fa
Feedback
Joseph Math Tutor

Joseph Math Tutor

رفتن به کانال در Telegram

Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580

نمایش بیشتر
1 855
مشترکین
+424 ساعت
+107 روز
+5030 روز
آرشیو پست ها
የካቲት 12/ 1929 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማና በዙሪያዋ የሚኖሩ ሰላማዊ ንፁሃን ኢትዮጵያዊያን ያለምንም የብሔር ፣ የሀይማኖት ፣ የፆታ እና የእድሜ ልዩነት በፋሺሽት ጣሊያን ጥቁር ሸሚዝ በለበሱ ወታደሮች ነውርና ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ሺዎች በመትረየስ አረር ተቆሉ ። በርካቶች ቤት ተዘግቶባቸው በቃጠሎ ከሰሉ ። በመኪና ተጎተቱ ። በአካፋ ተጨፈጨፉ ። ወደ ገደል ተወረወሩ ። በሌላም ብዙ የጭካኔ መንገድ ዜጎች እንደ ቅጠል ረገፉ ። የአዲስ አበባ ጎዳኖዎች በደም አባላ ጨቀዩ ። ወንዞቿ በደም ጎርፍ ቀሉ ። ጅቦችና አሞራዎች የሠውን ስጋ ለቀናት ተመገቡ ። .... መቼም አንረሣውም ! ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ለየካቲት 12 ሰማዕታት !

የካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ "አዲስ አበባን ቄራ አደረጓት" #Ethiopia | የዕለቱን ሁኔታ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ 'የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983' በሚለው መፅሐፋቸው እንዲህ ይተርኩ
+1
የካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ "አዲስ አበባን ቄራ አደረጓት" #Ethiopia  | የዕለቱን ሁኔታ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ 'የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983' በሚለው መፅሐፋቸው እንዲህ ይተርኩታል። " ... "ጥቁር ሸሚዝ" እየተባሉ የሚታወቁት የፋሽስት ደቀመዛሙርት በፋሽስቱ አገዛዝ አይዞህ ባይነት አዲስ አበባን ቄራ አደረጓት። የሠው ልጅ ጭንቅላት እንደ ዶሮ እየተቀነጠሰ ወደቀ። ቤቶች ከነነዋሪዎቻቸው ጋዩ። እርጉዝ ሴቶች በሳንጃ ተወጉ። የጭፍጨፋው ተቀዳሚ ዒላማ የተማሩ ኢትዮጵያውያን ነበሩ። በተለይም የጥቁር አንበሳ አባላት ከራስ እምሩ ጋር እጃቸውን ከሰጡ በኋላ በከተማይቱ ይገኙ ስለነበር በወረንጦ እየተለቀሙ ተረሸኑ። ይህ የምሁራን ጭፍጨፋ አንድ ትውልድ እንዳለ ያጠፋ በመሆኑም በሃገሪቱ የፖለቲካና ምሁራዊ ታሪክ ላይ የማይሻር ቁስል ጥሎ አለፈ።" በዚህ ዘግናኝ ጭፍጨፋ በሶስት ቀናት ውስጥ ብቻ ከ30 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን መስዋዕትነት ተቀበሉ። በሌላ በኩል ይሄ ጭፍጨፋ ሲወላውል የነበረውን፣ መሃል ሠፍሮ የነበረውን፣ "ጣልያኖች ቢያስተዳድሩን ምን ችግር አለው?" .....  ይል የነበረውን ኢትዮጵያዊ በሙሉ ለአንድ ዓላማ አብሮ እንዲቆምና 'ዱርቤቴ' እንዲል ያደረገ ክስተትም ነበር። #ክብር_ለሰማዕታት!

Practice Properly
Practice Properly

Applied ii chapter 1 part 3.pdf1.65 KB

Fallacy Proof 1+1=3

photo content

Solution
+2
Solution

Practice Properly
Practice Properly

Chapter 1 part 2

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ በታሰበው ዕቅድ ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሊያደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
+1
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ በታሰበው ዕቅድ ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሊያደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ መንግሥት ዕቅድ መያዙ ይታወቃል፡፡ በዕቅዱ ላይ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት ቢደረግም፤ ከክልሎች፣ ከትምህርት ቤቶች እና ከፀጥታ አካላት ጋር ውይይት አለመካሔዱን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ መንግሥት "ዕቅዱ ተግባራዊ ይሆናል ብሎ እስካሁን ውሳኔ አለማሳለፉን" የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በቀጣይ ሳምንታት ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና የሕዝብ ተወካዮችን ጨምሮ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ይደረጋል ብለዋል፡፡ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በተደረገው ውይይት ከሎጂስቲክስ እና ከአካዳሚክ ጉዳዮች ጋር እንዴት ይጣጣማል በሚለው ላይ ጥያቄ ከማቅረብ ውጪ፤ "ሀሳቡ ተግባራዊ ቢሆን እንደሚደግፉት" መግለጻቸውን ጠቅሰዋል። ከውይይቱ በኋላ ሀሳቡ ለፓርላማ እንደሚቀርብና የራሱ የሆነ ተቋም ተቋቁሞለት ሕግ ይወጣለታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኮራ አስረድተዋል። ዕቅዱ ተቀባይነት ካገኘ በ2019 ዓ.ም እንደሚተገበር ይጠበቃል ብለዋል፡፡ ሆኖም በውይይቱ ወቅት ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የትምህርት ማኅበረሰቡ ዕቅዱን ካልፈለገው የሚቀርበት ሁኔታ እንዳለም ጠቁመዋል፡፡ #ሪፖርተር

Chapter 1 Part 1

Solution
+3
Solution

Correction #5. B (n+1/n)

Practice Properly
Practice Properly

#URGENT 🔔 #ATTENTION‼️ #WARNING ⚠️ ባይረጋገጥም አንድ መረጃ በሰፊው እየተሰራጨ ይገኛል። ይህም የቴሌግራም Privacy & Security ላይ ችግር ተፈጥሯል የሚል መረጃ ሲሆን
#URGENT 🔔 #ATTENTION‼️ #WARNING ⚠️ ባይረጋገጥም አንድ መረጃ በሰፊው እየተሰራጨ ይገኛል። ይህም የቴሌግራም Privacy & Security ላይ ችግር ተፈጥሯል የሚል መረጃ ሲሆን random የሆኑ አካውንቶች ፣ ግሩፖች እና ቻናሎች target እየተደረጉ ነው እየተባለ ነው። ተጨማሪ መረጃ ከፎቶው ላይ መመልከት ትችላላችሁ። ስለዚህ አሁኑኑ ይህንን አድርጉ 👇 1. የአካውንታችሁን profile picture ማን ማየት እንዳለበት የምታስተካክሉበት setting ላይ My Contacts ወይም Nobody አድርጉት። ወይም ደግሞ ለጊዜው አጥፉት እና ባዶ ይቀመጥ። እዛው setting ላይ እንደ ስልክ ቁጥር ያሉ መረጃዎችንም ሌላ ሰው እንዳያይ አድርጉ። 2. የአካውንታችሁን Username ቀይሩ። 3. ቻናል ወይም ግሩፕ ካላችሁ cover ፎቶአቸውን አጥፉ። 4. የአካውንታችሁን password ቀይሩ። 5. Two step verification አብሩ። Recovery email ካላስገባችሁ አስገቡ እናም ሌላ ማድረግ አለብኝ የምትሉትን ነገር አድርጉ። እውነት እንደሆነ አልተረጋገጠም። ነገርግን እውነት ሊሆን ስለሚችል መጠንቀቁ አይከፋም። እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ ምንም ችግር የማይፈጠር ከሆነ ሁሉንም ወደቦታው ትመልሳላችሁ። እኛም አዲስ መረጃ ለማግኘት ጥረት እናደርጋለን። #SHARE‼️

+7
Physics - Oromia 2017 1st semester model.pdf8.84 KB

+9
SAT EXAM FINAL.pdf7.26 KB

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ይሰጣል። - ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ለ
+1
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ይሰጣል። - ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገልፀዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት የመልቀቂያ ፈተናው በወረቀት እና በበይነ መረብ ሲሰጥ እንደነበር፣ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግማሽ ዓመት አፈጻጸም መድረክ ላይ የተገኙት ሚኒስትሩ አስታወሰዋል፡፡ ዘንድሮ ፈተናውን ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት የተለያዩ ግብዓቶች ለክልሎች ድጋፍ እየተደረገ ሲሆን፤ በፈተና ጣቢያዎች በቂ የኢንተርኔት አቅርቦት እንዲኖር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመነጋገር ይሠራል ብለዋል። ክልሎች በቂ ኮምፒዩተር፣ ኔትዎርክ እና አማራጭ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በትኩረት እንዲዘጋጁ ያሳሰቡት ሚኒስትሩ፤ ለተማሪዎች በቂ ስልጠና መስጠት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በዚህም የክልል እና የከተማ መስተዳድሮች ሀገር አቀፍ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን እንደሚሰጥ አውቀው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል። በ2017 ዓ.ም ለመልቀቂያ ፈተናው ከተቀመጡ 585,882 ተማሪዎች መካከል 134,609 ወይም 23% ያህሉ ፈተናውን በኦንላይን የወሰዱ መሆናቸው ይታወሳል፡፡