fa
Feedback
Dilla Don Bosco ICT Center Digital Library

Dilla Don Bosco ICT Center Digital Library

رفتن به کانال در Telegram

A place where you get Student Text and Reference Books

نمایش بیشتر
374
مشترکین
+124 ساعت
+47 روز
+1930 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '24
سپتامبر '24
+27
در 0 کانال‌ها
اوت '24
+22
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+19
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+14
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+13
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+17
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+22
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+369
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
20 سپتامبر+3
19 سپتامبر+2
18 سپتامبر0
17 سپتامبر+1
16 سپتامبر0
15 سپتامبر+1
14 سپتامبر+3
13 سپتامبر+3
12 سپتامبر0
11 سپتامبر+1
10 سپتامبر+2
09 سپتامبر+1
08 سپتامبر+1
07 سپتامبر+1
06 سپتامبر0
05 سپتامبر+1
04 سپتامبر+1
03 سپتامبر+3
02 سپتامبر+1
01 سپتامبر+2
پست‌های کانال
2
#ምስጋና በፊስ ቡክ ገፅ #በBejai_Nerash_Naiker በተዘጋጀው 7ኛ mission 100k ነጻ የፍሬ ፈንድ የመምህራን የቢዝነስ ሀሳብ ውድድር ላይ እንድሳተፍ ሜንሽን ያደረጋችሁኝ: 1ኛ የስራ+1
#ምስጋና በፊስ ቡክ ገፅ  #በBejai_Nerash_Naiker በተዘጋጀው 7ኛ mission 100k ነጻ የፍሬ ፈንድ የመምህራን የቢዝነስ ሀሳብ ውድድር ላይ እንድሳተፍ ሜንሽን ያደረጋችሁኝ: 1ኛ የስራ ባልደረባዬ እና የምሰራቸውን ስራዎች ሁሌ የሚያበረታኝ  መ/ር #ግርማ_ታደሰ 2ኛ እየሰራሁ ያለሁት #የህፃናት_የኮዲንግ_ስልጠና በጣም አስፈላጊ እንደሆነ እና በሀሳብ የምትደግፈኝ ውዷ እህቴ #ሄለን_ጌታሁን ከካናዳ። 3ኛ ሀሳቡ ለሌሎች እንዲዳረስ በፌስ ቡክ ገፅ ሼር ያደረጋችሁ ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ 4ኛ ያቀረብኩትን ሀሳብ የወደዳችሁት እንዲሁም በጣም ገንቢ ሀሳብ የሰጣችሁኝ ውድ ወንድሞቼ፣እህቶቼ እና ተማሪዎቼ። #እጅግ_በጣም_አድርጌ_አመሰግናለሁ። እግዚአብሔር ይስጥልኝ ። በቀጣይ የጀመርኩትን #የህፃናት_የኮዲንግ_ስልጠና በተጠናከረ ሁኔታ እንድሰራ ይህ ውድድር ትልቅ ብርታት  ነው የሆነልኝ። በ2013 ዓ.ም ስልጠናውን ስጀምር ለረጅም ጊዜ ሳስበው እና ስመኘው የነበረ ነበር አሁን ላይ አብዛኛው የት/ቤታችን ተማሪዎች ስለ #ኮዲንግ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ሆኖል። ሶፍትዌር ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆን መስራት እንደሚቻል ስልጠናው ግንዛቤ ፈጥሯል። ከሁለት ሳምንት በፊት ደግሞ አራተኛ ዙር በ45 ተማሪዎች ስልጠናው ተጀምሯል። ስልጠናው በእስከ አሁኑ ጉዞ የተሳካ እንዲሆን ለደገፉችሁኝ የካማራ ኤዱኬሽን ኢትዮጵያ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች፣ የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ማኔጅመንት፣መምህራን፣ጓደኞቼ፣ወላጆች እና ተማሪዎቼ ከልብ አመሰግናለሁ። #መልካም_የገና_በዓል_ይሁንላችሁ አመሰግናለሁ
0
3
ውድድሩ ቅዳሜ ታህሳስ 27/2016 ዓ.ም ምሽት 1:00 ይጠናቀቃል። በቀረበው #ሀሳብ ላይ #ብቻ_ኮሜንት_እና_ላይክ አድርጉ። ውድ ጓደኛዬ መሀሪ አመሰግናለሁ 🙏 ለዚህ ልበ ቀና ወንድማችን ለብዙዎች እንዲተርፍ የተሻለ እንዲሰራና እንዲበረታታ ላይክና ኮሜንት በማድአግ እንተባበር። ወንድማችን መምህር አንዱአለም 100,000 ብር ሽልማት በሚያስገኝ ውድድር ላይ #coding_for_kids ብሎ እየተወዳደረ ይገኛል። ውድድሩ #በlike እና #comments ብዛትና መመጣጠን ላይ የተመሰረተ በመሆኑ የእኛን ድጋፍ በእጅጉ ይፈልጋል። አንዱ በዲላ ዶንቦስኮ ት/ቤት ተማሪዎችን በራሱ ተነሳሽነት ኮዲንግ በማስተማር ሀገር አቀፍ ተወዳዳሪዎች እና ተሸላሚዎች ማድረጉ ይታወሳል። ታታሪው አንዱ ከትምህርት ቤት ውጪ በራሱ ይህንን የኮዲንግ ትምህርት ቤት ቢከፍት ደግሞ ይህንን እድል ላላገኙ ልጆቻችን፣ እህት ወንድሞቻችን እድሉን እንዲያገኙ ይረዳቸዋል። እንደምታውቁት መጪው ጊዜ የቴክኖሎጂ እንደመሆኑ ትውልዱን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያገናኝ እንደ መምህር አንዱአለም ያለን ታታሪ በመደገፍ ዲላና አካባቢዋ ላይ ያሉ ልጆቻችን የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እናድርግ። ከኛ የሚጠበቀው ነፃ የሆነው #ላይክ_እና #ኮሜንታችን አንድ ላይ ነው። በውድድሩ ስር #Andualem_Tsegaye #Zeleke ባስቀመጠው የመወዳደርያ ሀሳብ ላይ በመሄድ ሪአክት ( #ላይክ፣❤) ማድረግ እና #ኮሜንት ላይ የሚያበርታውን ነገር መፃፍ( በርታ ፣ good luck) #ላይክ እና #ኮሜንት አንድ ላይ አንድ ድምፅ ማለት ነው። #ሊንኩን ከታች👇 አስቀምጫለሁ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=7070810486329832&id=100002028524680&mibextid=Nif5oz
0
4
አመሰግናለሁ መሀሪ🙏 ለዚህ ልበ ቀና ወንድማችን ለብዙዎች እንዲተርፍ የተሻለ እንዲሰራና እንዲበረታታ ላይክና ኮሜንት በማድአግ እንተባበር። ወንድማችን መምህር አንዱአለም 100,000 ብር ሽልማት በሚያስገኝ ውድድር ላይ coding for kids ብሎ እየተወዳደረ ይገኛል። ውድድሩ በlike እና comments ብዛትና መመጣጠን ላይ የተመሰረተ በመሆኑ የእኛን ድጋፍ በእጅጉ ይፈልጋል። አንዱ በዲላ ዶንቦስኮ ት/ቤት ተማሪዎችን በራሱ ተነሳሽነት ኮዲንግ በማስተማር ሀገር አቀፍ ተወዳዳሪዎች እና ተሸላሚዎች ማድረጉ ይታወሳል። ታታሪው አንዱ ከትምህርት ቤት ውጪ በራሱ ይህንን የኮዲንግ ትምህርት ቤት ቢከፍት ደግሞ ይህንን እድል ላላገኙ ልጆቻችን፣ እህት ወንድሞቻችን እድሉን እንዲያገኙ ይረዳቸዋል። እንደምታውቁት መጪው ጊዜ የቴክኖሎጂ እንደመሆኑ ትውልዱን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያገናኝ እንደ መምህር አንዱአለም ያለን ታታሪ በመደገፍ ዲላና አካባቢዋ ላይ ያሉ ልጆቻችን የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እናድርግ። ከኛ የሚጠበቀው ነፃ የሆነው ላይክ እና ኮሜንታችን አንድ ላይ ነው። በውድድሩ ስር Andualem Tsegaye Zeleke ባስቀመጠው የመወዳደርያ ሀሳብ ላይ በመሄድ ሪአክት ( ላይክ፣❤) ማድረግ እና ኮሜንት ላይ የሚያበርታውን ነገር መፃፍ( በርታ ፣ good luck) ላይክ እና ኮሜንት አንድ ላይ አንድ ድምፅ ማለት ነው። ሊንኩን ከታች አስቀምጣለሁ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=7070810486329832&id=100002028524680&mibextid=Nif5oz
0
5
በህፃናት የኮዲንግ ስልጠና የበለጠ ለመስራት እየተወዳደርኩ ነው ሀሳቤን ከታች ባለው የፌስ ቡክ ገፅ እየገባችሁ በላይክ እና ኮሜንት ደግፉኝ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid035maiHMbCSKw8d7pnzKx6MAVW1NNnwmDtgR5X9zPVvu8oBFHp1pQEwo32mQfrsSLql&id=100002028524680&mibextid=Nif5oz
0
6
بدون متن...
0
7
አራተኛ ዙር የህፃናት የኮምፒውተር ኮዲንግ ስልጠና ተጀመረ። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሶስት አመታት ከ6-10 ክፍል ተማሪዎች ስልጠናው እየተሰጠ ነው ። እንዲህ አይነት ስልጠና በከተማው እና በክ+4
አራተኛ ዙር የህፃናት የኮምፒውተር ኮዲንግ ስልጠና ተጀመረ። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሶስት አመታት ከ6-10 ክፍል ተማሪዎች ስልጠናው እየተሰጠ ነው ። እንዲህ አይነት ስልጠና በከተማው እና በክልሉ ብቸኛ ሲሆን በአራቱ ዙር ስልጠና ከመቶ ሃምሳ በላይ ህፃናት ተጠቃሚ ሆነዋል። ሰልጣኞቹ መሰረታዊ ኮዲንግ በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር ይማራሉ። ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ስልጠናውን በጥሩ ውጤት ያጠናቀቁ ተማሪዎች በአፍሪካ ኮዲንግ ቻሌንጅ ውድድር እየተሳተፉ ይገኛሉ። በ2023 በተደረገው ውድድር በኢትዮጵያ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ያገኙት በ2014 ዓ.ም ስልጠናውን የወሰዱ ተማሪዎች ነበሩ። በአራተኛው ዙር ስልጠና አርባ አምስት ህፃናት ከመስቀለ እየሱስ፣ዋለሜ ዶን ቦስኮ፣አቡነ ጎርጎሪዮስ፣ዲላ ዩኒቨርስቲ ኮሚዩኒቲ እና ዲላ ሁለተኛ ትምህርት ቤቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ። በእራስ ተነሳሽነት የተጀመረው ስልጠና በአሁን ሰዓት አብዛኛው የትምህርት ቤቶቻችን ተማሪዎች ስለ ኮዲንግ ፅንሰ ሀሳብ እንዲኖራቸው አድርጓል። በተጨማሪም የሶፍትዌር ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆኑ ፈጣሪም መሆን እንደሚቻል አሳይቷል። በሀሳብ ለደገፉችሁኝ እና ላበረታታችሁኝ የትምህርት ቤታችን አስተዳደር፣መምህራን፣ወላጆች፣የቀድሞ ተማሪዎቼ ፣ጎደኞቼ፣ የካማራ ኤዱኬሽን ኢትዮጵያ የስራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ከልብ አመሰግናለሁ። መ/ር አንዱአለም ዲላ ዶን ቦስኮ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢ.ቴ.ማ
0
8
የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን👇 በታሪክ አጋጣሚ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲን የተቀላቀሉት ሶስቱ መንትዮች ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው። *** የአብ+2
የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን👇 በታሪክ አጋጣሚ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲን የተቀላቀሉት ሶስቱ መንትዮች ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው። *** የአብቃል አበበ፣ የአብፀጋ አበበ እና የአብስራ አበበ የተሠኙት ሶስት መንትዮች በ2015 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ የተሠጠዉን የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና እያንዳንዳቸዉ ከ340 በላይ የሆነ ዉጤት በማምጣት ሶስቱም መንትያሞች አዲስ አበባን ዩንቨርሲቲን ተቀላቅለዋል። ዩንቨርሲቲዉ በዛሬዉ ዕለት ደማቅ ዝግጅት አዘጋጅቶ አዲስ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ሲሆን ተማሪዎችም በለተደረገላቸዉ ልዩ አቀባበል ዕጅጉን መደሰታቸዉን ገልፀዋል። በቀጣዮቹ አምስት ቀናትም አዲስ ተማሪዎችን ማዕከል ያደረጉ ልዩ ዝግጅቶች በዩንቨርሲቲዉ ይካሄዳሉ። ######################## AAU Celebrates as it Admits Historic Triplets *** Today, Yabkal Abebe, Yabtsega Abebe and Yabsira Abebe joined AAU after successfully passing the 2023 school leaving national examinations. Each of the triplets scored more than 340 points on the highly competitive national examinations. The triplets expressed their joy over the unique and colourful ceremony welcoming them to the university. This year AAU is organizing events colourfully welcoming fresh undergraduate students.
0
9
በቴሌግራም መመዝገብ ይቻላል ስልጠናው ታህሳስ 13/2016 ዓ.ም 2:00 ሰዓት ይጀምራል። የተማሪውን ስም የክፍል ደረጃ እና ትምህርት ቤት በሚከተለው አድራሻ ይላኩልን ቴሌግራም አድራሻ: @anduic
በቴሌግራም መመዝገብ ይቻላል ስልጠናው ታህሳስ 13/2016 ዓ.ም 2:00 ሰዓት ይጀምራል። የተማሪውን ስም የክፍል ደረጃ እና ትምህርት ቤት በሚከተለው አድራሻ ይላኩልን ቴሌግራም አድራሻ: @anduict ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ
0
10
بدون متن...
0
11
በያሳምንቱ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ዜናዎችን ለማግኘት በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክበብ የተዘጋጀውን ክሊክ ዶን ቦስኮ የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ።👇
0
12
አራተኛ ዙር የህፃናት ኮዲንግ ስልጠና ምዝገባ ተጀመረ። ቀናት: ከህዳር 27 እስከ ታህሳስ 11/2016 ዓ.ም ቦታ: ዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ክፍል ደረጃ: ከ6ኛ እስከ 10ኛ ክፍል+1
አራተኛ ዙር የህፃናት ኮዲንግ ስልጠና ምዝገባ ተጀመረ። ቀናት: ከህዳር 27 እስከ ታህሳስ 11/2016 ዓ.ም ቦታ: ዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ክፍል ደረጃ: ከ6ኛ እስከ 10ኛ ክፍል #ስልጠናው_ታህሳስ_አስራ_ሶስት 2:00 #ሰዓት_ይጀምራል አዘጋጅ: የዲላ ዶን ቦስኮ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል
0
13
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_ደስ_አለን #Congratulations በት/ቤታችን በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት 604 የተመዘገበው በተማሪ #ሮብሰን_መርጊያ ሲሆን ከ 504-586 ውጤት ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የሚከተሉት ናቸው። የሁሉንም ተማሪዎች መረጃ በኔት ወርክ መጨናነቅ ማግኘት አልተቻለም ውጤቱ ከዚህ ከፍ ሊል ይችላል። #ተፈጥሮ_ሳይንስ 1.  ይሁን አበበ  586 2.  ሱራፊል እንዳለ  573 3. ሌንጂሳ አብረሃም 567 4. ምናለ ቸሩ   552 5. ምንተስኖት አበበ 533 6. ፍላጎት በቀለ  530 7.  ኤልዳና ሙሉጌታ  525 8. ነብዩ ዳንኤል 504 #በማህበራዊ_ሳይንስ 1. ያብቃል አበበ 471 2. ሰሎሜ ታደሰ 442   በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ      ▶️ ተማሪዎች      ▶️ መምህራን      ▶️ ወላጆች እና      ▶️ የት/ቤቱ አስተዳደር በቀጣይ የሁሉንም ተፈታኝ ጠቅላላ ውጤት እናሳውቃለን ICT & E-learning Center
0
14
بدون متن...
0
15
የቀድሞ፣የአሁን የዲላ ዶን ቦስኮ ት/ቤቶች መምህር፣ተማሪ፣ አስተዳደር ሰራተኛ ወይም የት/ቤቶቹ አድናቂ ነዎት? ስለ ት/ቤቶቹ ☑️ የቀድሞ ፎቶዎች ☑️ ስኬታማ የሆኑ የት/ቤቶቹ ተማሪዎች መሳጭ ታሪክ
የቀድሞ፣የአሁን የዲላ ዶን ቦስኮ ት/ቤቶች መምህር፣ተማሪ፣ አስተዳደር ሰራተኛ ወይም የት/ቤቶቹ አድናቂ ነዎት? ስለ ት/ቤቶቹ ☑️ የቀድሞ ፎቶዎች ☑️ ስኬታማ የሆኑ የት/ቤቶቹ ተማሪዎች መሳጭ ታሪክ ☑️ የተለያዩ ቪዲዮዎች ☑️ ስለ ት/ቤቶቹ አጭር ታሪክ ☑️ ስለ ር/መምህራን እና መምህራን       ስራዎች ☑️አሁናዊ የት/ቤቶቹ ስራዎች የሚያገኙበትን የፊስ ቡክ ገፅ እንተቁመዎ👇👇 https://www.facebook.com/groups/715959666071910/?ref=share
0
16
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ፤ ከመስረም 7 እስ+1
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ፤ ከመስረም 7 እስከ 11 ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል። መስከረም 14 የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል። በተመሳሳይ በዛው ዕለት የሬድዮ እና የቴሌቪዥን ትምህርት ስርጭት ይጀምራል። የ1ኛ ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና ከጥር 27 እስከ የካቲት 1 እንደሚሰጥ የሚያሳየው የትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር ከየካቲት 4 እስከ 8 ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ዝግ ሆነው የተማሪዎች ፈተና የሚታረምበት ውጤት የሚጠናቀርበትና የሚገለፅበት ወቅት እንደሆነ ገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር እንደሚያሳየው የካቲት 18 የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርት መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ከግንቦት 12 እስከ ግንቦት 23 የአጠቃላይ የትምህርት ማጠቃለያ (የ12ኛ ክፍል) ፈተና ይሰጣል። ከግንቦት 26 እስከ 30 የ6ኛ ክፍል አንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 3 እስከ 7 የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ የማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና ጊዜ እንደሚሆን ይፋ ተደርጓል። የሁለተኛ ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና ወቅትም ከሰኔ 17 እስከ 21 ሲሆን ከሰኔ 24 - 28 ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ዝግ ሆነው ፈተና የማረም፣ ውጤር የሚጠናቀርበት ፣ እና የሚገለፅበት እንደሚሆን ካሌንደሩ ያሳያል። ሰኔ 30 ወላጆች እና የትምህርት ማህበረሰቡ በተገኙበት የአመቱ ትምህርት ማጠናቀቂያ ይሆናል። * * * ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ እንደሚደረግ ማሳስቢያ ሰጥቷል።
0
17
የዲላ ዶን ቦስኮ መስቀለ ኢየሱስ ትምህርት ቤት ር/መምህር መልዕክት ለ2016 ዓ.ም አዲስ አመት። የትምህርት ቤታችን መምህራን፡ ተማሪዎች ና ወላጆች በሙሉ። እንኳን 2016 ዓ፡ም በሰላም አደረሳችሁ።
የዲላ ዶን ቦስኮ መስቀለ ኢየሱስ ትምህርት ቤት ር/መምህር መልዕክት ለ2016 ዓ.ም አዲስ አመት። የትምህርት ቤታችን መምህራን፡ ተማሪዎች ና ወላጆች በሙሉ። እንኳን 2016 ዓ፡ም በሰላም አደረሳችሁ። አንተ ግን ያው አንተ ነህ ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም። መዝ 101(102)፥27 ። አዲሱ ዓመት የሰለም ፣ የጤና ፣ የፍቅር የደስታ  ዓመት እንድሆንለችሁ እመኛለሁ። 🌼🌼መልካም አዲስ አመት🌼🌼
0
18
🌼 በአዲስ አመት አዲስ ነገር 🌼 ከተመሰረተ 13ኛ ዓመቱን የያዘው አንጋፉው የት/ቤታችን ኢኮቴ / ICT/ ክበብ ዘወትር ሐሙስ በሚኒ ሚዲያ የሚተላለፈው ክሊክ ዶን ቦስኮ የቴክኖሎጂ ዜናዎች እና ፕሮግራሞችን አዲስ በተከፈተው የቴሌግራም ቻናል ወቅታዊ የሆኑ የቴክኖሎጂ መረጃዎችን እንደሚያቀርብላችሁ ሲገልፅ በደስታ ነው። ቻናሉን ይቀላቀሉ ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ።       🌼መልካም አዲስ አመት🌼 የቻናሉ ሊንክ ከታች አለላችሁ👇
0
19
#ባለውለታዎቻችን_ነገር_ግን_ውለታቸው_ያልተከፈላቸው #ትምህርትቤቶቻችን!!! በዲላ እና አከባቢው ያሉ ተማሪዎችን በስነ ሞግባር እና በእውቀት በማነፅ ትልቅ ድርሻ በመወጣት ካሉ ት/ቤቶች መካከል የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤቶቹ የዶን ቦስኮ ት/ቤቶች ግንባር ቀደሞቹ ናቸው። ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር የጀመሩበት አመታት: 1.የመስቀለ እየሱስ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት     በ1958 ዓ.ም 2. የዶን ቦስኮ ዋለሜ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት     በ1980ዓ.ም 3.  ዶን ቦስኮ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ1991       ዓ.ም በነዚህ ት/ቤት በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች በመማር በአሁን ሰዓት በውጪ እና በሀገር ውስጥ በተለያዩ የሙያ መስክ በስራ ተሰማርተው ይገኛሉ። በት/ቤቶቹ የ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እጅግ በጣም አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ በየዓመቱ ወደ ቀጣዩ ክፍል ያልፋሉ። ለአብነት በ2014 ዓ.ም እንደ ሀገር ከ 1000 በላይ ት/ቤቶች ምንም ተማሪ ባላሰለፉበት፤ ከ900,000 ተፈታኞች ተማሪዎች 30,0000 ተማሪዎች ብቻ ባለፉበት፤በዲላ ከተማ ካሉ 6 ት/ቤቶች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው የዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ነበር። በዳላ ከተማ 6ቱ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከ 1700 በላይ  ተማሪዎች ያስፈተኑ ሲሆን 5ቱ ት/ቤቶች በአጠቅላይ ያሳለፉት የተማሪዎች ቁጥር 39 ሲሆን የእኛ ት/ቤት ግን ከ154 ተማሪዎች 75 ተማሪዎችን አሳልፏል። ይህም በከተማው ብሎም በዞኑ ከፍተኛ ውጤት ነው። አስተዳደሩም ይሁን መምህራን ተማሪዎቻቸውን ቤተሰባው በሆነ እንክብካቤ ስነ ምግባራቸውን እና የተሻለ እውቀት በመስጠት ይተጋሉ። ነገር ግን በከተማው ህብረተሰብ፣የተለያዩ ቢሮዎች እና ተማሪዎች የሚጠበቀውን ያክል እውቅና እና ድጋፍ ሲደረግላቸው አይታይም። እንዳውም አሁን አሁን    ት/ቤቶቹን መውቀስ እና መክሰስ የተለመደ ሆኗል። በመላው ሀገሪቷ ያሉ የዶን ቦስኮ ት/ቤቶች የሚሰሩትን አይነት ስራ ነው እየሰሩ ያሉት። ካለው የክፍል ጥበት አንፃር ባለው ውስን ቦታ ተማሪን በመግቢያ ፈተና ፈትኖ ማስገባት በሌሎች ከተሞች ት/ቤቶችም የተለመደ ነው።  ተማሪዎቻችን በእውቀት እና በስነ ምግባር ታንፀው ለሀገር ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ መስራት የት/ቤቶቹ አላማ ነው ብዬ አስባለሁ። የቀድሞ የት/ቤቶቹ ተማሪዎች እና ወላጆች ት/ቤቶቹን መደገፍ እና እውቅና መስጠት ይኖርባችኋል መልዕክቴ ነው። በቡድንም ይሁን በተናጠል ት/ቤታችሁን ጓብኙ። ት/ቤቶቹ ሁሌም ለናንተ በራቸው ክፍት ነው። መጪው አመት የሰላም፣የፍቅር እና የስራ ይሁንልን። መልካም ጊዜን ተመኘሁ ጳጉሜ 2/2015 ዓ.ም ዲላ
0
20
List of Our School Telegram Channels👇
0