fa
Feedback
DERARTU TULU GENERAL SECONDARY SCHOOL/ ደራርቱ ቱሉ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት/ Mana Barumsaa Daraartuu Tulluu Sadarkaa Lammaffaa Waliiga

DERARTU TULU GENERAL SECONDARY SCHOOL/ ደራርቱ ቱሉ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት/ Mana Barumsaa Daraartuu Tulluu Sadarkaa Lammaffaa Waliigalaa

رفتن به کانال در Telegram
5 437
مشترکین
-224 ساعت
+287 روز
+9330 روز
آرشیو پست ها
ቀን: 23/11/2018 ዓ.ም ለ9 -10ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ የመጽሐፍ መመለሻ መርሃ ግብር 1. Grade 9 — Monday/27/11/2018 morning 2:30 up to 9:00 Only. 2. Grade 10. - Tuesday 28/11/2018 Morning 2:30 up to 9:00 only ማሳሰቢያ 1. ሁሉም ተማሪዎች በተመደበላቸው ቀንና ሰዓት በመገኘት መጽሐፋቸውን እንዲመልሱ። 2. ከተመደበው ቀንና ሰዓት ውጭ የመጽሐፍ መመለስ አይፈቀድም። ት/ቤቱ

‎                           ቀን 19/11/2018 ዓ.ም ‎ማስታወቂያ ‎ ‎ለ11ኛ እና ለ12ኛ ክፍል ቶፕ 30 ተማሪዎች በሙሉ ‎ ‎እንደሚታወቀው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ከ2 ሳምንት በፊት ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል ።በመሆኑ ብዙ ተማሪዎች ትምህርቱ ላይ እየተገኛችሁ አይደለም ።ስለሆነም የትምህርት ቤታችን የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ቶፕ 30 የሆናችሁ በሙሉ እስካሁን ትምህርት ላይ ያልተገኛችሁ ከእናንተ የምጠበቀው መስፈርት በመሟላት ከነገ ሰኞ 20/11/2018 ዓ.ም ጀምራችሁ በአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤት ጠዋት 2፡00 ላይ እንድትገኙ እንደዚሁም ውጤት መግለጫ ካርዳችሁንም እንድትረከቡ እያሳወቅን ያልተገኘ ተማሪ ለምፈጠረው ችግር ራሳችሁ ሀላፍነት የምትወስዱ እና ለ2019 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የማንመዘግባችሁ እና ካርዳችሁንም የማንሰጣችሁ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን። ‎  ‎                               ት/ቤቱ ‎

ለደራርቱ ቱሉ ከ9ኛ_12ኛ ክፍል ተማሪዎች 👉ነጻ የኮንፒዮተር ስልጠና የሲልከን ክራፍት ፋውንዴሽን በክረምት መርሀግብር የተለያዩ የኮንፒዮተር ኮርሶችን አስተምሮ እለምዓቀፍ የምስክር ወረቅት ስለሚሰጥ በቀን 20_21/112018ዓ.ም ት/ቤት በመገኘት እንድትመዘገብ በአክብሮት እናሳውቃለን። ት/ቤቱ

ቀን: 14/11/2018 ዓ.ም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ የመጽሐፍ መመለሻ መርሃ ግብር ============================ 1. Natural Science —ሐሙስ (Thursday) 16/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 እስከ 9:00 ሰዓት ብቻ። 2. Social Science — ዓርብ (Friday)17/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 እስከ 9:00 ሰዓት ብቻ። ማሳሰቢያ 1. ሁሉም ተማሪዎች በተመደበላቸው ቀንና ሰዓት በመገኘት መጽሐፋቸውን እንዲመልሱ። 2. ከተመደበው ቀንና ሰዓት ውጭ የመጽሐፍ መመለስ አይፈቀድም። ት/ቤቱ Guyyaa: 14/11/2018 A.L.I Barattoota Kutaa 12ffaa Maraaf: ============================ Sagantaa Kitaabota Deebisuu 1ffaa. Natural ScienceKamisa, Guyyaa 16/11/2018 A.L.I  sa'aatii 2:30 hanga 9:00 qofa. 2ffaa. Social ScienceKamisaJimaata, Guyyaa 17/11/2018 A.L.I  sa'aatii 2:30 hanga 9:00 qofa. Hubachiisa 1. Barattoonni hundi guyyaa fi sa'aatii isiniif ramadame irratti argamuun kitaabota isin bira jiru akka deebistan ni hubachiifna. 2. Guyyaa fi sa'aatii ramadameen alatti kitaabota deebisuun hin hayyamamu. Mana Barumsaa

‎                           ቀን 12/11/2018 ዓ.ም ‎ማስታወቂያ ‎ ‎ለ11ኛ እና ለ12ኛ ክፍል ቶፕ 30 ተማሪዎች በሙሉ ‎ ‎እንደሚታወቀው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ባሳወቀው መመሪያ መሰረት ከባለፈው ሰኞ 06/11/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል ።በመሆኑ ብዙ ተማሪዎች ትምህርቱ ላይ እየተገኛችሁ አይደለም ።ስለሆነም የትምህርት ቤታችን የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ቶፕ 30 የሆናችሁ በሙሉ ከእናንተ የምጠበቀው መስፈርት በመሟላት ከነገ ሰኞ 13/11/2018 ዓ.ም ጀምራችሁ በአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤት ጠዋት 2፡00 ላይ እንድትገኙ እያሳወቅን ያልተገኘ ተማሪ ለ2019 ዓ.ም በትምህርት ቤታችን መመዝገብም ሆነ መሸኛ መውሰድ የማትችሉ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን ። ‎  ‎                               ት/ቤቱ ‎

‎ ቀን 08/11/2018 ዓ.ም ‎ማስታወቂያ ‎ ‎ለ11ኛ እና ለ12ኛ ክፍል ቶፕ 30 ተማሪዎች በሙሉ ‎ ‎እንደሚታወቀው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ባሳወቀው መመሪያ መሰረት ከባለፈው ሰኞ 06/11/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል ።በመሆኑ ብዙ ተማሪዎች ትምህርቱ ላይ እየተገኛችሁ አይደለም ።ስለሆነም የትምህርት ቤታችን የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ቶፕ 30 የሆናችሁ በሙሉ ከእናንተ የምጠበቀው መስፈርት በመሟላት ከነገ 09/11/2018 ዓ.ም ጀምራችሁ በአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤት ጠዋት 2፡00 ላይ እንድትገኙ እያሳወቅን ያልተገኘ ተማሪ ለ2019 ዓ.ም በትምህርት ቤታችን መመዝገብም ሆነ መሸኛ መውሰድ የማትችሉ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን ። ‎ ‎ ት/ቤቱ

Transportation is ready for social science national exam.Our students have to be punctual. We wish you every good things come
+5
Transportation is ready for social science national exam.Our students have to be punctual. We wish you every good things come to you.

በሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንዲቻል የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት በተመረጡ ክላስተር ማዕከላት ከሐምሌ 6 ጀምሮ መሰጠት እንደሚጀምር ተገለፀ። (ሀምሌ 4/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበ
+7
በሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንዲቻል የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት በተመረጡ ክላስተር ማዕከላት ከሐምሌ 6 ጀምሮ መሰጠት እንደሚጀምር ተገለፀ። (ሀምሌ 4/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ለተመረጡ ቶፕ 30 የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች በክረምት መርሐ ግብር  ማጠናከሪያ ትምህርት ለመስጠት በቂ ዝግጅት በማድረግ ሰኞ ሐምሌ 6 በተመረጡ የክላስተር ማዕከላት ትምህርቱ መሰጠት ይጀምራል:: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በከተማ አስተዳደሩ በሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንዲቻል የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርቱ እንደሚሰጥ ገልፀው ፤ ትምህርቱ በሳምንት 5ቀን ለክረምት ወቅት ብቻ በተዘጋጀ  ኮንደንስድ ካሪኩለም እንደሚሰጥ ገልፀው በማስተማሪያ ስነዘዴው x ን የማረም  ስትራቴጂ ተግባራዊ በማድረግ ተማሪዎች ስህተቶቻቸውን እያረሙ በርካታ ጥያቄዎች የሚሰሩበት እንዲሁም  ትርፍ ጊዜያቸውን አልባሌ ቦታ እንዳያውሉ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተዋል:: ዶክተር ዘላለም በመርሃ ግብሩ 51,523 ተማሪዎችና 1,800 መምህራን ትምህርቱን ለመስጠት ምዝገባ ማካሄዳቸውን ገልፀው በመርሀ ግብሩ የሚሳተፉ የመንግስት እና የግል ተማሪዎች በተገለፀው ቀን በተመረጡ  63 ክላስተር ማዕከላት በመገኘት ትምህርቱን እንዲከታተሉና ስራው በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲመራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል::

ደራርቱ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህት ቤት የ2018 ዕቅድ አፈጻጸም ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት አካሄደ ። ======================== ሀምሌ :4/2018 ዓ.ም(ወረዳ 8 ኮሙኒኬሽን) በአቃ
+7
ደራርቱ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህት ቤት የ2018 ዕቅድ አፈጻጸም ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት አካሄደ ። ======================== ሀምሌ :4/2018 ዓ.ም(ወረዳ 8 ኮሙኒኬሽን) በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደራርቱ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህት ቤት የ2018 ዕቅድ አፈጻጸም ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት አካሄደ ። በዕለቱ የአፈፃፀም ሪፖርቱን ሠነድ ያቀረቡት በትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ዘሪሁን ካሳሁን ሲሆኑ በበጀት አመቱ የተከናወኑ አንኳር ተግባራት ቀርበዋል ። የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ መጠነ ማቋረጥ የቀነሰበት ፣ ምቹ ስራ አካባቢ እና ጥራት ያለው የመማር ማስተማር ቴክኖሎጂ ተኮር ግብአት የተሟሉበት እንዲሁም ሴት ተማሪዎችን ለማበረታታት ስልጠና እና የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁስ በመደበኛነት ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱን ሪፖርቱ ያትታል ። ከዚሁ ጋር አጠቃላይ ተማሪ ውጤት ትንተና የቀረበ ሲሆን ትምህርት ቤቱ ባለው ሁኔታ የተማሪዎች ውጤት መሻሻሉ ያመላክታል ። 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች አልባሌ ቦታዎች እንዳይውሉ እና ለቀጣይ ሀገር አቀፍ ፈተና ለማዘጋጀት ይረዳ ዘንድ ሁሉም ወላጆች ልጆቻቸውን የክረምት ትምህርት በማስተማር የወላጅ ግዴታቸውን እንዲወጡ ያሳሰቡት በመማር ማስተማር ም/ርዕሰ መምህር አቶ ታሪኩ ገብሬ ናቸው ። ደራርቱ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በኢትዮጵያ ካሉ ቀደምት እና ታዋቂ ትምህርት ቤቶች ተርታ በመመደብ ወደ ደረጃ 4 መካተቱ ትልቅ ስኬት ነው ለዚህ ደሞ ባለድርሻ አካላት የአስተዳደር ድጋፍ የወላጅ እና መምህራን ጥረት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ በቀጣይም እጅ ለእጅ ተያይዘን ትምህርት ቤቱን ወደ ተሻለ ደረጃ እንደርሳለን ሲሉ የገለፁት በትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ዘሪሁን ካሳሁን ናቸው::

አካውንቱ ላይ የማገባው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ብቻ ነው።

የመክረምት ማጠናከሪያ አካውንቱ የተከፈተው በደራርቱ ርዕሰ መ/ር ዘሪሁን ፣አቶ ሃለፎም የክ/ከተማ ሱፐቫይዘር እና የአቡነ ጎርጎርዮስ ር/መ ገንዘቤ መሆኑን አሳውቃለው።