cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Hijra Tube [Official]

ሒጅራ ቲዩብ ኢስላማዊ ድረገፅ ትኩስ ትኩስ የሙስሊሙን አለም የተመለከቱ መረጃዎች ጠቃሚ ፅሁፎችና ዳእዋዎች ይቀርቡበታል

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
9 998
مشترکین
-724 ساعت
-177 روز
-10430 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
ሰኢድ አህመድ ይባላል በአፋር ክልል የአዋሽ 7ኪሎ ልጅ የአእምሮ ህመምተኛ ከጠፋብን አንድ ወር ከአስራ አምስት በላይ ሆኖታል +251945145927 +251911053974 +251913347801
نمایش همه...
👍 4
☘ዓሹራን የመጾም ትሩፋት 🔅ቡኻሪይ እንደዘገቡት ዐብዱሏህ ኢብን ዐባስ ረዲየሏሁ ዐንሁ የዓሹራን ጾም አስመልክተው ሲናገሩ የሚከተለውን ብለዋል (ነቢዩም ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለ እንደ ዓሹራ ቀንና እንደ ረመዷን ወር ሆን ብለው <በጉጉት ጠብቀው> ሲጾሙ አይቻቸው አላውቅም! ) ብለዋል ነቢዩም፥ ( የዓሹራ ቀን ጾም ያለፈውን ዓመት ወንጀል ያስምራል(ያስሰርዛል) ብዬ አሏህ ላይ ተስፋ አደርጋለሁ ) ብለዋል። 🔅አንድን ቀን በመጾም የዓመት ወንጀል መማር ለሙእሚኖች ታላቅ የአሏህ ሱብሓነሁ ወተዓላ ስጦታ ነው እድሉም ለሁሉም ክፍት ነው መሽቀዳደም እና መወዳደር ያማረው ሰው በሙሉ እንዲህ አይነቱ የኸይር ስራ ሜዳ ላይ ይሽቀዳደም! 🔅የዓሹራ ቀን ጾም ያለፈውን ዓመት ወንጀል ያስምራል ያሰርዛል በቀላል ስራ ይህን የሚያህል ምንዳ የሚገኝ ሆኖ ሳለ ብዙ ለአኼራቸው ግድ የለሽ የሆኑ ሰዎች እድሉን ችላ ሲሉ እንመለከታለን፤አዱኒያዊ ጥቅም ቢሆን ግን አይዘናጉም ነበር፤ አልፎም እድሉ ላይ በመሻማት ይፋጁ ነበር ግን {አብዛኞች የሰው ልጆች አያውቁም} አርሩም 6 ☄የዓሹራእ ጾም ሙሐረም ስንተኛው ቀን ላይ ነው?... የዓሹራእ ጾም ማለት የሙሐረም ወር 10ኛው ቀን ላይ ሲሆን ከፊቱ ወይም ከኋላው አንድ ቀን (9ኛውን ወይም 11ኛውን) ቀን ጨምሮ መጾም ይመረጣል ምክንያቱም ነቢዩ ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ዓሹራን ሲጾሙና ሷሓባዎችም እንዲጾሙት በመከሯቸው ጊዜ አይሁዶች የሚያከብሩት ቀን እንደሆነ ለነቢዩ ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ሲነግራቸው የሚከተለውን ብለዋል፤ ( አሏህ ካለ የሚመጣው ዓመት ላይ 9ኛውንም ቀን እንጾማለን ) ብለዋል ከዚህም በመነሳት ዑለማዎች ዘጠነኛውንም ቀን መጾም ሱና ነው ብለዋል። 🔅ከዓሹራ ጋር 9ኛውን ቀን መጾም ምክንያቶች አሉት ከነዚህም መሀል አንዱ 10ኛውን ቀን ብቻ መጾም ከአይሁዶች ጋር መመሳሰልን ስለሚያመጣ አንድ ቀን ጨምሮ መጾሙ ከነሱ ጋር መለያየትን ያስገኛል፤ ከጠመሙ ህዝቦች ጋር መመሳሰል በዲናችን ክልክል ከመሆኑ አንጻር እነሱን ለመቃረን ተብሎ ሸሪዓችን አንድን ነገር ማድረግ ሲከለክል ወይም ደግሞ ሲያዝ ሁሉ እናያለን ይህም ሆኖ ሳለ ግን ብዙ ሙስሊሞች አይሁድና ነሳራ ያደረጉትን ለማድረግ ሲሽቀዳደሙ እንመለከታለንል! 🔅ይህ በእንዲህ እንዳለ ምናልባት የቀን አቆጣጠር ላይ ስህተት ቢፈጠር እና የወሩ መግቢያ አሻሚ ቢሆን ሁለቱን ቀናት መጾም የዓሹራን ቀን ማግኘት ላይ እርግጠኛ ያደርጋል፤በላጩ 9 እና 10ኛውን ቀን መጾሙ ሲሆን ያልተመቸው ሰው 10 እና 11ኛውን ቀን መጾም ይችላል።እንዲሁ ዋናውን የዓሹራን ቀን ብቻ እንጂ ሌላ ተጨማሪ ቀን መጾም ያልቻለ ሰው ብቻውን መጾም እንደማይከለከል ዑለማዎች ገልጸዋል። 🔅ጁሙዓ ወይም ቅዳሜ ቀንን ለብቻው (ከፊት ወይም ከኋላ አንድ ቀን ሳይጾሙ) ነጥሎ መጾም እንደማይቻል በሐዲሶች የተገለጸ ሲሆን አጋጣሚ ዓሹራ ጾም በጁሙዓ ወይም ቅዳሜ ዕለት ቢሆን መጾም አይከለከልም። 🔅ዓሹራ ጾም ብቻ ሳይሆን ሌሎችም እንደ ቀዷ ወይም የነዝር (ስለት) እና መሰል ምክንያት ያላቸው ጾሞችንም መጾም አይከለከልም። ☄ዓሹራን መጾም የቱን ወንጀል ነው የሚያስምረው? ዓሹራን መጾም ያለፈውን ዓመት ወንጀል እንደሚያሠርዝ ጠቅሰናል ይህ ምህረት ጥቃቅን ወንጀሎችን ነው የሚመለከተው ወይስ ከባባዶችንም ጭምር? ይህን አስመልክተው ኢማም አንነወዊይ የሚከተለውን ብለዋል፤ " የዓረፋ ጾምም ይሁን የዓሹራ ሌሎችም ወንጀልን ያስምራሉ የተባሉ ኢባዳዎች ጥቃቅን የሚባሉ ወንጀሎችን በሙሉ ያሰርዛሉ ጥቃቅን ወንጀሎች የሌሉበት እንደሆነ በምትኩ መልካም ስራዎች ይመዘገቡለታል አላህ ዘንድም ያለው ደረጃ ይጨምራል ጥቃቅን ወንጀሎች የሌሉበት ሆኖ አንድ ወይም ከዛ በላይ ከባድ ወንጀል ያለበት እንደሆነ ወንጀሉን ያቀለዋል ብለን አሏህ ላይ ተስፋ እናደርጋለን" ☄ቀዷ ያለበት ሰው ዓሹራ መጾም ይችላልን? እንደ ዓሹራ ያሉ ሱና ጾሞችን ያለምንም ጥርጣሬ ለመጾም ያለብንን ቀዷ ፈጠን ብለን ማውጣቱ ይመረጣል።ቀዳውን ሳይጾም ወቅቱ የሚያልፍ የሱና ጾም የደረሰበት ሰው በቀጣይ ለቀዳ ሰፊ ጊዜ እስካለው ድረስ ፈርዱን ቀዳ ሳያወጣ ሱና ቢጾም ችግር አይኖረውም። 🔅ከዓሹራ ጋር በተያያዘ የሚፈጠሩ ቢድዓዎች  ታላቁ የዲን መሪ ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ይህን በተመለከተ የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ "በዓሹራ ቀን ሰዎች ገላቸውን ሲታጠቡ፤ ሲኳኳሉ፤ሂና ሲቀቡ፤ልዩ ሰላምታ ሲለዋወጡና ሲጨባበጡ፤ልዩ ምግብም ሲሰሩ እና ልዩ ደስታ ሲደሰቱ ይታያል ይህ ነገር በሸሪዓችን መሰረት አለውን?" እሳቸውም ሲመልሱ {{ ይህን አስመልክቶ ከነቢዩ ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም የተገኘ አንድም ሷሒሕ ሐዲስ የለም ሷሓቦቻቸውም ይህን አስመልክተው ያሉት ነገር የለም ቀደምት የዲን መሪዎችም አራቱም መሪዎች (ኢማም፥አቡ ሐኒፋ፣ማሊክ፣ሻፊዒ እና አሕመድ) ይሁን ሌሎችም ከነሱም ውጪ ያሉት ታዋቂ የሸሪዓ እውቀት ምንጭ የሚባሉ መጻህፍት ባለቤቶችም በዚህ ጉዳይ ከነቢዩም ይሁን ከሷሓቦች ወይም ከተከታዮቻቸው ምንም የዘገቡት ነገር የለም) ብለው መልሰዋል። 💥ከቢድዓ በመጠንቀቅ በዲኑ የተፈቀዱ ነገሮችን ብቻ በመስራት ወደ አላህ እንቃረብ! 💥የዘንድሮ (የ1446ዓ.ሂ) ዓሹራ የሚሆነው የፊታችን ማክሰኞ  (ከነገ ወዲያ) ሙሐረም 10  ሲሆን ከፊቱ ሰኞን ወይም ከኋላው ረቡዕን  መጾም ተገቢ ነው። ከ11ኛው ቀን ይልቅ ከፊት ያለውን 9ኛውን ቀን መጾሙ ተመራጭ ነው። በተለይ ዘንድሮ 9ኛው ቀን ዕለቱም ሰኞ  ስለሆነ ሰኞ ቀን የመጾምን ትሩፋትም ያስገኛል። ሁለት ቀን መጾም የሚከብደው ሰው 10ኛውን ቀን ብቻ መጾምም ይችላል። አላህ ይወፍቀን! ✍ ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም @ዛዱል መዓድ
نمایش همه...
👍 7
Photo unavailableShow in Telegram
አፋልጉኝ ራህማን አህመዲን ሙክታር ትባላለች ትላንት ቅዳሜ 06/11/2016 ከጡዋቱ 5:00 አካባቢ ከወጣች አልተመለሰችም ኬንቴሪ አካባቢ ራህማንን ያየ በዚህ ስልክ ቁጥር ይጠቁሙን ለአላህ ብለው +251917864805 +251930844450 0948676175 0961150726
نمایش همه...
👍 1
🥣የአሹራ ቀን ፆም! 📌ለመልካም ስራ አስተዋሽ እንሁን ከኢብኑ አባስ (▫️) ተይዞ፡ ነቢዩ (▫️) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ اللَّهُ - صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ﴾ “የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፍቃድ የአሹራን ቀን ፆም ዘጠነኛውን ጨምሬ እፆማለሁ።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1134 ከአቢ ቀታዳ (▫️) ተይዞ፡ ነቢዩ (▫️) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿صيامُ يومِ عاشوراءَ، إنِّي أحتَسِبُ على اللَّهِ أن يُكَفِّرَ السَّنةَ الَّتي قبلَهُ﴾ “የአሹራ ቀን ፆም ያለፈውን አመት ኃጢአት እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162
نمایش همه...
👍 8
ለእሁድ ከኢትዩጱያ ወደ ሳዑዲ የፈለጉትን እቃ በአማና እናደርሳለን! ይደውሉ  0956107730
نمایش همه...
1
Repost from Seid Social
ጋዛ ወደ 2 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ አላት ። ከዚህ ከሁለት ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ ከ 200 ሺህ እስከ 300 ሺህ የሚጠጉት ቁርአን ሀፊዞች ናቸው ። ያ ማለት ከመቶ የጋዛ ሰው 15ቱ ሀፊዝ ናቸው ማለት ነው ። በእያንዳንዱ የጋዛ ቤትም አንዳንድ የቁርአን ሀፊዝ አለ ። ይህም በአለም ጋዛን በቁርአን ቀዳሚ ያደርጋታል። ስለዚህ እስራኤል 100 ጋዛዊያንን በገደለች ቁጥር 15 የቁርአን ሀፊዞችን አብራ ትገድላለች። እስካሁን ኦፊሴላዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የተገደሉት ፍልስጤማዊያን ንፁሀን 39,000 ገደማ እንደሆኑ ቢነገርም ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ግን ከ 180,000 በላይ ንፁሀን ጋዛዊያን በጦርነቱ ሙተዋል ። ከጋዛ ህዝብ 10% ገደማ እንደማለት ነው። እጅግ ልብ አይሰብርም ??? ወደ ቁርአን ሀፊዞቹ ስንመጣ በቅድሙ ስሌት በእስካሁኑ ጦርነት ወደ 27,000 ቁርአን ሀፊዞች ተገድለዋል ማለት ነው ። ይህ ህይወት ባለው ኡማ ውስጥ ቢደረግ አንድ ሙስሊም እንኳ ተኝቶ ያድር ነበር ወይ? በየማማ ጦርነት ጊዜ 360 የቁርአን ሀፊዞች ሲገደሉ በአቡበክር ሲዲቅና በሶሀቦቻቼው ላይ የደረሰው ድንጋጤና ስብራትን ሲራን የሚያውቅ ያውቀዋል ። ዛሬ ላይ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሀፊዞች ጋዛ ላይ በጅምላ ሲጨፈጨፉ እንኳንስ ሊያስደነግጠን ሊያሳስበንም አልቻለም ! ዛሬ ላይ በዚያች ጋዛ ምድር ብቻ ከ 1,000 በላይ ጥንታዊ መስጅዶች በመሰቀል ጦረኞቹና በፅዮናዊያኑ ጥምረት ሲወድም ሊያመን አልቻለም ። የራሳቼው ጉዳይ ብለን ጋዛዊያንን ክደናቸዋል !! ይሄ ረሱላችን ፊት ስንቀርብ የሚያሳፍረን አይመስላችሁም ? ሸፈአቸውን ለመከጀል አንገታችንን ቀና ማድረግ ይቻለን ይሆን ?? ሲያዩን የሚያፍሩብን አይመስላችሁም ??? 👉 t.me/Seidsocial
نمایش همه...
😭 24👍 11
Photo unavailableShow in Telegram
ربنا أخرجنا منها فإن عدنا فإنا ظالمون ጌታችን ሆይ ከ እሳት ውስጥ አውጣን፣ ወደ ዱንያም መልሰን።ተመልሰን ትእዛዝህን የምንጥስ ከሆነ እውነትም ለዚህ ቅጣት የተገባን ነን ይላሉ እሳት ውስጥ የሚቀጡ ሰዎች። ግን ምን ያደርጋል አሁን ረፍዷል! 😭 قال ٱخسـٔوا فیها ولا تكلمون እዛው እርጉ እንዳትናገሩም ምንም አይነት ድጋሚ እድል የላችሁም ይባላሉ።😭😭 አሏህ ይጠብቀን🤲
نمایش همه...
😭 5👍 2 1
Photo unavailableShow in Telegram
የጭንቅ ጊዜ ዱአ اللَّهُمَّ إِنِّي عَبْدُكَ، ابْنُ عَبْدِكَ، ابْنُ أَمَتِكَ، نَاصِيَتِي بِيَدِكَ، مَاضٍ فِيَّ حُكْمُكَ، عَدْلٌ فِيَّ قَضَاؤُكَ، أَسْأَلُكَ بِكُلِّ اسْمٍ هُوَ لَكَ، سَمَّيْتَ بِهِ نَفْسَكَ، أوْ أَنْزَلْتَهُ فِي كِتَابِكَ، أَوْ عَلَّمْتَهُ أَحَداً مِنْ خَلْقِكَ، أَوِ اسْتَأْثَرْتَ بِهِ فِي عِلْمِ الغَيْبِ عِنْدَكَ، أَنْ تَجْعَلَ القُرْآنَ رَبِيْعَ قَلْبِي، وَنُورَ صَدْرِي، وجَلَاءَ حُزْنِي، وَذَهَابَ هَمِّي አላህ ሆይ እኔ ባሪያህ፣ የወንድ ባሪያህም፤ የሴት ባሪያህም ልጅ ነኝ፡፡ ሁሉ ነገሬ በእግህ ነው፡፡ ውሳኔህ በኔ ላይ ተፈጻሚ ብይንህ ፍትሃዊ ነው፡፡ ቁርአንን የቀልቤ መርጊያ፣ የልቦናዬ ብገርሃን፣ የሐዘኔ መፅናኛና የጭንቄ ማስወገጃ ታደርግልኝ ዘንድ በስሞችህ ሁሉ እማፀንሃለሁ፡፡ አንተ ራስህን በጠራህባቸው ወይም ኪታብህ ውስጥ ባሰፈርካቸው÷ ከፍጡራንህ ለአንዱ ባስተማርካቸው ወይም ለማንም ባልገለፅካቸው ስሞችህ፡፡ አልሏሁምመ ኢንኒ ዐብዱከ ኢብኑ አብዲከ ኢብኑ አመቲከ ናሲየቲከ ቢየዲከ ማዲን ፊይየ ሑክሙክ አድሉን ፊይየ ቀዳኡከ አስአሉከ ቢኩልሊ ኢስሚን ሁወ ለከስምመይቱ ቢሂ ነፍሰከ አው አንዘልተሁ ፊኪታቢከ ቢሂ ነፍሰከ አው አንዘልተሁ ፊኪታቢከ አው አልለምተሁ አሐደን ሚን ኸልቂከ አዊስተእስርተ ቢሂ ፊይ ኢልሚን ገይቢ ኢንደከ አንተጅአለል ቁርአን ረኒዐ ቀልቢ ወኑረ ሰድሪ ወጀላአ ሑዝኒ ቀዘሃበ ሐምሚ
نمایش همه...
14👍 6
🌸 ሰኞና ሀሙስን መፆም🌸 አቡ ሁረይራ [رضي الله عنه] እንዳስተላለፉት የኣሏህ መልእክተኛ [صلى الله عليه وسلم] የሚከተለውን ብለውል፦ የጀነት በሮች ሰኞና ሀሙስ ይከፈታሉ።ወንድሙ ጋር የተኳረፈ ሰው ብቻ ሲቀር ከኣላህ ጋር ምንም ለማያጋራ እያንዳንዱ (የኣሏህ) ባሪያ ይቅርታ ይደረግለታል። በሌላ ሀዲስ👇👇 وعن ابي هريرة رضي الله عنه عن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال: (تعرض الأعمال يوم الاثنين والخميس، فاحب ان يعرض عملي وانا صائم) رواه  الترمذي، አቡ ሁረይራ ባወሩት ሀዲስ ረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ኣሉ፦ በሰኞና በሀሙስ ቀናት ስራዎች ወደ ኣላህ ይወጣሉ፣እኔ ፆመኛ ሁኜ ስራዬ ወደ ኣላህ እንዲወጣ እወዳለሁ ቲርሚዚይ ዘግበውታል። 💥ኢንሻኣሏህ ነጌ መፆም ኣንርሳ ካልቻልን ሌሎችን እናስታውስ أدال علي الخير کفاعله او كما قال رسول، ወደ ኸይር ኣመላካች ልክ እንደሰሪው ነው ረሱል እንዳሉት          {ሙስሊም፤ማሊክ ና አቡ ዳውድ ዘግበውታል}
نمایش همه...
👍 5 1
Photo unavailableShow in Telegram
وَكُلُّهُمْ آتِيهِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ فَرْدًا [ ሱርቱ መርየም፣ - 95 ] ሁሉም በትንሣኤ ቀን ለየብቻ ኾነው ወደርሱ መጪዎች ናቸው፡፡ ወዳጄ በዚህች አለም ብዙዎች ልወዱህም ልጠሉህም ሊያሞግሱህም ሊተቹህም ይችላሉ! ብዙ ተከታይ ብዙ አድናቂ ሊኖርህ ይችላል የቅርድም የሩቅም ዘመድ ልጅና ሚስት በጣም የተዋቡ ቤትና መኪናም ሊኖርህ ይችላል ግና ምን ዋጋ አለው? ያቺ መራራ ሞት የመጣች ጊዜ ተከታዮችህም ወዳጆችህም የቅርብም ሆነ የሩቅ ዘመዶችህ የምትወዳቸው ወላጆችህና ልጆችህ ሚስህም ከአንተ ይነጠላሉ ጌታ አሏህ በከበረው ቃሉ እንዳለው ብቻህን ሆነህ ጌታህን ትገናኘዋለህ! ታዲያ ለዚያች ብቻህን ሆነህ ጌታህን ለምትገናኝባት ቀን መልካም ሰርተህ ከሆነ ምን የምያምር መገናኘት ነው? ከዚህ ውጭማ ከሆነ ምን የሚያስጠላ መገናኘት ነው? አላህ በእዝነቱ መልካም ሰርተን እርሱን የምንገናኝ ያድርገን አሚን ያረብ🤲 وَمَا تَفْعَلُوا مِنْ خَيْرٍ يَعْلَمْهُ اللَّهُ ۗ وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ وَاتَّقُونِ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ [ አል-በቀራህ - 197 ] ከበጎም ሥራ የምትሠሩትን ሁሉ አላህ ያውቀዋል፡፡ ተሰነቁም፤ ከስንቅም ሁሉ በላጩ ጥንቃቄ (አላህን መፍራት) ነው፡፡ የአእምሮዎችም ባለቤቶች ሆይ! ፍሩኝ፡፡ فَمَن كَانَ يَرْجُو لِقَاءَ رَبِّهِ فَلْيَعْمَلْ عَمَلًا صَالِحًا وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا (ሱረቱ አል ከህፍ፥ - 110) «የጌታውንም መገናኘት የሚፈልግ ሰው፤ መልካም ሥራን ይሥራ፡፡ በጌታውም መገዛት አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ ✍ሙከሚል
نمایش همه...
😭 6👍 5
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.