fa
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Assaye Derbie

کانال Assaye Derbie (@asayede) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 337 مشترک است و جایگاه 2 647 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 350 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 337 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 25 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -108 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.62% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 538 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 808 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 26 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

14 337
مشترکین
-424 ساعت
-317 روز
-10830 روز
آرشیو پست ها
‹‹ግደሉ›› የሚሉትን ታቅፎ ‹‹አትግደሉ›› የሚሉትን አፋኙ መንግሥት‼️ አሳዬ ደርቤ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ቅስቀሳ የሚያደርጉ የመንግሥት አመራሮች፣ ፓስተሮችና በሐይማኖት ውስጥ የተደበቁ ተኩላዎች እኩይ አላማቸው በመንግሥት የሚደገፍ በመሆኑ በፍጹም ነጻነት በየሚዲያው እየወጡ ወለጋ ላይ በፈሰሰው የንጹሐን ደም ፈንታ ለተገደሉት ዜጎች የሚፈስሰውን እንባ እያወገዙ የጭፍጨፋውን ምክንያትና ተገቢነት ማስረዳታቸውን ቀጥለዋል፡፡ እኒህ ጸረ አማራ ኃይሎች ከ1600 በላይ ንጹሐንን ካስጨፈጨፉ በኋላም የተለመደ ቅስቀሳቸውን አጠናክረው ቢቀጥሉም የሚያበረታታቸው እንጂ የሚቆጣጠራቸው መንግሥት አገሪቷ ላይ የለም፡፡ በሌላ መልኩ ግን አሳፋሪው የአማራ ክልል መንግሥት ኦነጎች ወለጋ ላይ በፈጸሙት አረመኔያዊ ድርጊት የአማራ ፋኖዎችን እያፈነ ወደ ማጎሪያ ካምፕ ማስገባቱን አጠናክሯል፡፡ በአዲስ አበባም፣ በግፍ ለተጨፈጨፉ አማራዎች ኀዘናቸውን የሚገልጹትንና የተቃውሞ ድምጽ የሚያሰሙትን እየመረጡ የማሰር ዘመቻው በበላይ በቀለ ወያ ተጀምሯል፡፡ ከባድ መሣሪያ ታጥቀው፣ ግዙፍ ሠራዊት አደራጅተው የሥልጣን ትግል ከለኮሱትና ንጹሐንን ከሚጨፈጭፉት የትሕ-ኦነግ ኃይሎች ይልቅ ‹‹ዜጎችን አታስገድል›› የሚል ሰላማዊ ትግል የሚያሳስበው የብልጽግና መንግሥት ወንጀለኞችን ታቅፎ የሚቃወሙትን እያሳደደ ነው፡፡ ከዩኒቨርስቲ ተማሪ መሀከልም አሸባሪ እያፈላለገ ነው፡፡ በንጹሐን ላይ የሚፈጸመው እልቂት ሦስተኛውን ዙር የአባይ ግድብ ሙሊት ማደናቀፍ በሚፈልጉ የግብጽና የሱዳን ተላላኪዎች የሚፈጸም ነው›› በሚል መግለጫ ተላላኪዎቹንና ጨፍጫፊዎቹን አዝሎ፣ ግድቡን በአማራዎች ደም ሊሞላው ያሰበ ይመስል ‹‹ጭፍጨፋው ይቁም›› የሚሉ ድምጾችን ለማፈን ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ከእኛ የሚጠበቀው ሦስት ነገር ነው፡፡ 1. ወንጀል አለመሥራትና ሕግን አለመተላለፍ 2. ወንጀልን እና ወንጀለኛን በመቃወም የሚመጣን የትኛውንም እርምጃ ንቆ ማለፍ እና ደግሞ…. ተገቢነት በሌለው የአምባገነኖች ቅጣት አለመሸነፍ

ፍትሕ ኦነግ በፈጸመው ጭፍጨፋ ለታሠሩ አማራዎች ሁሉ‼️ ፍትሕ በግፍ ለተጨፈጨፉ 1600 ነፍሶች‼️ ፍትሕ ለመላው የአማራ ሕዝብ‼️
ፍትሕ ኦነግ በፈጸመው ጭፍጨፋ ለታሠሩ አማራዎች ሁሉ‼️ ፍትሕ በግፍ ለተጨፈጨፉ 1600 ነፍሶች‼️ ፍትሕ ለመላው የአማራ ሕዝብ‼️

"ይነጋል ባልነው ቀን ፣ ጨለማው ገነነ "አሻጋሪ" ያልነው ፥ አሸባሪ ሆነ !" ብሎ የገጠመው ፥ በላያ ታፈነ። የሕዝብ ድምጽ የሆኑ አንቂዎችንና ገጣሚዎችን በማፈን ላይ የሚገኘው አካል፣ ከሰሞኑን "በ
"ይነጋል ባልነው ቀን ፣ ጨለማው ገነነ "አሻጋሪ" ያልነው ፥ አሸባሪ ሆነ !" ብሎ የገጠመው ፥ በላያ ታፈነ። የሕዝብ ድምጽ የሆኑ አንቂዎችንና ገጣሚዎችን በማፈን ላይ የሚገኘው አካል፣ ከሰሞኑን "በማደንዘዝ ጥበብ" ዙሪያ ሥልጠና የሰጣቸውን አክቲቪስቶች ወደ ሥራ አስገብቷል።

መገን ብልጽግና‼️ ▬▬▬ ባለፈው የቆየ ቪዲዮ ለጥፎ ከ1600 በላይ አማራዎችን ደም አፈሰሰ። የሕዝብም ቁጣ ቀሰቀሰ። ተቃውሞው ሲበረታበትም፣ የሱዳን ወታደሮችን 6 አስከሬን ለጥፎ የ1600 ንጹሐን እልቂት የፈጠረውን ቁጣ ቀለበሰ። እና ደግሞ ሲገደል የከረመው የአማራ ሕዝብ የሚሞትበትን ጦርነት ለኮሰ። የብልጽግና ነገር ይገርማል‼️ ስትደግፈው ግጭት ለኩሶ ይጨፈጭፍኻል። የተረኛ እና የብሔርተኛ ማሊያ ለብሶ ያሳድድኻል። ስትቃወመው ደግሞ አገራዊ ጦርነት ቀስቅሶ ያሰባስብኻል። በዚያም ጦርነት ላይ እራስህን መከላከል ካልቻልክ ምድርህን አስወርሮ በሱዳን እጅ ወልቃይትን ለህውሓት የማቀበል ሥራ ይፈጽምብኻል ። ብርቱ ሆነህ ከተገኘህ ደግሞ በጦርነቱ እኩሌታ ላይ ከጠላት ጋር ቁጭ ብሎ ይደራደርብኻል። ወይም ደግሞ እራሱ የለኮሰውን ጦርነት ለብቻህ አሰረክቦህ ይሰወርብኻል። የሆነው ሆኖ... ይሄን መድረክ እንደ ናትናኤል መኮነንና ደረጀ ሃብተወልድ ላሉ የጦር መሪዎች አስረክቤ ከመውጣቴ በፊት "የወገኖቻችንን ነፍስ ፈጣሪ ይማር!" እላለሁ። መንግሥት በሚል ሥም ጠላት የተሸከመው ሕዝብም ወኪል አልባ መሆኑን አውቆ አምላክ ይጠብቀው ዘንድ እመኛለሁ።

photo content

photo content

የምዕራብ ወለጋው ጭፍጨፋ ከመከሰቱ በፊት በመንግሥት የተከናወኑ ተግባራት፦ አሳዬ ደርቤ ➔ የአማራ ድምጽ የሆኑ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ከእስር ቤት ታጎሩ፤ ➔ለብአዴን የግርድና ወንበር አስጊ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 12 ሺህ ፋኖዎች ታሰሩ፤ ➔እንደ ዮሐንስ ቧያለውና አቶ ገዱ ያሉ አፈንጋጭ አመራሮች ተቀነሱ፤ ➔ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፖርላማቸውን ሰብስበው ከመንግሥት ቀርቶ ከአክቲቪስት በማይጠበቅ የጥላቻ ንግግር ሕዝብን አነሳሱ፤ ➔ከወራት በፊት ኢሰመኮ በጸጥታ ኃይሎች መፈጸሙን ገልፆ እርምጃ እንዲወሰድ የጠየቀበት ቪዲዮ "በኦሮሞዎች ላይ ፋኖዎች የፈጸሙት" ተብሎ ሶሻል ሚዲያ ላይ ተለቀቀ፥ ➔ ከዚያም ከአንድ ሺህ በላይ አማራዎችን ያስጨፈጨፈው አካል በኅዘን ሳምንት ፈንታ የችግኝ ተከላ ሳምንት አውጆ እንጦጦ ጫካ ተደበቀ። እናም እልኻለሁ... ለተገደሉ ወገኖችህ ፍትሕን፣ በሕይወት ላሉት የመኖር መብትን የምትሻ ከሆነ ...ዋነኛ ጥያቄህ "በወገኖቼ ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ በገለልተኛ ወገን ይጣራልኝ" የሚል ይሁን!! ያን ጊዜ ቶሌ ላይ ያስገደለህን አካል ቦሌ ላይ ታገኘዋለህ! Share

መግደል መብት ሆኖ ፥ ለሽፍቶች ሲታደል መደበቁን ትተህ ፥ "እንቢኝ አትንኩኝ በል" ወልዲያ
+1
መግደል መብት ሆኖ ፥ ለሽፍቶች ሲታደል መደበቁን ትተህ ፥ "እንቢኝ አትንኩኝ በል" ወልዲያ

photo content

photo content

ጽሑፉ ከላይ ስላለ አንብቡት
ጽሑፉ ከላይ ስላለ አንብቡት

ማሩኝ›› የምትልበት ከመምጣቱ በፊት ‹‹በቃኝ›› በል! አሳዬ ደርቤ ይህቺን ሕጻን አስታወሳችኋት? ከመንፈቅ በፊት ከምዕራብ ወለጋ ጭፍጨፋ አምልጠው ከተፈናቀሉ አማራዎች ጋር ያገኟት ጋዜጠኞች ሲጠይቋት የሰጠችው መልስ እንደሚከተለው ነበረ፡፡ ‹‹ስምሽ ማን ነው?›› ‹‹አንሻ ሠኢድ›› ‹‹የት ነበር የምትኖሪው?›› ‹‹ዳንዴ ቀበሌ›› (ምዕራብ ወለጋ) ‹‹በምን ምክንያት ነው ያፈናቀሏችሁ? ‹‹ነፍጠኛ ናችሁ ነው የሚሉት›› ‹‹ነፍጠኛ ማለት ምን ማለት ነው?›› ‹‹ወላሂ አላውቀውም!›› በጣም የሚያሳዝነው ነገር ታዲያ ያን ጊዜ ይህቺ ሕጻን በየዋህ አንደበቷ ብሶቷን ስታወራን ባለመቆጣታችን እና ጥቃቷን ባለማስቆማችን የተነሳ በቅርቡ ደግሞ የአንሻን የመፈናቀል እድል የተነፈጋት ሕጻን ‹‹ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም›› የሚል ልመናዋ ዋጋ አጥቶ ከሺህ ከሚቆጠሩ አማራዎች ጋር ተገደለች፡፡ እይውልህ ወንድማለም…. ያለ መንግሥት ፍላጎት የሚፈጸምን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለማስቆም የመጀመሪያ እርምጃ የተፈጸመውን ወንጀል ዜጎች እንዲያወግዙትና እንዲማሩበት ማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛው እርምጃ ደግሞ ወንጀለኛውን መቅጣት ወይም ደግሞ ማጥፋት ነው፡፡ በአማራዎች ላይ የሚፈጸመው ጭፍጨፋ ግን በመንግሥት የሚቀነባበርና አገር አፍርሶ አዲስ አገር የመሥራት ግብ ያለው በመሆኑ በመቶዎችና በሺህዎች የሚቆጠሩ ንጹሐን በተገደሉበት እለት መንግሥት አትክልት ውስጥ ሲደበቅ ታየዋለህ፡፡ አንተ ‹‹ይሄን ያህል ሕይወት ከገበርን አይበቃም ወይ?›› እያልክ ስትጮህ እሱ ‹‹መቼ ተጀምሮ ነው የሚያበቃው›› የሚል ትርጓሜ ሊሰጠው በሚችል ዝምታ ያልተቀበረ አስከሬን ተራምዶ ችግኝ ሲተክል ትመለከተዋለህ፡፡ በክልሉ ውስጥ የፈጸመብህን ጥቃት የሚያስረሳ፣ ያንተን ሥም በክፉ የሚያስነሳና ለሌላ ዙር ጭፍጨፋ የሚያነሳሳ… በቪዲዮ የተደገፈ ጥቃት በክልልህ ውስጥ አቀናብሮ የወንጀሉ ተጋሪ ካደረገህ በኋላ እንባህን ቀምቶ ደምህን ሲያፈስስ ታገኘዋለህ፡፡ እናም እልኻለሁ… የተፈጸመብን ጉድ ወደፊት ከታቀደልን እቅድ ጋር ሲነጻጸር ኢምንት ነው፡፡ ያለፈው አረመኔያዊ ድርጊት ወደፊት ከሚከሰተው ጥፋት ጋር ሲወዳደር ምንም ነው፡፡ ‹‹አትንካኝ›› ብለህ መነሳት እስካልቻልክ ድረስ ከትንሽ ጊዜ በኋላ የአማራ ሕዝብን ቀርቶ ብአዴንን በሚያስደነግጥና ለመላው ዓለም በሚሰቀጥጥ አረመኔያዊ ማንነት ሲመጣ ታየዋለህ፡፡ ኦነግን ያጠፋዋል ብለህ ስትጠብቅ ብልጽግናን አክስሞ ቶሌ ቀበሌ ላይ ያየኸውን ዘግናኝ እልቂት ቦሌ ድረስ ሲያመጣው ትታዘባለህ፡፡ አሁን ላይ እንደ ሕዝብ ‹‹ወገኔን አትግደሉ›› ብሎ መቆጣት የሚያመጣውን እስራት ፈርተህ ስትርመጠመጥ፣ የሆነ ጊዜ ላይ በቤተሰብና በግለሰብ ደረጃ ከአፈሙዝ ስር ተንበርክከህ ‹‹እባካችሁ እኔን አትግደሉኝ›› እያልክ ስትማጸን እራስህን ታገኘዋለህ፡፡ እናም ይህ እንዳይሆንብን የምንሻ ከሆነ፣ እጅና እግራችንን አስረው ከገጀራ ስር ሊጥሉን የሚሞክሩ የክልል አመራሮችን እና ፖለቲከኞችን ‹‹ይሄን ማድረግ አትችሉም›› እንበላቸው፡፡ እራሳችንን አንቅተን ሕዝባችንን እንቀስቅሰው፡፡ ሥልጣን ላይ ያለው ኃይል ከፋፍሎ ሊውጠን ሲያስብ አንድ ሆነን እንትፋው፡፡ እስካሁን ለጥፋት የዳረገን አስተሳሰብ ‹‹ወገኔን አትንኩብኝ›› በሚል ሕዝባዊ ቁጣ አስፈሪ ሆነን በመገኘት ፈንታ ‹‹እኔን ምን አገባኝ›› በሚል የፍርሐት አሮንቃ ውስጥ መዘፈቃችን ነውና በጅምላ የታወጀብንን እልቂት በጋራ እናክሽፈው፡፡ share

photo content

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች "የአማራዎች እልቂት የምክር ቤቱ አጀንዳ የሚሆነው ስንት ንጹሐን ሲገደሉ ይሆን?" እያሉ ነው።
+2
የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች "የአማራዎች እልቂት የምክር ቤቱ አጀንዳ የሚሆነው ስንት ንጹሐን ሲገደሉ ይሆን?" እያሉ ነው።

photo content

አዲስ አበባ ላይ ኮሽታ ሲፈጠር ሽንት በሽንት የሚሆነው አካል "አትጨፍጭፈን" የሚል መፈክር ይዘው የወጡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ጨፍጭፎ በትኗቸዋል። #እምቢኝ_በል-አማራ‼️
+1
አዲስ አበባ ላይ ኮሽታ ሲፈጠር ሽንት በሽንት የሚሆነው አካል "አትጨፍጭፈን" የሚል መፈክር ይዘው የወጡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ጨፍጭፎ በትኗቸዋል። #እምቢኝ_በል-አማራ‼️

photo content

photo content

እነዚህ ጋር አብሬ ባንድ አገር መኖር አልችልም! 😭