es
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Ir al canal en Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Mostrar más
1 160
Suscriptores
-124 horas
+17 días
+530 días
Archivo de publicaciones
الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات ፕሮግራማችን ባማረ ሁኔታ ተጠናቋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲን ታሪካዊ የመብት ትግል ላጋሩን፤ እንደ ታላቅ ወንድም፤ እንደ አሚር እና እንደ ኡስታዝ ሆነው ምክራቸውን ላካፈሉን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የቀድሞ አሚር ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ ከልብ እናመሰግናለን። እንዲሁምፕሮግራሙ እንዲሳካ ለተነቀሳቀሱ እህት እና ወንድሞች ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ ማለት እንወዳለን! መጀመሪያ አካባቢ ስለነበረው የኔትዎርክ መቆራረጥ ይቅርታ እየጠየቅን፤ በቀጥታ መከታተል ላልቻላችሁ ሪከርድ የሚለቀቅ ይሆናል። ህያው ምስክር ፕሮግራማችን በቀጣይም ከሌላ እንግዳና ሌላ አስተማሪ የትግል ታሪክ ጋር በቅርቡ የሚመለስ ይሆናል። ©aaumsu @fivekjemaa

https://t.me/aaumsu?livestream=734f01b6cb97f0269e ፕሮግራማችን ሊጀምር ስለሆነ ተቀላቀሉ።

15 ደቂቃ ብቻ ይቀረዋል!!! @aaumsu

Less than 2 hours left for our program, are we ready all?

ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል! ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ! ዛሬ ከምሽቱ 3
ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል! ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ! ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ ! @aaumsu

🎉ደርሷሷልል ❕ 🔥 ሕያው ምስክር ~ 1 ~ 🔥 ዘመናትን ሲሸጋገር የቆየው የ ጭቆና ብትር በ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ!! እነሆ ታሪካዊው መድረካችን 1 ብሎ ለ ዛሬ ቀጠሮውን ይዟል! እውነታዎችን በማስተንተን ማንነትን በ አግባቡ መገንባት ላይ ያተኮረው "የሕያው ምስክር" መድረክ በ ታሪክ ገጽ ደምቆ የሰፈረወን የ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል ሊያስቃኛቹ ዝግጅቱን አጠናቋል !! 🗯የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የነፃነት ጉዞ ምን ይመስል ነበር !? 🗯አምስቱ ዋና ጥያቄዎቻቸው ምን ምን ነበሩ ?! 🗯እጅግ ፈታኝና ተስፋ አስቆራጭ የነበረው ትግል በምን መልኩ መፍትሄ ሊያገኝ ቻለ ?! በ ሙስሊምነታቸው ሲደርስባቸው የነበረውን መራራ በደል "ከሙተነቂቦች መንደር" በ ጥቂቱ ልናስቃኛችሁ ሞክረናል፣ በ ዛሬው ምሽት በ 2017 ስለ ተደረገው የተቀናጀ እና ብዙዎችን ስላስደመመው፣ ጠይቆ ታግሎ ማንነትን እና መብትን በማስከበር ረገድ ትልቅ ተምሳሌት ሆኖ ስላለፈው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል በ ጥልቅ እንዳስሳለን። ✨ከ ሃይስኮል እስከ ኮሌጅ ✨ከ ዩኒቨርሲቲ እስከ ሥራው ዓለም ድረስ ስለ ችግሮቻችን ያሰሰበው ሁሉ፣ ለተጨነቀ እና ለመፍትሄው ለተብሰለሰል ሁሉ ለመንገዳችን ትልቅ ስንቅ ምንሰንቅበት ልዪ መድረክ ነው! 🗓ዛሬ(ጁምዐ) ማታ 3:00 በቀጠሯችን እንገናኝ! @aaumsu

ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል! ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ! ዛሬ ከምሽቱ 3
ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል! ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ! ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ ! @aaumsu

🎉ደርሷሷልል ❕ 🔥 ሕያው ምስክር ~ 1 ~ 🔥 ዘመናትን ሲሸጋገር የቆየው የ ጭቆና ብትር በ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ!! እነሆ ታሪካዊው መድረካችን 1 ብሎ ለ ዛሬ ቀጠሮውን ይዟል! እውነታዎችን በማስተንተን ማንነትን በ አግባቡ መገንባት ላይ ያተኮረው "የሕያው ምስክር" መድረክ በ ታሪክ ገጽ ደምቆ የሰፈረወን የ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል ሊያስቃኛቹ ዝግጅቱን አጠናቋል !! 🗯የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የነፃነት ጉዞ ምን ይመስል ነበር !? 🗯አምስቱ ዋና ጥያቄዎቻቸው ምን ምን ነበሩ ?! 🗯እጅግ ፈታኝና ተስፋ አስቆራጭ የነበረው ትግል በምን መልኩ መፍትሄ ሊያገኝ ቻለ ?! በ ሙስሊምነታቸው ሲደርስባቸው የነበረውን መራራ በደል "ከሙተነቂቦች መንደር" በ ጥቂቱ ልናስቃኛችሁ ሞክረናል፣ በ ዛሬው ምሽት በ 2017 ስለ ተደረገው የተቀናጀ እና ብዙዎችን ስላስደመመው፣ ጠይቆ ታግሎ ማንነትን እና መብትን በማስከበር ረገድ ትልቅ ተምሳሌት ሆኖ ስላለፈው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል በ ጥልቅ እንዳስሳለን። ✨ከ ሃይስኮል እስከ ኮሌጅ ✨ከ ዩኒቨርሲቲ እስከ ሥራው ዓለም ድረስ ስለ ችግሮቻችን ያሰሰበው ሁሉ፣ ለተጨነቀ እና ለመፍትሄው ለተብሰለሰል ሁሉ ለመንገዳችን ትልቅ ስንቅ ምንሰንቅበት ልዪ መድረክ ነው! 🗓ዛሬ(ጁምዐ) ማታ 3:00 በቀጠሯችን እንገናኝ! @aaumsu

🗯ድምጽ አልባው እምባ! 🔥ከዛው ከዲላ ከሙተነቂቦች መንደር..ነፃነት'ን በልመና 'በመንገዱ' ላይ ላላችሁ ሁሉ ያጠነክራችሁ ዘንድ ዛሬ የ አንዷን እህቴ ታሪክ ፈተና ላጋራችሁ ወደድኩ... ትላለች•• ከመስጂድ መልስ ቁርስ ሰአት ሲደርስ ሁሌም በምንገባበት የጀርባ በር ሄድኩ። እንደሁሌውም ተረኛ ጠባቂው ማን ይሆን ..¿ እያልኩ ። ኡፍ ያቺ ሴት ከሆነች በቃ አታስገባኝም !! ሳልወድ በግዴ ጠዋት ወደ መስጂድ ስወጣ << ሰላም አደራቹ ለ2 ወር ብቻ >> ብዬ የምለማመጣቸው ነገር ትዝ አለኝ። ክላስ ልንጨርስ 2 ወር ነበር የቀረን። እስከዛው ድረስ ነጻነት'ን በልመና !¡ እንደፈራሁት አትገቢም አለኝ። <<እንዲ ለብሶ መግባት አይቻልም !! ከላይ የተሰጠን ትእዛዝ ነው። ከዚ ቡሃላ በዚ በር እንዳትመጪ>>አለኝ። በፊት በር ሄድኩ። የዋናው በር ጋር ስደርስ የተወሰኑ ሰዎች ሰብሰብ ብለው ስለነበር ልብ አላሉኝም። አልሃምዱሊላህ id አሳይቼ ብቻ ገባሁ። በሰላም በመግባቴ ደስ እንዳለኝ ክላስ እንዳላረፍድ እየተሯሯጥኩ ወደ ካፌ ሄድኩ። ያለ ወትሮ ከካፌ ውጪ በሩ ላይ ዳቦ እየሰጡ ነበርና ተጠግቼ ሚልካርዴን ሰጠሁት። <<ይሄን ለብሳችሁ አትምጡ አልተባላቹም!! አይሰሙምኮ>> እያለ አምባረቀብኝ። እንዴት ክው እንዳልኩ: ጸጥ አልኩት። መልስ ከምመላለስ ብዬ ትቼው መንገድ ስጀምር <<ነይ!! ነይ!! >>አለኝ ። ስመለስ አይዲሽን አምጪ ሲለኝ ሁሌም እንደምለው ID አልያዝኩም ብዬ ሚል ካርዴን ሰጠሁት። "ያለ id መስጂድ መሄድ አይታሰብም" እያልኩ በ ውስጤ። "አይዲሽን ስታመጪ ሚልካርዱ ይመለሳል!" አለኝ።  ከእህቶች ጋር ባወራም መፍትሄ አላገኘሁም። ካፌ ሳልደርስ ሳምንታት አለፉ ምግብ መግዣ ብርም አለቀብኝ። ከበፊትም ቤተሰቦቼን ብር መጠየቅ አልወድም ነበር። አሁን ግን ግድ ሆነብኝ።ሳገኝ እየበላው ብዙውን ጊዜ በ ባዶ እያሳለፍኩ ቀስ በ ቀስ እየደከምኩ በመጨረሻ ታምሜ ሆስፒታል የሄድኩበትን ጊዜ አልረሳም። እጄ ላይ ካኑላ እንደተደረገ ወደ ካፌ ስሄድ ያለ ሚልካርድ አናስገባም ብለው አባረሩኝ፣ ውጪ ያገኘውት ጥላ ስር ቁጭ ብዬ ሳለቅስ <<እዚህ ጋር እንዲ ለብሶ መቀመጥ አይቻልም !!ልጆች ይደነግጣሉ !!>> ያሉኝን ቀን መቼም አረሳውም ። ታድያ ምን ይሻላል?!? ከዶርምሜቴ ጋር እያውጠነጠንን 1 አስደናቂ ሃሳብ ጓደኛዬ ፈለቀላት። የሚገርመው እስልምናን ምታከብር ክርስቲያን ነበረች። ያኔ የሚሰጠን ሚል ካርድ ወረቀት ነበርና ቲክ ተደርጎ ሲያልቅ ሌላ ይተካል። የሷ ወረቀት ስላለቀ ሳታስረክብ አዲስ ወረቀት ተቀበለች። ያለቀውን ሚልካርድ ስም በውሃ አነካክተን አስለቀቅነው።በቦታው የኔን ስም ጽፈንበት ሚልካርድ ወደ ሚቀየርበት ቢሮ ሄደን አስቀየርን። ከዛ በዛ አድርጌ ካፌ መግባት ጀመርኩ። አቤት ዱዓ፣ ጭንቀት .. ለምን ኒቃብ ለበሽ ብቻ !!" ብዙ ያልተነኩና የልተዳሰሱ አሻራዎች ያሉበት መንገድ! ✨ሕያው ምስክር ~ 1 ~ ዲላ ዩኒቨርስቲ የነፃነት ትግል!! 🗓ነገ(ጁምዐ) ከ ምሽቱ 3:00 እንገናኝ! @aaumsu

🔥ለ ሱመያ ልጆች የተዘጋጀ ታላቅ መድረክ! 🔥ለ ኢማም አህመድ ኢብኑ ኢብራህም አል ጋዚ ልጆች የተዘጋጀ ታላቅ መድረክ! " የ ጥያቄ አለን ትውልድ ሚዘነጋው ትግል የለም!" የ ትግስት፣ የ ታማኝነት
🔥ለ ሱመያ ልጆች የተዘጋጀ ታላቅ መድረክ! 🔥ለ ኢማም አህመድ ኢብኑ ኢብራህም አል ጋዚ ልጆች የተዘጋጀ ታላቅ መድረክ! " የ ጥያቄ አለን ትውልድ ሚዘነጋው ትግል የለም!" የ ትግስት፣ የ ታማኝነት፣ የ ጽናት፣ የ ጥንካሬ፣ የ አንድነት ምሳሌ ሆነው ስላለፉ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!! በ ሕያው ምስክር 1! 🗓ነገ(ጁምዐ) ከ ምሽቱ 3:00 በዚው ቴሌግራም ቻናል ይጠብቁን! @aaumsu

🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ            ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨ 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ } የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- " የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት ያወርድለታል....... ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣ ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣ ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣ ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
መልካም ጁምዓ🌟
@fivekjemaa

🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨ 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آ
🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ            ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨ 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ } የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- " የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት ያወርድለታል....... ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣ ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣ ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣ ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ ‣ በዛሬው ዕለተ Exit exam ለሚወስዱ እህት/ወድሞቻችን አላህ ፈተናውን ገር እንዲያደርግላቸው በዱዓ እናስታውሳቸው 🤲🤲 🤲 اللهم وفّق إخواننا وأخواتنا المقبلين على امتحان الخروج غدًا، ويسّر لهم كل عسير، وافتح عليهم فتوح العارفين، وارزقهم النجاح والتوفيق. 🌟መልካም ጁምዓ🌟 🌟መልካም ፈተና ለተፈታኝ እህት ወንድሞች🌟 @fivekjemaa

💥አደለም ማስክሽን ከ አንገት በላይ ራሱ መከፈት አለብሽ ገና 🔥ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ሙተነቂቦች መንደር~3 መስጂድ ውስጥ ዙሁር ተሰግዶ ሱና ለመስገድ ልቆም ስል ወደ መስጅድ ስትገባ አየዋት፣ ደና አትመስልም ... ወደ እኔ እየተጠጋች ስትመጣ ሁኔታዋ ግራ ገባኝ። ስሟን እየጠራው በ አትኩሮት ሳያት እያለቀሰች ነው፣ ሄጄ 'ምን ሆነሽ ነው!?' ብዬ አቀፍኳት፣ ጥያቄዎቼ ሳያበቁ ለቅሶዋ እየጨመረ እዛው እንዳቀፍኳት ራሷን ሳተች። በ ድንጋጤ አጠገቤ የነበረችውን ልጅ ጠርቼ ለ ሁለት ይዘናት መሬት ቁጭ አልን፣ ስሟን ደጋግመን እየጠራን ለመቀስቀስ ብንሞክርም ልትነቃ አልቻለችም። እንደ ምንም ራሳችንን አረጋግተን ወደ ክሊኒክ ልንወስዳት ይዘናት ወጣን... ነርሶቹ 'ተረጋጉ ተረጋጉ ደና ናት!' እያሉ አልጋ ላይ አስተኝተው ግሉኮስ ሰኩላት። ግራ እንደተጋባን እስክትነቃ አጠገቧ ቁጭ ብለን ጠበቅን፣ የግልኮስ ማነስ ነው ሲሉን ወደ መስጂድ ስትገባ ይዛው የነበረውን ምግብ አስታውሼ ቁርስ አልበላችም ማለት ነው ከድካሙ ከፀሀዩጋ ተደማምሮ ይሆናል ብለን ገመትን ግን ለምን እንደዛ አለቀሰች ?!?ከመብሰልሰል እና ከመገመት ውጪ ምንም ማድረግ አልቻልንም..... አልሃምዱሊላህ ከሰዓታት ቆይታዎች በሗላ ነቃች፣ ነገር ግን አሁንም ከቅድሙ በባሰ እምባዋ ግጥም ብሎ መንሰቅሰቅ ጀመረች !! "ይቅርታ አድርጉልኝ" "ይቅርታ አድርጉልኝ" እያለች ታለቅሳለች የሆነችው ምኑም ሳይገባን አብረናት ማልቀስ ጀመርን... "በ አላህ አፍው በሉኝ ይቅርታ!" እያለች እየደጋገምች ታለቅሳለች እንደምንም አንዴ በልመና፣ነርሶቹ ሲቆጡም ተረጋጋች። የዚህን ሁሉ ምክንያትም በለቅሶ ታጅባ መንገር ጀመረች ..... ምግብ ይዤ በ ዋናው በር ወደ ግቢ ለመግባት ስሄድ ማስክሽን አውልቂ ብለው በጣም አስቸገሩኝ፣ ዋናው በር ማለት እንግዲ እኛ ሃራም ነው የተባልን ይመስል ድርሽ ማንልበት በር ነው፣ እንኳ ኒቃብ ማስክም እሺ ብለው አያስገቡም። ቀጠለች እኔም ፊቴን አልከፍትም ብዬ በ ሁለተኛው በር ለመሞከር በዛ ጠራራ ጸሐይ ዞሬ ሄድኩኝ። እሱ በር ደሞ ለመስጂድ የቀረበ እና አብዛኛውን ጊዜ ሙስሊም ተማሪዎች ሚጠቀሙት በር ነው እና እንደ ዋናው በር አያስቸግሩም ነበር፣ ምንም እንደማይሉኝ ተስፋ እያረኩ መታወቂያዬን ለ ጥበቆቹ እያሳየው ወደ ውስጥ ልገባ ስል "ነይ ነይ ፊትሽን ክፈቺ እንጂ!!" አሉኝ የቆሙት ጥበቆች አሷ ትፈትሸኝ ለሷ አሳያለው አልኩኝ ወደ ሴቷ ጥበቃ እየጠቆምኩኝ በጣም እየተባባሰባቸውም ስለሆነ ሊሰሙኝ አልቻሉም፣ ረጅም ሰዓት ቆሜ ተከራከርኩ ግን ከማመናጨቅ ውጪ ሊያስገቡኝ ፍቃደኛ አልነበሩም። በጣም ደክሞኝም ስለነበር ማስኩን ከፍቼ አሳየዋቸው እና አለፍኩ።ወደ ውስጥ እየገባሁ ማስኬን ሳስተካክል አይቶኝ በድጋሚ ጠርቶ "ጭራሽ አውልቂ አይቻልም ስልሽ ትለብሺያለሽ እንዴ!!" አለ በቁጣ ••"የምን ማስክ! የምን ፊት መሸፈን ነው! አደለም ማስክሽን ከ አንገት በላይ ራሱ መከፈት አለብሽ ... " እያለ ስለጅልባቤ እንኳ ሳይቀር ለመስማት በሚሰቀጥጥ መልኩ ሲያወራ አልቻልኩም እና ምግቡን እንደያዝኩ ቀጥታ ወጥቼ ወደ መስጅድ ነበር የሄድኩት፣ እዛ እናንተን ሳይ ደሞ ብላ አሁንም መንሰቅሰቅ ጀመረች። "እናንተ ኒቃቡን አናወልቅም ብላችሁ ለሱ ስትታገሉ እኔ ግን ማስኬን ዝቅ አደረኩኝ, ጭራሽ ማስኬን ዝቅ ሳረግላቸው ደሞ ጸጉርሽን አንገትሽን አሉኝ!!!" በአሏህ አውፍ በሉኝ•• °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° 🍂ሁሉም ስለምንታገልለት እስልምና እና ስለ ትግሉ በደምብ እስከተረዳ ድረስ! 🍂የ አንዱ ህመም ሌላውን እስከተሰማው ድረስ! 🍂ጠላት ፊት በ 1 እስከቆምን ድረስ በ ጥንካሬ እስከጸናን ድረስ፣ በ አላህ እስከተመካን እና እስከታገልን ድረስ የ አሸናፊዎች መንገድ ላይ ነን!! °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✨ሕያው ምስክር ~ 1 ~በ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ስለተደረገው ታሪካዊ የ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል ሙሉ ሁኔታ ሚዳሰስበት ልዩ መድረክ! 🗓 (ነሐሴ, 15) ጁምዐ ምሽት 3:00LT በ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይፋዊ ቴሌግራም ቻናል @aaumsu ©aaumsu @fivekjemaa

ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ! ጁምዓ (ነሐሴ 15) ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀ
ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ! ጁምዓ (ነሐሴ 15) ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ ! ልብ ጭቆናን አሻፋረኝ ብሎ የሰራውን ተዓምር የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ትግል ሕያው ምስክር ሆኖ እንቃኛለን። የሌቱ ጨለማ ከሚደርሰው በደል በላይ አያስፈራም ብለው 11 ምሽቶችን ከውጪ ስላሳለፉ እንቁዎች ታሪክ እንዳስሳለን። ቻለንጁን እንቀላቀል ! @aaumsu

ሕያው ምስክር - 1 መብታቸው ይከበር ዘንድ 11 ምሽቶችን ከውጪ አድረዋል። መብታቸው ይከበር ዘንድ ለ11 ቀናት ያክል ከክላስ፣ ከምግብ እና ንባብ እንዲርቁ ተደርገዋል። የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ማለት ነው። ሆኖም በምንም ሳይሸበሩ፤ ምንምም ወደሗላ እንዲሉ ሳያደርጋቸው ታገሉ። መብታቸውን እንዳስከበሩም ያለፋቸውን በክብር ተምረው፤ በነፃነት ሕያዎታቸውን ቀጠሉ። ሙሉ ታሪኩን በመጪው ጁምዓ ከምሽቱ 3 ሰዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል (@aaumsu) ይጠብቁ። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSVSeWBf3/ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ። @aaumsu

🚫"የ ጥበብ መጀመርያ እየሱስን ማወቅ ነው"❗️ 🔥ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ሙተነቂቦች መንደር~2
በ ጊዜ ውስጥ እኔም ያ ውድ የሆነውን ባለ ግርማ ሞገሶቹን ስብስብ ለመቀላቀል ታደልኩ!! ፊታቸውን በመሸፈን ጥሩ ነገር ለማበርከት ከሚታገሉት ውስጥ ለመሆን በቃው🍂!!
የ አዲስ ተማሪዎች መግብያ ጊዜ ደረሰ! ተማሪን ለመቀበል ዋናው በር ላይ በ ኒቃብ መታየት ስለማይታሰብ እኔም በ ማስክ ከተምኩ። እንደዛም ሆኖ አንዱ ኃላፊ እየተከታተለኝ እንደነበር አስተውያለው በኔ አቅጣጫ መምጣት ጀመረ: ሲደርስ "አንቺ!!" ብሎ አንገቴ ላይ ያደረኩትን የ ክበብ መታወቅያ ያዝ በማድረግ፣ "ይሄ የ ምን ክበብ ነው?!" አለኝ •• እኔም "ተማሪ..." ሕዝብ ፊት እሱንም ስንት አይነት ተማሪ እያለ መቶ ያደረኩትን መታወቅያ በ ንቀት ይዞ እያናገረኝ መሆኑ ሴትነቴን ቢፈታተነውም ዋጥ አድርጌው "የ ሴቶች ማህበር ነው!" አልኩት በ ኩራት እና በ ድፍረት!! እያፌዘ 'የ ሴቶች ማህበር ነው' ብሎ አመናጭቆ ከ አንገቴ ላይ ወረወረው! እንደዛም እየሆነ  አዲስ ግቢውን ከሚቀላቀሉ ተማሪዎች መካከል ኒቃብ ሚልብሱ እህቶች አይጠፉም ነበር። ነገራቶች በጣም የከረሩበት ዓመት ላይ 1 ፍሬሽ ኒቃቢስት ወደ ግቢው ልትገባ ስትል ተመለከትኩ፣ ደስታም ሃዘንም እየተፈራረቀብኝ ምን ሊሏት እንደሚችሉ እያሰብኩ ወደሷ አመራው ... አዲሱ ኃላፊ የተባለው እንዳየን "ቆይ ቆይ ቆይ!! ወዴት ነው!? ሕጉን አታውቁም?! እንዲ ለብሶ መግባት አይቻልም! " አለ ተኮሳትሮ። ያ ራህማን ዛሬ ደሞ ይሄ ከየት ነው የመጣው እያልኩ በ ውስጤ "አይ አዲስ ስለሆነች ነው፣ ለ ዛሬ ትግባ! አስፈላጊ ከሆነ በ ሴት መፈተሽ ትችላለች" አልኩ ፈጠን ብዬ "አይ አይ!! በጭራሽ ውስጥ አውልቃው ትግባ" አለኝ! "እንደዛማ አይሆንም! ፍሬሽ ነች ለ ዛሬ ትግባ .." እንዲው እየተከራከርን ቆይተን በ አቋሙ እንደጸና የ ግል ሃብቱ ይመስል በፍጹም አላስገባም ብሎ መለሳት! በማስታውሰው ከነሱ ጋር የነበረው የመጨረሻ ንግግሬ ክላስ እየሄድኩ ID የቀሙን ጊዜ ነበር! 🍃ካፌውንም ላይብረሪውንም ምኑንም ምኑንም ከተውነው ቦሃላም አንዳንዴ ደስ ሲላቸው ዶርም ድረስ እየመጡ ኒቃብ መልበሳችንን ሲያዩ id ያችንን ወስደውት ይሄዳሉ። ከሁሉም በላይ ሚገርመኝ ደሞ ፈርመንም ቢሆን መታወቅያችንን ለመቀበል ቢሮ ስንሄድ እንደ ወጉ ሕጎችን ስለማክበር እና ስለ secularism ምክር ቢጤ ነገር ሲሰጡን ሁሌም ማፈጥበት ከራሳቸው ግድግዳው ራስጌ ላይ ያለው "የ ጥበብ መጀምርያ እየሱስን ማወቅ ነው" ሚለው ግልፅፅፅ ብሎ ሚታየው ጽሑፍ ነው ... ሁለት ሆነን ክላስ ለመግባት እየሄድን ነበር አንዱ የ ጥበቃ ኃላፊ id አምጡ ብሎ ጠራን  ••• 'እእ አልያዝንም' አልነው! በቃ ሁሌም እንደዛ ነው ምንለው፣ ቀምተው ዲሲፕሊን አስፈርመው ስለሆነ ሚሰጡን •• "ወደ ክላስ እየሄድን ነው id ደሞ አልያዝንም" እያልን እንደምንም ለማለፍ ሞከርን፣...ግትር ሲልብን ኃላፊው በ ቅርብ ተቀይሮ የገባም ስለሆነ፣ እስኪ እናሳየው ምንም አያመጣም ብለን አውጥተን አሳየነው። ተቀበለንና "ሂዱ በቃ!" አለን ንቀት በተሞላበት አነጋገር! "እንዴ ምን ማለት ነው?! ከፈለክ በ ሴት ጥበቃ እንፈተሽ ግን id ወስደህብን እንዴት ነው ግቡ ውስጥ ምንንቀሳቀሰው, ተማሪ መሆናችንን ለማረጋገጥ አልነበር ?! ይሄው id ያችን፣ ተማሪ ነን! ክላስ ረፍዶብናል ስጠን!" እያልን መጠይቅ ያዝን... መለሰ "ሲጀመር እናንተ እንደ አሸባሪ አልሸባብ ስትሆኑ ነው እንጂ እምነታችሁ እኮ ይሄን አያዝም!" ብሎ "ID ከፈለጋችሁ እሱን ነገር አውልቁና ማስክ አድርጋችሁ መጣችሁ ውሰዱ!" እያለ ስለ ኒቃብ ሲያወራ "በቃ በቃህ አንተ ስለ እምነታችንም ሆነ ስለ ልብሱ ምንም አታውቅም id ውንም ከፈለክ ውሰደው" ብለን በ ንዴት እየበገንን ወደ ክላስ ሄድን። ሕያው ምስክር ~ 1 🗓: የ ፊታችን ጁምዐ(ነሐሴ,15) ከ ምሽቱ 3:00LT በ ልዩ መድረክ! @aaumsu

እህቶች ብቻ የተጋሩት ታሪክ! በ እህቶች ብቻ የታበሰ እምባ! 💭ዝምተኛው ትግል! 🔥ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ሙተነቂቦች መንደር 1 ልክ እንደ ትናንት ከ 3 ዓመት በፊት አንዷ እህቴ ላይ የደረሰውን ነገር ሳይ ነበር ውስጤ የ ትግል እሳት የተቀጣጠለው! ግቢ መግብያ 2 ሰዓት ነበር። በ ሰዓቱ በማላስታሰው ምክኒያት ሙስሊም ተማሪዎች የምንጠቀመው ከ መስጅዳችን(ሙሃጂሪን) ፊት ለፊት ያለውን የ መግብያ በር መጠቀም እንደማንችል እና በ ዋናው በር እንድንዞር ተደረገ፣ ሄድንም! ከዛ ጥበቆች ፊታችሁን እየከፈታችሁ ... አሉን። በጊዜው ብዙ በ ኒቃብ ኒያህ ማስክ ሚጠቀሙ፣ በ ግቢው ፍርሃት ኒቃብ ማይለብሱ እህቶች ነበሩ። ነገር ግን አንዲት ብቸኛና ጠንካራ ሙተነቂብ ጓደኛችን ነበረች፣ ቀላል ባይሆንም ከ ID ያችን ጋር እያስተያዩን እኛ እንደምንም ገባን፣ ቀድሚያት ስለነበር ኒቃቢስት ጓደኛችንን ወደ ሗላ ዞሬ ሳገኛት ከ ድንጋጤ የተነሳ ትንፋሿ ይቆራረጥ ነበር፣ ሁኔታዋ አሁንም ከ አዕምሮዬ አይጠፋም! በጋለ ስሜት ለምን ሚለውን 'መልስ የሌለውን ጥያቄ' ጠየኩ፣ ለምን ?! እንዴት ሂጃብ መልበስ ሀበሻ ውስጥ ይከለከላል!? አልኩ... ግን መልስ የለም!!! የዛች ቀን ለኔ ትልቅ ማንቂያ እና ለ ጽናትም ሰበቤ ነበረች! ዓመቱ ID ሲቀማ፣ ሲመለስ፣ ሲፈረም እንደምንም አለቀ። ጊዜ ጊዜን ተክቶ ወደ ግቢ መመለሻ ጊዜያችን ደርሶ እኛም ተመለስን፣ ግቢውም ያደርስ የነበረውን በደል አክርሮ እና አጠናክሮ ጠበቀን! መሳቀቅ ዚክርና ዱዓ እያረጉ ገብቶ መውጣት፣ መሰደብ፣ መደበቅ የዚህ ዓመት ዋና ስራችን ሆነ ሲመታ እንደሚጠነክር ሚስማር እንደሚባለ የ ኒቃቢስቶች ቁጥር ከ 1 ወደ 2, 3 እየጨመረ መጣ! ቢሆንም ከ ስድብና እንግልታቸው የተነሳ ማስክ ለብሰን እንኳ ብቻችንን መንቀሳቀስ ለኛ ሰቀቀን ነበረ፣ ክላስ ካፌ፣ የግቢ በር ብቻችንን መግባት ልክ እንደ ምድር ጀሀነም ነበር ለኛ። የተማሪዎች ካፌ ቲከሩ "ፊታችሁን ካልከፈታችሁ አትገቡም" ብሎ የምሩን ከመለሰን ቀን ቦሃላ ድርሽ ብለን አናቅም ..... ወሰንንንንንን! ምናልባት ካፌ በመቅረት ውስጥ ከ ጥበቆቹ ፊትም ዞር እንል ይሆናል፣ በዚህ ሚቀንስልን ጭቅጭቅ እና መጋተት ካለ ብለን ድጋሜ ካፌ ላንመጣ ወስንን! በ ታሪክ ከተነገረን ግቢያችን በ ቁጥር በዛ ያሉ ወደ 43 ሚጠጉ ኒቃብስቶችን ፊታችሁን ሸፈናችሁ ብሎ ጠቅልሎ ያባረረበት ጊዜ ነበር፣ የኛ ሁኔታም ኒቃብ ከሚለብሱት እኩል ወደዛ ሚያቀና ይመስል ነበር...በዚም መልኩ ጊዜያት ያልፉ ነበር•• እናም 1 ቀን ወደ መስጂድ እየሄድን ሳለን ወደ መውጫው በር እንደተቃረብን የየቀን ዱዓችን ውስጥ ሚኖረው የጥበቃው ኃላፊ አገኘን፣ ከብዙ ስድብ፣ አድካሚና አሰልቺ ንግግር ቦሃላ "ቆይ ግን አሁን አንቺ አዲስ እዚ ያመጣሽው ነገር ነው እንጂ ታች ሀገርሽ ስትማሪ እንዲ ትለብሺ ነበር?!" አለ ወደ ለበስኩት ማስክ እየጠቆመ .. ጓደኛዬ እጄን ጥብቅ እያረገች ዝም በይው ትለኛለች፣ "አዎ እኔ እንዲው ለብሼ ነው የተማርኩት አዲስ ነገር አደለም!" አልኩት የ ጥላቻ ንዝነዛውን እንደቀጠለ "እሺ አሁን አንቺ ጁንታ ሁኚ ሸኔ ሁኚ ፋኖ ሁኚ በምንድነው ማቀው?!" ሕያው ምስክር ~ 1 የ ፊታችን ጁምዐ ማታ ከ ምሽቱ 3 ሰዓት ይጠብቁን ! @aaumsu

ጥያቄዎቻችን የፍትሕ፤ የእኩልነት እና የዜግነት ጥያቄዎች ናቸው! በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVrkmnYF/ በመግባት ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ። @aaumsu

እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ፦ ሀገራችን ኢትዮጵያ ዜጎቿን ያለ ልዩነት በእኩልነት እያገለገለች ነው? ዜጎች ሀገራቸውን በእኩልነት ያገለገሉ ዘንድ እድሎች አሉን? የሀገር ተቋማት ላይ እኩል ውክልና አለን? የሀገር ሀብት በፍትሐዊነት ተከፋፍሏልን? የሀገር መገለጫዎች ሁሉንም ይገልፃሉን?! መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVMj5B8o/ በመግባት ሪፖስት ያድርጉ። @aaumsu

ሕያው ምስክር - 1 የ11 አመታት ችግሮች የተፈቱበት የ11 ሌሊቶች ትግል በዲላ ዩኒቨርስቲ ! ከጥንት እስከ አሁን፤ ከትላንት እስከ ዛሬ፤ ከድሮ እስከ ዘንድሮ ከደቡብ እስከ ሰሜን፤ በምስራቁም ሆነ
ሕያው ምስክር - 1 የ11 አመታት ችግሮች የተፈቱበት የ11 ሌሊቶች ትግል በዲላ ዩኒቨርስቲ ! ከጥንት እስከ አሁን፤ ከትላንት እስከ ዛሬ፤ ከድሮ እስከ ዘንድሮ ከደቡብ እስከ ሰሜን፤ በምስራቁም ሆነ በምዕራቡ የኢትዮጵያ ክፍል በዳዮች ሰበብ እየፈጠሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሲያንገላቱ፤ መብቶቻቸውን እየጣሱ፤ ከትምህርት እያፈናቀሉ ዘልቀዋል። በዚህም ሕዝበ ሙስሊሙ በማህበራዊ መስተጋብር፤ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ፤ በፖለቲካዊ ተሳትፎ መድረስ ካለበት ሳይደርስ አሁንም ድረስ ስለመብቱ እየጠየቀ፤ እየታገለ፤ ስለ ዘላቂ መፍትሔ እየተጓዘ አለ። ጨቋኝን ጨቋኝ የመውረሱን ያክል የነፃነት ታጋይንም ስለነፃነቱ የሚጠይቅ ትውልድ ወርሶ በደል ባለበት ቦታ ሁሉ ጥያቄ አለን እያልን፤ ስለመብታችን እየታገልን፤ መብታችንንም እያስከበርን አለን። የጥያቄ አለን ትውልድ የሚዘነጋው ትግል የለምና በእኛ ትውልድ በደቡቡ የሀገራችን ክፍል በዲላ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰን በደል፤ የተደረገን እልህ አስጨራሽ ትግል፤ ለአስራ አንድ ቀናት ከግቢ ውጪ ታድሮ የተፈፀመን ገድል በሕያው ምስክር - 1 የምንቃኝ ይሆናል። እንግዳችን፦ ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ (በሰዓቱ የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት አሚር) መድረክ መሪ፦ ዘይድ ሷዲቅ (የቀድሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ) ቀን፦ ነሐሴ 15 / 2018 ዓ.ል ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ መድረኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል (@aaumsu) ላይ ነው። @aaumsu