fa
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Assaye Derbie

کانال Assaye Derbie (@asayede) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 337 مشترک است و جایگاه 2 647 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 350 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 337 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 25 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -108 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.62% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 538 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 808 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 26 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

14 337
مشترکین
-424 ساعت
-317 روز
-10830 روز
آرشیو پست ها
"የኦሮሞ ደም ከእኔ ጅስም የሚቀዳ ነው" በሚል መፈክር ዙፋን አስረክባ ከፈን በተቀበለችው የጎንደር ከተማ "ደማችን በእጃችሁ አለ" የሚል ቁጣ እየተሰማ ነው‼️ ብራቮ ጎንደር ዩኒቨርስቲ! እምቢኝ‼️
+2
"የኦሮሞ ደም ከእኔ ጅስም የሚቀዳ ነው" በሚል መፈክር ዙፋን አስረክባ ከፈን በተቀበለችው የጎንደር ከተማ "ደማችን በእጃችሁ አለ" የሚል ቁጣ እየተሰማ ነው‼️ ብራቮ ጎንደር ዩኒቨርስቲ! እምቢኝ‼️

photo content

photo content

photo content

የጠመንጃ አያያዛቸውን እና አስተያየታቸውን ስትመለከት ከስራቸው ያለው ዝሆን እንጂ በእነሱ አምሳያ የተፈጠረ ሕፃን አይመስልህም‼️ የምር እላችኋለሁ ይሄንን ፎቶ ስመለከት ከሕፃኑ ልጅ በላይ ያሳዘኑኝ
የጠመንጃ አያያዛቸውን እና አስተያየታቸውን ስትመለከት ከስራቸው ያለው ዝሆን እንጂ በእነሱ አምሳያ የተፈጠረ ሕፃን አይመስልህም‼️ የምር እላችኋለሁ ይሄንን ፎቶ ስመለከት ከሕፃኑ ልጅ በላይ ያሳዘኑኝ እነሱ ናቸው።

ይሄንን እጅ እዩት ፥ ይሄንን ጣት እዩት አሻራው ላይ አለ ፥ ሰባት መቶ ሕይወት። ዛሬ በሥልጣኑ ከአስከሬን መሀከል ፥ ማዘንን ቢነፍግም ባይገነዝ እንኳን በካቴና ታስሮ ፥ መታየቱ አይቀርም።
ይሄንን እጅ እዩት ፥ ይሄንን ጣት እዩት አሻራው ላይ አለ ፥ ሰባት መቶ ሕይወት። ዛሬ በሥልጣኑ ከአስከሬን መሀከል ፥ ማዘንን ቢነፍግም ባይገነዝ እንኳን በካቴና ታስሮ ፥ መታየቱ አይቀርም።

በሕይወት የቆየሁኝ እኩዮቼ ከሚገደሉበት አካባቢ ስላልተገኘሁ ነው‼️ ፍትሕ በወተት ፈንታ ጥይት በሚጋብዙ ጀግና አባቶች ለተገደሉ እኩዮቼ!
በሕይወት የቆየሁኝ እኩዮቼ ከሚገደሉበት አካባቢ ስላልተገኘሁ ነው‼️ ፍትሕ በወተት ፈንታ ጥይት በሚጋብዙ ጀግና አባቶች ለተገደሉ እኩዮቼ!

የአገሪቷን ጫካዎች ሁሉ... የሕፃናት መታረጃ ቄራ ያደረገ መንግሥት ስለ አረንጓዴ ልማት ጉዳት እንጂ ስለ ጠቀሜታው የሚያወራበት ሞራል የለውም‼️ #በቃን!
የአገሪቷን ጫካዎች ሁሉ... የሕፃናት መታረጃ ቄራ ያደረገ መንግሥት ስለ አረንጓዴ ልማት ጉዳት እንጂ ስለ ጠቀሜታው የሚያወራበት ሞራል የለውም‼️ #በቃን!

photo content

የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች አረመኔውን ሥርዓት አውግዘዋል።
የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች አረመኔውን ሥርዓት አውግዘዋል።

ያን የመሰለ ሥምህን እና ተጽዕኖ ፈጣሪነትህን ወርውረህ የጨፍጫፊ መንግሥት አማካሪ እስከሆንክ ድረስ "ጨፍጭፋቸው ብዬ አልመከርኩም" ማለት አትችልም‼️ ስለዚህ... የወገኖቻችን ደም በእጅህ አለ‼️
ያን የመሰለ ሥምህን እና ተጽዕኖ ፈጣሪነትህን ወርውረህ የጨፍጫፊ መንግሥት አማካሪ እስከሆንክ ድረስ "ጨፍጭፋቸው ብዬ አልመከርኩም" ማለት አትችልም‼️ ስለዚህ... የወገኖቻችን ደም በእጅህ አለ‼️

ለብአዴን እንኩቶዎች ‼️ አሳዬ ደርቤ የአማራ ባንክ ሥራ በጀመረበት ቀን በኦሮሚያ ክልል ከተጨፈጨፉ አማራዎች መሀከል እስካሁን የ614 አማራዎች አስከሬን ተቀብሯል፡፡ እናንተ ግን በኦሮሚያ ክልል ከተነጠፈው አስከሬን ይልቅ በአማራ ክልል ውስጥ የሚገለጽ ኀዘን የአገርን ሕልውና ያጠፋ ይመስል የሚሠራውን የማያውቅ ማቶ ተከትላችሁ መንዘላዘሉን ቀጥላችኋል፡፡ እውን ግን እናንተ ከአማራ አብራክ ወጥታችሁ፣ በአማራ ባሕል ያደጋችሁ አማራዎች ናችሁ? በፍጹም‼️ በሕይወቱ ፈንታ አሟሟቱ ያምር ዘንድ ከሚጸልየው ሕዝብ አብራክ የወጣችሁ ብትሆኑ ኖሮማ ኀዘኑን በማድበስበስ ፈንታ ፍትሕን አረጋግጣችሁ ደሙን ታብሱ ነበር፡፡ ‹‹ቀብሬን አሳምረው›› እያለ እድር ሲመሠርት የኖረው ሕዝብ በራቢስ እንደተለከፈ ውሻ በጅምላ መቃብር ውስጥ ሲገባ ድምጻችሁን አጥፍታችሁ አትመለከቱም ነበር፡፡ እውን ግን እናንተ የአማራን ሕዝብ የምትወክሉ አመራሮች ናችሁ? በፍጹም‼️ አመራር ብትሆኑ ኖሮማ ኃላፊነታቸውን ወደ ጎን ትተው ግድያውን ያስፈጸሙ ባለሥልጣናት ቀብረር ብለው በኩራት ሲራመዱ እንደ ወንጀለኛ አንገት ደፍታችሁ ከኋላ ከኋላ አትከተሉም ነበር፡፡ እኔ እምለው ግን... ሞራላችሁን፣ ማንነታችሁን፣ ኅሊናችሁን፣ ጥላችሁ በፈርስ የተሞላ ጨጓራሁን እያሻሻችሁ ሕዝባችሁን ለማዋረድና በጅምላ ለማረድ አቅደው ከሚንቀሳቀሱ አረመኔዎች ጎን የምትርመጠመጡት ምኑ እንዳይቀር ፈርታችሁ ነው? ‹‹ሥልጣናችን እንዳይቀርብን›› እንዳትሉ መናገርን፣ ማዘንን፣ ማሰብን፣ ሰዋዊ ሥሜትን፣ የሚነጥቅ ሥልጣን ባርነት እንጂ ሹመት አይባልም፡፡ እኒህን ሁሉ ሰዋዊ ባሕርያት ያጣ ሰው የመቃብር ሳጥን ውስጥ የተጋደመ አስከሬን እንጂ ከአገር ወንበር ላይ የተሾመ ባለሥልጣን አይባልም፡፡ ባንድ ወቅት የቀድሞ ጌታችሁ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ አፈናውን ማጧጧፍ ሲያስብ ከኦሮሚያ ክልል የወጡ የሕዝብ ተወካዮች አዋጁን ሲቃወሙ እናንተ ግን እጃችሁን ወደላይ ከዘረጋችሁ በኋላ አንገታችሁን ወደ ኋላ አዙራችሁ በግርምትና በፍርሀት ስሜት ስትመለከቷቸው ነበር፡፡ ትናንትናም በዚያው ምክር ቤት ውስጥ ‹‹የሰባት መቶ አማራ ሞት ለአጀንዳ አይበቃም›› ሲባል መቃወሙ ቀርቶባችሁ ዳፍንት እንደያዘው በግ ዐይናችሁን አንሸዋራችሁ በዶክተር ደሳለኝ ድፍረት ስትገረሙ ነበር፡፡ አፈር ብሉ አቦ! የአማራ ሕዝብ ከሌሎች ባያስበልጡት እንኳን እኩል የሚያደርጉት ሁሉም ጸጋዎች አሉት፡፡ እራሱን አስከብሮ ለመኖር የሚያስችል እውቀትም ሆነ ሐብት፣ የሕዝብ ብዛትም ሆነ የዳበረ እሴት አለው፡፡ ሆኖም ግን የሌሎች ክልል ወገኖቹ የሚወክሏቸውንና የሚታገሉላቸውን ልጆች ወልደው መንግሥት ሲያደርጉ ‹‹የሚከፋፍሉህንና የሚሸጡህን ወልደህ ተዋረድ›› ተብሎ የተረገመው የአማራ ሕዝብ ግን በመንግስት ወንበር ላይ እንደ እናንተ ያለ ጠላት በመሾሙ የተነሳ የማንም መቀለጃ ሆነ፡፡ ትናንት ክልሉ ሲወረር ከበላይ አካል ባገኛችሁት ፍቃድ ‹‹ተነስ›› ስትሉት ጨርቄን ማቄን ሳይል የተነሳውን ፋኖ ከተጠቀማችሁበት በኋላ ሕጋዊ ሆኖ የሚቀጥልበትን መንገድ በማመቻቸት ፈንታ ከዚያው አካል በመጣ መመሪያ መሠረት ‹‹ሕገ-ወጥ›› ተብሎ በአስር ሺህ የሚቆጠር ፋኖ በዘራፊ እጃችሁ ታፈነ፡፡ በቅርቡ ደግሞ በሕይወት መኖር የከለከላቸውን ሰባት መቶ አማራዎች ወደ መቃብር ያወረደው ኃይል ‹‹ለሞቱ ሰዎች ሲደረግ የነበረው የለቅሶ ባሕል ችግኝ በመትከል ተቀይሯል›› የሚል አዋጅ በማውረዱ የተነሳ ይሄንኑ ተግባራዊ ለማድረግ እየተንደፋደፋችሁ ነው፡፡ ሆኖም ግን ልታዋርዱት የምትሞክሩት ክቡር ሕዝብ ይሄን ውዳቂ አስተሳሰባችሁን የሚሸከምበት ጫንቃ ስለሌለው የኀዘን ቀን አውጃችሁ፣ ባንድራ ዝቅ አድርጋችሁ ተቃውሞውን እና ኀዘኑን በሰላማዊ መንገድ እንዲገልጽ ማድረግ ይኖርባችኋል፡፡ ያንን ማድረግ ካልቻላችሁ ግን በቀጣይ ቀናት ያለእናንተ ይሁንታ ወደ አደባባይ ወጥቶ ኀዘኑን ብቻ ሳይሆን ቁጣውንም ጭምር የሚገልጽ ይሆናል፡፡

photo content

በባሕር ዳር ከተማ የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች በማንነታቸው ለተጨፈጨፉት ድምፅ እያሰሙ ነው! በሁሉም ቦታዎች ተጠናክሮ ይቀጥል።
በባሕር ዳር ከተማ የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች በማንነታቸው ለተጨፈጨፉት ድምፅ እያሰሙ ነው! በሁሉም ቦታዎች ተጠናክሮ ይቀጥል።

በትሕነግ የሥልጣን ዘመን ብአዴኖች ሁለት ጊዜ አልቅሰዋል። መለስ ዜናዊ ሲሞት እና ዶክተር ቴዎድሮስ ለዓለም የጤና ድርጅት ሲመረጥ፤ በኦነግ ጊዜ ደግሞ የእነ ዳግማዊት ብልጽግና አምርሮ ሲያለቅስ የታየ
በትሕነግ የሥልጣን ዘመን ብአዴኖች ሁለት ጊዜ አልቅሰዋል። መለስ ዜናዊ ሲሞት እና ዶክተር ቴዎድሮስ ለዓለም የጤና ድርጅት ሲመረጥ፤ በኦነግ ጊዜ ደግሞ የእነ ዳግማዊት ብልጽግና አምርሮ ሲያለቅስ የታየው አንድ ጊዜ ሲሆን... እርሱም ሰላም ያሳጣን መሪ የሰላም ኖቬል የተሸለመ ቀን ነበር። እንኩቶዎች‼️

photo content

photo content

የአራት ዓመቱ ሲቃ ፤ በአራት ደቂቃ ሙዚቃ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ‹‹ብልጭልጭ ቢሆን ዳሱ ማን ሊታደም ከድግሱ›› በሚል አዝማች የብልጽግናን እቃቃ አናንቆታል። ‹‹ዘር ያወረው ድንበር- ማላውን የረሳ ሳ
የአራት ዓመቱ ሲቃ ፤ በአራት ደቂቃ ሙዚቃ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ‹‹ብልጭልጭ ቢሆን ዳሱ ማን ሊታደም ከድግሱ›› በሚል አዝማች የብልጽግናን እቃቃ አናንቆታል። ‹‹ዘር ያወረው ድንበር- ማላውን የረሳ ሳር ያለመልማል ዛሬም - በእልፍ አእላፍ ሬሳ›› በሚል ስንኝ ከሚነጠፈው ሳር ሥር የጅምላ መቃብር መኖሩን መስክሯል፡፡ ‹‹ተናገር አፌ ደፍረህ -ሳትናወጥ ቀርቶ ዝም አይሆንም ሜዳ ፥ ተራራ ሞት መጥቶ›› በማለት አፋቸውን ለጉመው የተቀመጡ ሰዎችን መከሯል፡፡ ‹‹ትንሽ ጋብ እንዳለ - የጭብጨባ ጩኸት እረጭ ሲል ውሸት - ይናገራል እውነት›› በሚል ስንኝ ከቀልማዳ አንደበት ውስጥ የሰው እውነተኛ ማንነት ይፋ እንደሚወጣ ይናገራል፡፡ (ይሄም በሌላ መልኩ ሲገለጽ ልክ እንደ ባለፈው የፓርላማ ንግግር ማለት ነው) ‹‹ቂምን ሻረውና- ወይ ፍቅርን አንግሰው ሁለት ሆኖ አያውቅም- አንድ ነው አንድ ሰው፡፡›› በሚል ግጥም እንደ እስስት መልኩን የሚለዋውጠውን አካል ከፍቅርና ከጥላቻ መሀከል ይመርጥ ዘንድ መክሮታል፡፡ ‹‹እያመመው መጣ›› እያመመው መጣ! እያመመው መጣ!›› በሚል አዝማችም ብልጽግና ያመጣብንን ሕመም በሚገርም ዜማ ዘፍኖታል፡፡ ጃንሆይ በልባችን ውስጥ ሺህ ዓመት ንገሥ!

ዘውግ ያወረው ድንበር ፥ መሀላውን የረሳ ሳር ያለመልማል ዛሬም ፥ በእልፍ አእላፍ ሬሳ ንጉሡ!!
ዘውግ ያወረው ድንበር ፥ መሀላውን የረሳ ሳር ያለመልማል ዛሬም ፥ በእልፍ አእላፍ ሬሳ ንጉሡ!!

Share አድርገው!! በወለጋ አካባቢ የሚኖሩ ወገኖቻችን መንግሥት እስከፈቀደላቸው ቀን ድረስ ኖረው ተጨፈጨፉ፡፡ በሰዓታት ጥቃትም ከሰባት መቶ በላይ ንጹሐን ተቀጠፉ፡፡ ይሄው አካል በሰጠን ነጻነት ል
Share አድርገው!! በወለጋ አካባቢ የሚኖሩ ወገኖቻችን መንግሥት እስከፈቀደላቸው ቀን ድረስ ኖረው ተጨፈጨፉ፡፡ በሰዓታት ጥቃትም ከሰባት መቶ በላይ ንጹሐን ተቀጠፉ፡፡ ይሄው አካል በሰጠን ነጻነት ልክ የምንንቀሳቀሰው ብሎም በተፈቀደልን መጠን ልክ ኀዘናችንን የምንገልጸው እኔ እና አንተ ደግሞ ወገኖቼን አስጨፍጭፈኻል ተብሎ ሊወገዝ የሚገባው አካል ጥቃቱን እንዲያወግዝልን እና የኀዘን ቀን እንዲያውጅልን በመለማመጥ ላይ እንገኛለን! የለም የለም ወንድማለም! በቁጥር ሲሰላ ከአንድ ቀበሌ ነዋሪ የሚበልጥ ሕዝብ የተጨፈጨፈበትና የዓለም ሚዲያዎች ‹‹የሰው ልጅ እንደ ዶሮ መቀላቱን ገልጸው ያወገዙት ጥቃት የደረሰበት አካል ወደ አደባባይ ወጥቶ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ኀዘኑንም ሆነ ተቃውሞውን መግለጽ መብቱ ብቻ ሳይሆን ግዴታውም ጭምር ነው፡፡ ስለዚህ የሱፍ ኢብራሒም እንዳለው የታወጀብንን የዘር ማጥፋት ለማስቆም ጠንካራ ትግል የሚጠይቅ ቢሆንም ይሄን ትግል ግን ሰላማዊ በተቃውሞ ሰልፍ መጀመር ይኖርብናል፡፡ እንዲህ አይነት ሐሳብ ሲመጣ የተቃውሞ ሰልፍ ትርጉም አልባ መሆኑን የሚነግሩን ኃይሎች ዋነኛ ዓላማ የታወጀብን ማለቂያ የለሽ እልቂት በፌስቡክ ፖስት ተወስኖ እንዲቀር ማድረግ ነውና እነሱን ሳትሰማ ለሟች ወገኖቻችን ኀዘናችንን፣ ለገዳዮቹ ደግሞ ቁጣችንን የምንገልጽበት የአደባባይ መድረክ መፍጠር ግድ ይለናል፡፡ ሼር እና ፖስት በማድረግ ለሌሎች አጋሩት፡፡