ሁላችንም የዚህ እድል ተጠቃሚ እንሁን። ሌሎች ተማሪዎችንም በማስከተል የአጅሩ ተካፋይ እንሁን።
"مَنْ سَلَكَ طَرِيقًا يَلْتَمِسُ فِيهِ عِلْمًا، سَهَّلَ اللَّهُ لَهُ بِهِ طَرِيقًا إِلَى الْجَنَّةِ" «በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድ የጀመረ  ሰው አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ ﷺ
ማሳሰቢያ መቅረት አይፈቀድም!!! 💫ደርሱ የሚሰጥበት ቀን፡ ሰኞ፣ ማክሰኞ እና እሮብ ⏰ :- ከመግሪብ - ኢሻ 🕌🕌  ቦታ፡ አል-አቅሷ መስጂድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

اَلسَّلَامُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللّٰـهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋 💥 የደርስ ማስታወሻ:::::::::::::::::: ✅   በመጀመሪያው ሴሚስተር ላይ ይሰጥ የነበረው የኡምደቱል አህካም ደርሳችን በአላህ ፍቃድ ከተወሰኑ ጊዜያት እረፍት በኋላ ዛሬ ይጀምራል። በመጀመሪያው ሴሚስተር በሳምንት ሁለት ቀን ይሰጥ የነበረው ደርሳችን አሁን እሮብንም በመጨመር በሳምንት ሶስት ከመጝሪብ እስከ ኢሻ የሚሰጥ ይሆናል። «በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድ የጀመረ  ሰው አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ ﷺ ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/Qirat4k/479 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/Qirat4k ⏰ :- ከመግሪብ - ኢሻ   🕌🕌   4ኪሎ ተማሪዎች መስጅድ ©aau4kilomsj

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በትላንትናው እለት ለEBC ካስገቡት ደብዳቤ፦ ፨ ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ል አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ስቃይ እና እንግልት እየደረሰብን
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በትላንትናው እለት ለEBC ካስገቡት ደብዳቤ፦ ፨ ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ል አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ስቃይ እና እንግልት እየደረሰብን ነው። ፨ መመሪያው በአንቀፅ 6.6 ሒጃብን (ኒቃብ) በመከልከል እንዲሁም በአንቀፅ 11.1 የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ልብስ የሆነውን ነጠላ ከአላስፈላጊ ልብስ በመጥቀስ ግልፅ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፅሟል። ፨ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ርብርብ ግማሽ ክ/ዘመንን በስኬት የተሻገረው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጥያቄያችንን በመቀበል ድምፃችንን አሰምቶ ለፍትሕ ያለውን ውግንና በተግባር ያሳይ። ፦ በአላህ ፈቃድ ድምፃችንን በሰላማዊ መንገድ በሁሉም ለሁሉም እናሰማለን። አለምአቀፍ ሚዲያዎችን ጨምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ጠይቀን ምላሽ ያልሰጡንን ሁሉ በቢሯቸው ተገኝተን ከፍትሕ ጎን ይቆሙ ዘንድ እንወተውታለን። ፍትሕ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች! ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ በEBC እና ፋና ዋና ፅ/ቤት በመገኘት አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! --------
+4
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ በEBC እና ፋና ዋና ፅ/ቤት በመገኘት አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! -------------------------------------------- መጋቢት 22 / 2018 ዓ.ል -------------------------------------------- ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ከሆኑ ቡሃላ የሙስሊም ተማሪዎችን ሒጃብ (ኒቃብ) የመልበስ ሰብዓዊ መብት የሚከለክል ኢ- ሕገመንግስታዊ መመሪያ ወጥቶ ተማሪዎች ለመጠነ ሰፊ እንግልት መዳረጋቸው የሚታወቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ ላለፉት 18 ወራት ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች የተደረገ ሲሆን ባለፉት ሳምንታት ውስጥ በማህበራዊ ሚዲያ በተደረገ ዘመቻ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ ሐብት የሆኑት እነ EBC: FANA እና ሌሎች ሚዲያዎች የተማሪውን ድምፅ እንዲያስተጋቡ፤ ዩኒቨርሲቲውን እና አመራሩንም ተጠያቂ እንዲያደርጉ ሲጠየቅ ነበር። ሆኖም ምላሽ ባለመገኘቱ በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሚዲያዎቹ ጽ/ቤት በመገኘት ሚዲያዎቹ ሚዛናዊ እና ፍትሐዊ ዜናዎችን በመስራት እና ዘገባዎችን በማውጣት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ሆነው ሀላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ ጠይቀዋል። በአላህ ፈቃድ መሠል እንቅስቃሴዎች በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ እስኪቆም ድረስ የሚቀጥል ይሆናል። በቀጣይ የሚኖሩ እንቅስቃሴዎችን እና ውጤቶችንም የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም! ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!! ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም! @aaumsu

April the fool - ክፉ ልማድ! ~ ዛሬ April 1 ነው። በዚህ ቀን April Fools' Day or All Fools' Day የሚባል ልማድ የሚከተሉ ሰዎችን ተጠንቀቁ። ሙስሊም የሆነ ሰው ራሱን የማንም ቆሻሻ ባህል ማራገፊያ አያደርግም። በዚህ ዘመን ከነጮች ከተቀዱ ነውረኛ ባህሎች ውስጥ አንዱ ይሄ April the Fool የተሰኘው የጅላጅሎች ልማድ ነው። ያልተከሰቱ ሃሰተኛ ነገሮችን በመንገር ሰዎችን በማስደንገጥ ይዝናናሉ። ሰዎች ላይ ከሚፈጠረው ከባድ ድንጋጤ ይልቅ የራሳቸውን ቅፅበታዊ ደስታ ያስቀድማሉ። ይሄ ልማድ በጣም ጎጂ ነው። ከያዛቸው ጥፋቶች ውስጥ ለመጥቀስ ያክል፦ 1ኛ:- ውሸት አለበት። ውሸት በኢስላም ሐራም ነው። ለቀልድ እያሉ ማቅረቡ እውነታውን አይቀይረውም። ነብያችን ﷺ እንዲህ ይላሉ፡- وَيْلٌ لِلَّذِي يُحَدِّثُ بِالْحَدِيثِ لِيُضْحِكَ بِهِ الْقَوْمَ فَيَكْذِبُ وَيْلٌ لَهُ وَيْلٌ لَهُ "ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ እየዋሸ ወሬን የሚያወራ ሰው ወዮለት! ወዮለት! ወዮለት!" [አቡ ዳውድ፣ ነሳኢይ፣ ቲርሚዚይ እና አሕመድ የዘገቡት ሲሆን ሸይኹል አልባኒይ “ሐሰን” ብለውታል፡፡] 2ኛ፦ ሰዎችን ማስደንገጥ አለበት። ይሄ ከዚህ ልማድ ጋር በሰፊው የተቆራኘ ጥፋት ነው። ሰዎችን ማስደንገጥ መዝናኛ ሊሆን አይገባም። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:– لا يحل لمسلم أن يروع مسلماً "ለሙስሊም ሙስሊምን ሊያስደነግጥ አይፈቀድለትም።" አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 5004] 3ኛ፦ በአጥፊዎች መመሳሰልና የሌሎችን ብልሹ ባህል ማስፋፋት አለበት። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ "በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው።" [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 3401] ስለዚህ ይህን ክፉ ልማድ በመፈፀም ራሳችንን ወንጀል ላይ፣ ሌሎችን ድንጋጤና አደጋ ላይ ከመጣል ልንቆጠብ ይገባል። = ©Ustaz Ibnu-Munewor @fivekjemaa

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ በEBC እና ፋና ዋና ፅ/ቤት በመገኘት አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! --------
+4
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርሲቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ በEBC እና ፋና ዋና ፅ/ቤት በመገኘት አቤቱታ አቀረቡ ! ! ! -------------------------------------------- መጋቢት 22 / 2018 ዓ.ል -------------------------------------------- ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ከሆኑ ቡሃላ የሙስሊም ተማሪዎችን ሒጃብ (ኒቃብ) የመልበስ ሰብዓዊ መብት የሚከለክል ኢ- ሕገመንግስታዊ መመሪያ ወጥቶ ተማሪዎች ለመጠነ ሰፊ እንግልት መዳረጋቸው የሚታወቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ ላለፉት 18 ወራት ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች የተደረገ ሲሆን ባለፉት ሳምንታት ውስጥ በማህበራዊ ሚዲያ በተደረገ ዘመቻ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ ሐብት የሆኑት እነ EBC: FANA እና ሌሎች ሚዲያዎች የተማሪውን ድምፅ እንዲያስተጋቡ፤ ዩኒቨርሲቲውን እና አመራሩንም ተጠያቂ እንዲያደርጉ ሲጠየቅ ነበር። ሆኖም ምላሽ ባለመገኘቱ በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሚዲያዎቹ ጽ/ቤት በመገኘት ሚዲያዎቹ ሚዛናዊ እና ፍትሐዊ ዜናዎችን በመስራት እና ዘገባዎችን በማውጣት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ሆነው ሀላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ ጠይቀዋል። በአላህ ፈቃድ መሠል እንቅስቃሴዎች በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ እስኪቆም ድረስ የሚቀጥል ይሆናል። በቀጣይ የሚኖሩ እንቅስቃሴዎችን እና ውጤቶችንም የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም! ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!! ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም! @aaumsu

በታላቁ መሪ ንጉስ አባጅፋር ስም የተሰየመውን "ቻሌንጅ 7" በመቀበል፣ መብታችሁን ለማስከበርና ድምፃችሁን ለማሰማት እያሳያችሁት ያለው ቁርጠኝነት እጅግ የሚያስመሰግን ነው። በፌስቡክ ገጹ ላይ እየሰጣ
+5
በታላቁ መሪ ንጉስ አባጅፋር ስም የተሰየመውን "ቻሌንጅ 7" በመቀበል፣ መብታችሁን ለማስከበርና ድምፃችሁን ለማሰማት እያሳያችሁት ያለው ቁርጠኝነት እጅግ የሚያስመሰግን ነው። በፌስቡክ ገጹ ላይ እየሰጣችሁት ያለው አስተያየትና መረጃዎችን የማጋለጥ ተግባር፣ ለውጥ የሚመጣው በተደራጀና በሰላማዊ ትግል መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል። እስካሁን አስተያየታችሁን የሰጣችሁና ስክሪንሾት በመላክ ተሳትፏችሁን ያረጋገጣችሁ ጀግኖች፣ ለፍትህ የምታደርጉት ጉዞ የብዙዎችን ልብ እያነሳሳ ነው። ይሁን እንጂ ትግላችን ግቡን እንዲመታ ድምፃችን ከዚህ በላይ መጎላት ይኖርበታል። ሌሎች ተማሪዎችና የፍትህ ፈላጊዎችም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም፣ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የመብት ረገጣና የአመራር ብቃት ጉድለት ለአለም እንዲታወቅ በማድረግ የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናድሳለን። ዝምታ ለበደል እውቅና መስጠት በመሆኑ፣ አሁኑኑ ሊንኩን በመጫን "ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!" የሚለውን ድምፃችሁን አሰሙ። አስተያየታችሁን ስክሪንሾት በማንሳት በቦታችን መላክ አትርሱ፤ የእናንተ ተሳትፎ የነገውን ብሩህና ፍትሃዊ የዩኒቨርሲቲ ህይወት ይወስናል። ድል ለፍትህ! @aaumsu

💥የአያሙል ቢድ ጾም ነገ ረቡዕ ይጀምራል!💥 ➡️ ነቢዩ (ﷺ) በየወሩ ሶስት ቀናትን መጾም ለሚፈልግ ሰው፤ በጨረቃ አቆጣጠር 13ኛ፣ 14ኛ እና 15ኛ ቀናትን እንዲጾም መክረዋል። [ቲርሚዚና ነሳኢ] 🖊 እነዚህ ቀናት ጨረቃ ሙሉ ሆና በምትታይበት ብርሃናማ ሌሊቶች ምክንያት "አያሙል ቢድ" (ነጭ ቀናት) ይባላሉ። በእነዚህ ቀናት መጾም በሱና ደረጃ እጅግ የተወደደና ትልቅ ምንዳ ያለው ተግባር ነው። ☑ የሸዋል ወርም ግማሽ ልንደርስ ነው ፤ የስድስቱ ቀናት ጾም በሮች ግን አሁንም ክፍት ናቸው።እስካሁን 6ቱን የሻዋል ቀናት ያልጾመ ከነዚህ አያሙል ቢድ ቀናት ጋር አንድ ላይ ነይቶ በመጾም የተደራረበ ምንዳን ሊያገኝ ይችላል ። በረመዳን ያገዘን ጌታ ኒያ ካለን አሁንም ያግዘናል። የአላህን ውዴታ ለማግኘት እነዚህ ቀናት ጥቂት ናቸው!
አላህ በሐዲሰል ቁድሲይ እንዲህ ይላል፦ "ባሪያዬ በትርፍ ስራዎች (በነዋፊል) ወደ እኔ መቃረቡን አይተውም፣ እኔ እስክወደው ድረስ።"
✨💫ክቡራት ሆይ! የአላህን እገዛ ጠይቁ፤ እነዚህን ታላቅ ቀናት መጾም እንዳትዘነጉ። አላህ ለታዛዥነቱ ይምራን! አላህ ይወፍቀን!

💥 ደርስ ማስታወሻ ::::::::::::::::::::::: 🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋 ✅ ኢንሻአላህ  ዛሬ ሙዳራቱ ናስ (በመልካም መኗኗር)የተሰኘው የአደብ ደርስ ይኖረናል :: 📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ ⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመጝሪብ እስከ ዒሻ ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/Qirat4k/672 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/Qirat4k

🔖አንድ ሰው ወደ ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ መጥቶ "እከሌ እንዲህ ስሰድብህ ነበር" አለው። እርሳቸውም፦ "ያ የሱ መዝገብ ነው፤ በፈለገው ነገር ይሙላው" አሉ። 👉አንድ ሰው ወደ ወህብ ኢብኑ ሙነቢህ መጥቶ "እከሌ ይሳደብህ ነበር" አለው። እርሳቸውም፦ "ሼይጣን ካንተ ዉጭ ሌላ መልዕክተኛ አላገኘም ነበር ወይ?!" አሉት ። 🎯አንድ ሰው ለአንድ ሰው "እከሌ ሰደበህ" ቢለው ስነግረው ፣ እንዲህ ሲል መለሰ፦ "እሱ ቀስት ወርውሮብኝ ነበር፤ ነገር ግን አልመታኝም፤ ታዲያ ለምን ቀስቱን አንስተህ ልቤ ውስጥ ትሰካዋለህ?" ✍አንድ ሰው ወደ ኢማሙ ሻፊዒይ መጥቶ "እከሌ በክፉ ያነሳሃል" አለው። እርሳቸውም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፦ "እውነት ከሆነ  (አሚያማ) ሰው ነህ፤ ውሸት ከሆነ ደግሞ ወንጀለኛ (ፋሲቅ) ነህ።" ያ ሰውም አፍሮ ተመለሰ። 🤲አላህ ከወሬና ከነገር (ከቂል ወል-ቃል) ይጠብቀን።

‎👋‎👋اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋‎👋 እስከ አሁን ቴምር ያልወሰዳችሁ እህት፣ወንድሞች የፊታችን  እሁድ, መጋቢት 27 (April 05) የመጨረሻ ቀን ስለሆነ እስከ እሁድ ድርስ እንድትወስዱ እናሳስባለን። ለወንዶች 👉ዶርም ያላችሁ B block ዶርም ቁጥር 302 መታችሁ መውሰድ ትችላላችሁ። 👉ዶርም የሌላችሁ እንዲሁም የማይመቻችሁ በዚ ስልክ ደውሉ 0905877461 ለሴቶች 👉ዶርም ያላችሁ የሴቶች ዶርም C block ዶርም ቁጥር 115 ወይም 407 መጣችሁ መውሰድ ትችላላችሁ። 👉ዶርም የሌላችሁ እና ለማይመቻችሁ በዚህ ቦት @fivekjemaa_bot  አናግሩን ።

ቻሌንጅ 7 — የንጉስ አባጅፋር ልጆች ለዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ! ንጉስ አባጅፋር ለፍትሕ ፀንተው በመቆም እና በጥበብ በመታገል የሚታወቁ ታላቅ መሪ ናቸው። ዛሬም በእርሳቸው ስም በሰየምነው በዚህ ቻሌንጅ፤ ፍትሕን በማጓደልና ሃይማኖታዊ መብታችንን በመጣስ ላይ ስላሉት የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ድምፃችሁን በንቃት ታሰሙ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና መላው የፍትህ ፈላጊዎች ሆይ! በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲያችን ከፍተኛ አመራር ደረጃ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ከሀገሪቱ ሕገ-መንግሥትም ሆነ ገዥው ፓርቲ በይፋ ከሚያራምደው "መደመር" እና የውይይት ባህል ጋር በእጅጉ የሚጋጩ ሆነው አግኝተነዋል። የዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ አመራር የተማሪዎችን ሃይማኖታዊ መብቶች የሚጥስ መመሪያ ከማውጣት ባለፈ፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የሚቀርቡ አማራጮችን ሁሉ በዝግተኝነትና በእምቢተኝነት አልፏቸዋል። እንዲህ ዓይነት የውይይት በር የዘጉ እና መሠረታዊ የዜጎችን መብት የረገጡ ግለሰቦች ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ሆነው መቅረባቸው እጅግ የሚያስገርም ብቻ ሳይሆን፣ ፓርቲው ለዜጎች መብትና ለሙስሊም ተማሪዎች ያለውን ትክክለኛ አቋም ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው። ስለሆነም ዝምታ መፍትሄ አይሆንም! መብታችን የሚከበረው ድምፃችንን በአንድነት ስናሰማ ብቻ በመሆኑ፣ ሁላችሁም የቀረበውን የፌስቡክ ሊንክ https://www.facebook.com/reel/1529200765593420/?app=fbl በመጫን በቪዲዮው ስር እየተፈጠረ ያለውን የመብት ጥሰት እና የአመራር ብቃት ጉድለት በማጋለጥ፣ "ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!" የሚል አስተያየታችሁን (Comment) እንድታሰፍሩ እናሳስባለን። ፍትህ እንዲሰፍንና ብሶታችን ለሚመለከተው አካል እንዲደርስ ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ! በመጨረሻም የጻፋችሁትን አስተያየት ስክሪንሾት (Screenshot) በማንሳት በቦታችን @Niqab_issueBot በኩል ላኩልን። ድል ለፍትህ! ©aaumsu @fivekjemaa