fa
Feedback
የኦርቶዶክስ ገድላት እና ድርሳናት

የኦርቶዶክስ ገድላት እና ድርሳናት

رفتن به کانال در Telegram
220
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
የጳውሎስ ኩረጃ ክፍል ፥ ፩ ፨ ጳውሎስ ብዙ ጊዜ ከመፀሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም ከመፀሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውጭም በጣም ብዙ ፁሁፎችን እንደቀዳ ይታወቃል። ጳውሎስ ክርስቲያኖች እንደሚያስቡት መንፈስ ቅዱስ እየነገረው ወይም እየገለጠለት ሳይሆን የሚፅፈው ከሚያቸውና ከሚሰማቸው እንዲሁም ከሚያነባቸው ነገሮች እየቀዳ ነበር። ለምሳሌ፦ሐዋሪያት ስራ 17፥23 ተመልከት። ለማንኛውም ከኩረጃዎቹ መካከል ዛሬ አንዱን እንይ፦ “መጽሐፍ፦ "#በእርሱ #የሚያምን #ሁሉ #አያፍርም" ይላልና።”   — ሮሜ 10፥11 “For the scripture saith, Whosoever believeth on him shall not be #ashamed.”   — Romans 10:11 (KJV) እንዲሁም በተመሳሳይ ሮሜ 9፥33 ላይ ይገኛል። ጳውሎስ ይሄንን ጥቅስ የወሰደው ከኢሳያስ መፀሐፍ ሲሆን የወሰደው ጥቅስ አሁን ካለው የኢሳያስ ጥቅስ ጋር ልዩነት ፈጥሯል። ጳውሎስ "shall not be ashamed"(አያፍርም)። የሚል ቃል ሲጠቀም ኢሳያስ ላይ ያለው ንባብ ደግሞ "shall not make haste"(አይፈጥንም/አይቸኩልም) ይላል። “Therefore thus saith the Lord GOD, Behold, I lay in Zion for a foundation a stone, a tried stone, a precious corner stone, a sure foundation: "#he #that #believeth #shall #not #make #haste".”   — Isaiah 28:16 (KJV)   በእርግጥ ኢሳያስ ላይ አማርኛ ተርጓሚዎች "አያፍርም" ብለውታል ነገር ግን የእብራይስጡ ቃል ፈፅሞ እንደዛ የሚል ፍቺ የለውም። እንግሊዘኛውም(KJV) "haste መቻኮል" በሚል ነው የፈታው። ሲቀጥል ይሄንኑ የእብራይጥ ቃል በ1954ቱ የአማርኛ መፀሐፍ ቅዱስ ትርጉም ላይ እዚህ ቦታ ላይ ብቻ ነው "አያፍርም" ብለው የፈቱት ሌላ ሁሉም ቦታ ላይ "መፍጠን፣መቸኮል..." ብለው ነው የፈቱት። ይሔንን በዚህ መልኩ ካየን ዕብራይስጡ ቅጂ "haste" እያለ ጳውሎስ ከየት አምጥቶ "ashamed" ሊለው ቻለ ለሚለው ጥያቄ መልሱ፥ ምክንያቱም ጳውሎስ ይሔንን ጥቅስ የገለበጠው ከዕብራይስጡ ባይብል ሳይሆን ከ"LXX" ማለትም ከሴፕቱጀንት ቅጂ ስለሆነ ነው። LXX ላይ ደግሞ "Ashamed" የሚለው ንባብ ይገኛል።   የሴፕቱጀንት ቅጂ ከ280BC አካባቢዎች  ጀምሮ ወደ ግሪክ ቋንቋ መተርጎም የጀመረ ቅጂ ነው።   ፥በውስጡም ዛሬ በፕሮቴስታንቶች ዘንድ ተቀባይነት የሌላቸውን የባይብል ክፍሎች ይዟል(እነ መፀሐፈ ሲራክ ፣ መቃቢያን ...) ፨፨ የራሳቸውን የባይብል ማብራሪያ ይመልከቱ፦ {11-13. For the scripture saith—in Isa 28:16, a glorious Messianic passage. Whosoever believeth on him shall not be ashamed—Here, as in Ro 9:33, "the quotation is from the Septuagint", which renders those words of the original, "shall not make haste" (that is, fly for escape, as from conscious danger), "shall not be put to shame," which comes to the same thing.} (Jamieson-Fausset-Brown Bible Commentary on rome 10:11) ፨ ይህ የባይብል ማብራሪያ ጳውሎስ "በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም"/"Whosoever believeth on him shall not be ashamed" የሚለውን ንባብ የወሰደው ከሴፕቱጀንቱ እንደሆነ ይነግረናል...። የዕብራይስጡም የሴፕቱጀንቱም ንባብ ተመሳሳይ ሐሳብ እንዳላቸው ለመናገር ቢሞክርም ጳውሎስ ጥቅሱን ከሴፕቱጀንት እንደወሰደው ይመሰክራል። የሚገርመው ነገር ጳውሎስ ጥቅሱን ሲገለብጥ በጣም በሚገርም ሁኔታ በግዴለሽነት በሚመስል መልኩ ሴፕቱጀንት ውስጥም እብራይስጡ ውስጥም የሌለ ቃል ጨምሮ ተናግሯል ፤ "whosoever" ወይም "πας" የሚለው ቃል በሴፕቱጀንቱም ቅጂ በእብራይስጡም ቅጂ ውስጥ የማይገኝ ቃል ነው። ፨የባይብል ማብራሪያዎችን ተመልከት፦    ፦"Expositor's Greek Testament"    ፦"vincent's word studies"   ይሄ የሚያሳየን ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንደማይፅፍ ይልቁንም ከቅጂዎች እየገለበጠ እንደሚፅፍ ሲፅፍም እንደሚሳሳት ነው። ~ በእውነቱ ይሔ የጳውሎስ ስህተት የተፈጠረው በኩረጃ ምክንያት ለመሆኑ ማሳያ አይሆንምን? ከፈጣሪ መገለጥ ቢሆን ኖሮ በትክክል መገልበጥ ይከብደው ነበርን? ፨ በእውነቱ ጳውሎስ እየተሳሳተ፣እየጨመረ እየቀነሰ ከሴፕቱጀንት ቅጂ የገለበጣቸውን ፁሁፎች ከአምላክ መገለጥ ናቸው ማለት ጥሩ ስራ ነውን?? ፨ ሲቀጥል ጳውሎስ ሲኮርጅበት የነበረው የሴፕቱጀንት ባይብል ወይስ የእብራይስጡ ባይብል ነው ትክክሉ ወይስ ራሱ ጳውሎስ ኮርጆ የፃፈው ፁሁፍ?? https://t.me/eotc_degl

ሥስት ቀንና ሥስት ሌሊት በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ እንደምታወቀው ኢየሱስ ሞቶ በሦስተኛው ቀን እና ሌሊት ተነስቶዋል ተብሎ በክርስትና እምነት ይታመናል ይሄንን አስመልክቶ ባይብል እንዲሂ ይላል “ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት #ቀንና ሦስት #ሌሊት ይኖራል።”   — ማቴዎስ 12፥40 በዚህ ጥቅስ መሰረት ኢየሱስ በምድር ውስጥ ሥስት ቀንና ሥስት ሌሊት እንደሚቆይ ያሳይ እንጂ ሞቶ ሶስት ቀንና ሌሊት ለመቆየቱ ምንም ምያሳየው ነገር የለም። ይልቁንስ ኢየሱስ ምድር ውስጥ መቆየቱን ምሳሌ የመጣው በዮናስ ነው ዮናስ በዓሣ ነባሪ ሆድ ሳይሞቶ ሥስት ቀንና ሌሊት ቆይቶዋል። ይህ ምሳሌ መምጣቱ ኢየሱስም ላለመሞቱን በቂ ማስረጃ ነው። ሞቶ ነበር ብንል እንዃን ኢየሱስ የሞተው በአርብ ቀን መሆኑን ቀጥሎ ባሉት ከቤተክርስቲያን መፅሀፍት ያሳይናል  👇 ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት 15 ይሁዳም መድኃኒታችንን ክርስቶስን አሳልፎ በመስጠቱ ስለ ተቀበለው ሠላሳ ብር ትንቢት ተናገረ ። መድኃኒታችንም በሚሰቀልበት ዐርብ ሌሊት ስለ ሐዋርያት መበተን ተናገረ ።  👇 መልክአ ቅዱሳን በአማርኛ 3 ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤ የትላንቱም የዛሬውም የነገውም አለኝታዬ አንተ ስለሆንክ። በዕለተ ዐርብ የእግርህ ደም እንደጎርፍ ውሀ በወረደ ጊዜ። ለተሰቀልክበት መስቀልህ ሰላም እያልኩ እጅ እነሣለሁ። ለላብነት ያክል እነዚህ ሁለትን የቤተክርስቲያን መፅሀፍት እንደሚያሳዩን ከሆነ የተሰቀለው አርብ መሆኑን ግልፅ አድርገው ያሳያሉ ነገር ግን አንዳንድ ክርስቲያኖች የተሰቀለው ሀሙስ ነው ብለው ውሃ መያነሳ ሙግት ይሞግታሉ ይሁን እንጂ የተሰቀለበት ሰዓት በአራቱ ወንጌላት የተለያየ ሰዓት መሆኑን ያሳያል ለምሳሌ ማቴዎስ 27:46 " ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ" ኢየሱስ ይሄንን ድምፅ የሰማበት ሰዓት ዘጠኝ ሰአት ነበረ ይላል ስለዚህ ዘጠነኛው ሰአት አልተሰቀለም። ዘጠነኛው ሰዓት ደሞ ካልተሰቀለ "ስድስት ሰዓትም ያህል ነበረ " የሚለውን ሉቃስ 23፥44 እና ማርቆስ 15:2⁵ በሰቀሉትም ጊዜ ሦስት ሰዓት ነበረ። ውድቅ ያረገዋል ምክንያቱም ሥስት ሰዓትና ስድስት ሰዓት ከዘጠኝ ሰዓት ስለምቀድሙ። የኔ ዋና ሀሳቤ ለምን ተለያዩ ሰይሆን ከነዚህ ሰዓታት ለምሳሌ ማርቆስ 15:2⁵ በሰቀሉትም ጊዜ ሦስት ሰዓት ነበረ። የምለውን እንውሰድ እና አንድ ሙሉ ቀን 12:00 -12:00 ስሆን ነው እንደማርቆስ አቆጣጣር የተሰቀለው ሥስት ሰዓት ነው። ቆጠራው ምጀምረው 3:00-12:00 ስለዚህ #አርብ ሙሉ ቀን ሰይሆን ዘጠኝ ሰዓት  ብቻ ነው። #አርብ ሌሊት ግን ሙሉ ነው። #ቅዳሜ ሙሉ ቀን ሙሉ ሌሊት እሁድ ደሞ ተነስቶዋል ለመነሳቱም ቀጥሎ ያለው የቤተክርስቲያን መፅሐፍት የሳያሉ  ድርሳነ ሚካኤል በአማርኛ 8 ወዳጆቼ ሆይ ዛሬ አነዚህ ሁለቱ በዓላት የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል በዓልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳበት የከበረች #እሑድ ሰንበት የተባበሩበት በዓል ነው። አንሆ ታላቅ ፀጥታ አየሁ የሚከለክለን ሁከት የለም።  መጽሐፈ ሜላድ 6 : ፴፮ ---- ይኽችም ዕለተ #እሁድ ጌታችን #የተነሣባት #ቀንናት በአካላዊ ቃሉ ሰማይና ምድርን ለፈጠረው ለአብ ፍጹም ምስጋናን አቅርቡለት አሉ ። እነኚሁ ሁለት ጥቅስ ከሞት የተነሳው እሁድ ነው። ስለዚህ ድምር ስናወጣ አርብ ሙሉ ቀን ስለማይሞላ ያለው ዘጠኝ ሰአት + አርብ ሙሉ ሌሊት +ቅዳሜ ሙሉ ቀን + ቅዳሜ ሙሉ ሌሊት =ሁለት ሙሉ ሌሊት እና እንድ ሙሉ ቀን ከዘጠኝ ሰዓት ስለዚህ " የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል።” ማቴዎስ 12፥40 የተባለው በምን ስሌት ነው የምመጣው? ማሳሰቢያ የተሰራው በማርቆስ 15:2⁵ ባለው መሰረት ነው እንጂ በሌላም ወንጌሎች ብንሰራው ልዩነቱ አለው። 📕ወንድም አምዳላ ናሲር ለየተኛውም ሀሳብ እና አስተያየት 👉@amdala5👈 እንደዚህ እና መሰል ትምህርቶችን ለመከታተል ቻናላችንን ይጎበኙ እና ያስጎበኙ https://t.me/comparativeRelgion/410 https://t.me/comparativeRelgion/410 https://t.me/comparativeRelgion/410

"የትውልድ ታሪክ" ፨ ጳውሎስ ወደ ቲቶ በላከው ደብዳቤ ላይ "ከትውልዶች ታሪክ" ራቅ ከንቱ እና የማይጠቅሙ ናቸውና በማለት አስጠንቅቆታል፦ “ነገር ግን ሞኝነት ካለው ምርመራና "ከትውልዶች ታሪክ" ከክርክርም ስለ ሕግም ከሚሆን ጠብ ራቅ፤ የማይጠቅሙና ከንቱዎች ናቸውና፤” — ቲቶ 3፥9 ፨ ወደ ጢሞቴዎስ በላከው መልዕክቱም ላይ እንዲሁ የትውልዶች ታሪክ ክርክርን የሚያመጡ እና የማይጠቅሙ ስለሆኑ ሰዎች "መጨረሻ ወደ ሌለው ወደ #ትውልዶች #ታሪክ #እንዳያዳምጡ" አዝዞ ነበር፦ “ወደ መቄዶንያ በሄድሁ ጊዜ፥ አንዳንዶች ልዩ ትምህርትን እንዳያስተምሩና ወደ ተረት መጨረሻም ወደሌለው "ወደ ትውልዶች ታሪክ" #እንዳያደምጡ ልታዛቸው በኤፌሶን ትቀመጥ ዘንድ ለመንሁህ፤ እንደ እነዚህ ያሉ ነገሮች ክርክርን ያመጣሉና በእምነት ግን ላለ ለእግዚአብሔር መጋቢነት #አይጠቅሙም።” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥3-4 እንግዲህ በዚህ መልኩ ጳውሎስ ስለ ትውልዶች ታሪክ ምን እንዳለ ካየን ጳውሎስ እንዲህ ክፉኛ የጠላቸውና ያወገዛቸው "የትውልዶች ታሪኮች" የት የት እንደሚገኙ እንይ፦ 1) የማቲዎስ ወንጌል መጀመሪያ መክፈቻው ለራሱ "በትውልዶች ታሪክ" ታጅቦ ነው፦ “የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ "የኢየሱስ ክርስቶስ #ትውልድ መጽሐፍ"።” — ማቴዎስ 1፥1 እስከ ቁጥር 17 ድረስ ያለ ማቆራረጥ የእየሱስ የትውዶች ዝርዝር ተቀምጧል። ይሔ "የትውልዶች ታሪክ" በሌሎች ወንጌላቶች ላይም ተዘግቧል(ሉቃስ 3፥23-38) ስለዚህ ይሔ መፀሐፍ የእየሱስን የትውልዶች ታሪክ የተሸከመ #ከንቱ እና #የማይጠቅም መፀሐፍ ነው ማለት ነው ክርስቲያኖች ሆይ ጳውሎስን የምትወዱ ከሆነ እሱ በነገራችሁ መሰረት "የትውልዶች ታሪክ" ከንቱ እና የማይጠቅም ስለሆነ ራቁት! 2) 1ደኛ ዜና መዋዕል፥ ይህ የብሉይ ኪዳን መፀሐፍ ደግሞ ሳያቋርጥ ማለት ይቻላል ከምዕራፍ 1 እስከ ምዕራፍ 9 ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለምንም የማይጠቅም "የትውልዶችን ታሪክ" ብቻ ነው የተሸከመው፤ ትውልዶችን ይዘረዝራል ስለነዛ ትውልዶች አሰልቺ ምንም የማይጠቅም ከንቱ ታሪክ ይተርካል በቃ፤ ከፍታችሁ ማየት ትችላላችሁ ገና ምዕራፍ አንድ ቁጥር አንድ ስከፍቱ እከሌ እከሌን ወለደ ብሎ ይጀምራል... በነገራችን ላይ ሁሉም የመፀሐፍ ቅዱስ ክፍል ማለት ይቻላል ፀባያቸው እንደዚህ ነው በተለይ ብሉይ ኪዳን ላይ ያሉት እነ ኦሪት ፤ በቃ የትውልዶች ታሪኮችን ነው የሚተርኩት/የሚያወሩት። ይሔ ደግሞ በገዛ በራሳችሁ ሐዋሪያ ተብዬ የተተቸ እና የተነቀፈ ተግባር ነው ... "የትውልዶች ታሪኮችን #ከማዳመጥ #ከልክሏል" ስለዚህ እከሌ እከሌን ወለደ ፤ እከሌ እከሌን ሲወልድ ይህን ያህል አመቱ ነበር ፤ በእከሌ ስፍራ ተቀበረ ፤ ይህን ያህል ልጆች ነበሩት ፤ ሲነግስ ይህን ያህል አመቱ ነበር ፤ ልጆቹ እከሌ እከሌ ናቸው ... ከሚል #ከንቱ ከሆነው የትውዶችን ታሪክ ከተሸከመው #መፀሐፍ #ቅዱስ #ትርቁ ዘንድ የእኔም የጳውሎስም ጥሪ ነው፦ “ወደ መቄዶንያ በሄድሁ ጊዜ፥ አንዳንዶች ልዩ ትምህርትን እንዳያስተምሩና ወደ ተረት #መጨረሻም #ወደሌለው #ወደ #ትውልዶች #ታሪክ ""#እንዳያደምጡ"" #ልታዛቸው በኤፌሶን ትቀመጥ ዘንድ ለመንሁህ፤ እንደ እነዚህ ያሉ ነገሮች ክርክርን ያመጣሉና #በእምነት #ግን #ላለ #ለእግዚአብሔር #መጋቢነት #አይጠቅሙም።” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥3-4 “ነገር ግን ሞኝነት ካለው ምርመራና "ከትውልዶች ታሪክ" ከክርክርም ስለ ሕግም ከሚሆን ጠብ #ራቅ፤ #የማይጠቅሙና #ከንቱዎች #ናቸውና፤” — ቲቶ 3፥9 ®✍ https://t.me/eotc_degl

ይኸው እዚህ ላይ ደግሞ የፀሐይን አካሃዷን ሲገልፅላችሁ ጭራሽ #በእርምጃ(እየተራመደች) 😆 ምናምን የረገጠችውን እያየች እየተጠነቀቅች ነው የምትሄደው ይለናል... አንድምታ ዘመፀሐፈ ሔኖክ 21፥23
ይኸው እዚህ ላይ ደግሞ የፀሐይን አካሃዷን ሲገልፅላችሁ ጭራሽ #በእርምጃ(እየተራመደች) 😆 ምናምን የረገጠችውን እያየች እየተጠነቀቅች ነው የምትሄደው ይለናል... አንድምታ ዘመፀሐፈ ሔኖክ 21፥23 https://t.me/eotc_degl

"የስላሴ እሳቤ" እና "የተደበቀው እውነት" መጻሕፍ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ አዳማ እና ደሴ ይገኛሉ። አዳማ ማግኘት የምትፈልጉ call +251966640370 ደሴ ማግኘት የምትፈልጉ፦ አረብገንዳ ሸህ አብዱ መክተባ   ሸርፍተራ ፋጡማህ መክተባ አሕመድ መክተባ ይገኛል አዲስ አበባ ደግሞ call 0920781016

ይሔንን ልጥፍ አስመልክቶ አንዳንዶች ሔኖክ ስለ ፀሐይና ጨረቃ ያወራቸው ነገሮች በቀጥታ አይፈቱም ስላሉ እስቲ ከራሳቸው ምንጮች ቀጥታ ይፈታል አይፈታም የሚለውን እንይ ብዬ አሰብኩና 🤔 "ከአንድምታቸ
ይሔንን ልጥፍ አስመልክቶ አንዳንዶች ሔኖክ ስለ ፀሐይና ጨረቃ ያወራቸው ነገሮች በቀጥታ አይፈቱም ስላሉ እስቲ ከራሳቸው ምንጮች ቀጥታ ይፈታል አይፈታም የሚለውን እንይ ብዬ አሰብኩና 🤔 "ከአንድምታቸው ጀምሪያለሁ" ... ያው አለማስተዋል ነው እንጂ እዛው ፁሁፌ ላይ መፀሐፈ አክሲማሮስን ጠቅሼ ነበር... ለማንኛውም እዚህ ልጥፍ ላይ በግልፅ እንደምናየው ሔኖክ ያየው ነገር በሌላ ነገር የሚፈታ እንዳልሆነ ነው። "ፀሐይ ስታበራ ውላ በምዕራብ ገብታ በሰሜን ዙራ በምስራቅ ትወጣለች" ፨ ደግሞ የሚገርመው ነገር ታች ዝቅ ብሎ ... "አድማስ እንደ ሲኦሎ መዝጊያ እንደ ሸማኔ መወርወሪያ ያለ ነው በዚያ ውስጥ ለውስጥ ትሄዳለች ይህም አይበዛም እንጂ ሌሊትና መዓልት ይፈራረቃል።" አንድምታ ዘመፀሐፈ ሔኖክ 21፥12 በማለት ፀሐይ በአድማስ(በሰማይ) ውስጥ ለውስጥ ትሄዳለች በዚህ ጉዞዋም በትንሹ ሳይበዛ ሌሊትና ቀን እንደሚፈራረቅ ያትታል...😄 ይሔ የመፀሐፈ ሔኖክ 21፥12 አንድምታ ነው። ስለዚህ እንኳን ትርጉም ሊኖረው እንደውም ፀሃይዋ በየት እንደምትሄድ የመንገዷን እርዝመት ምናምን ያብራራል እንጂ በጭራሽ ክርስቲያኖች ለመሸፋፈን እንደምትፈልጉት ሌላ የወጣ ትርጉም ኖሮት አይደለም! ስለዚህ ባይብላችሁ ብቻ ሳይሆን አሁን አንድምታችሁም ተወቃሽ ሆኗል የባይብሉን ስህተት ይበልጥ በማጉላት ስህተትን ተሸክሟልና! https://t.me/eotc_degl https://t.me/eotc_degl

የባይብል ግጭቶች ክፍል አርባ አንድ “የዓዲን ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ አምስት።” — ነሀምያ 7፥20 VS “የዓዲን ልጆች፥ አራት መቶ አምሳ አራት።” — ዕዝራ 2፥15 ጥያቄው የዓዲን ልጆች 454 ወይስ 655 655-454=201 የዕዝራ ፀሀፊ የት ወሰደው? ወንድም አምዳላ ናሲር @amdala5 https://t.me/comparativeRelgion

የባይብል ግጭቶች ክፍል አርባ “የአዶኒቃም ልጆች፥ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት።” — ዕዝራ 2፥13 VS “የአዶኒቃም ልጆች፥ ስድስት መቶ ስድሳ ሰባት።” — ነሀምያ 7፥18 ጥያቄው የአዶኒቃም ልጆች 666 ወይስ 667? 667-666=1 የት ጥሎት ነው የዕዝራ ፀሐፊ? 📕 ወንድም አምዳላ ናሲር @amdala5 https://t.me/comparativeRelgion

የክርስቲያኖች ጥያቄ የኛ መልስ እናንተ ሙስሊሞች ከአንድ በላይ ሚስት ታገባላችሁ ይህ አድራጎት ሴቶችን መበደል አይሆንም? መልስ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት በሁሉም ክርስቲያኖች ዘንድ እንደ ሞኝነት ነው የሚታያቸው። የሚገርው ነገር የእስልምና ሃይማኖት እንጂ ከእስልምና ሃይማኖት ውጭ የየትኛውም ሃይማኖት ክርስትናን ጨምሮ የሚስት ገደብን ያስቀመጠ የለም። እስኪ በዚህ ዙሪያ ባይብል ምን ይላል ወደ ሚለው ነጥብ እናምራ A ሁለት ሚስቶች በኦሪት.ዘዳግም 21፡25 ‹‹ለአንድ ሰው አንዲት የተወደደች አንዲት የተጠላች ሁለት ሚስት ቢኖሩት። በመጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማይ 27፡34‹‹ዳዊትም ደግሞ ኢይዝራኤላዊቱን አካናሆምን ወሰደ፤ ሁለትም ሚስቶች ሆኑለት።›› በመጽሐፈ ዜና መዋለ ካልዕ 24፡3‹‹የደሄም ሁለት ሚስቶች አጋባው፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።›› በኦሪት.ዘፍጥረት 4፡22 ‹‹ላሕሜ ሁለት ሚስቶች አገባ።›› ከዚሁ ምዕራፍ 32፡22‹‹በዚያች ሌሊት ያዕቆብም ተነሳ ሁለቱን ሚስቶቹን አንዲቱን ሴት አገልጋዮቹንና አሥራ አንድ ልጆቹን ይዞ በያቦቅ መልካ ተሻገረ።›› B ሰባት ሚስቶች በትንቢተ.ኢሳይያስ 4፡ ‹‹በዚያን ቀን ሰባት (7) ሴቶች የገዛ እንጀራችን እንበላለን፤ የገዛ ልብሳችንም እንለብሳለን፤ ስምህ ብቻ በእኛ ላይ ይጠራ፤ መሰደባችንንም እርቅ ብለው አንዱን ወንድ ይይዙታል።›› C አሥራ አራት ሚስቶች በመጽሐፈ ዜና መዋዕል 13፡21 ‹‹አብያም ፀና አሥራ አራት (4) ሚስቶችን አገባ፤ ሀያ ሁለትም ወንዶች ልጆችና አሥራ ስድስት ልጆችን ወለደ፡፡›› D አሥራ ስምንት ሚስቶችና ስልሳ (60) ዕቁባቶች በመጽሐፈ ዜና መዋዕል 1፡21 ‹‹ሮብዓምም ከሚስቶቹና ከቁባቶቹ ሁሉ ይልቅ የአቤሴሎምን ልጅ መዓካን ወደደ፤ አሥራ ስምንት (18) ሚስቶችና ስድሳ (60) ዕቁባቶች ነበሩት።›› E ሰባት መቶ (700) ሚስቶችና ሦስት መቶ (300) ዕቁባቶች በመጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 11፡2-3 ‹‹ከእነዚህ ጋር ሰለሞን በፍቅር ተጣበቀ፤ ለእርሱም ወይዛዝርት የሆኑ ሰባት መቶ (700) ሚስቶችና ሦስት መቶም (300) ዕቁባቶች ነበሩት።›› F በቁጥር ያልተገደቡ ብዙ ሚስቶች በ1ኛ ዜና መዋዕል 14፡3‹‹ዳዊትም በኢየሩሳሌም ብዙ ሚስቶችን አገባ።›› ተጨማሪ በመጽሐፈ መሳፍንት 8፡29-30 ‹‹የኢዩአስ ልጅ ይሩባኤል ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ከዚያም ተቀመጠ፤ ብዙ ሚስቶች ስላገባ ሰባ (70) ልጆች ነበሩት፡፡›› G ለባሏ ሚስት ያጋባች ሴት በኦሪት.ዘፍጥረት 6፡3-4 ‹‹አብራሃምም በከነዓን ምድር አሥር ዓመት ከተቀመጠ በኋላ የአብራሃምም ሚስት ሣራ ግብፃዊት ባሪያውን አጋርን ወስዳ ለባልዋ ለአብራሃም ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠችው። እርሱም ወደ አጋር ገባ።›› ከዚሁ ምዕራፍ 30፡10-1 ‹‹ልያም መውለድን እንዳቆመች ባየች ጊዜ፤ ባሪያዋን ዘለፋን ወሰደችለት፤ ሚስት ትሆነው ዘንድ ለያዕቆብ ሰጠችው።,, ዝንጀሮ የራሱዋን ሳታይ በሌላው ትስቃለች አሉ✍ 📕 ወንድም አምዳላ ናሲር ለየተኛውም ሀሳብና አስተያየት 👉 @amdala5👈 እንደዚህና መሰል ትምህርቶችን ለመከታተል ቻናላችንን ይቀላቀላሉ 👇👇 https://t.me/comparativeRelgion/404 https://t.me/comparativeRelgion/404 https://t.me/comparativeRelgion/404

🪴ጥያቄ ለክርስቲያኖች 🌹 የማቴዎስ ወንጌል 16፡28 " የሰው ልጅ ከመላዕከት ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል፡፡ እውነት እላችኋለሁ የሰው ልጅ በመንግስቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከሚቆሙት #ሞትን #የማይቀምሱ #አንዳንድ አሉ፡፡» በዚህ አንቀጽ የሚስማማ ከርስቲያን ይኖር ይሆን? የሰው ልጅ የኢየሱስ መንግስት እስከአሁን እንዳልመጣ ሁሉም የከርስቲያን ወገን ይስማማበታል በኢየሱስ ዘመን የነበሩ ሰዎች ኢየሱስ እስኪመለስ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አሉ ተብሏል ስለዚህ ኢየሱስ ካረገ ከሁለት ሺህ ዓመት በላይ ነው እውን እስከ አሁን በዚያ ዘመን የነበረ ሰው አሁን በሕይወት ያለ አለ ብለው ይገምታሉን? ታዲያ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው በዚህ ከቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ» ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ይህ አባባል ማንኛውንም የሰው አዕምሮ የማይቀበለው ነው፡፡ ይህ አንቀጽ በምን መልኩ የአምላከ ቃል» ሊሆን ይችላል? መጽሐፍ ቅዱስ ትከከለኛው የእምነት መለኪያ እና እንከን የሌለበት «የፈጣሪ ቃል ነው የምንል ከሆነ ይህን አንቀጽ እንዴት ይመለከቱታል? share share share አድርጉ ወንድም አምዳላ ናሲር ለየተኛውም ሀሳብ እና አስተያየት 👉@amdala5👈 እንደዚህ እና መሰል ትምህርቶችን ለመከታተል ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/comparativeRelgion

🍷🍷ወይን የማይጠጣ ሰው ደህንነት የለውም🙌🤣 ወይንም የተፈጠረው ለሰው ደስታ ነው።👻 ለሚያለቅስ ለሚያዝን ሰው ወይን አጠጣው። ☠🙆‍♂🍺🍺🍻🍻 ፨ መፀሐፈ ሲራክ 34፥26-28 26፥የሰው ደኀንነቱ ወይን መጠጣት ነው መጥኖ ለሚወጣም ሰው ተድላ ደስታው ነው "እሱ ለሰው ተድላ ደስታ ሊሆን ትፈጥሯልና" #ወይን #ለማይጠጣ #ሰው #ደኅንነቱ #ምንድነው። 27፥ለልቡና ፈጽሞ ተድላ ደስታ ነው ወይንን መጥኖ በጊዜው #መወጣት #ደግ #ነው። 28፥ወይን የልቡና ኀዘንን ያስረሳል #ለሚያለቅስ #ሚያዝንም #ሰው #ወይን #አጠጣው። የምር ግን ክርስቲያኖች አሳዘናችሁኝ የምሬን ነው ይሄ አሁን መለኮታዊ ትዕዛዝ(አምላክ ያዘዘው ትዕዛዝ) ነው ብላችሁ ታስባላችሁ??? እውን አምላክ መጥፎ ነገር ያዛልን? ቆይ ወይን ለማይጠጣ ሰው ደህንነቱ ምንድነው ማለት ምን ማለት ነው?? ሰው ወይን ሲጠጣ ነው ደህና የሚሆነው? ካልጠጣ ደህና አይሆንም ማለት ነው?? ለዛ ነዋ ሉጥ ወይን ተጎንጭቶ ከገዛ ልጆቹ ተኝቶ ልጆችን ከገዛ ልጆቹ ወልዶ ደህንነትን ያገኛት! አይ ደህንነት! ክርስቲያኖች ሆይ ንቁ! https://t.me/eotc_degl

የተደበቀው እውነት ገበያ ላይ ውሏል። የምትፈልጉ +251920781016 ዐብዱ ብላችሁ ይደውሉ!
የተደበቀው እውነት ገበያ ላይ ውሏል። የምትፈልጉ +251920781016 ዐብዱ ብላችሁ ይደውሉ!

የተላኩት ለአለም ወይስ ለአረቦች? ከሚለው የቀጠለይጫኑት የምለውን በመንካት የመጀመሪያውን ማንበብ ይችላሉ 2 ለዓለም ለመላካቸው ቅዱስ ቁርዓን «ለዓለማት መጣ» ብሎ መናገሩ وَمَا أَرْسَلْنَاكَ إِلَّا رَحْمَةً لِلْعَالَمِين (ሙሐመድ ሆይ!) ለዓለማት እዝነት አድርገን እንጂ ሌላ አልላክንህም። አል-አንቢያ 21፡107 ተፍሲር ኢብንከሲር ይመልከቱ وقوله [ تعالى ] : ( وما أرسلناك إلا رحمة للعالمين ) : يخبر تعالى أن الله جعل محمدا صلى الله عليه وسلم رحمة للعالمين ، أي : أرسله رحمة لهم كلهم ("ለዓለማት እዝነት አድርገን እንጂ አልላክንህም")፡- አላህ ሙሐመድን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ለዓለማት እዝነት እንዳደረገው ይነግረናል። ፦ ለሁሉም ምሕረት አድርጎ ላካቸው። ኢብኑ አባስ/ረ.ዐ/ ይመልከቱ «ለዓለማት» የሚለውን ቃል ሲተረጉሙት «ለሰው ልጅና ለጂኖች {አጋንንት» በሚለው ተርጉመውታል፡፡ أُولَٰئِكَ الَّذِينَ هَدَى اللَّهُ ۖ فَبِهُدَاهُمُ اقْتَدِهْ ۗ قُلْ لَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ أَجْرًا ۖ إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرَىٰ لِلْعَالَمِي «እነዚህ ነብያት እነዚያ አላህ የመራቸው ናቸው፤ በመንገዳቸውም ተከተል፤ “በርሱ (በቁርዓን) ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፤ እርሱ ለዓለማት ግሳጼ እንጂ ሌላ አይደለም በላቸው፡፡» አል-አንዓም 6፡90 تَبَارَكَ الَّذِي نَزَّلَ الْفُرْقَانَ عَلَىٰ عَبْدِهِ لِيَكُونَ لِلْعَالَمِينَ نَذِيرًا «ያ ፉርቃንን በባሪያው ላይ ለዓለማት አስፈራሪ ይኾን ዘንድ ያወረደው (አምላከ) ከብርና ጥራት ተገባው፡፡» አል-ፉርቃን 25፡1 ተጨማሪ ዩሱፍ/ 12፡104፣ ኢብራሒም 14፡1፣ ሰበእ 34፡28 ይመልከቱ፡፡ ከጃቢር ኢብኑ አብደላህ /ረ.ዐ/ በተወራው ሐዲስ የአላህ መልክተኛ እንዲህ አሉ “ከእኔ በፊት ለነበሩት ነብያት ያልተሰጡ አምስት ስጦታዎች ተሰጥተውኛል፡፡” ከነሱም መካከል አንዱን ብንጠቅስ፡- “... ከእኔ በፊት የነበረ ማንኛውም ነብይ ይላክ የነበረው ለሕዝቦቹ ብቻ ሲሆን እኔ ግን ለዓለም ሁሉ ተላክሁ፡፡” ቡኻሪ 1/533 ሙስሊም ሀ/370-371/ ከአቢ ሁረይራ ረ.ዐ) በተወራው ሐዲስ ደግሞ የአላህ መልክተኛ እንዲህ አሉ “የሙሐመድ ነብስ በእጁ በሆነችው ይሁንብኝ ከዚህ ኡመት ሕዝብ አይሁዳዊም ይሁን ከርስቲያን የኔን መላክ ሰምቶ ሳያምን ቢሞት የእሳት ጓድ ቢሆን እንጂ ሌላ የለም፡፡” ሙስሊም 1፡134/ ከአቢ ሙሳ /ረ.ዐ/ በተወራው ሐዲስ ደግሞ የአላህ መልክተኛ እንዲህ አሉ “ወደ ቀዩም ወደ ጥቁሩም ተልኬአለሁ፡፡” አህመድ 4/416 ጦበራኒ ሙጅመኡ ዘዋኢድ 8/258/ ከአብደላህ ኢብኑ አባስ (ረ.ዐ/ በተወራው ሐዲስ ደግሞ የአላህ መልክተኛ እንዲህ አሉ “ወደ ቀዩም ወደ ጥቁሩም ተልኬአለሁ፡፡” አህመድ 1250 📕 ወንድም አምዳላ ናሲር ለየተኛውም አስተያየት 👉@amdala5👈 መሰል ትምህርቶችን ለመከታተል ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/comparativeRelgion/395

ነቢዩ ሙሐመድ /ሰ.ዐ.ወ/ ተልዕኳቸው ለመላው የዓለም ሕዝብ ወይስ ለአረቦች ብቻ? መልክተኝነታቸውስ መላውን የዓለም ሕዝብ ይመለከታል? ወይስ ከሳቸው በፊት እንደነበሩት ነቢያት በሕዝቦቻቸው ላይ የተገደበ ይሆናል? ለዚህ ጥያቄ በቂ መልስ ይሰጠናል፡- 1 ለዓለም ለመላካቸው የቅዱስ ቁርዓኑ ጥሪ «እናንተ ሰዎች ሆይ» ብሎ መናገሩ ነው፡፡ የቀደምት ነቢያቶች ሕዝቦቻቸውን በሚጣሩበት ጊዜ «ሕዝቦቼ ሆይ» በማለት ነበር፤ ይህ የሚያስረዳው ደግሞ መልክተኝነታቸው ለሕዝቦቻቸው ብቻ የተገደበ መሆኑን ነው፡፡ ይህንን እውነታ ቅዱስ ቁርዓን እንዲህ በማለት ይናገራል፡- لَقَدْ أَرْسَلْنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوْمِهِ فَقَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ «ኑህን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላከነው፤ አላቸውም “ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፤ ለናንተ ከርሱ ሌላ ምንም አምላከ የላችሁም፤ እኔ በናንተ ላይ የከባድ ቀንን ቅጣት እፈራላችኋለሁ፡፡ አል-አዕራፍ 7፡59 وَإِلَىٰ ثَمُودَ أَخَاهُمْ صَالِحًا ۗ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ۖ قَدْ جَاءَتْكُمْ بَيِّنَةٌ مِنْ رَبِّكُمْ ۖ هَٰذِهِ نَاقَةُ اللَّهِ لَكُمْ آيَةً ۖ فَذَرُوهَا تَأْكُلْ فِي أَرْضِ اللَّهِ ۖ وَلَا تَمَسُّوهَا بِسُوءٍ فَيَأْخُذَكُمْ عَذَابٌ أَلِيم «ወደ ሰሙድም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ አላቸው “ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ ምንም አምላክ የላችሁም፤...”፡፡» አል-አዕራፍ 7፡73 وَلُوطًا إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِ أَتَأْتُونَ الْفَاحِشَةَ مَا سَبَقَكُمْ بِهَا مِنْ أَحَدٍ مِنَ الْعَالَمِين ሎጥንም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ “አስቀያሚን ሥራን ትሰራላችሁን? በርሷ ከዓለማት አንድም አልቀደማችሁም፡፡ አል-አዕራፍ 7፡8ዐ وَإِلَىٰ مَدْيَنَ أَخَاهُمْ شُعَيْبًا ۗ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ۖ قَدْ جَاءَتْكُمْ بَيِّنَةٌ مِنْ رَبِّكُمْ ۖ فَأَوْفُوا الْكَيْلَ وَالْمِيزَانَ وَلَا تَبْخَسُوا النَّاسَ أَشْيَاءَهُمْ وَلَا تُفْسِدُوا فِي الْأَرْضِ بَعْدَ إِصْلَاحِهَا ۚ ذَٰلِكُمْ خَيْرٌ لَكُمْ إِنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِين «ወደ መድየንም (ምድያን) ወንድማቸውን ሹዓይብን (ላክን)፤ አላቸው “ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፤ ከርሱ በቀር ምንም አምላክ የላችሁም፤...”፡፡» አል-አዕራፍ 7፡85 ነገር ግን ቁርዓን የወረደላቸው ነብዩ ሙሐመድ /ሰ.ዐ.ወ/ ከቀደምት ነቢያት በተለየ ሁኔታ ነበር ዳዕዋ የሚያደርጉት፡፡ ዳዕዋቸው ጥሪያቸው በጊዜና በቦታ ሳይገደብ ሁሉንም የሰው ዘር የሚመለከት ነበር፡፡ ይህም በቁርዓን አስተምህሮ መሰረት ጥሪያቸውን «እናንተ ሰዎች ሆይ!» በሚለው አገላለጽ መጠቀማቸው ለመላው የሰው ዘር መላካቸው የሚቀጥሉት አንቀጾች ይህንን ያመላክታሉ፡- مَا أَصَابَكَ مِنْ حَسَنَةٍ فَمِنَ اللَّهِ ۖ وَمَا أَصَابَكَ مِنْ سَيِّئَةٍ فَمِنْ نَفْسِكَ ۚ وَأَرْسَلْنَاكَ لِلنَّاسِ رَسُولًا ۚ وَكَفَىٰ بِاللَّهِ شَهِيدًا «ከደግ ነገር የሚያገኝህ ከአላህ (ችሮታ) ነው፤ ከመከራም የሚደርስብህ ከራስህ ጥፋት ነው፤ ለሰዎችም ሁሉ መልከተኛ ኾነህ ላክንህ፤ መስካሪም በአላህ በቃ፡፡» አል-ኒሳእ 4፡79 «እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ዘንድ በእርግጥ አስረጅ መጣላችሁ፤ ወደናንተም ገላጭ የሆነን ብርሃን (ቁርዓንን) አወረድን፡፡ “እናንተ ሰዎች ሆይ! እውነቱ ከጌታችሁ በእርግጥ መጣላችሁ (በርሱ) የተመራም ሰው የሚመራው ለራሱ ነው፤ የተሳሳተም ሰው የሚሳሳተው (ጉዳቱ) በራሱ ላይ ነው፤ እኔም በናንተ ላይ ተጠባባቂ አይደለሁም" በላቸው፡፡» ይቀጥላል ______ 📕ወንድም አምዳላ ናሲር ለየተኛውም ሀሳብ 👉 @amdala5👈 https://t.me/comparativeRelgion

ፀሀይ እና ጨረቃ (1) የፀሃይ መጓጓዧ ሰረገላ(ጋሪ)። > ፀሀይ ጧት እና ማታ በጋሪ ይሮጣል(ይመላለሳል) 52※“የፀሐይ ሥራህ መንገዱም መመለሱም ይህ ነው። 53※በተመለሰም ጊዜ ስሳውን ከንትሮስ ሊፈጽም ይመለሳል ተመልሶም በምሥራቅ ይወጣል ለዘለዓለም የሚኖር ታላቅ ብርሃንም ይህ ነው። 54※ጌታ እንዳዘዘ በሱ አምሳል የሚጠራ ከምሥራቅ የሚወጣ ደገኛ ብርሃን ይህ ነው። 55※እንዲህ ሆኖ ይወጣል ይገባል መጕደልም የለበት "#በሠረገላ #ሆኖ በመዓልትም በሌሊትም ይሮጣል" እንጂ አያርፍም።” — መፀሐፈ ሔኖክ 21፥52–55 (1.2) የዚህ የፀሃይ መጓጓዣ የጋሪው(የሰረገላው) ሹፌር ደግሞ #ንፋስ ነው። (ንፋስ የፀሃይን ጋሪ ይነዳል)፦ 11※“ወደሚሄድባቸውም ሠረገላዎች ባወጣ ጊዜ "#ሰረገላዎችን #የሚነዳ #ነፋስ #ይነፍሳል"።” -- መፀሐፈ ሔኖክ 21፥11 ፨ጥያቄ- ፀሐይ መጓጓዣ ጋሪ አለውን? ማስረጃ ስጡን! ፨ጥያቄ- ጋሪውስ የሚነዳው በነፋስ ነውን? ማስረጃ ስጡን! (2) ጨረቃም በሰረገላ(በጋሪ) ላይ ይቀመጣል፦ 1※“የዚህን የፀሐይ ሥራት ካየሁ በኋላ ስሙ ጨረቃ የሚባል የታናሹን ብርሃን ሌላ ሥራት አየሁ። 2※ክብነቱም እንደ ሰማይ ክብ ነው "#በሚቀመጥባት #በሠረገላውም" ነፋስ ይነፍሳል።” — መፀሐፈ ሔኖክ 22፥1–2 ፨ጥያቄ-ጨረቃ በጋሪ(በሰረገላ) ላይ ይቀመጣልን? ከተቀመጠ ማስረጃ ስጡን! (3) ኮከቦችም በሰረገላዎች(በጋሪዎች) ይዞራሉ(ይጓጓዛሉ)፦ 7※“ጨረቃና ፀሐይ ከዋክብትም “#በሰማይ #ሠረገላዎች #ሁሉ #የሚዞሩ #ቅንየታት #የሚባሉ #ኮከቦችም” ሁሉ ለሌሊትና ለቀንም መሪዎች ይሆኑ ዘንድ በነዚህ ሁሉ ላይ ሾሞታልና አሳየኝ።” — መፀሐፈ ሔኖክ 24፥7 ፨ጥያቄ-ኮከቦችም በጋሪ ይጓጓዛሉን? (4) ፀሃይ እግሮቿን በመስኮትዋ ታወጣለች፦ 8※“ዑርኤል "በሰማይ ያለ ፀሐይ በሚመላለስባቸው በሠረገላዎች ዙሪያ" «#የፀሐይ #እግሮች #ከነሱ #የሚወጡባቸው #የተከፈቱ #አሥራ #ሁለት #መስኮቶችን» እንዲህ አሳየኝ።” — መፀሐፈ ሔኖክ 24፥8 በነገራችን ላይ እየሱስም በፀሐይ እግር(ጮሯ) ላይ ተቀምጦ ያውቃል፦ «ተአምረ እየሱስ ተአምር 20» ፨ጥያቄ- እንደ መፀሐፈ ሔኖክ ገለፃ ከሆነ ፀሃይ የሚወጣው በምስራቅ ባሉ ስድስት መስኮቶች ነው(መፀሐፈ ሔኖክ 21፥5-6)። ታዲያ እዚህ ጥቅስ ላይ እንዴት የፀሃይ እግሮች የሚወጡባቸው 12 የተከፈቱ መስኮቶችን አሳየኝ ሊል ቻለ? የፀሐይ መውጫ 6 መስኮቶች ናቸው ወይስ 12 ?? ፨ሲጀመር ፀሐይ መግቢያ እና መውጫ መስኮት አላትን? ማስረጃችሁን አምጡ! (5) ፨ፀሃይ በሰማያት ውስጥ ድንኳን አላት፦ ፨ከእፍኙ(ከሰማይ) ትወጣለች። ፨አወጣጧም ከሰማያት #ዳርቻ ነው! ፨ዙረቷም እስከ #ዳርቻቸው ነው! ፨ከትኩሳቷም/ከብርሃኗ/ከሙቀቷ #የሚሰወር #የለም! መዝሙር 19 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ "#ሰማያት" የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል። … ⁵ "#በእነርሱም #ውስጥ #የፀሐይን #ድንኳን #አደረገ"፥ እርሱም እንደ ሙሽራ "ከእልፍኙ ይወጣል"፤ እንደ አርበኛ በመንገዱ ለመሮጥ ደስ ይለዋል። ⁶ "አወጣጡ ከሰማያት ዳርቻ ነው"፥ "ዙረቱም እስከ ዳርቻቸው ነው"፤ "ከትኩሳቱም የሚሰወር የለም"። ፨ጥያቄ- ከላይ የተዘረዘሩት 5ቱ ሐሳቦች እውነት፡ናቸውን? ከሆኑ ማስረጃችሁን ወዲህ በሉት! ለምሳሌ ከትኩሳቷ የሚሰወር ብዙ ነገር አለ የፀሐይን ብርሃን የማያገኙ ፍጡሮች ብዙ አሉ! ይሄ ፀሐፊው አፅናፈ አለማችን ምን ያክል ግዙፍ እንደሆነ ሳያውቅ እንደፃፈው ማሳያ ነው። (6) በምስራቅ ሰማይ 6 መስኮቶች አሉ በምዕራብ ሰማይም 6 መስኮቶች አሉ በነዚህ መስኮቶች ፀሃይ እና ጨረቃ እንዲሁም አንዳንድ ከዋክብት #ይወጣሉ #ይገባሉ፦ 5※“የበራ የፀሐይ መውጫ በምሥራቅ ባሉ በሰማይ መስኮቶች ነው መግቢያውም በምዕራብ ባሉ በሰማይ መስኮቶች ነው። 6※ፀሓይ የሚወጣባቸው ስደስት መስኮቶችን አየሁ ፀሐይም የሚገባባቸው ቦታዎች ስድስት መስኮቶችንም አየሁ። 7※ጨረቃም በነዚያ መስኮቶች ይወጣል ይገባል። 8※ከሰማይ ኮከቦችን የሚመሩ ኮከቦችም ከሚመሯቸው ኮከቦች ጋራ በነዚያ ደጃፎች ይወጣሉ ይገባሉ እኒህም መስኮቶች ስድስቱ በምሥራቅ ስድስቱ ፀሐይ በሚገባበት በምዕራብ ናቸው።” — መፀሐፈ ሔኖክ 21፥5–8 ፨ለዚህም ማስረጃ ስጡን እውነት ከሆነ? (7) ፀሐይ እና ጨረቃ በምዕራቡ መስኮት ይገቡ እና ወደ መስዕ(ሰሜን ምስራቅ) ዞረው ያበሩና በምስራቅ መስኮት ይወጣሉ፦ ※"በምዕራብ መስኮት ይገባሉ #ወደ #መስዕ ይዞራሉ በሰማይ ሁነው እያበሩ በምሥራቅ መስኮት ይወጣሉ።" — መፀሐፈ ሔኖክ 26፥5 መፀሐፈ አክሲማሮስም https://t.me/eotc_degl/192 ፀሐይ ከምስራቅ ወጥታ ወደ ምዕራብ ገብታ ከዛ ደግሞ ወደ ሰሜን ዙራ መልሳ በምስራቅ እንደምትወጣ ይናገራል። ፨ይሔም እውነት ከሆነ ማስረጃ አምጡ ከእውነታ ጋር የማይጣረስ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማስረጃ ካላችሁ አቀብሉን! ክርስቲያኖች ሆይ ከላይ በመፀሐፍ ቅዱሳችሁ ስለ ፀሐይና ስለ ጨረቃ እንዲሁም ስለ ከዋክብት የተዘረዘሩት ሐሳቦች እውነት ናቸው የምትሉ ከሆነ ማስረጃችሁን አምጡ!! አለበለዚያ ግን መፀሐፍ ቅዱሳችሁ የፈጣሪ ቃል እንዳልሆነና ስህተት እንዳለበት ብዙው ተረት ተረት እንደሆነም አምናችሁ ስህተት ወደ ሌለበት የአላሕ ቃል ወደሆነው ቁርኣን ትመጡ እና እስልምናንም ትቀበሉ ዘንድ ጥሪዬ ነው። ፨፨፨ قُلْ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ تَعَالَوْا إِلَىٰ كَلِمَةٍ سَوَاءٍ بَيْنَنَا وَبَيْنَكُمْ أَلَّا نَعْبُدَ إِلَّا اللَّهَ وَلَا نُشْرِكَ بِهِ شَيْئًا وَلَا يَتَّخِذَ بَعْضُنَا بَعْضًا أَرْبَابًا مِّن دُونِ اللَّهِ ۚ فَإِن تَوَلَّوْا فَقُولُوا اشْهَدُوا بِأَنَّا مُسْلِمُونَ የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በእኛና በእናንተ መካከል ትክክል ወደ ኾነች ቃል ኑ፡፡ (እርሷም) አላህን እንጅ ሌላን ላንገዛ፣ በርሱም ምንንም ላናጋራ፣ ከፊላችንም ከፊሉን ከአላህ ሌላ አማልክት አድርጎ ላይይዝ ነው፤ በላቸው፡፡ እምቢ ቢሉም፡- እኛ ሙስሊሞች መኾናችንን መስክሩ በሏቸው፡፡ {ቁርኣን 3~64} https://t.me/eotc_degl

ቁርኣን ይጋጫልን? ክፈል ሁለት የመጀመሪያ ሙስሊም ማን ነው? በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው!!!! ይህ ጥያቄ አብዛኛውን ጊዜ ተጠይቆ ምላሽ የተሰጠበት ቢሆንም ተደጋግሞ ከመነሳቱ አንጻር ምላሹን ማቅረብ ስለሚኖርበት ኢንሻአላህ ከዚህ በታች መልሶችን ዘርዘር አድርጌ ለማንሳት እሞክራለሁ፡፡ በነኝህ ሰዎች ተደጋግሞ የሚነሳው ጥያቄ ታዲያ በብዙ ቦታዎች ላይ የተለያዩ ነብያት ሙስሊም እንደሆኑ ከተገለጸ በኋላ በሌላ ቦታ ደግሞ ነብዩ ሙሀመድ የመጀመሪያ ሙስሊም እንደሆኑ ይገልጻል ይህ አይጋጭም ወይ? የሚል ነው፡፡ አዎ በርግጥም አይጋጭም፡፡ ተከተለኝማ!||| አንቀጾችን ከታች ካስቀመጥን በኋላ ወደ ምላሹ እንዘልቃለን፡፡ ቁርአን ኢብራሂምን እስማኢልን ሙስሊም ይላቸዋል፡- Surah Al-Baqarah (البقرة), verses: 127 وَإِذْ يَرْفَعُ إِبْرَٰهِۦمُ ٱلْقَوَاعِدَ مِنَ ٱلْبَيْتِ وَإِسْمَٰعِيلُ رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّآ إِنَّكَ أَنتَ ٱلسَّمِيعُ ٱلْعَلِيمُ ኢብራሂምና ኢስማኢልም «ጌታችን ሆይ! ከእኛ ተቀበል፡፡ አንተ ሰሚውና ዐዋቂው አንተ ነህና» የሚሉ ሲኾኑ ከቤቱ መሠረቶቹን ከፍ ባደረጉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ ያእቆብና ልጆቹ ሙስሊሞችም ሙስሊም መሆናቸውን ይገልጻል፡- Surah Al-Baqarah (البقرة), verses: 132 وَوَصَّىٰ بِهَآ إِبْرَٰهِۦمُ بَنِيهِ وَيَعْقُوبُ يَٰبَنِىَّ إِنَّ ٱللَّهَ ٱصْطَفَىٰ لَكُمُ ٱلدِّينَ فَلَا تَمُوتُنَّ إِلَّا وَأَنتُم مُّسْلِمُونَ And Abraham instructed his sons [to do the same] and [so did] Jacob, [saying], "O my sons, indeed Allah has chosen for you this religion, so do not die except while you are Muslims." በተመሳሳይ እየሱስ እና ሐዋሪያቱ እንኳ ሙስሊሞች መሆናቸውን ይናገራል፡፡ ወደ ሐዋርያትም Surah Al-Ma’idah (المآئدة), verses: 111 وَإِذْ أَوْحَيْتُ إِلَى ٱلْحَوَارِيِّۦنَ أَنْ ءَامِنُوا۟ بِى وَبِرَسُولِى قَالُوٓا۟ ءَامَنَّا وَٱشْهَدْ بِأَنَّنَا مُسْلِمُونَ And [remember] when I inspired to the disciples, "Believe in Me and in My messenger Jesus." They said, "We have believed, so bear witness that indeed we are Muslims [in submission to Allah]." «በኔና በመልክተኛዬ እመኑ» በማለት ባዘዝኩ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «አመንን፤ እኛ ሙስሊሞች መኾናችንን መስከር» አሉ፡፡(አል-ማኢዳ ምዕ.4 ቁ.111) ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመጀመሪያ ሙስሊም እንደሆኑ የሚገልጽበት አንቀጽ ደግሞ Surah Al-An’am (الانعام), verses: 162 قُلْ إِنَّ صَلَاتِى وَنُسُكِى وَمَحْيَاىَ وَمَمَاتِى لِلَّهِ رَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ : Say, "Indeed, my prayer, my rites of sacrifice, my living and my dying are for Allah, Lord of the worlds. لَا شَرِيكَ لَهُۥ وَبِذَٰلِكَ أُمِرْتُ وَأَنَا۠ أَوَّلُ ٱلْمُسْلِمِينَ No partner has He. And this I have been commanded, and I am the first [among you] of the Muslims." ስግደቴ፣ መገዛቴም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው» በል፡፡ «ለእርሱ ተጋሪ የለውም፡፡ በዚህም (በማጥራት) ታዘዝኩ፡፡ እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ» (በል)፡፡ (ሱረቱ እል-አንአም ምዕ.6 ቁ.162-163) አሁን ወደ መልሱ እንዝለቅ 👇 በመጀመሪያ ኢስላም ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን እንመልከት፡-ኢስላም የሚለው ቃል ሁለት ትርጉሞች አሉት፡፡የመጀመሪያው እጅ መስጠት ያለ ተቃውሞ መታዘዝ የሚል ሲሆን በአረብኛው ኢስቲስላም ተብሎ ይጠራል፡፡ሁለተኛው ደግሞ ሰላም ማለት ነው ሲሆን በአጠቃላይ ኢስላም ማለት በአጭሩ ለእላህ ያለ ተቃውሞ በመታዘዝ እጅ በመስጠት ሰላምን መጎናጸፍ ማለት ነው፡፡» እስልምና ማለት ይህ መሆኑን ከተረዳን ሁሉም ነብያት ሙስሊሞች ነበሩ፡፡ ሁሉም ነብያት ለአላህ እጅ የሰጡ፤ለፈቃዱ ያደሩ፤ ትእዛዙን የተገበሩ በመሆናቸው በቁርአኑ አገላለጽ ‹‹ሙስሊሞች›› (ለአላህ ታዛዦች) ተሰኝተዋል፡፡ ኢብራሂም፣ ኢስማኢል፣ እየሱስ ሙሳ፣ የእየሱስ ሐዋሪያት፣ ዩሱፍና ሌሎችም በየዘመናቱ የነበሩ አማኞች ሁሉ ‹‹ሙስሊሞች›› የተባሉትም ከእዚህ አንጻር ነው፡፡ አምላክ ከጥንት ጀምሮ ለሰው ልጅ የመረጠው ሐይማኖትም እስልምና ብቻ ነው፡፡ እርሱም የአምላክን ትእዛዝ ያለ ተቃውሞ መሙላት ነው፡፡ ታዲያ ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) የመጀመሪያ ሙስሊም መሰኘታቸው ከምን አንጻር ነው ከተባለ የመጀመሪያነታቸው ከነበሩበት ማህበረሰብ አንጻር ነው የሚል ይሆናል፡፡ ተፍሲር ኢብን ከሲር ለአንቀጹ ማብራሪያ የሰጡትን ማብራያ ይመልከቱ፡፡ ለዚህ ንግግር ማስረጃው ምንድን ነው ከተባለ ሌሎችም ነብያቶች ተመሳሳይ ገለጻ ተጠቅመዋል የሚል ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ሙሳ የአምላከን አንድ ታአምር ባዩ ጊዜ እንዲህ ብለዋል፡- “ሙሳም ለቀጠሯችን በመጣና ጌታውም ባነጋገረው ጊዜ፡- «ጌታዬ ሆይ! (ነፍስህን) አሳየኝ ወደ አንተ እመለከታለሁና» አለ፡፡ (አላህም)፡- «በፍጹም አታየኝም ግን ወደ ተራራው ተመልከት፡፡ በስፍራውም ቢረጋ በእርግጥ ታየኛለህ» አለው፡፡ ጌታው ለተራራው በተገለጸ ጊዜ እንኩትኩት አደረገው:: ሙሳም ጮሆ ወደቀ፡፡ በእንሰራራም ጊዜ «ጥራት ይገባህ፡፡ ወዳንተ ተመለስኩ፡፡ እኔም (በወቅቱ) የምእምናን መጀመሪያ ነኝ» አለ፡፡” (ሱረቱ አል-አእራፍ ምዕ.7፡143) ሙሳ ይህንን ቃል ሲጠቀም ከሱ በፊት የነበሩ ነብያት አነ ኑህ አብርሀምና ሌሎችም ነብያትና ምዕመናን አማኞች አይደሉም ለማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን ከሙሳ ህዝብ አንጻር አላህ እንደማይታይ ካረጋገጡና ካመኑ ሰዎች መካከል ሙሳ የመጀመሪያነታቸውን ነው የሚገልጸው፡፡ ይህ አገላለጽ ቁርአን ውስጥ የተለመደ ነው፡፡ በማስረጃ እናድረገው:: የፊርአውን ደጋሚዎችም እንዲህ ብለዋል፡- «እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡» (ሱረቱ አል-ሹአራእ ምዕ.26፡51) የፊርአውን ደጋሚዎች የመጀመሪያ አማኞች መሆናቸውን ሲገልጹ ሙሳንና ወገኖችን አማኞች አይደሉም እያሉ አይደለም ከፊርአውን ወገኖች መካከል የመጀመሪያዎቹ አማኞች መሆናቸው መግለጻቸው ነው :: ስለዚህም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የሌሎች ነብያት እምነት የሆነውን እስልምና የሰበኩ ቢሆንም ከነበሩበት ትውልድ አንጻር የመጀመሪያ ሙስሊም መሆናቸው ነው፡፡ አንቀጹ በአጭሩ ሲብራራ ይህን ይመስላል፡፡ ግጭት ተብለው የሚፎከርባቸው ትችቶች እንዲህ ሲፍታቱ በዚህ መልኩ ገለባዎች(ክሶች) ናቸው፡፡ ወንድም አምዳላ ናሲር ሀሳብዎን 👉@amdala5👈 ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇 https://t.me/comparativeRelgion/392

ቁርኣን ይጋጫልን? ክፍል አንድ ከሰማይና ከምድር ቀድሞ የተፈጠረው ማነው? በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ አዛኝ በሆነው!!! አብዛኛውን ሰው የተጋጨ የሚመስለው ነጥብ ይህ ከላይ በርዕሱ ያስቀመጥኩት ጉዳይ ነው፡፡አንቀጾችን እናስቀመጥና እንድ ባንድ ለማየት እንሞክራን፡፡ ምድር ቀድማ ተፈጥራለች ለሚለው ሀሳብ የሚቀርበው የቁርአን አንቀጽ 2፡29 هو الذي خَلَقَ لَكُم مَّا فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثم استوى إلى السَّمَاءِ فَسَوَّاهُنَّ سَبْع حماوات ن وهو يكُن شَيْءٍ عَلِيمٌ [٢:٢٩] ‹‹እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ ሰማይ ቀድማ ተፈጥራለች ለሚለው ደግሞ 79:27 «ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡ ከፍታዋን አጓነ፤ እስተካከላትም፡፡ ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡ ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡›› 79፡27-30 ይህ ጥያቄ በሁለት መከራከሪያ ነጥቦች መመለስ ይቻላል፡፡ 1 ቀዳሚ መከራከሪያ ነጥብ የመጀመሪያው አንቀጽ ማለትም 2፡29 ምድርን አስመልክቶ የተጠቀመው ቃል ኸለቀ የሚል ነው፡፡ ትርጓሜውም ፈጠረ ማለት ነው፡፡ይህ ማስገኘትን የሚገልጽ ነው፡፡ ወደ ሁለተኛው አንቀጽ ስንመጣ ግን ማለትም 79፡27-30 ምድርን አስመልከቶ የሚጠቀመው ቃል «ደሀሀ የሚል ነው፡፡ ትርጓሜውም መፈጠርን ሳይሆን የሚገልጸው ዘረጋት-አስዋባት- አሳመራት የሚል ትርጓሜን ይዟል፡፡ግዙፉን የአረብኛ ዲክሽነሪ ሊሳኑል አረብን መመልከት ይቻላል፡፡ይህም ምድርን ስለመፍጠር ሳይሆን የሚገልጸው ከተፈጠረች በኋላ ስለተደረጉ ፊቸሪንግ ወይንም የማሳመር ስራዎች ነው፡፡ እነኝህም የሚፈልቁ ምንጮችን ማድረግ፣ጋራዎችን ማደላደል ወዘተ ማለት ነው፡፡ ይህንን ለመረዳት ቀጥሎ ያሉትን አንቀጾች ማየት በቂ ነው፡፡ ‹‹ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡ ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡ >> 79፡31-33 2 ሁለተኛ መከራከሪያ ነጥብ ከቃላት አጠቃቀም አንጻር ሱመ (ከዚያም) የሚለው ቃል በአረብኛ የቋንቋ አጠቃቀም የጊዜ ቅደም ተከተልን ብቻ አይገልጽም፡፡ይህ ቃል መጣ ማለት የግድ አንዱ ተግባር ከሌላው ተግባር ያለውን የጊዜ ቅደም ተከተል ይገልጻል ማለት ብቻ አይደለም፡፡ በአረብኛ ሰዋሰው መሰረት ሱመ የሚለው ቃል «በተጨማሪም, ወይንም /moreover} ለሚለው ቃል በትርጓሜነት ያገለግላል፡፡ ማስረጃውን በምስሌ በምሳሌ ማስቀመጥ እንችላለን፡፡ « ይህም ቀጥተኛ ሲኾን መንገዴ ነው፤ ተከተሉትም፡፡ (የጥመት) መንገዶችንም አትከተሉ፡፡ ከ(ቀጥተኛው) መንገዱ እናንተን ይለያዩዋችኋልና፡፡እነሆ ትጠነቀቁ ዘንድ በርሱ አዘዛችሁ፡፡ ከዚያም ለሙሳ በዚያ መልካም በሠራው ላይ (ጸጋችንን) ለማሟላት ነገርንም ሁሉ ለመዘርዘር መጽሐፉን (ለእስራኤል ልጆች) መሪና እዝነት ይኾን ዘንድ ሰጠነው፡፡ እነርሱ በጌታቸው መገናኘት ሊያምኑ ይከጀላልና፡፡>> 6:153 ቀጥተኛው መንገዴ የተባለው ቁርአን ሲሆን እዚህ ጋ አላህ(ሱ.ወ) ስለቁርአን ከገለጸ በኋላ በሱመ አያያዥነት ተውራትን አስከትሎ ገለጸ፡፡ ስለዚህ የጊዜ ቅደም ተከተል ቢሆን ኖሮ ከሱመ በፊት ቁርአን ሳይሆን መገለጽ የነበረበት ተውራት ነበር፡፡ ግን ሱመ እዚህ ጋር ለመግለጽ ስለነበር አገልግሎቷ ከቁርአን በኋላ ተገለጸች፡፡ ለዚህ እጅግ በጣም ብዙ የአረብኛ ሰዋሰው መጽሀፍትን በማስረጃነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ለአብነት ያክል አንዱን ልጥቀስ "Written Arabic - An Approach to the Basic Structures" by A.F.L. Beeston (cost about $25.00), Chapter 3, note 22, ማጠቃለያ በአጭሩ ቅደም ተከተሉ ሲተነተን በመጀመሪያ ምድር ተፈጠረች ነገር ግን አሁን ባለንበት መልኩ የተዘረጋች አልነበረችም፡፡ ከዚያም ቀጥሎ ሰማይ ተፈጠረች ከሰማይ መፈጠር በኋላ ምድር ተዘረጋች በዚህ መልኩ ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡ ጋራዎችም ተደላደሉ፡፡(ተፍሲር ኢብን አባስ) ምንጭ - ተፍሲር አድዋዕ አል በያን (0)16-18) Islam question and answer q-70217 Dr, Muhammed salih al-munajjid (ዌብሳይት) ወሏሁ አእለም!! ከኡስታዝ አቡ ዩስራ እና ከኡስታዝ የህያ ኢብን ኑህ የተዘጋጀ በተባባልነው መሰረት በክፍል ክፍል ስለሚናይ ትምህርቱ ተዳራሽነት እንዲኖረው ሼር ሼር በማድረግ ሁላችንም  የበኩላችንን ድርሻ እንወጣ #Share #share ወንድም አምዳላ ናሲር ሀሳብ እና አስተያየት ካለዎት 👉@amdala5 👈 እንደዚህ እና መሰል ትምህርቶችን ለመከላከል ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇👇 https://t.me/comparativeRelgion

← ውዳሴ ማርያም በአማርኛ: 7 ፭. ሁል ጊዜ ብርሃንነት ያለውን ፋና የተሸከምሽ የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ። ይኸውም ፋና የዓለም ብርሃን ነው። ጥንት ከሌለው ብርሃንም የተገኘ ብርሃን ነው። #ከእውነ
← ውዳሴ ማርያም በአማርኛ: 7 ፭. ሁል ጊዜ ብርሃንነት ያለውን ፋና የተሸከምሽ የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ። ይኸውም ፋና የዓለም ብርሃን ነው። ጥንት ከሌለው ብርሃንም የተገኘ ብርሃን ነው። #ከእውነተኛ አምላክ #የተገኘ #እውነተኛ አምላክ ነው። ያለ መለወጥም ከአንቺ ሰው የሆነው ነው። በመምጣቱም (ሰው በመሆኑም) በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለምንኖር ለእኛ አበራልን በልዩ የጥበቡ ምሥጢር በሥጋዌ የልቦናችንን እግር ወደ ሰላም መንገድ አቀናልን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን። አንደኘው አምላክ አንደኛውን አስገኘው በጥቅሱ መሰረት አስገኚው አንድ አምላክ ተገኚው አንድ አምላክ ድምሩ ሁለት አምላክ ይሄንን ደሞ ባይብል ይቃረነዋል 👇 " ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን? የአባቶቻችንን ቃል ኪዳን ለማስነቀፍ እኛ እያንዳንዳችን ወንድማችንን ስለ ምን አታለልን? " (ትንቢተ ሚልክያስ 2:10) መገኛት ሚችለው አምላክ መገኛት ማይችለውን አምላክ አስገኘ ማለት አላዋቂነት ነው😁😁😁 ወንድም አምዳላ ናሲር https://t.me/comparativeRelgion

← ሰይፈ ሥላሴ 1:፴፰ አሌፍ ቤት ጋሜል ዳሌጥ ፤ ሄ ዋው ዛይ ሔት ጤት ፤ ዮድ ካፍ ላሜድ ሜም ኖን ሳምኬት ዔ ፤ ፌ ፤ ጻዴ ቆፍ ፤ ሬስ ፤ ሳን ታው በሚባሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያ
← ሰይፈ ሥላሴ 1:፴፰ አሌፍ ቤት ጋሜል ዳሌጥ ፤ ሄ ዋው ዛይ ሔት ጤት ፤ ዮድ ካፍ ላሜድ ሜም ኖን ሳምኬት ዔ ፤ ፌ ፤ ጻዴ ቆፍ ፤ ሬስ ፤ ሳን ታው በሚባሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያመንኩ አቤቱ አምላኬ ሆይ ልመናየ ወዳንተ ትቀርብ ዘንድ እማፀናለሁ ። እግዚአብሔር ስሞች ነው ተባለ ትርግሙ ግን ለኔ ከሥላሴ ትምህርት ባሰብኝ😁😁😁 https://t.me/comparativeRelgion

ክርስቲያኖች ሰውን አምላክ ነው ብሎ  ማሳመን ሲከብዳቸው። ወደ ቁርኣን ገብተው በቁርኣናችሁ እኮ ዒሳ ሽባ ተርትሯል፣እውር አብርቷል ፣የአላህ ቃል ፣የአላህ መንፈስ ..... ማለት ጀመሩ። ይህም ብዙ ርቀት አላስኬድ ሲል። የቁርኣኑ ዒሳ ኢየሱስ አይደልም 😂 ነገር ግን የቁርኣኑ ዳዊት ፣ኑህ፣ሉጥ የመፅሀፍ ቁዱሱ አይደለም ሲሉ አንሰማምሳ  ለምን ይሆን? 👇 https://t.me/comparativeRelgion