5killo Jem'a official Channel
رفتن به کانال در Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
نمایش بیشتر1 162
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
+730 روز
آرشیو پست ها
🎉ደርሷሷልል ❕
🔥 ሕያው ምስክር ~ 1 ~ 🔥
ዘመናትን ሲሸጋገር የቆየው የ ጭቆና ብትር በ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ!!
እነሆ ታሪካዊው መድረካችን 1 ብሎ ለ ዛሬ ቀጠሮውን ይዟል! እውነታዎችን በማስተንተን ማንነትን በ አግባቡ መገንባት ላይ ያተኮረው "የሕያው ምስክር" መድረክ በ ታሪክ ገጽ ደምቆ የሰፈረወን የ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል ሊያስቃኛቹ ዝግጅቱን አጠናቋል !!
🗯የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የነፃነት ጉዞ ምን ይመስል ነበር !?
🗯አምስቱ ዋና ጥያቄዎቻቸው ምን ምን ነበሩ ?!
🗯እጅግ ፈታኝና ተስፋ አስቆራጭ የነበረው ትግል በምን መልኩ መፍትሄ ሊያገኝ ቻለ ?!
በ ሙስሊምነታቸው ሲደርስባቸው የነበረውን መራራ በደል "ከሙተነቂቦች መንደር" በ ጥቂቱ ልናስቃኛችሁ ሞክረናል፣ በ ዛሬው ምሽት በ 2017 ስለ ተደረገው የተቀናጀ እና ብዙዎችን ስላስደመመው፣ ጠይቆ ታግሎ ማንነትን እና መብትን በማስከበር ረገድ ትልቅ ተምሳሌት ሆኖ ስላለፈው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል በ ጥልቅ እንዳስሳለን።
✨ከ ሃይስኮል እስከ ኮሌጅ
✨ከ ዩኒቨርሲቲ እስከ ሥራው ዓለም ድረስ ስለ ችግሮቻችን ያሰሰበው ሁሉ፣ ለተጨነቀ እና ለመፍትሄው ለተብሰለሰል ሁሉ ለመንገዳችን ትልቅ ስንቅ ምንሰንቅበት ልዪ መድረክ ነው!
🗓ዛሬ(ጁምዐ) ማታ 3:00 በቀጠሯችን እንገናኝ!
@aaumsu
🗯ድምጽ አልባው እምባ!
🔥ከዛው ከዲላ ከሙተነቂቦች መንደር..ነፃነት'ን በልመና!¡
'በመንገዱ' ላይ ላላችሁ ሁሉ ያጠነክራችሁ ዘንድ ዛሬ የ አንዷን እህቴ ታሪክ ፈተና ላጋራችሁ ወደድኩ...
ትላለች••
ከመስጂድ መልስ ቁርስ ሰአት ሲደርስ ሁሌም በምንገባበት የጀርባ በር ሄድኩ። እንደሁሌውም ተረኛ ጠባቂው ማን ይሆን ..¿ እያልኩ ። ኡፍ ያቺ ሴት ከሆነች በቃ አታስገባኝም !! ሳልወድ በግዴ ጠዋት ወደ መስጂድ ስወጣ << ሰላም አደራቹ ለ2 ወር ብቻ >> ብዬ የምለማመጣቸው ነገር ትዝ አለኝ። ክላስ ልንጨርስ 2 ወር ነበር የቀረን። እስከዛው ድረስ ነጻነት'ን በልመና !¡
እንደፈራሁት አትገቢም አለኝ። <<እንዲ ለብሶ መግባት አይቻልም !! ከላይ የተሰጠን ትእዛዝ ነው። ከዚ ቡሃላ በዚ በር እንዳትመጪ>>አለኝ። በፊት በር ሄድኩ። የዋናው በር ጋር ስደርስ የተወሰኑ ሰዎች ሰብሰብ ብለው ስለነበር ልብ አላሉኝም። አልሃምዱሊላህ id አሳይቼ ብቻ ገባሁ።
በሰላም በመግባቴ ደስ እንዳለኝ ክላስ እንዳላረፍድ እየተሯሯጥኩ ወደ ካፌ ሄድኩ። ያለ ወትሮ ከካፌ ውጪ በሩ ላይ ዳቦ እየሰጡ ነበርና ተጠግቼ ሚልካርዴን ሰጠሁት።
<<ይሄን ለብሳችሁ አትምጡ አልተባላቹም!! አይሰሙምኮ>> እያለ አምባረቀብኝ። እንዴት ክው እንዳልኩ: ጸጥ አልኩት። መልስ ከምመላለስ ብዬ ትቼው መንገድ ስጀምር <<ነይ!! ነይ!! >>አለኝ ።
ስመለስ አይዲሽን አምጪ ሲለኝ ሁሌም እንደምለው ID አልያዝኩም ብዬ ሚል ካርዴን ሰጠሁት።
"ያለ id መስጂድ መሄድ አይታሰብም" እያልኩ በ ውስጤ።
"አይዲሽን ስታመጪ ሚልካርዱ ይመለሳል!" አለኝ።
ከእህቶች ጋር ባወራም መፍትሄ አላገኘሁም። ካፌ ሳልደርስ ሳምንታት አለፉ ምግብ መግዣ ብርም አለቀብኝ። ከበፊትም ቤተሰቦቼን ብር መጠየቅ አልወድም ነበር። አሁን ግን ግድ ሆነብኝ።ሳገኝ እየበላው ብዙውን ጊዜ በ ባዶ እያሳለፍኩ ቀስ በ ቀስ እየደከምኩ በመጨረሻ ታምሜ ሆስፒታል የሄድኩበትን ጊዜ አልረሳም።
እጄ ላይ ካኑላ እንደተደረገ ወደ ካፌ ስሄድ ያለ ሚልካርድ አናስገባም ብለው አባረሩኝ፣ ውጪ ያገኘውት ጥላ ስር ቁጭ ብዬ ሳለቅስ <<እዚህ ጋር እንዲ ለብሶ መቀመጥ አይቻልም !!ልጆች ይደነግጣሉ !!>> ያሉኝን ቀን መቼም አረሳውም ።
ታድያ ምን ይሻላል?!?
ከዶርምሜቴ ጋር እያውጠነጠንን 1 አስደናቂ ሃሳብ ጓደኛዬ ፈለቀላት። የሚገርመው እስልምናን ምታከብር ክርስቲያን ነበረች።
ያኔ የሚሰጠን ሚል ካርድ ወረቀት ነበርና ቲክ ተደርጎ ሲያልቅ ሌላ ይተካል። የሷ ወረቀት ስላለቀ ሳታስረክብ አዲስ ወረቀት ተቀበለች። ያለቀውን ሚልካርድ ስም በውሃ አነካክተን አስለቀቅነው።በቦታው የኔን ስም ጽፈንበት ሚልካርድ ወደ ሚቀየርበት ቢሮ ሄደን አስቀየርን። ከዛ በዛ አድርጌ ካፌ መግባት ጀመርኩ።
አቤት ዱዓ፣ ጭንቀት .. ለምን ኒቃብ ለበሽ ብቻ !!"
ብዙ ያልተነኩና የልተዳሰሱ አሻራዎች ያሉበት መንገድ!
✨ሕያው ምስክር ~ 1 ~ ዲላ ዩኒቨርስቲ የነፃነት ትግል!!
🗓ነገ(ጁምዐ) ከ ምሽቱ 3:00 እንገናኝ!
@aaumsu
🔥ለ ሱመያ ልጆች የተዘጋጀ ታላቅ መድረክ!
🔥ለ ኢማም አህመድ ኢብኑ ኢብራህም አል ጋዚ ልጆች የተዘጋጀ ታላቅ መድረክ!
" የ ጥያቄ አለን ትውልድ ሚዘነጋው ትግል የለም!"
የ ትግስት፣ የ ታማኝነት፣ የ ጽናት፣ የ ጥንካሬ፣ የ አንድነት ምሳሌ ሆነው ስላለፉ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!! በ ሕያው ምስክር 1!
🗓ነገ(ጁምዐ) ከ ምሽቱ 3:00 በዚው ቴሌግራም ቻናል ይጠብቁን!
@aaumsu
🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ
ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨
💎 { إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا }
የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
" የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት
ያወርድለታል.......
ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣
ሰለዋት ጭንቀትን ይቀንሳል፣
ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
መልካም ጁምዓ🌟@fivekjemaa
Repost from 5killo Jem'a official Channel
🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ
ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨
💎 { إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا }
የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
" የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት
ያወርድለታል.......
ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣
ሰለዋት ጭንቀትን ይቀንሳል፣
ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
‣ በዛሬው ዕለተ Exit exam ለሚወስዱ እህት/ወድሞቻችን አላህ ፈተናውን ገር እንዲያደርግላቸው በዱዓ እናስታውሳቸው 🤲🤲
🤲 اللهم وفّق إخواننا وأخواتنا المقبلين على امتحان الخروج غدًا، ويسّر لهم كل عسير، وافتح عليهم فتوح العارفين، وارزقهم النجاح والتوفيق.
🌟
መልካም ጁምዓ🌟
🌟መልካም ፈተና ለተፈታኝ እህት ወንድሞች🌟
@fivekjemaa💥አደለም ማስክሽን ከ አንገት በላይ ራሱ መከፈት አለብሽ ገና❕
🔥ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ሙተነቂቦች መንደር~3
መስጂድ ውስጥ ዙሁር ተሰግዶ ሱና ለመስገድ ልቆም ስል ወደ መስጅድ ስትገባ አየዋት፣ ደና አትመስልም ... ወደ እኔ እየተጠጋች ስትመጣ ሁኔታዋ ግራ ገባኝ። ስሟን እየጠራው በ አትኩሮት ሳያት እያለቀሰች ነው፣ ሄጄ 'ምን ሆነሽ ነው!?' ብዬ አቀፍኳት፣ ጥያቄዎቼ ሳያበቁ ለቅሶዋ እየጨመረ እዛው እንዳቀፍኳት ራሷን ሳተች። በ ድንጋጤ አጠገቤ የነበረችውን ልጅ ጠርቼ ለ ሁለት ይዘናት መሬት ቁጭ አልን፣ ስሟን ደጋግመን እየጠራን ለመቀስቀስ ብንሞክርም ልትነቃ አልቻለችም። እንደ ምንም ራሳችንን አረጋግተን ወደ ክሊኒክ ልንወስዳት ይዘናት ወጣን...
ነርሶቹ 'ተረጋጉ ተረጋጉ ደና ናት!' እያሉ አልጋ ላይ አስተኝተው ግሉኮስ ሰኩላት። ግራ እንደተጋባን እስክትነቃ አጠገቧ ቁጭ ብለን ጠበቅን፣ የግልኮስ ማነስ ነው ሲሉን ወደ መስጂድ ስትገባ ይዛው የነበረውን ምግብ አስታውሼ ቁርስ አልበላችም ማለት ነው ከድካሙ ከፀሀዩጋ ተደማምሮ ይሆናል ብለን ገመትን ግን ለምን እንደዛ አለቀሰች ?!?ከመብሰልሰል እና ከመገመት ውጪ ምንም ማድረግ አልቻልንም.....
አልሃምዱሊላህ ከሰዓታት ቆይታዎች በሗላ ነቃች፣ ነገር ግን አሁንም ከቅድሙ በባሰ እምባዋ ግጥም ብሎ መንሰቅሰቅ ጀመረች !!
"ይቅርታ አድርጉልኝ"
"ይቅርታ አድርጉልኝ" እያለች ታለቅሳለች
የሆነችው ምኑም ሳይገባን አብረናት ማልቀስ ጀመርን... "በ አላህ አፍው በሉኝ ይቅርታ!" እያለች እየደጋገምች ታለቅሳለች እንደምንም አንዴ በልመና፣ነርሶቹ ሲቆጡም ተረጋጋች። የዚህን ሁሉ ምክንያትም በለቅሶ ታጅባ መንገር ጀመረች .....
ምግብ ይዤ በ ዋናው በር ወደ ግቢ ለመግባት ስሄድ ማስክሽን አውልቂ ብለው በጣም አስቸገሩኝ፣ ዋናው በር ማለት እንግዲ እኛ ሃራም ነው የተባልን ይመስል ድርሽ ማንልበት በር ነው፣ እንኳ ኒቃብ ማስክም እሺ ብለው አያስገቡም። ቀጠለች እኔም ፊቴን አልከፍትም ብዬ በ ሁለተኛው በር ለመሞከር በዛ ጠራራ ጸሐይ ዞሬ ሄድኩኝ። እሱ በር ደሞ ለመስጂድ የቀረበ እና አብዛኛውን ጊዜ ሙስሊም ተማሪዎች ሚጠቀሙት በር ነው እና እንደ ዋናው በር አያስቸግሩም ነበር፣ ምንም እንደማይሉኝ ተስፋ እያረኩ መታወቂያዬን ለ ጥበቆቹ እያሳየው ወደ ውስጥ ልገባ ስል "ነይ ነይ ፊትሽን ክፈቺ እንጂ!!" አሉኝ የቆሙት ጥበቆች አሷ ትፈትሸኝ ለሷ አሳያለው አልኩኝ ወደ ሴቷ ጥበቃ እየጠቆምኩኝ በጣም እየተባባሰባቸውም ስለሆነ ሊሰሙኝ አልቻሉም፣ ረጅም ሰዓት ቆሜ ተከራከርኩ ግን ከማመናጨቅ ውጪ ሊያስገቡኝ ፍቃደኛ አልነበሩም። በጣም ደክሞኝም ስለነበር ማስኩን ከፍቼ አሳየዋቸው እና አለፍኩ።ወደ ውስጥ እየገባሁ ማስኬን ሳስተካክል አይቶኝ በድጋሚ ጠርቶ "ጭራሽ አውልቂ አይቻልም ስልሽ ትለብሺያለሽ እንዴ!!" አለ በቁጣ ••"የምን ማስክ! የምን ፊት መሸፈን ነው! አደለም ማስክሽን ከ አንገት በላይ ራሱ መከፈት አለብሽ ... " እያለ ስለጅልባቤ እንኳ ሳይቀር ለመስማት በሚሰቀጥጥ መልኩ ሲያወራ አልቻልኩም እና ምግቡን እንደያዝኩ ቀጥታ ወጥቼ ወደ መስጅድ ነበር የሄድኩት፣ እዛ እናንተን ሳይ ደሞ ብላ አሁንም መንሰቅሰቅ ጀመረች።
"እናንተ ኒቃቡን አናወልቅም ብላችሁ ለሱ ስትታገሉ እኔ ግን ማስኬን ዝቅ አደረኩኝ, ጭራሽ ማስኬን ዝቅ ሳረግላቸው ደሞ ጸጉርሽን አንገትሽን አሉኝ!!!"
በአሏህ አውፍ በሉኝ••
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
🍂ሁሉም ስለምንታገልለት እስልምና እና ስለ ትግሉ በደምብ እስከተረዳ ድረስ!
🍂የ አንዱ ህመም ሌላውን እስከተሰማው ድረስ!
🍂ጠላት ፊት በ 1 እስከቆምን ድረስ
በ ጥንካሬ እስከጸናን ድረስ፣ በ አላህ እስከተመካን እና እስከታገልን ድረስ የ አሸናፊዎች መንገድ ላይ ነን!!
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
✨ሕያው ምስክር ~ 1 ~በ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ስለተደረገው ታሪካዊ የ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል ሙሉ ሁኔታ ሚዳሰስበት ልዩ መድረክ!
🗓 (ነሐሴ, 15) ጁምዐ ምሽት 3:00LT
በ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይፋዊ ቴሌግራም ቻናል @aaumsu
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ
በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ
ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ
ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ!
ጁምዓ (ነሐሴ 15) ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ !
ልብ ጭቆናን አሻፋረኝ ብሎ የሰራውን ተዓምር የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ትግል ሕያው ምስክር ሆኖ እንቃኛለን። የሌቱ ጨለማ ከሚደርሰው በደል በላይ አያስፈራም ብለው 11 ምሽቶችን ከውጪ ስላሳለፉ እንቁዎች ታሪክ እንዳስሳለን።
ቻለንጁን እንቀላቀል !
@aaumsu
ሕያው ምስክር - 1
መብታቸው ይከበር ዘንድ 11 ምሽቶችን ከውጪ አድረዋል። መብታቸው ይከበር ዘንድ ለ11 ቀናት ያክል ከክላስ፣ ከምግብ እና ንባብ እንዲርቁ ተደርገዋል። የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ማለት ነው። ሆኖም በምንም ሳይሸበሩ፤ ምንምም ወደሗላ እንዲሉ ሳያደርጋቸው ታገሉ። መብታቸውን እንዳስከበሩም ያለፋቸውን በክብር ተምረው፤ በነፃነት ሕያዎታቸውን ቀጠሉ።
ሙሉ ታሪኩን በመጪው ጁምዓ ከምሽቱ 3 ሰዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል (@aaumsu) ይጠብቁ። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSVSeWBf3/ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ።
@aaumsu
🚫"የ ጥበብ መጀመርያ እየሱስን ማወቅ ነው"❗️
🔥ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ሙተነቂቦች መንደር~2
በ ጊዜ ውስጥ እኔም ያ ውድ የሆነውን ባለ ግርማ ሞገሶቹን ስብስብ ለመቀላቀል ታደልኩ!! ፊታቸውን በመሸፈን ጥሩ ነገር ለማበርከት ከሚታገሉት ውስጥ ለመሆን በቃው🍂!!የ አዲስ ተማሪዎች መግብያ ጊዜ ደረሰ! ተማሪን ለመቀበል ዋናው በር ላይ በ ኒቃብ መታየት ስለማይታሰብ እኔም በ ማስክ ከተምኩ። እንደዛም ሆኖ አንዱ ኃላፊ እየተከታተለኝ እንደነበር አስተውያለው በኔ አቅጣጫ መምጣት ጀመረ: ሲደርስ "አንቺ!!" ብሎ አንገቴ ላይ ያደረኩትን የ ክበብ መታወቅያ ያዝ በማድረግ፣ "ይሄ የ ምን ክበብ ነው?!" አለኝ •• እኔም "ተማሪ..." ሕዝብ ፊት እሱንም ስንት አይነት ተማሪ እያለ መቶ ያደረኩትን መታወቅያ በ ንቀት ይዞ እያናገረኝ መሆኑ ሴትነቴን ቢፈታተነውም ዋጥ አድርጌው "የ ሴቶች ማህበር ነው!" አልኩት በ ኩራት እና በ ድፍረት!! እያፌዘ 'የ ሴቶች ማህበር ነው' ብሎ አመናጭቆ ከ አንገቴ ላይ ወረወረው! እንደዛም እየሆነ አዲስ ግቢውን ከሚቀላቀሉ ተማሪዎች መካከል ኒቃብ ሚልብሱ እህቶች አይጠፉም ነበር። ነገራቶች በጣም የከረሩበት ዓመት ላይ 1 ፍሬሽ ኒቃቢስት ወደ ግቢው ልትገባ ስትል ተመለከትኩ፣ ደስታም ሃዘንም እየተፈራረቀብኝ ምን ሊሏት እንደሚችሉ እያሰብኩ ወደሷ አመራው ... አዲሱ ኃላፊ የተባለው እንዳየን "ቆይ ቆይ ቆይ!! ወዴት ነው!? ሕጉን አታውቁም?! እንዲ ለብሶ መግባት አይቻልም! " አለ ተኮሳትሮ። ያ ራህማን ዛሬ ደሞ ይሄ ከየት ነው የመጣው እያልኩ በ ውስጤ "አይ አዲስ ስለሆነች ነው፣ ለ ዛሬ ትግባ! አስፈላጊ ከሆነ በ ሴት መፈተሽ ትችላለች" አልኩ ፈጠን ብዬ "አይ አይ!! በጭራሽ ውስጥ አውልቃው ትግባ" አለኝ! "እንደዛማ አይሆንም! ፍሬሽ ነች ለ ዛሬ ትግባ .." እንዲው እየተከራከርን ቆይተን በ አቋሙ እንደጸና የ ግል ሃብቱ ይመስል በፍጹም አላስገባም ብሎ መለሳት! በማስታውሰው ከነሱ ጋር የነበረው የመጨረሻ ንግግሬ ክላስ እየሄድኩ ID የቀሙን ጊዜ ነበር! 🍃ካፌውንም ላይብረሪውንም ምኑንም ምኑንም ከተውነው ቦሃላም አንዳንዴ ደስ ሲላቸው ዶርም ድረስ እየመጡ ኒቃብ መልበሳችንን ሲያዩ id ያችንን ወስደውት ይሄዳሉ። ከሁሉም በላይ ሚገርመኝ ደሞ ፈርመንም ቢሆን መታወቅያችንን ለመቀበል ቢሮ ስንሄድ እንደ ወጉ ሕጎችን ስለማክበር እና ስለ secularism ምክር ቢጤ ነገር ሲሰጡን ሁሌም ማፈጥበት ከራሳቸው ግድግዳው ራስጌ ላይ ያለው "የ ጥበብ መጀምርያ እየሱስን ማወቅ ነው" ሚለው ግልፅፅፅ ብሎ ሚታየው ጽሑፍ ነው ... ሁለት ሆነን ክላስ ለመግባት እየሄድን ነበር አንዱ የ ጥበቃ ኃላፊ id አምጡ ብሎ ጠራን ••• 'እእ አልያዝንም' አልነው! በቃ ሁሌም እንደዛ ነው ምንለው፣ ቀምተው ዲሲፕሊን አስፈርመው ስለሆነ ሚሰጡን •• "ወደ ክላስ እየሄድን ነው id ደሞ አልያዝንም" እያልን እንደምንም ለማለፍ ሞከርን፣...ግትር ሲልብን ኃላፊው በ ቅርብ ተቀይሮ የገባም ስለሆነ፣ እስኪ እናሳየው ምንም አያመጣም ብለን አውጥተን አሳየነው። ተቀበለንና "ሂዱ በቃ!" አለን ንቀት በተሞላበት አነጋገር! "እንዴ ምን ማለት ነው?! ከፈለክ በ ሴት ጥበቃ እንፈተሽ ግን id ወስደህብን እንዴት ነው ግቡ ውስጥ ምንንቀሳቀሰው, ተማሪ መሆናችንን ለማረጋገጥ አልነበር ?! ይሄው id ያችን፣ ተማሪ ነን! ክላስ ረፍዶብናል ስጠን!" እያልን መጠይቅ ያዝን... መለሰ "ሲጀመር እናንተ እንደ አሸባሪ አልሸባብ ስትሆኑ ነው እንጂ እምነታችሁ እኮ ይሄን አያዝም!" ብሎ "ID ከፈለጋችሁ እሱን ነገር አውልቁና ማስክ አድርጋችሁ መጣችሁ ውሰዱ!" እያለ ስለ ኒቃብ ሲያወራ "በቃ በቃህ አንተ ስለ እምነታችንም ሆነ ስለ ልብሱ ምንም አታውቅም id ውንም ከፈለክ ውሰደው" ብለን በ ንዴት እየበገንን ወደ ክላስ ሄድን። ሕያው ምስክር ~ 1 🗓: የ ፊታችን ጁምዐ(ነሐሴ,15) ከ ምሽቱ 3:00LT በ ልዩ መድረክ! @aaumsu
እህቶች ብቻ የተጋሩት ታሪክ!
በ እህቶች ብቻ የታበሰ እምባ!
💭ዝምተኛው ትግል!
🔥ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ሙተነቂቦች መንደር 1
ልክ እንደ ትናንት ከ 3 ዓመት በፊት አንዷ እህቴ ላይ የደረሰውን ነገር ሳይ ነበር ውስጤ የ ትግል እሳት የተቀጣጠለው! ግቢ መግብያ 2 ሰዓት ነበር። በ ሰዓቱ በማላስታሰው ምክኒያት ሙስሊም ተማሪዎች የምንጠቀመው ከ መስጅዳችን(ሙሃጂሪን) ፊት ለፊት ያለውን የ መግብያ በር መጠቀም እንደማንችል እና በ ዋናው በር እንድንዞር ተደረገ፣ ሄድንም!
ከዛ ጥበቆች ፊታችሁን እየከፈታችሁ ... አሉን። በጊዜው ብዙ በ ኒቃብ ኒያህ ማስክ ሚጠቀሙ፣ በ ግቢው ፍርሃት ኒቃብ ማይለብሱ እህቶች ነበሩ። ነገር ግን አንዲት ብቸኛና ጠንካራ ሙተነቂብ ጓደኛችን ነበረች፣ ቀላል ባይሆንም ከ ID ያችን ጋር እያስተያዩን እኛ እንደምንም ገባን፣ ቀድሚያት ስለነበር ኒቃቢስት ጓደኛችንን ወደ ሗላ ዞሬ ሳገኛት ከ ድንጋጤ የተነሳ ትንፋሿ ይቆራረጥ ነበር፣ ሁኔታዋ አሁንም ከ አዕምሮዬ አይጠፋም!
በጋለ ስሜት ለምን ሚለውን 'መልስ የሌለውን ጥያቄ' ጠየኩ፣ ለምን ?! እንዴት ሂጃብ መልበስ ሀበሻ ውስጥ ይከለከላል!? አልኩ... ግን መልስ የለም!!!
የዛች ቀን ለኔ ትልቅ ማንቂያ እና ለ ጽናትም ሰበቤ ነበረች!
ዓመቱ ID ሲቀማ፣ ሲመለስ፣ ሲፈረም እንደምንም አለቀ።
ጊዜ ጊዜን ተክቶ ወደ ግቢ መመለሻ ጊዜያችን ደርሶ እኛም ተመለስን፣ ግቢውም ያደርስ የነበረውን በደል አክርሮ እና አጠናክሮ ጠበቀን! መሳቀቅ ዚክርና ዱዓ እያረጉ ገብቶ መውጣት፣ መሰደብ፣ መደበቅ የዚህ ዓመት ዋና ስራችን ሆነ። ሲመታ እንደሚጠነክር ሚስማር እንደሚባለ የ ኒቃቢስቶች ቁጥር ከ 1 ወደ 2, 3 እየጨመረ መጣ! ቢሆንም ከ ስድብና እንግልታቸው የተነሳ ማስክ ለብሰን እንኳ ብቻችንን መንቀሳቀስ ለኛ ሰቀቀን ነበረ፣ ክላስ ካፌ፣ የግቢ በር ብቻችንን መግባት ልክ እንደ ምድር ጀሀነም ነበር ለኛ።
የተማሪዎች ካፌ ቲከሩ "ፊታችሁን ካልከፈታችሁ አትገቡም" ብሎ የምሩን ከመለሰን ቀን ቦሃላ ድርሽ ብለን አናቅም ..... ወሰንንንንንን!
ምናልባት ካፌ በመቅረት ውስጥ ከ ጥበቆቹ ፊትም ዞር እንል ይሆናል፣ በዚህ ሚቀንስልን ጭቅጭቅ እና መጋተት ካለ ብለን ድጋሜ ካፌ ላንመጣ ወስንን!
በ ታሪክ ከተነገረን ግቢያችን በ ቁጥር በዛ ያሉ ወደ 43 ሚጠጉ ኒቃብስቶችን ፊታችሁን ሸፈናችሁ ብሎ ጠቅልሎ ያባረረበት ጊዜ ነበር፣ የኛ ሁኔታም ኒቃብ ከሚለብሱት እኩል ወደዛ ሚያቀና ይመስል ነበር...በዚም መልኩ ጊዜያት ያልፉ ነበር••
እናም 1 ቀን ወደ መስጂድ እየሄድን ሳለን ወደ መውጫው በር እንደተቃረብን የየቀን ዱዓችን ውስጥ ሚኖረው የጥበቃው ኃላፊ አገኘን፣ ከብዙ ስድብ፣ አድካሚና አሰልቺ ንግግር ቦሃላ "ቆይ ግን አሁን አንቺ አዲስ እዚ ያመጣሽው ነገር ነው እንጂ ታች ሀገርሽ ስትማሪ እንዲ ትለብሺ ነበር?!" አለ ወደ ለበስኩት ማስክ እየጠቆመ ..
ጓደኛዬ እጄን ጥብቅ እያረገች ዝም በይው ትለኛለች፣ "አዎ እኔ እንዲው ለብሼ ነው የተማርኩት አዲስ ነገር አደለም!" አልኩት የ ጥላቻ ንዝነዛውን እንደቀጠለ "እሺ አሁን አንቺ ጁንታ ሁኚ ሸኔ ሁኚ ፋኖ ሁኚ በምንድነው ማቀው?!"
ሕያው ምስክር ~ 1
የ ፊታችን ጁምዐ ማታ ከ ምሽቱ 3 ሰዓት ይጠብቁን !
@aaumsu
ጥያቄዎቻችን የፍትሕ፤ የእኩልነት እና የዜግነት ጥያቄዎች ናቸው!
በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVrkmnYF/ በመግባት ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ።
@aaumsu
እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ፦
ሀገራችን ኢትዮጵያ ዜጎቿን ያለ ልዩነት በእኩልነት እያገለገለች ነው? ዜጎች ሀገራቸውን በእኩልነት ያገለገሉ ዘንድ እድሎች አሉን? የሀገር ተቋማት ላይ እኩል ውክልና አለን? የሀገር ሀብት በፍትሐዊነት ተከፋፍሏልን? የሀገር መገለጫዎች ሁሉንም ይገልፃሉን?!
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVMj5B8o/ በመግባት ሪፖስት ያድርጉ።
@aaumsu
ሕያው ምስክር - 1
የ11 አመታት ችግሮች የተፈቱበት የ11 ሌሊቶች ትግል በዲላ ዩኒቨርስቲ !
ከጥንት እስከ አሁን፤ ከትላንት እስከ ዛሬ፤ ከድሮ እስከ ዘንድሮ ከደቡብ እስከ ሰሜን፤ በምስራቁም ሆነ በምዕራቡ የኢትዮጵያ ክፍል በዳዮች ሰበብ እየፈጠሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሲያንገላቱ፤ መብቶቻቸውን እየጣሱ፤ ከትምህርት እያፈናቀሉ ዘልቀዋል። በዚህም ሕዝበ ሙስሊሙ በማህበራዊ መስተጋብር፤ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ፤ በፖለቲካዊ ተሳትፎ መድረስ ካለበት ሳይደርስ አሁንም ድረስ ስለመብቱ እየጠየቀ፤ እየታገለ፤ ስለ ዘላቂ መፍትሔ እየተጓዘ አለ።
ጨቋኝን ጨቋኝ የመውረሱን ያክል የነፃነት ታጋይንም ስለነፃነቱ የሚጠይቅ ትውልድ ወርሶ በደል ባለበት ቦታ ሁሉ ጥያቄ አለን እያልን፤ ስለመብታችን እየታገልን፤ መብታችንንም እያስከበርን አለን። የጥያቄ አለን ትውልድ የሚዘነጋው ትግል የለምና በእኛ ትውልድ በደቡቡ የሀገራችን ክፍል በዲላ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰን በደል፤ የተደረገን እልህ አስጨራሽ ትግል፤ ለአስራ አንድ ቀናት ከግቢ ውጪ ታድሮ የተፈፀመን ገድል በሕያው ምስክር - 1 የምንቃኝ ይሆናል።
እንግዳችን፦ ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ (በሰዓቱ የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት አሚር)
መድረክ መሪ፦ ዘይድ ሷዲቅ (የቀድሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ)
ቀን፦ ነሐሴ 15 / 2018 ዓ.ል
ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ
መድረኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል (@aaumsu) ላይ ነው።
@aaumsu
#ሚሽካት
የመጀመሪያ ታሪካችን ይሄን ይመስል ነበር። ቀጣይ በ አላህ ፍቃድ የተሻሉ እና የተለያዩ የታሪክ ገጾችን የሚዳስሱ ጠቃሚ እና አስተማሪ ታሪኮችን በማቅረብ የምንቀጥል ይሆናል።
በመሃል ደግሞ ልዩ ልዩ ሰርፕራይዞችም ስለሚኖሩን በንቃት ተከታትላችሁ እንድትጠቀሙ እንጠይቃለን ✨
🍂ከመጀመሪያው ታሪካችን የወሰዳችሁት ትምህርት፣ የተፈጠረባችሁ ጥያቄ እንዲሁም ተጨማሪ ያገኛችሁት ግንዛቤ ካለ ከታች ባለው 'comment section' ልታጋሩን ትችላላችሁ።
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኅብረት ከሩፋይዳ የሴቶች ፋውንዴሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ !
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን መብት ለማስጠበቅ፣ ማህበራዊ ግንዛቤን ለማሳደግ እና አቅማቸውን ለመገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኅብረት ከሩፋይዳ የሴቶች ፋውንዴሽን ጋር ተፈራርሟል። ይህ አጋርነት ተማሪዎች በግቢው ውስጥ የሀይማኖት ማንነታቸውና መብታቸው እንዲከበር፣ የስነ-ልቦና እና የጤና ድጋፍ እንዲያገኙ፣ እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ዝግጅቶችን በአንድነት ለማመቻቸት ያለመ ነው። በፊርማው ስነ-ስርዓት የኅብረቱ ፕሬዚዳንት ሙሐመድ ኢድሪስ አሊ፤ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ሀንጋቱ አብዱልዋሀብ እንዲሁም ሌሎች የህብረቱና የፋውንዴሽኑ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ወደፊት በሚሰሩ ዝርዝር ተግባራትም ውይይት ተደርጓል::
አላህ ለመልካም ለውጥ እና ለተሻለ ሁኔታ ሰበብ ያደርገው ዘንድ ዱዓችን ነው ! ! !
@aaumsu
ከታሪክ ገጾች📖…እስካለንበት ተጨባጭ ✍️
✨በማይፈራው ፣ጽኑው ሰዒድ እና በግፈኛው ገዢ ሐጃጅ መካከል የተደረገ የታሪክ ምልልስ✨
የመጨረሻው ክፍል
ሰኢድ ቢን ጁበይር (ረሕመቱላህ ዐለይህ) በርግጥም ከታላላቁ ኡለማዖች መሀከል አንዱ ነበር።
እንዲሁም ከአብደላህ ኢብኑ አባስ ውድ ባልደረቦች ሲሆን በጣም አዋቂ ፣አላህን ፈሪ ፣ኢባዳን የሚያበዛ ፣እንደውም በ2 ሌሊቶች ቁርአንን ያኸትም እንደነበርና እሱ ባለበት ሌላው አካል ፈትዋ እንዲሰጥ የማይፈለግበት ደረጃ ድረስ አላህ ከፍ ያደረገው ምርጥ ሰው ነበር።
ኢብኑ ዐባስን ሰዎች መጥተው ጥያቄ ሲጠይቁት እንኳ ፦ "በመካከላችሁ ሰኢድ ቢን ጁበይር የለምን?" በማለት ደረጃውን ከፍ አድርገው ይመለከቱት ነበር።
ሰዒድ ኢብኑ ጁበይርም ከዓመታት በኋላ፣በግፈኛው ሐጃጅ ኢብኑ ዩሱፍ ፊት እስረኛ ሆኖ ቀረበ።
ይህም ፍትሕ የጎደለውን አስተዳደር በመቃወም በተነሳው እንቅስቃሴ ውስጥ ስለተሳተፈ ነበር።
በሰዐቱ ሰኢድ ከዐብዱርረሕማን ቢን ሙሐመድ ቢን አል-አሽዐስ ጋር አብሮ ነበር። በሰራዊቱ አጠቃላይ ወጪ ዙሪያ ሀጃጅ ኃላፊ አድርጎ የሾማቸው የነበረ ቢሆንም አብዱራህማን እንዲሁም ሰኢድ የሃጃጅ አካሄድ ትክክለኛ እና ስርአት ያለው እንዳልሆነ በመረዳት ከሱ ተቃራኒ በሆነ መልኩ ተንቀሳቅሰው ነበር።
ስለዚህ ከጊዜያት በኋላ ሀጃጅ ከዐብዱራህማን ጋር በነበረው ጦርነት ላይ ድልን ሲቀዳጅ ሰኢድ ተፈላጊ ሆነ፤ በመጨረሻም ተይዞ ወደ ሐጃጅ ተላከ።
ያ ምንም ዓይነት የጦር ኃይል ወይም ስልጣን የሌለው ታላቅ ሊቅ በግፈኛው ገዥ ፊት ቆመ።
ሐጃጅ ያለፈውን እያስታወሰ፡
"በአደራዬ አላካፈልኩህም ነበርን? ሥራ አልሰጠሁህም ነበርን? እንዲህ እንዲህ አላደረኩልህምን?" በማለት ጠየቀው።
ሰኢድም በተረጋጋ መንፈስ፡
«አዎ» እያለ መለሰ።
ከዚህ በኋላ ሐጃጅ ሊደርስበት ወደሚፈልገው ዋናው ጥያቄ አለፈ፡
«ታዲያ በእኔ ላይ እንድትነሳና የአሚሩል ሙእሚኒንን ቃል ኪዳን እንድታፈርስ ምን አነሳሳህ?»
ሰኢድም፡ «ከኢብኑ አል-አሽዐስ ጋር ለመቀጠል የታማኝነት ቃል ኪዳንን ይዤ ነበረ» በማለት መለሰ።
ሐጃጅ በጽኑ ተቆጣ። ከዚህ ቀደም ለዐብዱልመሊክ ቢን መርዋን ሰጥቶት የነበረውን ታማኝነትና ቃል ኪዳን እያስታወሰ፣ እንዴት ከእሱ ጋር የነበረውን ሁለት ቃል ኪዳኖችን ትቶ የኢብኑ አል-አሽዐስን ብቻ እንደሚይዝ በመገረም ወቀሰው።
ውይይቱ ወደ ከረረ ደረጃ ሲሸጋገርም
ሐጃጅ በስሙ ላይ በመጫወት እንዲህ አለ፦
"አንተ 'ሸቂይ ኢብኑ ኩሰይር' ነህ!"
("ሰዒድ"ማለት ደስተኛ፣ ዕድለኛ ሲሆን "ሸቂይ" ደግሞ እድለ ቢስ ማለት ነው።
"ጁበይር" ማለት
የተሰበረን የሚጠግን፣ የተበላሸን የሚያስተካክል ሲሆን "ኩሰይር" ደግሞ ሰባሪ ማለት ነው።)
በዚህ የጭንቀት ሰዓትም ቢሆን ሰኢድ ከራሱ ላይ እርጋታው እንዲወገድ አልፈቀደም፣እንደዛው ረጋ ባለ መልኩ ቀጠለ ፣ጽናቱንም አልለቀቀም።
ሐጃጅ፡
«ወላሂ እገድልሃለሁ!» ብሎ በዛቻና በቁጣ ሲጮህበት…
ሰዒድም፡
“ያን ጊዜማ እናቴ የሰየመችኝ ስም እውነት ይሆናል፤ እኔም (ለእውነት ሞቼ) በእርግጥም ደስተኛ (ሰዒድ) እሆናለሁ!» በማለት የሞትን ጥላ እንደ ክብርና እንደ እውነተኛ ድል ተቀበለው።”
ሐጃጅ ሰኢድ እንዲገደል አዘዘ፤ አንገቱም ተቀላ (ረሕመቱላህ ዐለይህ)።
ግና ሰኢድ አካሉ ሄደ እንጂ ታሪኩና ስሙ አልሞተም። ከዚህ ግድያ በኋላ ሐጃጅ ረጅም ዕድሜ አልኖረም። በተኛበት ሕልሙ ሰኢድ እየመጣ የልብሱን ጫፍ በመያዝ፡ “አንተ የአላህ ጠላት፣ በምን ምክንያት ገደልከኝ?" እያለ ይጠይቀው ነበር።
ሐጃጅ በቅዠት እየተረበሸ፡
"የእኔና የሰኢድ ቢን ጁበይር ጉዳይ ምን አገናኘን! ምን አገናኘን!" በማለት ፀፀቱን ይገልፅ ነበር።
ከዚህ ክስተት በኋላም ሐጃጅ ከዚያ በፊት በሰዎች ላይ ያሳየውን ግፍ ማሳየት እንዳቆመ ይነገራል።
የዚህ ታሪክ ፍጻሜ እዚህ ላይ ቢያከትምም፣ ትምህርቱ ግን ገና ጀምሯል።
ሰኢድ ከሐጃጅ ፊት የቆመው ሞት የማይቀር ውሳኔ መሆኑን ተረድቶ፣ የሰው ልጅ እውነተኛ ዋጋ የሚለካው ፍርሃት ሲጫነውና ከመርሆቹ እንዲወርድ ሲጠየቅ በሚያሳየው አቋም መሆኑ ስለገባው ነው።
ለዚህም ነው የሰኢድ ቢን ጁበይር ስም ከዘመናት በኋላም ህያው የሆነው፤ የሐጃጅ ኃይልና ስልጣን ግን ጠፍቷል።
ዘመናት ሊለወጡ፣ የፈተና መልክና ቅርጽ ሊቀያየር ይችላል፤ ነገር ግን የጽናት ትርጉም ከቶውን አይለወጥም።
ዛሬም ቢሆን፣ ማንኛውም ሰው እምነቱን፣ መርሆቹን ወይም የሚያምንባቸውን እሴቶች ከባድ ፈተና፣ ግፊት ወይም ፍርሃት ውስጥ ወድቀው ሲያገኛቸው የሰኢድ ቢን ጁበይርን ታሪክ ሊያስታወስ ግድ ይላል።
መንገዱ ቀላል አልነበረም፤ ጽናትም ያለ ዋጋ አልመጣም፤ ነገር ግን አንዳንድ አቋሞቻችን ጋር አስፈላጊ ሲሆን መከራንም ጭምር ተቀብለን ለአላህ ብለን መቆም እና መፅናት እንደሚገባን ያስገነዝበናል።
ትምህርቱ ሰኢድ የኖረበትን ዓይነት ሁኔታዎች ማለፋችን ወይም በዘመናችን ያለውን ልዩነት ሁሉ ከእርሱ ታሪክ ጋር ማመሳሰላችን አይደለም።
ይልቁንም ከታሪኩ የምንወስደው ቁምነገር
ሰው በእምነቱ ላይ ሲፈተን እንዲጸና፣ በአላህ እንዲታገዝ፣ አላህም ትዕግሥቱን እንደሚመለከት እና ፈተናው ቢረዝምም ማብቂያ እንዳለው ማወቁ ነው።
ዛሬም ቢሆን፣ አንድ ሙስሊም በሃይማኖቱ መጽናት ከባድ በሆነበት ፈተና ውስጥ ሲያልፍ፣ የሰኢድ ቢን ጁበይር ታሪክና የጽናት መንገዱ ከቶውንም በምቾት የተነጠፈ እንዳልነበር ያስታውሰናል። ትዕግሥት ሁሌ መንገዱ ይቀላል ሳይሆን ፣ ሰውየው ለምን ዓላማ መከራን መቀበል እንደሚገባው ማወቁን ያሳያል።
እርግጥ ነው ሰኢድ ሞቷል፤ አቋሙ ግን እንደ ትምህርት ዘልቆ ኑሯል። ዘመናትን ቢሻገሩም የጽናት ትርጉሙ አልተለወጠም።
የአላህ እዝነት በሰኢድ ላይ ይስፈን፤ ታሪኩንም ከእርሱ በኋላ ለሚመጡት ሁሉ መማሪያ ያድርግለት።
በእውነት ላይ መጽናት በሰላምና በምቾት ሰዓት የሚወራ ባዶ ቃል ሳይሆን፣ ለጽናት እውነተኛ ዋጋ መከፈል በሚጀምርበት ሰዓት ላይ የሚገለጥ ጽኑ አቋም መሆኑን አስተምሮናል።
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
2) ኢትዮጵያስ ሁሉንም ዜጎቿን በእኩልነት እያገለገለች ነውን?
3) የኢትዮጵያ የሆኑ ነገሮች ሁሉ በእኩልና በፍትሃዊ መልኩ ሁሉም እየተወከሉበት፣እኩል ተጠቃሚ ሆነውበታል? ሁሉንስ ከግምት ያስገቡ ሆነው ተዋቅረዋልን?
የሙስሊሞች ጥያቄ ከመስጂድ ቅጥር ውጭ ይዘልቃል። ወደ ታሪክ አካታችነት ይሄዳል። ወደ ትምህርት ስርዓትና አተገባበር ያመራል። ወደ አካታች ኢኮኖሚም ይገባል። ወደ የቅርስና የባህል ጥበቃ ይሄዳል። ወደ ሀገራዊ ምልክቶችና መገለጫዎችም ይደርሳል።
ወደ ሴቶችና ህፃናት መብትም ይዘልቃል። የ ሰብዓዊ መብት ጉዳይም ነው። ወደ አሳታፊና አካታች የተቋማት ግንባታ ይሄዳል። ፍትሃዊ ውክልናንም ይመለከታል። ወደ ፍትሕ ስርዓቱ ይገባል። በዜግነት ጉዳዮች በኩል ይመዘዛል።
ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎች ከመስገድና ከመነገድ በላይ የዘለቁ ጥያቄዎች የፍትሕ፣ የእኩልነት፣ የውክልና እና የሙሉ ዜግነት ጉዳዮች ናቸው!
ይህ የሙስሊሞች ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የኢትዮጵያ የሀገር ግንባታ ጥያቄዎች ናቸው። የአካታችነትና በሁሉም እርከን በፍትሃዊነት የመወከል ጥያቄ ነው። የሀገር ባለቤትነት ጥያቄ ነው።
ይድረስ ለኮሚሽነሮቹ!
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በሀገራዊ የምክክር ሂደት ውስጥ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ጥያቄዎች በስምንቱ አጀንዳዎች ዉስጥ የተዘረዘሩትን ሰብስቦ በአንድ “የሃይማኖት ጉዳይ” ሳጥን ውስጥ መክተት የመፍትሔ መንገድ ሳይሆን የመዋቅራዊ ችግሩን ሥር የሚያስቀጥል አካሄድ ነው።
እውነተኛ ሀገራዊ መግባባት የሚገኘው የዜጎችን መብት በአስተዳደራዊ ማጣሪያዎች ወይም በሃይማኖታዊ ሳጥኖች ውስጥ በመክተት ሳይሆን፣ እውነተኛ አካታችነት ማለት የሙስሊሞችንም ሆነ የየትኛውም ወገንን በየተነሱበት አጀንዳዎች ስር ከነአውዳቸው ሳይሸፋፈኑና በጥቅል ገለጻ ስር ሳይደበቁ በዚያው በተጠቀሱበት አኳኋን ምክረ ሀሳቦቹ በየተገቢው አጀንዳ ውስጥ ማስቀመጥና መፍትሄ እንዲያገኝ ማድረግ ሲቻል ብቻ ነው።
እውነተኛ ፍትሕ ማለት በየተቋሙ ያለውን መዋቅራዊ እንቅፋት መለየትና ማስወገድ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ ማለት ሁሉም ዜጎች በሀገራቸው ውስጥ እኩል ባለቤትነት እንዲሰማቸው ማድረግ ነው።
Repost from AAU - Muslim Students Union
በእውነት የሚገርመው ምንድን ነው? አንዲት ሙስሊም ተማሪ በሂጃቧ ምክንያት ብትገለል፣ ይህ የሴቶች መብት ጉዳይ ነው ወይስ የመጅሊስ ጉዳይ? የሙስሊሞች ታሪካዊ ቅርሶች በብሔራዊ ትረካ ውስጥ ቢጠፋ፣ ይህ የባህልና ቅርስ ጉዳይ ነው ወይስ የሃይማኖት ጉዳይ? ከወለድ ነፃ ፋይናንስ በበቂ ሁኔታ አለመዳረሱ የአሳታፊ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ጉዳይ ነው ወይስ የሃይማኖት ጉዳይ?
አንድ ሙስሊም ዜጋ በመንግሥት ተቋማት ውስጥ እኩል ዕድል እንዲኖረው ሲጠይቅ ይህ የዜግነት ጥያቄ ነው ወይስ የሃይማኖት?
በፌደራልም ሆነ በክልል በቢሮክራሲ፣ በዳኝነት፣በሕዝብ ተወካዮች ተቋማት ወይም በውሳኔ ሰጪ መድረኮች የሚነሱ የውክልና ጥያቄዎች የሃይማኖት ጉዳይ ናቸውን?
እነዚህ ጥያቄዎች መልሳቸው ግልጽ ነው። ችግሩ የሃይማኖት ተቋማት ችግር አይደለም። ችግሩ የሀገራዊ ተቋማት አካታችነት ችግር ነው።
"ጥያቄ ስታነሱ ሴኩላሪዝም ትዝ አለኝ"
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በሀገራችን የታዘብኩት አንድ የቆየ አሳሳቢ አዝማሚያ አለ። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በታሪክ፣ በፍትሕ፣ በውክልና፣ በትምህርት፣ በኢኮኖሚ፣ በሰብዓዊ መብቶች፣ በተቋማት አካታችነት ወይም በሕገ-መንግሥታዊ መብቶች ዙሪያ ማንኛውንም ጥያቄ ሲያነሱ፣ ወዲያውኑ “ሴኩላሪዝም” ትዝ የሚላቸው መገኖች አሉ።
በሁሉም መስክና ስፍራ እኩልነት በተግባር ጥያቄ ሲነሳ እነዚህ ወገኖች ሴኩላሪዝምን (የመንግስት ነፃ በመሆን ዓለማዊነትን) ጉዳይ በማንሳት ውይይቱን ወደ “ሃይማኖት ጉዳይ” ብቻ ለመግፋት የሚሞክሩ አካላትን ደጋግመን ታዝበናል።
እነዚህ አካላት ጉዳዩን በዜግነት፣ በሰብዓዊ መብት፣ በሕገ-መንግሥታዊ እኩልነት፣ በተቋማዊ ፍትሕ ወይም በሀገር ግንባታ ማዕቀፍ ከማየት ይልቅ ወደ ሃይማኖታዊ ማዕቀፍ ብቻ ለማሳነስ ይሞክራሉ።
በዚህ ሂደት የሙስሊሞች ጥያቄ ዜጎች የሚያነሱት ሀገራዊ ጥያቄ ሳይሆን የአንድ ሃይማኖት ውስጣዊ ጉዳይ እንደሆነ ለማቅረብ ይሞክራሉ።
ይህ ግን ለሴኩላሪዝም ጥብቅና መቆም አይደለም፤ የዜግነት ጥያቄን ባህሪ መቀየርና በሴኩላሪዝም ስም ማፈን ነው።
ሴኩላሪዝም ማለት መንግሥት ሃይማኖት ሳይኖረው በገለልተኛነት የሁሉምና ለሁሉም የሚመች፣ ሁሉም ዜጎች በእኩልነት በሀገራቸው ጉዳዮች እንዲሳተፉ የሚያስችል የገለልተኝነት መርህ እንጂ ማንኛውንም ማህበረሰብ ከሀገራዊ ጉዳዮች ማግለል ወይም ጥያቄዎቹን ወደ ሃይማኖት ሳጥን ውስጥ መክተት አይደለም።
የሙስሊሞችን ማንኛውንም ጥያቄዎች ወደ “ሃይማኖት” ማውረድ የእኩል ዜግነትን ክርክር ከመሰረቱ ማዛባት ነው።
የሀገራዊ የምክክሩ ትምህርት
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
በቅርቡ በተካሄዱ ሀገራዊ ውይይቶች አንድ አሳሳቢ አዝማሚያ ታይቷል። ከሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚነሱ የታሪክ፣ የፍትሕ፣ የውክልና፣ የኢኮኖሚ፣ የሴቶች መብት፣ የትምህርት፣ የባህል፣ የመሬት አጠቃቀም፣ የፋይናንስ፣ የሲቪክ ተሳትፎ እና የተቋማት አካታችነት ጥያቄዎችን በሙሉ “የሃይማኖት ጉዳይ” በሚል ርዕስ ስር ለማጠቃለል የተደረገ ጥረት ታይቷል።
ይህ ከቀላል የአጀንዳ አመዳደብ ስህተት በላይ ነው። ይህ የታሪካዊ ማግለል ዘመናዊ ቅጂ ነው።
ጥያቄዎችን “ባለቤት አልባ” ማድረግ
ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የተደራጁ በርካታ ሚኒስቴሮችና ተቋማት አሏት። የንግድ ጉዳይ የንግድ ተቋማትን ይመለከታል። የባህልና ቱሪዝም ጉዳይ ተቋማቱን ይመለከታል። የትምህርት ጉዳይ የትምህርት ተቋምን ይመለከታል።
የሙስሊም ሴቶች መብት ጉዳይ የሴቶች ጉዳይ ሚኒስትርን ይመለከታል። አይመለከተኝም ካለ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስያሜውን "የሙስሊም ያልሆኑ ሴቶች ጉዳይ ሚኒስቴር" ብሎ ይቀይር።የሙስሊም ሴቶች ጉዳይ የመጅሊስ ጉዳይ ብቻ የሚሆንበት ሁኔታ ማብቃት አለበት።
የአካታች ፋይናንስ ጉዳይ የፋይናንስ ተቋማትን ይመለከታል። የተቋማት አካታችነት ጉዳይ የመንግሥት ተቋማትን ይመለከታል።
እነዚህን ሁሉ በ“ሃይማኖት” ስም ወደ አንድ ተቋም መግፋት ማለት ጥያቄውን ከሚመለከተው ዋና ተቋም የማራቅ ስልት ነው።
በዚህ ሁኔታ ተጠያቂ የሆኑ ተቋማት ከኃላፊነታቸው ይሸሻሉ።በተጨማሪም ጥያቄው መፍትሔ የሚያገኝበትን መንገድ ያጣል።
ምክንያቱም የሃይማኖት ጉዳይ ተቋም በካቢኔ ውክልና፣ በመከላከያ ፖሊሲ፣ በትምህርት ሥርዓት፣ በመሬት አጠቃቀም ወይም በብሔራዊ ታሪክ አጻጻፍ ላይ ውሳኔ የመስጠት ሕጋዊ ሥልጣን የለውም።
ስለዚህ ጥያቄው ከአንድ ቢሮ ወደ ሌላ ሲዘዋወር ይቆያል፤ መፍትሔ ግን አያገኝም።
የታሪክ ጥያቄ የኢትዮጵያ ታሪክ ሲጻፍ ሙስሊሞች በምን ያህል ተካተዋል? የሀገሪቱ የንግድ ታሪክ፣ የስልጣኔ ታሪክ፣ የሙስሊም ሊቃውንት ታሪክ፣ የሙስሊም መሪዎች አስተዋጽኦ፣ የሙስሊም ማህበረሰቦች የሀገር ግንባታ ሚና በብሔራዊ ትረካ ውስጥ ምን ያህል ቦታ አግኝተዋል?
ይህ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። ይህ የታሪክ ፍትሕ ጥያቄ ነው።
"ሙስሊሞች እኩል ዜጎች ከሆኑ"
✅✅✅✅✅✅✅✅✅
1) በሀገራዊ ታሪክ ውስጥ እኩል ተወክለዋልን?
2) በባህልና ቱሪዝም ተቋማት ሥራዎች ውስጥ እኩል ተካተዋልን?
3) በትምህርት መጻህፍት ትረካዎች ውስጥ እኩል ተገልጸዋልን?
4) በፖሊሲ ውሳኔዎች ውስጥ እኩል የመወሰን ድምፅ አላቸውን?
5) በተቋማት ውስጥ እኩል ውክልና አላቸውን?
6) በውሳኔ ሰጪ መድረኮች ውስጥ እኩል ተሳትፎ አላቸውን?
7) በሀገራዊ ምልክቶችና መገለጫዎች ውስጥ እኩል ታይተዋልን?
8) በብሔራዊ ትረካዎች ውስጥ እኩል ቦታ አግኝተዋልን?... በርካታ ጥያቄዎችን ጨምሩበት።
እነዚህን ጥያቄዎች ማንሳት ልዩ ጥቅም መጠየቅ አይደለም። እነዚህን ጥያቄዎች ማንሳት የእኩል ዜግነት ጥያቄ ነው።
የሙስሊሞች ጉዳይ የሃይማኖት ጉዳይ ነውን?
⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕
የጥያቄውን ትክክለኛ ባህሪ መለየት አስፈላጊ ነው። አንድ ሙስሊም ዜጋ ሀገሩን በወታደራዊ ተቋማት ለማገልገል ሲፈልግ ከእምነቱ ወይም ከሙስሊምነቱ አንዳንድ መገለጫዎች እንዲተው ከተጠየቀ፣ ይህ የሃይማኖት ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የተቋማት አካታችነት፣ የእኩል ዕድል እና የዜግነት ጥያቄ ነው።
አንዲት ሙስሊም ሴት በአለባበሷ ወይም በሃይማኖታዊ ማንነቷ ምክንያት በሥራ ቦታ ዕድል ከተነፈገች፣ ይህ የሠራተኛ መብት፣ የእኩልነት እና የሕገ-መንግሥታዊ መብት ጉዳይ ነው።
አንድ ሙስሊም ተማሪ በሙስሊምነቱ ወይም በሃይማኖታዊ መገለጫው ምክንያት ከትምህርት ቤት ከተገለለ፣ ይህ የመጅሊስ ጉዳይ ሳይሆን የትምህርት መብት፣ የዜግነት እና የሕግ የበላይነት ጉዳይ ነው።
መስጂዶች ሲቃጠሉ፣ሲፈርሱ ወይም ኢማሞች ሲገደሉ፣ ይህ የሀገሪቱ የሰላምና የደህንነት አጀንዳ እንጂ የሙስሊሞች ጉዳይ አይደለም።
የሕግ ማስከበር እና የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ ያለባቸው ተቋማትን የሚመለከት ጉዳይ ነው።
በአጠቃላይ ጥያቄውን የሚወስነው ጉዳዩን ያነሳው ሰው ሙስሊም መሆኑ ሳይሆን የተጣሰው መብት፣ የተፈጠረው ችግር እና መፍትሔ የሚሰጠው ተቋም ነው። ስለዚህ ሙስሊሞች የሚያነሱትን እያንዳንዱን ጥያቄ “የሃይማኖት ጉዳይ” ብሎ መፈረጅ የጥያቄውን እውነተኛ ባህሪ መሸፈን እና ከተጠያቂ ተቋማት ማራቅ ነው።
ኢትዮጵያ እኩል የሁላችንም ነች? ከቃል ባሻገር በተግባር እንዴት ይገለጻል?
🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒
“እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?” የሚለው ጥያቄ በመሠረቱ የተሳሳተ ጥያቄ ነው።
መቅረብ ያለባቸው ጥያቄዎች የሚከተሉት ናቸው።
1) ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውንና ወገናቸውን የማገልገል እኩል እድል አግኝተዋልን?
Repost from AAU - Muslim Students Union
"እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?"
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
የዜግነት ጥያቄዎችን በ“ሃይማኖት ጉዳዮች” ሳጥን ውስጥ የማፈን መዋቅራዊ አደጋ እና የተቋማዊ ማግለል አሰራር አደጋ።
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶
በአሕመዲን ጀበል
🔴🔴🔴🔴🔴🔴
“እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?” የሚለው አባባል አዲስ አይደለም። በዘመናት የተወረሰ፣ በትውልዶች የተደጋገመ፣ ዛሬም በይፋ ባይነገርም በተለያዩ መንገዶች የሚገለጽ የሚታይ አመለካከት ነው።
በቀድሞ ዘመን በቀጥታ ይነገር ነበር፤ ዛሬ ግን በተቋማት አሰራር፣ በፖሊሲ አቀራረብ፣ በሚዲያ ትረካዎች፣ በሀገራዊ ውይይቶች እና በውሳኔ ሰጪ መድረኮች ውስጥ በዘመናዊ መልክ ተሸፍኖ መቀጠሉን እናያለን። ይህ አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ጥያቄዎች ወደ መንፈሳዊና ኢኮኖሚያዊ ብቻ የማድረግ ስልታዊ ማግለል መገለጫ ነው።
በምክክሩ ሙስሊሞች የገጠማቸው ተግዳሮቶች
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶
እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ ምክክር ሙስሊም ተሳታፊዎችን ከገጠሟቸው ተግዳሮቶች አንዱና ዋነኛው በርካቶች ዘንድ "ሙስሊም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?" የሚለው እይታ መኖሩን መታዘቡና ከዚሁ እይታ የተነሳ ሙስሊሞች ከሃይማኖት ጉዳዮች አጀንዳ ውጭ ባሉ ጉዳዮች የሚያነሷቸው ጥያቄዎችና ምክረ ሀሳቦች በሚያዙ ቃለጉባኤዎች ዉስጥ እንዳይካተቱ የሚታገሉ አካላትን በግልጽ መጋፈጣቸው ነው።
የሚገርመው አብዛኞቹ መሰል አካላት የራሳቸው አንዳች አጀንዳዎች፣ጥያቄዎች የሌላቸውና የነርሱ አጀንዳ የሙስሊሞች አጀንዳ እንዳይካተት ማድረግ እስኪመስል ራሳቸውን አጋልጠዋል።
በዚህ ስንኩል አመለካከት ባለቤቶች መካከል በሀላፊነት ላይ ያሉትም ጭምር ሆነው መገኘታቸው አሳዛኙ ሁኔታ ነው።
ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በሀገር ግንባታ፣ በሀገር ባለቤትነት ጉዳዮች፣በታሪክ ፣የጋራ ሀገራዊ ማንነት እና እሴቶች፣ብዝኃነት እና አስተዳደር ጉዳዮች፣ የባህል፣ ታሪክ እና ቅርስ ጥበቃ ጉዳዮች ጥያቄዎች አሏቸው።
በመንግሥት ምሥረታ፣ በተቋም ግንባታ፣ሰላም ግንባታ፣ግጭት መንስኤዎች እና አፈታት መንገዶች፣ ማህበራዊ ኢኮኖሚ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶአደሮች ጉዳዮች፣ህገ መንግስታዊ እና ህጋዊ ማዕቀፍ በሰብአዊ መብቶች ጥበቃ፣የመልካም አስተዳደር ችግር እና የሙስና ጉዳዮች ምክረሀሳብ አሏቸው።
ሙስሊሞች በ8ቱም አጀንዳዎች የሚያነሷቸው ጥያቄዎችና ምክረ ሀሳቦች ከየአጀንዳዎቹ ስር ተሰርዘው ወደ ሃይማኖት አጀንዳ ብቻ ይሂዱ የሚለው እይታ የተሳታፊዎች ብቻ አልነበረም። ኮሚሽኑ በመደባቸው ጥቂት አወያዮች፣ አስተባባሪዎችና ጥቂት ኮሚሽነሮች ዘንድም ተንጸባርቋል።
ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በየአጀንዳዎቹ ሥር ያነሷቸውን ምክረ ሀሳቦች ለቃቅሞ ወደ የሃይማኖት አጀንዳ ሥር ለመውሰድ መሞከር ማለት ተራ የአሰራር ጉዳይ አይደለም።እንድምታው አደገኛ ነው።
"ከሀገራዊ አጀንዳዎች ለማራቅ ወደ ሃይማኖት ጉዳዮች ግፏቸው!"
✅✅✅✅✅✅💢💢💢💢💢💢💢
አንድም የናንተን ሀሳብ ከሃይማኖት አንፃር ብቻ ነው የምናየው እያሉ ነው።አልያም ከሃይማኖት ጉዳይ በቀር ስለሌላው አይመለከታችሁም ፣ወይም ከሃይማኖት አጀንዳ እንድትወጡ አንፈቅድላችሁም ነው። ይህ በራሱ ሌላ ሀገራዊ ምክክር የሚፈልግ ሸውራራ እይታ ነው።
በመጀመሪያ እይታ ይህ አባባል ቀላል ጥያቄ ሊመስል ይችላል። ግን በውስጡ ጥልቅ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና መዋቅራዊ እሳቤ ይዞ ይመጣል።
ለምን? ምክንያቱም ይህ አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከሀገሪቱ አጠቃላይ ጉዳዮች እየገፋ ወደ “ሃይማኖት” ብቻ ለመወሰን ይሞክራል። በፍትሕ ላይ ጥያቄ ቢያነሱ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ። በታሪክ ላይ ቢናገሩ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ። በኢኮኖሚ ላይ ቢጠይቁ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ። በተቋማት ውክልና ላይ ቢወያዩ ወደ ሃይማኖት ይገፋሉ።
የጥያቄው ርዕስ ቢቀየርም የሚቀርበው መልስ አንድ ነው፤ “ይህ የሃይማኖት ጉዳይ ነው” የሚለው።ነገር ግን ይህ የችግሩ መፍትሔ አይደለም፤ የችግሩ መሸፈኛ ነው።
ሁለቱ አደገኛ እሳቤዎች
❌❌❌❌❌❌❌
“እስላም ከሰገደና ከነገደ ሌላ ምን ይፈልጋል?” የሚለው አባባል ሁለት አደገኛ እሳቤዎችን ይሸከማል።
ሀ) ሙስሊሞችን ማሳነስ
🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶
ይህ አባባል ሙስሊሞችን ከሀገር ግንባታ፣ ከእውቀት ምርት፣ ከሳይንስ፣ ከፖለቲካ፣ ከባህል፣ ከተቋማት ግንባታ፣ ከውሳኔ ሰጪነት እና ከሀገራዊ አጀንዳዎች ውጭ ያሉ ሰዎች እንደሆኑ ያቀርባቸዋል።
ሙስሊሙ እንደ መምህር አይታይም። እንደ ሳይንቲስት አይታይም። እንደ ዳኛ አይታይም። እንደ ፖሊሲ አውጪ አይታይም። እንደ ታሪክ ባለቤት አይታይም። እንደ ሙሉ ዜጋም አይታይም። እንደ ሃይማኖታዊ ማህበረሰብ ብቻ እንዲታይ ይደረጋል።
ለ) ሙስሊሞችን በሁለት መስኮች ብቻ መገደብ
🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺
ሁለተኛው አደገኛ እሳቤ ሙስሊሞችን በሁለት መስኮች ብቻ በመስገድና በመነገድ ለመገደብ ያለ ፍላጎት ነው።
ይህ አመለካከት ሙስሊሞች በመስጂድ ውስጥ እንዲቆዩ ወይም በንግድ እንዲሰማሩ ሊፈቅድ ይችላል። ነገር ግን በታሪክ አጻጻፍ፣ በሀገራዊ ትረካ፣ በትምህርት ፖሊሲ፣ በተቋማት ግንባታ፣ በመከላከያ፣ በዳኝነት፣በሲቪል ሰርቪስ፣ በሚዲያ ፣ በባህል ተቋማት፣ በውሳኔ ሰጪ መድረኮች፣ በሀገራዊ ምልክቶች እና በሀገር ባለቤትነት ስሜት ውስጥ እኩል ተሳታፊ እንዳይሆኑ በተዘዋዋሪ መንገድ ይገፋፋል።
የዜግነት ጥያቄን ወደ ሃይማኖት ነጻነት ማውረድ
⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕
የችግሩ መሠረት አንድ ነው፤ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሚያነሱትን ማንኛውንም ጥያቄ እንደ “ሃይማኖታዊ ጥያቄ” ብቻ መመልከት።
ነገር ግን እውነተኛው ጥያቄ ይህ ነው፦
ሙስሊሞች በዚህች ሀገር ላይ የሚያነሱት ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ ብቻ ነውን? መልሱ ግልጽ ነው። አይደለም።
ሙስሊሞች የሚያነሱት ጥያቄ የዜግነት ጥያቄ ነው። ስለ ፍትሕ ሲናገሩ፣ ስለ ተቋማዊ ውክልና ሲጠይቁ፣ ስለ ታሪክ አጻጻፍ ሲከራከሩ፣ ስለ ባህል ቅርስ ሲጠይቁ፣ ስለ ኢኮኖሚ ተሳትፎ ሲወያዩ፣ ስለ ኢስላማዊ ፋይናንስ ሲነሱ፣ ስለ እኩል ትምህርት ዕድል ሲናገሩ፣ ስለ አሳታፊ የሥራ ዕድል ሲጠይቁ፣ ስለ ሴቶች መብት ሲያነሱ፣ ስለ ሰብዓዊ መብቶች ሲወያዩ፣ ስለ መሬት አጠቃቀም ሲከራከሩ፣ ስለ ተቋማት አካታችነት ሲጠይቁ፣ ስለ ውሳኔ ሰጪነት ሲወያዩ፣ የሚያነሱት ጥያቄ የዜግነት ጥያቄ ነው።
ይህ የመስጂድ ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የሂጃብ ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የመጅሊስ ጥያቄ ብቻ አይደለም። ይህ የእኩል ዜግነት ጥያቄ ነው።
የጥያቄውን ባህሪ የመቀየር አደገኛነት
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥
አንድ ማህበረሰብ የሚያነሳውን የመብት ጥያቄ “ሃይማኖታዊ” ብቻ ብሎ መፈረጅ በእውነቱ የጥያቄውን ባህሪ መቀየር ነው።
የፍትሕ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የኢኮኖሚ ተሳትፎ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የባህልና ቅርስ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የታሪክ ውክልና ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የመንግሥት ተቋማት አካታችነት ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ ሊሆን አይችልም።
የሙስሊም ይሁን የክርስቲያን የሴቶች መብት ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የትምህርት ፖሊሲ ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። የውክልና ጥያቄ የሃይማኖት ጥያቄ እንዴት ሊሆን ይችላል?
እነዚህ ሁሉ የዜግነት፣ የፍትሕ፣ የእኩልነት እና የሀገር ግንባታ ጥያቄዎች ናቸው።
