fa
Feedback
⛪️መንፈሳዊ መጻሕፍትን እናንብብ እንወቅ⛪️

⛪️መንፈሳዊ መጻሕፍትን እናንብብ እንወቅ⛪️

رفتن به کانال در Telegram

በዚህ ቻናል የሚቀርቡ ፩.ተከታታይ የቤተክርስቲያን ትምህርቶች ፣ ፪. መንፈሳዊ መጻሕፍት ጥቆማ፤ ፫. የተለያዩ አጫጭር የቤተክርስቲያን መጣጥፎች ፣ ወጎች ፣ ታሪኮች ፤ ፬. ለተለያዩ ጥያቄዎች መልስ እና ወቅታዊ ትምህርቶችን እንማማራለን ፣ ፭. ዘወትር #ቃለ_ወንጌል የእለቱ(በግፃዌ) ይቀርባሉ። ተከታታይ ትምህርቶች ለማግኘት 👇👇 @EOTC_teketatay ለጥያቄ👉 @Temechache

نمایش بیشتر
4 957
مشترکین
+624 ساعت
+297 روز
+9530 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '26
اوت '26
+13
در 0 کانال‌ها
ژوئیه '26
+160
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '26
+193
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+182
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+137
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+88
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+75
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+93
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+86
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+99
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+96
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+91
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+112
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+85
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+87
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+126
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+139
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+169
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+178
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+299
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+404
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+470
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+324
در 1 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+446
در 2 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+510
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+131
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+115
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+166
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+214
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+190
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+166
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+164
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+237
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+140
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+74
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+50
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+46
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+68
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+20
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+49
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+237
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
02 اوت+5
01 اوت+8
پست‌های کانال
#ቃለ_ወንጌል 27/11/2018 ዮሐንስ 10:34-ፍጻሜ ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፦ “እኔ፦ ‘አማልክት ናችሁ አልሁ፡’ ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን? መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ፡ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደ ዓለምም የላከውን፦ ‘ትሳደባለህ፡’ ትሉታላችሁን? እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤ ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።” እንግዲህ ደግመው ሊይዙት ፈለጉ፤ ከእጃቸውም ወጣ። ዮሐንስም በመጀመሪያ ያጠምቅበት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ ዮርዳኖስ ማዶ እንደ ገና ሄደ በዚያም ኖረ። ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ መጥተው፦ “ዮሐንስ አንድ ምልክት ስንኳ አላደረገም፥ ነገር ግን ዮሐንስ ስለዚህ ሰው የተናገረው ሁሉ እውነት ነበረ፡” አሉ። በዚያም ብዙዎች በእርሱ አመኑ #መልእክታት ዕብራውያን 5:7-ፍጻሜ 1 ዮሐንስ 5:16-ፍጻሜ ሐዋ.ሥራ 4:14-19 ምስባክ መዝሙር 88:18-19 ወቅዱሰ እስራኤል ንጉሥነ ውእተ ዓሚረ ተናገርኮሙ በራእይ ለደቂቅከ ወትቤ እሬሲ ረድኤት በላዕለ ኃይል

2
‛‛ለሌሎች ይቅርታን ስትሰጥ፣ ለራስህ ሰላምን ትሰጣለህ።’’ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
246
3
#ቃለ_ወንጌል ዘሰንበተ ክርስቲያን               ማቴዎስ 8:1-ፍጻሜ    ከተራራም ሲወርድ ብዙ ሰዎች ተከተሉት። "እነሆ፥ አንድ ለምጻም ሰው መጥቶ፥ “አቤቱ! ከወደድህስ እኔን ማንጻት ይቻልሃል” እያለ ሰገደለት። 'እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና “እፈቅዳለሁ ንጻ” አለው፤ ያንጊዜም ከለምጹ ነጻ። 'ጌታችን ኢየሱስም፥ “ለማንም እንዳትናገር ተጠንቀቅ፣ ነገር ግን ሂድና ራስህን ለካህን አስመርምር፤ ምስክርም ሊሆንባቸው ሙሴ እንደ አዘዘ መባህን አቅርብ” አለው። ወደ ቅፍርናሆም በገባ ጊዜ የመቶ አለቃ ወደ እርሱ መጥቶ፦ “አቤቱ! ልጄ ሽባ ሆኖ እጅግ እየተጨነቀ በቤት ተኝቶአል” ብሎ ለመነው። ጌታችን ኢየሱስም “እኔ መጥቼ እፈውለዋለሁ” አለው። የመቶ አለቃውም መልሶ፥ “አቤቱ! አንተ ከቤቴ ጣራ በታች ልትገባ አይገባኝም ነገር ግን በቃልህ እዘዝ፤ ልጄም ይድናል፤ "እኔም እኮ የምገዛ ሰው ነኝ፣ የማዝዛቸውም ጭፍሮች አሉኝ፤ ይህን ሂድ ብለው ይሄዳል፤ ሌላውንም ና ብለው ይመጣል፤ አገልጋዬንም ይህን አድርግ ብለው ያደርጋል” አለው። ጌታችን ኢየሱስም ሰምቶ አደነቀ፤ ለሚከተሉትም እንዲህ አለ፥ “እውነት እላችኋለሁ፤ በእስራኤል ሁሉ እንዲህያለ እምነት አላገኘሁም፣ “ነገር ግን እላችኋለሁ፦ ብዙ ዎች ከምሥራቅና ከምዕራብ ይመጣሉ፤ በመን ግሥተ ሰማያትም ከአብርሃምና ከይስሐቅ፥ ከያዕቆብም አጠገብ ይቀመጣሉ። “የመንግሥትን ልጆች ግን በውጭ ወደ አለ ጨለማ ይጥሏቸ ዋል፤ በዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆ ናል።” "ጌታችን ኢየሱስም የመቶ አለቃውን እንዲህ አለው፥ “እንግዲህ ሂድ እንደ እምነትህ ይሁንልህ።” ልጁም በዚያ ሰዓት ዳነ፤ መስፍኑም ወደ ቤቱ በተመለሰ ጊዜ ልጁ ድኖ አገኘው። ጌታችን ኢየሱስም ወደ ጴጥሮስ ቤት በገባ ጊዜ የጴጥሮስን አማት በንዳድ ታማ ተኝታ አገኛት። እጅዋንም ይዞ ዳሰሳት፤ ንዳዱም ተዋት፤ ተነሥታም አገለገለቻቸው። "በመሸም ጊዜ አጋንንት ያደሩባቸውን ብዙዎችን ወደ እርሱ አመጡ፤ ኣጋንንትንም በቃሉ አወጣቸው። የታመሙትንም ሁሉ ፈወሰ። " ይህም ነቢዩ ኢሳይያስ፥ “ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንንም ተሸከመ” ብሎ የተናገረው ይፈጸም ዘንድ ነው። ጌታችን ኢየሱ ስም በዙሪያው የተሰበሰቡትን ብዙ ሰዎች በአየ ጊዜ ባሕሩን ተሻግረው እንዲሄዱ አዘዘ። “አንድ ጸሓፊ ወደ እርሱ መጥቶ፥ “መም ህር፥ ወደምትሄድበት ሁሉ ልከተልህን?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም፥ “ለቀበሮዎች ጒድጓድ አላቸው፤ ለሰማይ ወፎችም ጎጆ አላቸው፤ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም” አለው። “ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፥ “ጌታ ሆይ አስቀድሜ ልሂድና አባቴን ልቅበር ፍቀድልኝ” አለው። ጌታችን ኢየሱስም፥ “አንተስ ተከተለኝ፤ ሙታኖቻቸውን ይቀብሩ ዘንድ ሙታንን ተዋቸው” አለው። ወደ ታንኳ በወጣ ጊዜም ደቀ መዛሙርቱ ተከተሉት። እነሆም፥ የባሕሩ ማዕበል ታንኳውን እስኪደፍነው ድረስ በባሕሩ ውስጥ ታላቅ መናወጥ ሆነ፣ እርሱ ግን ተኝቶ ነበር። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው ቀሰቀሱትና፥ “አቤቱ! እንዳንሞት አድነን” አሉት። “እርሱም፡ “እናንተ እምነት የጐደላችሁ ምን ያስፈራችኋል?” አላቸው፤ ተነሥቶም ነፋሳትንና የባሕሩን ማዕበል ገሠጻቸው ታላቅ ጸጥታም ሆነ ሰዎችም፡ “ባሕርና ነፋሳትስ እንኳ የሚታዘዙለት ይህ ማነው?” እያሉ ተደነቁ። ወደ ማዶም ወደ ጌርጌሴኖን ሀገር በደረስ ጊዜ አጋንንት ያደሩባቸው ሁለት ሰዎች ከመቃብር ወጥተው ተቀበሉት፡ እነርሱም ማንም በዚያች መንገድ ማለፍ እስከማይችል ድረስ እጅግ ክፉዎች ነበሩ። ባዩት ጊዜም፥ “የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋርምን አለን? ጊዜው ሳይደርስ ልታሠቃየን ወደ ዚህ መጣህን?” እያሉ ጮኹ። “ከዚያም ብዙ የእሪያ መንጋዎች ከእነርሱ ርቀው ተስማርተው ነበሩ። "እነዚያ አጋንንትም፥ “ካወጣኸንስ በእሪያዎቹ መንጋ ላይ እንድናድር ወደዚያ ስደደን” ብለው ለመኑት፡ እርሱም “ሂዱ” አላቸው። "ወጥተውም ሄዱ፤ በእሪያዎቹም ላይ አደሩ፡ የእሪያዎችም መንጋዎች ሁሉ ከአፋፉ እየሮጡ ወደ ባሕር ውስጥ ወደቁ፣ በውኃው ውስጥም ሞቱ። "እረኞችም ሸሹ፤ ወደ ከተማይቱም ገብተው ነገሩን ሁሉ፥ አጋንንትም ባደሩባቸው የሆነውን አወሩ። “እነሆ፥ በከተማዋ ያሉት ሁሉ ጌታችን ኢየሱስን ሊቀበሉት ወጡ፤ ባዩት ጊዜም ከሀገራቸው እንዲሄድ ለመኑት። #መልእክታት 2 ቆሮንጦስ 10:1-ፍጻሜ  ያዕቆብ 3:1-9 ሐዋ፡ሥራ 28:17-ፍጻሜ ምስባክ                 መዝ· ፷፬ : ፱ – ፲ ሐወጽካ ለምድር ወአርወይካ ወአብዛኅኮ ለብዕላ ፈለገ እግዚአብሔር ምሉዕ ማያት ትርጉም ምድርን ጐበኘሃት አረካሃትም፥ ብልጽግናዋንም እጅግ አበዛህ፤ የእግዚአብሔር ወንዝ ውኆችን የተመላ ነው
349
4
የሚቆጣህ ጓደኛ ይኑርህ የጓደኝነት ትልቁ ፈተና አንዱ ሌላውን መገስጽ መቻሉ ወይም አለመቻሉ ነው፡፡ ሁላችንም እለት ተእለት ኃጢአት እንሠራለን፤ ለራሳችን ሰበብ እየፈጠርን ኃጢአቱ እንዳልተከስተ በማስመሰል ኃጢአታችንንም ላለመመልከት አይናችንን እናውራለን:: በእንደዚህ አይነት ጊዜያት ለኃጢአታችን ዓይኖቻችንን የሚከፍቱ ጓደኞች ያስፈልጉናል። ራስህን በጓደኛህ ቦታ አስቀምጠው:: የዚያን ሰው ዓይኖች ለመክፈት ፈቃደኛ ነህ? ያሉትን ሰበቦች ውሸት መሆናቸውን ልትነግረው ዝግጁ ነህ? የሰው ልጅ ስለ እርሱ መጥፎ ሲነገረው ቁስሉ እንደተነካ ይጮኻልና የጓደኛህን ቁጣ ለመጋፈጥ ተዘጋጅተሃል? ወይንስ በዝምታ ታልፈዋለህ? ጓደኞቻችንን በምንመርጥበት ጊዜ፣ ከእኛ ጋር ሀቀኛ ለመሆን ፈቃደኛ የሆኑትን እና አስፈላጊ ሲሆንም ንዴታችንን ለመቋቋም የተዘጋጁትን መምረጥ አለብን፡፡ እንደዚህ ያለ ሐቀኝነት ከሌለ፣ ጓደኝነት ጥልቀት የለውምና ምንም ፋይዳ የለውም:: ለጓደኛህ ትችት መግለጽ ግዴታህ ቢሆን የጓደኛህን ክብር ዝቅ እንዳታደርግ ተጠንቀቅ:: የእርሱን መልካም ነገሮችንም ከወቀሳህ ጋር አብረህ ማንሳትህ ተግሣጽህን ያለስልሳል:: እናም ጓደኛህን የምትገስጸው ከቀናነት እንጂ ከክፋት አይሁን፤ ቃላቶችህም በፍቅር እንጂ በቁጣ አይሁኑ:: #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
422
5
"በፈተና ጊዜ፥ ደካማው ሰው "እንደዚህ የደረሰብኝ'ኮ" እያለ የሚያመካኝበት ሌላ ሰውን ይፈልጋል፤ ብርቱው ሰው ግን በፈተናው ይጸና ዘንድ እግዚአብሔርን ይፈልጋል፡፡" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
413
6
#ቃለ_ወንጌል 25/10/2017                          ዮሐ 14:18-27   “የሙት ልጆች ትሆኑ ዘንድ አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ገና ጥቂት ጊዜ አለ፤ እንግዲህ ወዲህም ዓለም አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ፤ እኔ ሕያው ነኝና፤ እናንተም ሕያዋን ትሆናላችሁ። እኔ በአብ እንዳለሁ፥ አብም በእኔ እንዳለ ፤ እናንተም በእኔ፥ እኔም በእናንተ እንዳለሁ ያንጊዜ ታውቃላችሁ። ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለ የሚጠብቀውም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል፤ እኔም እወደዋለሁ፤ ራሴንም እገልጥለታለሁ።” የአስቆሮቱ ሰው ያይደለ ይሁዳም፥ “ጌታ ሆይ፥ ለዓለም ያይደለ ለእኛ ራስህን ትገልጥ ዘንድ እንዳለህ የተናገርኸው ምንድን ነው?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ አለው፥ “የሚወደኝ ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል፤ ወደ እርሱም መጥተን በእርሱ ዘንድ ማደሪያ እናደርጋለን። የማይወደኝ ግን ቃሌን አይጠብቅም፤ ይህም የምትሰሙት ቃል የላከኝ የአብ ቃል ነው እንጂ የእኔ ቃል አይደለም። “ከእናንተም ጋር ሳለሁ ይህን ነገርኋችሁ። ነገር ግን አብ በስሜ የሚልከው፤ የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል፤ እኔ የነገርኋችሁንም ሁሉ ያሳስባችኋል። መልእክታት ዕብራውያን 6:7-12 ይሁዳ 1:1-7 ሐዋ፡ሥራ 14:16-ፍጻሜ ምስባክ መዝ  73÷17-18 ወአንተ ገበርከ አድባረ ምድር ኵሎ ክረምተ ወሐጋየ ዘአንተ ፈጠርከ ወተዘከር ዘንተ ተግባረከ ትርጉም አንተ የምድርን ዳርቻ ዅሉ ሠራኽ በጋንም ክረምትንም አንተ አደረግኽ ይህን ፍጥረትኽን ዐስብ
505
7
አንገትህን ለሰይፍ እንደማትሰጥ ሁሉ፣ ጆሮህንም ለሐሜተኛው አታበድር። ሐሜተኛው ሰው በአንድ ጊዜ ሦስት ሰዎችን ይገድላል—ራሱን በክፉ ምላሱ፣ የሰሚውን ሕሊና በመርዙ፣ የጉዳዩን ባለቤት ደግሞ በሐሰት። ሐሜት እንደ እሳት ነው፤ አንዴ ከቀጣጠለ የትኛውንም ሰላማዊ ማህበረሰብ አመድ አድርጎ ይቀየረዋል።" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
447
8
#ቃለ_ወንጌል 24/10/2017                           ዮሐንስ 12:20-26       ከጽርዕ ሰዎችም ይሰግዱ ዘንድ ለበዓል የወጡ ነበሩ። እነርሱም ከገሊላ፥ የቤተ ሳይዳ ሰው ወደ ሆነው ወደ ፊልጶስ ሄደው፥ “አቤቱ፥ ጌታ ኢየሱስን ልናየው እንወድዳለን” ብለው ለመኑት። ፊልጶስም ሄዶ ለእንድርያስ ነገረው፤ እንድርያስና ፊልጶስም ሄደው ለጌታችን ለኢየሱስ ነገሩት። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “አሁን የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ጊዜው ደረሰ። "እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ የስንዴ ቅንጣት በምድር ላይካልወደቀችና ካልሞተች ብቻዋን ትኖራለች፤ ከሞተች ግን ብዙ ፍሬን ታፈራለች። ነፍሱን የሚወዳት ይጥላታል፤ በዚህ ዓለም ነፍሱን የሚጥላትም ለዘለዓለም ሕይወት ይጠብቃታል። መልእክታት ሮሜ 9:2ም4-ፍጻሜ 1 ዮሐንስ 1:4-ፍጻሜ ሐዋ፡ሥራ 14:1-7 ምስባክ                       መዝሙር 31:4-5 ኃጢአትየ ነገርኩ ወአበሳየ ኢኀባዕኩ ወእቤ አስተዋዲ ርእስየ ኀበ እግዚአብሔር በእንተ ኃጢአትየ ወአንተ ኅድግ ጽልሑቶ ለልብየ ትርጉም ኀጢአቴን ነገርሁ፤ በደሌንም አልሸሸግሁም ስለ ኀጢአቴ ወደ እግዚአብሔር ራሴን እከስሳለሁ፤ አልሁ አንተም የልቤን ሽንገላ ተውልኝ
570
9
በመንገድ እየሄድህ ሳለ በድልድይ ስር ስታልፍ ድንገት ከላይ የሚንጠባጠብ የቆሸሸ ውኃ ቢነካህ ሁኔታው ሊያናድድህ ይችላል። ነገር ግን ያ ቦታ እንደሚያፈስ እያወቅህ ተመላልሰህበት ከበሰበስህ ግን ጥፋቱ የአንተ እንጂ የማንም አይደለም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው አንዳንዴ ልክ እንደዚያ ጠብታ ሰይጣን ወደ ኅሊናህ ሊያስገባ የሚሞክረው ነፍስህን የሚያቆሽሽ ክፉ ሐሳብ ይኖራል። አንዴ የነካህ ክፉ ሐሳብ ግን ተመላልሶ እንዲያቆሽሽህ ከፈቀድህ ተወቃሹ አንተ እንጂ ሰይጣን አይሆንም። ዲያቆን አቤል ካሳሁን
521
10
"ዲያብሎስ በእናንተ ላይ እጅግ ክፉ ነገርን በማምጣት አሳዝኖአችኋልን? እናንተም ኢዮብን አብነት አድርጋችሁ እግዚአብሔር ይመስገን በማለት አሳዝኑት፡፡ ዲያብሎስን ድል ማድረግ ስትሹ ይህን መሣርያ ዘወትር ያዙ፤ ምስጋናን፡፡" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
704
11
#ቃለ_ወንጌል 23/10/2017                           ማቴዎስ 11:12-ፍጻሜ      ከመጥምቁ ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፤ የተገፉትም፤ ይናጠቋታል። ነበያትም ሁሉ፥ ኦሪትም እስከ ዮሐንስ ትንቢትን ተናግረዋልና። “ልትቀበሉትስ ብትወድዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይህ ነው። ዦሮ ያለው መስማትን ይስማ። "ይህቺን ትውልድ በምን እመስላታለሁ? በገበያ ተቀምጠው ጓደኞቻቸውን የሚጠሩ ልጆችን ትመስላለች። "እንዲህም ይሏቹዋል፦ እንቢልታ እየነፋን አቀነቀንላችሁ አልዘፈናችሁም፤ ሙሾም አወጣንላችሁ አላለቀሳችሁም። ዮሐንስ ሳይበላና ሳይጠጣ መጣ፤ እነርሱ ግን ጋኔን አለበት አሉት። የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ፤ እነርሱም እነሆ፥ የሚበላና የወይን ጠጅ የሚጠጣ፥ የቀራጮችና የኃጥኣን ወዳጅ ነው አሉት፤ ጥበብም ከልጆችዋ የተነሣ ጸደቀች።” ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ብዙ ተአምራት ያደረገባቸውን ከተሞች ንስሓ ስላልገቡ ይነቅፋቸው ጀመር፤ እንዲህም አላቸው። “ኮራዚ ወዮልሽ፤ ቤተሳይዳ ወዮልሽ፤ በእናንተ የተደረገው ተአምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን ማቅ ለብሰው፥ አመድም ነስንሰው አስቀድመው ንስሓ በገቡ ነበር። ነገርግን እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ጢሮስና ሲዶና ዕረፍትን ያገኛሉ። ቅፍርናሆም! አንቺም እስከ ሰማይ ከፍ ከፍ ብትዪ እስከ ሲኦል ትወርጃለሽ፤ በአንቺም የተደረገው ተአምራት በሰዶም ተደርጎ ቢሆን እስከ ዛሬ በኖረች ነበር። ነገር ግን እልሻለሁ፥ በፍርድ ቀን ከአንቺ ይልቅ የሰዶም ምድር ዕረፍትን ታገኛለች።” ያንጊዜም ጌታችን ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ፤ “የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፥ ይህን ምሥጢር ከጥበበኞችና ከዐዋቆች ሰውረህ ለሕፃናት ገልጸኸዋልና አመሰግንሃለሁ። አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲሁ ሆኖአልና። ሁሉም ከአባቴ ዘንድ ተሰጠኝ፣ ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቀው የለም፤ አብንም ከወልድ በቀር፥ ወልድም ሊገልጥለት ከሚፈቅደው በቀር የሚያውቀው የለም። እናንተ ደካሞች፥ ሸክማችሁም የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ፤ ከእኔም ተማሩ፤ እኔ የዋህ ነኝና፤ ልቤም ትሑት ነውና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍትን ታገኛላችሁ። ቀንበሬ ልዝብ፥ ሸክሜም ቀላል ነውና። መልእክታት ሮሜ13:1-11 1 ጴጥሮስ 2:13-ፍጻሜ ሐዋ፡ሥራ 7:44-54 ምስባክ                   መዝሙር 67:25-26 በጽሑ መላእክት ወቦሙ መዘምራን ማዕከለ ደናግል ዘባጥያተ ከበሮ በማኅበር ባርክዎ ለእግዚአብሔር ትርጉም አለቆች ደረሱ መዘምራንም አሏቸው ከበሮን በሚመቱ በደናግል መካከል እግዚአብሔርን በጉባኤ አመሰገኑት
664
12
በአካለ ሥጋ የሞተን ሰው መመለስ እንደማንችል እያወቅን ከልባችን የምናለቅስ ከኾነ፥ የመዳን ተስፋ ያለውንና በነፍሱ ለሞተ (ለኃጢአተኛ) ሰው አለማልቀሳችን እንደ ምን ያለ ስንፍና ነው? ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
571
13
#ቃለ_ወንጌል 22/11/2018                 ማርቆስ 13:14-21       “ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፥ በሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይውረድ ከቤቱም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይግባ፥ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ። በዚያን ወራትም ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው። ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤ በዚያን ወራት እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያልሆነ ደግሞም የማይሆን የመከራ ዓይነት ይሆናልና። ጌታስ ወራቶቹን ባያሳጥር፥ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም፤ ነገር ግን ስለ መረጣቸው ምርጦች ወራቶቹን አሳጠረ...... 2 ቆሮንጦስ 12:1-11 1 ጴጥሮስ 1:6-10 ሐዋ.ሥራ 5:26-34                        ምስባክ                  መዝሙር 15:4-5 ወኢይትኀበር ውስተ ማኅበሮሙ ዘደም ወኢይዜከር አስማቲሆሙ በአፉየ እግዚአብሔር መክፈልተ ርስትየ ወጽዋዕየ ትርጉም በደም ማኅበራቸው አልተባበርም ስማቸውንም በአፌ አልጠራም እግዚአብሔር የርስቴ ዕድል ፋንታና ጽዋዬ ነው።
770
14
የእግዚአብሔር ምሕረት ያስደንቃል። ያደረግነውን ብቻ አይደለም ይቅር የሚለን። የማይገባንን ገነትም ይሰጠናል!!!
538
15
+ ሰውማ እናታችን ጽዮን ይላል + ሰው በምድር ላይ ያቃተው ነገር ቢኖር ሰው መሆን ብቻ ነው:: ብዙ ነገር መሆን ችሎአል:: እንደ አሣ በባሕር እንደ ወፍ በሰማይ በርሮአል:: እንደ እንስሳ መኖር ችሎአል እንደ አውሬም መጨከን ተሳክቶለታል:: እንደ ንስር ከሩቅ አይቶአል:: እንደ ውኃ ሰርጎ ብዙ ተመራምሮአል:: ለብዙ ሰው የከበደው ነገር ቢኖር ሰው መሆን ነው:: አንዱ ወደ አንድ አባት ቀረብ ብሎ "ድንግል ማርያም እኮ እንደ እኛ ሰው ናት" አላቸው። እርሳቸውም "ልክ ነህ እርስዋ በተፈጥሮዋ  ሰው ናት ፣ አንተ ግን ሰው ነህ?" አሉት። ነገሩ ስድብ ይመስላል ፣ አስተውሎ ላየው ግን ሰው ነኝ ለማለትም መሥፈርት እንዳለው ያስታውሳል። "ኤልያስ እንደ እኛ ሰው ነበረ" ነገር ግን ዝናምን በጸሎቱ ያቆመ መሆኑን ስንሰማ ግን እኛም እንደርሱ ሰው ነን ለማለት እንፈራለን።  ንጉሥ ዳዊት ለልጁ ሰሎሞን "ሰው ሁን" ያለው ሰው መሆን ማለት እንደ ሰው ክብርን አውቆ መኖር ስለሆነ ነው። ክቡር ሆኖ ሳለ ካላወቀና በኃጢአቱ ከጸና እንደሚጠፉ እንስሳት ይመስላል። ሰው በምድር ላይ ያቃተው ነገር ቢኖር "ሰው መሆን ነው"!  አዋቂ መሆን ቀላል ነው! ኃያል መሆንም ይቻላል:: ባለ ጥበብ መሆንና መራቀቅም ይቻላል:: ጀግና መሆንም እንዲሁ:: ሰው ያቃተው ሰው መሆን ብቻ ነው:: ሰው መሆን ትልቅ ዋጋ አለው:: ይህንን ዋጋ ስንዘነጋ በአርኣያ ሥላሴ ለተፈጠረው ሰው ሌላ ሚዛን እንፈልግለታለን:: ሰውነቱን ትተህ በሀብቱ በእውቀቱ በዘሩ በቋንቋው ከመዘንከው አንተም ሰውነትህን ታጣለህ:: ሰው ለመሆን ብዙ መሥፈርቶች በመጽሐፍ ቅዱስ  ተቀምጠዋል ፣ የድንግል ማርያምን እናትነት መቀበልም ሰው የመሆን ምልክት ነው።  "ሰው እናታችን ጽዮን ይላል" ተብሎ እንደተጻፈ "ጽዮን እናታችን" ማለት ያልቻለ ምኑ ሰው ይባላል? በውስጥዋም ሰው ተወለደ የተባለው ስለ ጌታ ነው:: እሱን የሚመስሉ እውነተኛ ክርስቲያኖችም  ሰዎች ናቸው:: ሰው ከሆንክ "እናታችን ጽዮን" ትላለህ:: ጽዮንን "እናታችን" ብሎ ለመጥራት ግን "ወንድሜ ወንድሜ" መባባል ይቀድማል:: ይህን ማለት ያልቻለ ግን ሰው አይደለም:: ጽዮንም እናቱ አይደለችም:: ነቢዩ በባቢሎን ሆኖ ስለ ጽዮን ሲያስብ መዝሙር ለመዘመር ተቸግሮ ነበር::  "በባቢሎን ወንዞች አጠገብ በዚያ ተቀመጥን" ብሎ ነበር:: እኛም የአንዲትዋ የጽዮን ልጆች ሆነን በተለያየንበት ዘመናችን እንዲህ እንላለን :- በዘረኝነት ወንዝ ውስጥ ሆነን አክሱም ጽዮንን ባሰብናት ጊዜ አለቀስን የማረኩን ኃጢአቶቻችን ሳንላቀቃቸው የዝማሬ ቃል ፈለጉብን የእግዚአብሔርን ዝማሬ እንዴት በጥላቻ ልብ እንዘምራለን? የጽዮንንስ ዝማሬን ቂምና በቀል አርግዘን እንዴት እንዘምራለን? ታቦተ ጽዮን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ባላስብሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ከዘር ከነገዴ በላይ ቤተ ክርስቲያንን ባልወድድ! እናታችን ጽዮን ሆይ እባክሽን አንቺን እናታችን ብለን ሰው ለመሆን አብቂን:: ከራሳችን ጠብቂን የጥላቻን ዳጎን ሰባብሪልን::  ፍልስጥኤማውያን በአንቺ ግርማ የተነሣ ፈርተው የዳጎን መድረክን እንዳልረገጡት እልቂትና ደም መፋሰስ በአማላጅነትሽ የኢትዮጵያን ምድር አይርገጥ:: እንደ ጣዖት በልባችን የነገሠውን ክፋት ሰባብረሽ ከእግርሽ በታች አድርጊልን:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! ይህ በየቀኑ የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች የሚለቀቅበት ቻናል ነው ይቀላቀሉ 👇👇👇 @dnhenok_haile @dnhenok_haile
561
16
#ቃለ_ወንጌል 21/11/2017                          ማቴዎስ 19:1-16       ጌታችን ኢየሱስም ይህን ነገር ከፈጸመ በኋላ ከገሊላ ተነሥቶ ወደ ይሁዳ አውራጃ ወደ ዮርዳኖስ ማዶ ደረሰ። ብዙዎች በሽተኞችም ተከተሉት፤ በዚያም ፈወሳቸው። 'ፈሪሳውያንም ሊፈትኑት ወደ እርሱ መጥተው፥ “በማናቸውም በበደለችው ሁሉ ሚስቱን ሊፈታ ለሰው ይገባልን?” አሉት። እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው፥ “አላነበባችሁምን? በመጀመሪያ የፈጠራቸው እርሱ ወንድና ሴት አደረጋቸው።” እንዲህም አለ፥ “ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ትቶ ሚስቱን ይከተላል፤ ሁለቱም አንድ አካል ይሆናሉ። እንኪያስ ሁለት አይደሉም፤ አንድ አካል ናቸው እንጂ፤ እግዚአብሔርም አንድ ያደረገውን ሰው አይለይ።” እነርሱም፥ “እንኪያ የፍቺዋን ደብዳቤ ሰጥተው እንዲፈቱአት ሙሴ ለምን አዘዘ?” አሉት። እርሱም አላቸው፥ “ሙሴስ ስለ ልባችሁ ክፋት ሚስቶቻችሁን እንድትፈቱ ፈቀደላችሁ፤ ቀድሞ ግን እንዲህ አልነበረም። "እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ አመንዝራ ያደርጋታል፤ የተፈታችውንም ያገባ ያመነዝራል።” ደቀ መዛሙርቱም፥ “የባልና የሚስት ሥርዐት እንዲህ ከሆነስ መጋባት መልካም አይደለም” አሉት። “እርሱም አላቸው፥ “ይህ ለተሰጠው ነው እንጂ ለሁሉ የሚቻል አይደለም። «ከእናታቸው ማኅፀን እንዲሁ የተወለዱ ጃንደረቦች አሉና፤ ሰዎች የሰለቡአቸውም ጃንደረቦች አሉ፤ ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን ጃንደረባ ያደረጉ አሉ፤ መታገሥ የሚችል ግን ይታገሥ።” "ከዚህም በኋላ እጁን በላያቸው ጭኖ ይጸልይ ዘንድ ሕፃናትን አመጡለት፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ተቈጡአቸው። “ጌታችን ኢየሱስም፥ “ሕፃናትን ተዉአቸው፤ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና” አላቸው። እጁንም በላያቸው ጫነባቸውና ከዚያ ሄደ። መልእክታት ኤፌሶን 6:10-19 1 ዮሐንስ 5:1-6 ሐዋ፡ሥራ 8:26-ፍጻሜ ምስባክ                   መዝ· ፵ : ፩ – ፪ ብፁዕ ዘይሌቡ ላዕለ ነዳይ ወምስኪን እምዕለት እኪት ያድኅኖ እግዚአብሔር እግዚአብሔር የዐቅቦ ወያሐይዎ ወያበዕዖ ዲበ ምድር ትርጉም ለድሃና ለምስኪን የሚያስብ ብፁዕ ነው እግዚአብሔር ከክፉ ቀን ያድነዋል እግዚአብሔር ይጠብቀዋል፥ ሕያውም ያደርገዋል፥ በምድር ላይም ያስመሰግነዋል
728
17
#እግዚአብሔር! እግዚአብሔር የምድር ኃያላን ሁሉ የማይደርሱበት ከፍ ያለ አምላክ ነው፡፡(መዝ ፻፴፰፥፮) እንደ ሰናዖር ሰዎች ጡብ ከምረህ እስከ ሰማይ የሚደርስ ግንብ ብታቆም የልብሱን ጫፍ አታየውም፡፡ በየትኛውም መንኮራኩር ተጭነህ ሽቅብ ብትነጉድ ፍለጋውን አታገኘውም፡፡ በትዕቢት የምታደርገው ማንኛውም ዓይነት መንጠራራት ወደ ታች ያወርድህ እንደ ሆነ እንጂ ወደ ላይ አያወጣህም፡፡ ኀነገር ግን በትሕትና ራስህን ዝቅ ስታደርግ ያን ጊዜ እርሱም በፍቅር ዘንበል ይልልሃል፡፡ በልዕልና ከፍ ያለው እግዚአብሔር የሚታየው ዝቅ ዝቅ ለሚሉ እና የተዋረደ መንፈስ ገንዘብ ላደረጉ ትሑታን ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ራሱን በመካድ እና በትሕትና ስለኖረ ጌታውን ከአጠገቡ ቆሞ ያየው ነበር፡፡(ሐዋ ፳፯፥፳፫) #ቅዱስ_ጳውሎስ_ገጽ_169
582
18
#ቃለ_ወንጌል 20/11/2018                          ማቴዎስ 22:23-34      በዚያችም ቀን ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጡ። እንዲህም ብለው ጠየቁት፥ “መምህር ሆይ፥ ሙሴ ልጅ ሳይወልድ የሞተ ሰው ቢኖር ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካለት ብሎአል። እንግዲህ ሰባት ወንድማማቾች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ታላቁም ሚስት አገባና ልጅ ሳይወልድ ሞተ፤ ለወንድሙም ሚስቱን ተወ። እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው፥ ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ። ከሁሉም በኋላ ያቺ ሴት ሞተች። እንግዲህ ሙታን በሚነሡበት ጊዜ ከሰባቱ ለማንኛው ሚስት ትሆናለች? ሁሉም አግብተዋት ነበርና።” ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፥ “መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ባለማወቅ ትስታላችሁ። "ሙታንስ በሚነሡበት ጊዜ በሰማያት እንደ እግዚአብሔር መላእክት ሆነው ይኖራሉ እንጂ አያገቡም፤ አይጋቡምም። ስለ ሙታን መነሣት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ እንዲህ ተብሎ የተነገረውን አላነበባችሁምን? እኔ እግዚአብሔር የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንግዲህ የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም።” ሕዝቡም ሰምተው ትምህርቱን አደነቁ:: #መልእክታት 1 ቆሮንጦስ 13:33-51 ያዕቆብ 4:11-ፍጻሜ ሐዋ.ሥራ 23:22-ፍጻሜ                                  ምስባክ                            መዝሙር 12:3-4 ነጽረኒ ወስምዐኒ እግዚኦ አምላኪየ አብርሆን ለአዕይንትየ ከመ ኢይኑማ ለመዊት ወከመ ኢይበሉኒ ጸላእትየ ሞዕናሁ
846
19
"ጌታ ሆይ እርሻውን አቃጥለህ ሰብሉን ብትባርክ ምን ይጠቅማል? ዛፉንስ ቆርጠህ ቅርንጫፉን ብትባርክ ምን ይረባል? እናቴ እርሻ ናት እኔ ሰብል ነኝ:: እናቴ ዛፍ ናት እኔ ቅርንጫፍ ነኝ:: እባክህን እናቴ ብትክድ እኔ ባምን ምን ይጠቅማል:: ጌታ ሆይ የእናቴን ልብ በሃይማኖት አጽናልኝ" (ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ስለ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ የጸለየው ጸሎት) ቅዱስ ቂርቆስ ሆይ አንተ ሕፃን ሆነህ ትልቅ ነበርክ:: ትልቅ ሆነን ሕፃን የሆንን እኛን በምልጃህ አስበን! "የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል" መዝ 19፥7 እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርዔል አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ። ዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ
497
20
🌼🌼🌼እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርዔል አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።🌼🌼🌼
🌼🌼🌼እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርዔል አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።🌼🌼🌼
640