fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 740
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+17 روز
-630 روز
آرشیو پست ها
ADRA ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በፕሮጀክቱ አፈፃፀም ላይ በየጊዜው የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ከባለድርሻ እካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: በመድረኩ የመጀመርያ ዙር ተመራቂ ሰልጣኞችን በማደራጀት ሂደት ውስጥ ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች ለመለየት እና የመፍትሄ አቅጣጫ ለማስቀመጥ በአስተዳደሩ ከከተማና ከገጠር የተወጣጡ አራት ክላስተሮች በተገኙበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል:: በእለቱ ባለድርሻ አካላቱን ያወያዩት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊና የኤጀንሲው ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጥፋ ለተሳታፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት ዘርፉ አዲስ ከመሆኑ አኳያ ብዙ ያልተነኩ የስራ ዕድሎችን መፍጠር የሚያስችል በመሆኑ እንዲሁም በእስተዳደሩ በሚገኙ ገጠር ወረዳዎች ውስጥ ከተወሰኑት በቀር የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ እለመደረጉን እስታውሰው ይህን ሁሉ አጋጣሚ በእጃችን ይዘን ሰልጣኞቹን ለማደራጀትና ወደ ስራ ለማስገባት ምክንያት ምንደረድር ከሆን ችግሩ ያለው እኛው ጋር ነውም ብለዋል:: በዘርፉ የገጠሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ሰፋ ያለ ውይይትም የመጀመርያ ዙር ሰልጣኞች በገጠርም ሆነ በከተማው በአፋጣኝ ወደ ስራ የሚገቡበት ሁኔታ ምችችት እንዲደረግና ለዚህም ጉዳዩን በባለቤትነት የያዙት ባለድርሻ አካላት ተቀዳሚ ተግባራቸው አድርገው ሊወስዱትና ጉዳዩንም ከዳር ሊያደርሱት እንደሚገባ ተገልፇል:: በተጨማሪም ሰልጣኞች የወሰዱት የሙያ ክህሎት ወደ ሀብት እንዲለወጥ እንዲሁም ያሰለጠንናቸው ወጣቶች ወደ ስራ መሰማራታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ዘርፉ ላይ ያለውን የሀብት ብክነት እንደሚታደግ የተገለፀ ሲሆን ሁሉም የባለድርሻ አካላት በመረባረብ የስልጠናውን ውጤት ማሳየት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል:: በመጨረሻም ለሁለተኛ ዙር ስልጠና በተደረገው የሰልጣኝ የምልመላ ሂደት ላይ እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮች በመድረኩ በዝርዝር ተነስተው ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በገጠሩ ያሉ ወጣቶችን በምልመላው መስፈርት መሰረት ተመልምለው ለክላስተር ሀላፊዋች ወደ ስልጠናው እንዲገቡ ጠንከር ያለ መልእክትም ተላልፏል። በመድረኩ ማገባደጃም በአስተዳደሩ ከሚገኙ የከተማ እና የገጠር አራት ክላስተሮች የተወጣጡ የአንድ ማዕከል ባለሞያዎች እና ሀላፊዎች የጋራ ውይይት አካሂደዋል:: በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዳር 29/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ ዓመት በተቋሙ ለሚጀመረው የEASE ፕሮጀክት SIP Validation እና የፕሮጀክት ማስጀመርያ መድረክ አካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የስልጠና መርሀ-ግብር SIP(Strategic Investment Plan) ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በእለቱ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም ይህን የEASE ፕሮጀክት ትግበራ ላይ ሲውል የከተማና የገጠር ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ መሆን እንደሚገባው ተናግረው አያይዘውም መሰል ፕሮጀክቶች በአግባቡ ካልተመሩ እና በትክክል ለተቀመጠላቸው አላማ ማይውሉ ከሆነ ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው እንደሚያመዝን ጠቅሰው ኮሌጁ ከሌሎች ትምህርት በመውሰድ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት እቅድ መሰረት እንዲመራና የሚፈለገውን ግብ እንዲመታ አደራ ብለዋል:: በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ እሰፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም ይህ ፕሮጀክት የኮሌጁ የፈንድ ራይዚንግ ክፍል የመጀመርያ ስራ የሆነው የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀክት መሆኑን አስታውሰው በብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ታልፎና ብዙ ኮሚትመንት ተጨምሮበት ዛሬ ለደረስንበት ደረጃ መብቃቱን ጠቅሰው በነበረው ሂደት ላይም ቀላል ማይባሉ እድካሚና እሰልቺ መንገዶች ታልፈው እዚህ እንደደረሰ በመግለፅ ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ትልቁን ሚና ለተወጡት የፕሮጀክት አስተባባሪዎች ትልቅ ምስጋና አቅርበዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ 5 አመታት ውስጥ አንድ የራሱን አሻራ አሳርፎ የሚያልፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀው ዛሬ ይህ ፕሮጀክት ለሰራተኛው ሲቀርብም በተቻለ መጠን የሰራተኛውን ተሳትፎና የሁሉንም ሰው ርብርብ እንደሚጠይቅ ግንዛቤ ለመፍጠር ሲሆን የፕሮጀክት ውጤታማነት የሚለካውም በሁሉም የጋራ ተሳትፎ መሆኑንም አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል:: በመድረኩ የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀርት ሰነድ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለተቋሙ ሰራተኛ የቀረበ ሲሆን በዚህም ይህ ፕሮጀክት ከምን ተነስቶ እንደተጀመረና አላማውስ ምንድነው ከሚለው ጀምሮ የፕሮጀክቱን ዋና ሰነድ በዝርዝር አቅርበዋል:: በመጨረሻም የፕሮጀክቱን SIP(Strategic Investment Plan) እንዲሁም ከፕሮጀክቱ የሚጠበቁ ውጤቶችን በተመለከት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ በሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን አጠቃላይ በመድረኩ በቀረቡ ሰነዶች ላይ ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጎበታል:: ፕሮጀክቱ በዋናነት የስራ እድል ትስስርን ይፈጥራል የተባለ ሲሆን ይህም በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካቶችን የሞያ ክህሎትን በማሰልጠን ከገበያው ጋር የሚያስተሳስር መሆኑም ተገልፇል። በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዳር 28/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ወጣቶችን የስራ እድል ትስስርን የሚፈጥር ኘሮጀክት በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስትራቴጂክ ፕላን ቀርቦ ውይይት ተካሄዶል:: የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የስልጠና መርሀ-ግብር ስትራቴጂክ ፕላን ቀርቦ ውይይት ተካሔደ። ይህ ፕሮጀክት ለአምስት አመት እንደሚቆይ ተገልጿል። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7 ሚልየን ዶላር EASE Education and Skills for Employ Ability (EASE) ኢዱኬሽን ኤንድ ስኪል ፎር ኢምፑሊቲ ፕሮጀክትን የማስጀመር መርሀ-ግብር ተካሒዷል። ፕሮጀክቱ በዋናነት የስራ እድል ትስስርን ይፈጥራል ይህም በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካቶችን የሞያ ጥበብን ወይም ስኪልን በማሰልጠን ከገበያው ጋር ያስተሳስራል። በዚህ EASE ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተው መርሀ-ግብሩን ያስጀመሩት በድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ባስተላለፉት መልእክት ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ጠንካራ አመራር ሰጪነት ወሳኝ እንደሆነ ገልፀው ለታለመለት አላማም መሰረት አድርጎ መከናወን እንዳለበት አሳስበዋል። ኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በማኒፋክቸሪንግ ፣ በኤሌክትሮ ቴክኖሎጂና በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ የስልጠና መስኮች ከመማርና ማስተማር ጋር ያሉ የትምህርት ጥራትን አካቶ ተወዳዳሪነትን የሚጨምሩ የኢንዱስትሪ ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ የስልጠና መስኮችን ለመቅረፅ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው ሲሉ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ ተናግረዋል። ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዚህ በፊት በመደበኛ ከሚሰጠው ስልጠና ይህ EASE ፕሮጀክት ዋና አላማ አካታች የሆነ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠናው ይሰጣል ሲሉ የፕሮጀክቱ ዋና ኮርድኔተር አቶ ፋሲል ማዘንጊያሽ ገልጸዋል። ይህ EASE Education and Skills for Employ Ability ፕሮጀክት ኮሌጁ ከአምስት አመት በኋላ አሁን ካለበት ስልጠና የመስጠት አቅም በቴክኖሎጂ የተደገፈ መሰረተ ልማት የተሟላለት ኮሌጅ እንዲሆን ያስችለዋል ተብሏል። #DGC ህዳር 26/2017

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ቴሬሳ የተመራ የሱፕርቪዥን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ ምልከታ አካሄደ:: በሚኒስትር ድኤታው የተመራው የከፍተኛ አመራሮች ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በበጀት አመቱ እስከ አሁን የተሰሩ ትግበራዎች ላይ ምልከታ ያደረ ሲሆን ቡድኑ በቅድሚያ በኮሌጁ የተሰሩ ትግበራዎች ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ቀርቦለት በቀረበው ሪፖርት ላይም ቡድኑ ግብረ መልስ በመስጠት ምክረ ሀሳቦችንም አስቀምጧ። በተጨማሪም የሱፕርቪዥን ቡድኑ የቀረበለትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ በኮሌጁ ከክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራና ከተቋማት ግንባታ አኳያ የተሰሩ ሥራዎች ተዘዋውሮ የተመለከት ሲሆን በዚህም ተቋሙ አሰልጥኖ ወደ ስራ እዲገቡ ያደራጃቸውን ሰልጣኞች ያሉበትን ሁኔታ የተመለከተ ሲሆን እንዲሁም በኮሌጁ የተሟላ ድጋፍ በሰልጣኞች እየተሰሩ ያሉ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: በመጨረሻም ሚንስትር ድኤታው በኮሌጁ የተመለከቷቸውን የለውጥ ስራዎች እንዲሁም ሰልጣኞችን አሰልጥኖ ከስራ ጋር በማስተሳሰርና በማደራጀት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤታማ በመሆናቸውና በአስተዳደሩም ሆነ እንደ ሀገር ፍሬያቸው የሚታይ በመሆኑ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቢሮው በኩል አስፈላጊውን ትብብር እንዲሁም ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ገልፀዋል:: በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዳር 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች በአለም ለ37ኛ ጊዜ እንዲሁም በሀገራችን ለ36ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ቀን በዛሬው ዕለት አክብረዋል:: "ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የኤች.አይ.ቪ አገልግሎት ለሁሉም" በሚል መሪ ቃል በፖናል ውይይት የተከበረ ሲሆን መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዳሉትም በተቋሙ ያሉ ሰራተኞች በአብዛኛው ወጣት ከመሆናቸው አኳያ ለቫይረሱ ተጋላጭ ከሚያደርጉ ሁኔታዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግና ተቋሙ ለሚያሰለጥናቸው ሰልጣኞችም ተገቢውን ግንዛቤ በመፍጠር እንደ ሀገር የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አፅእኖት ሰተው ተናግረዋል:: በመድረኩ ከጤና ቢሮ በመጣ ባለሙያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ የቀረበ ሲሆን የቀረበውን ሰነድ ጨምሮ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በዚህም ሰራተኛው የቫይረሱ ስርጭት ላይ ያለውን ግንዛቤ እንዲያሳድግ ረድቶታል:: በተጨማሪም በመድረኩ ሁሉም ማህረሰብ የሚያስፈልጋቸውን የኤች.አይ.ቪ መከላከል እና መቆጣጠር አገልግሎቶች ገደብ ሳይኖር ተደራሽ ማድረግ ተገቢ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በተለይም ለቫይረሱ ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን ቅድሚያ መስጠት ተገቢ መሆኑን ተነግሯል፡፡ ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ህዳር 20/2017 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስልጠና አጠናቃቂ ለሆኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች የኢንተርፕሩንርሺፕ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል:: ስልጠና በዋናነት ሰልጣኝ ተማሪዎች መደበኛ ስልጠናቸውን አጠናቀው ሲወጡ ስራ ፈጣሪነትን ተላብሰው እንዲወጡና በሚፈጥሩትም ስራ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከመጥቀም ባሻገር ለሀገር ኢኮኖሚ እንዲተርፉ የሚያስችላቸው የንግድ ስራ ክህሎት ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል:: የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናውን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI)ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን ስልጠናው በቀጣዮቹ ቀናትም ቀጥሎ የሚሰጥም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ህዳር 14/2017 ዓ.ም

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተከናወነው የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ። በመድረኩ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀም በፕሮጀክቱ ተወካይ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በመጀመሪያ ዙር ስልጠና ላይ የታዩትን ጠንካራ ጎኖች እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ጭምር በሪፖርቱ ተመላክቷል። በዚህም በመጀመርያ ዙር የፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በቀጣይ ለሚሰጠው ስልጠና እንቅፋት እንዳይሆኑ ከወዲሁ ለማስተካከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመምከር የመፍትሄ አቅጣጫዋችን ማስቀመጥ ተችሏል። መድረኩ ቀጥሎም እንደ አገር አዲስ የሆነው የሶላር ቴክኒሺያን እና ኤክስፐርት የስራ መዘርዝር 'JOB BOX ' ሰነድ ከሲቪል ሰርቪስ በመጣ ባለሙያ የቀረበ ሲሆን ሰነዱንም የሚመለከታቸው ተቋማት ሁኔታውን በደንብ ገምግመው ግብረመልስ ተሰቶበታል። በቀጣይም የተሰራው የJOB BOX ሰነድ እንዲፀድቅና የሶላር ፒቪ ተጠቃሚ ተቋማት የሶላር ኤክስፐርት/ ቴክኒሺያን በመቅጠር የሶላር ዘርፍ ላይ ያለውን ከፍተኛ ክፍተት መሙላት እንደሚጠበቅባቸው የተገለፀ ሲሆን ይህም በADRA ፕሮጀክት የሰለጠኑ ባለሞያዋችም ከሚከፈትላቸው የስራ እድልም ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደላድል ይፈጥራልም ተብሏል። የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 13/2017 ዓ.ም