1 745
订阅者
+224 小时
+57 天
-230 天
帖子存档
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ የOSH( Occupational Safety & Health) የሙያ ደህንነት ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ጀመረ::
ኮሌጁ እየሰጠ የሚገኘው ይህ የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ በኢንጂነሪንግ እና በጤናው ዘርፍ የመጀመርያ ዲግሪ ተመርቀው ስራ ያልያዙ ወጣቶችን ትኩረት ያደረገ ሲሆን በመስፈርቱ መሰረት ተመልምለው የመጡ ወጣቶችንም ለማሰልጠንና ወደ ኢንዱስትሪው ለማሰማራት በማሰብ በመጀመርያ ዙር 31 ሰልጣኞችን ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ ይገኛል::
ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው የLife skills ስልጠናን ጨምሮ በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን በመለየት እና በመቆጣጠር የሰውን ህይወት እንዲሁም ንብረትን ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችሉትን የተግባር፣የንድፍ ሃሳብን ጨምሮ ኢንዱስትሪዎች ላይ የትብብር ስልጠናዎችን የሚወስዱ መሆኑም ተግልፇል::
የOSH( Occupational Safety & Health) ስልጠናው በአጫጭር ስልጠና መደብ የሚሰጥ ሲሆን ለቀጣዮቹ አንድ ወራትም የሚቆይ ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም
በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የሚሰጡ የሞያ ስልጠናዎች በሀገር ውጥ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ማእከል ማድረግ እንዳለበት ተገለፀ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ጋር የምክክር መድረክ አካሔደ።
እንደ ሀገር አቀፍ ያለውን የስራ እጥ ችግርን ለመቅረፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በዚህ የቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች ደሞ ያላቸው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም።
ይሁን እንጂ የሙያ ኮሌጆች የሚሰጡት ስልጠና ክህሎትን ከስራ ቅጥር ጋር ያገናኘ ባለመሆኑ ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች የሚወጡ ሰልጣኞች በስራ እጦት ሲቸገሩ ይስተዋላል። የድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት በሚቻልባቸው የስልጠናና የትምህርት መስኮች ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የሚሰጡ የሙያ ስልጠናዎች በሀገር ውጥ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ማእከል ማድረግ እንዳለበት የገለፁትና የኢንዱስትሪዎች ፍላጎት ተለይቶ ስራ እጥነትን መቅረፍ ያስችላል፣ ለዚህም ኢንዱስትሪዎች በራሳቸው የሚሰጡትን ስልጠና በማቆም ለኮሌጆች ሀላፊነቱን መስጠት አለባቸው ሲሉ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ ተናግረዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በአስተዳደሩ ባሉ ሁለት የሙያ ኮሌጆች የሚያሰለጥኑት ኢንዱስትሪ መር ስልጠናዎች ውጤት እያመጡ በመሆኑ ኢንዱስትሪዎች ከኮሌጆች ጋር በፈቃደኝነት ተቀራርበው መስራት አለባቸው ሲሉ ገልፀዋል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE (Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት
ኮሌጁ የኢንዱስትሪዎች ፍላጎትን በማጤን ከውጪ የሚመጡ ባለሞያዎችን በመተካት የኮሌጁ ምሁራንን በማብቃት ምሁራን ብቁ የሆኑ ሰልጣኞችን በማውጣት የተሻለ አፈፃፀም ማምጣት ያስችለናል ሲሉ ገልፀውልናል።
በመድረኩ የተገኙት ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተወጣጡና ባለድርሻ አካላት ውይይት አካሒደዋል።
ይህ EASE(Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት ከአለም ባንክ በተገኘ 6.7 ሚሊየን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የ5አመት የስልጠና መርሀግብር መሆኑ ተገልፇል።
#Diretv አማርኛ ታህሳስ 3/2017
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች "ከወጣቶች ጋር በመተባበር ሙስናን መከላከል የነገ ስብዕናን ለመቅረፅ" በሚል መሪ ቃል የፀረ-ሙስና ቀንን አከበሩ::
በአለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ የተከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አስመልክቶ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ቀኑን በፓናል ውይይት እንዲሁም በግንዛቤ መስጫ ስልጠና አክብረዋል፡፡
በመድረኩ ለሰራተኛው መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በመልዕክታቸው ሙስና የጋራ ጠላታችን መሆኑን ጠቅሰው በጋራ የማንታገለው ከሆነ እንደ ኮሌጅ ብሎም እንደ ሀገር ለማስመዝገብ ለምናስበው እድገት እንቅፉት መሆኑና ወደ ኃላ የሚያስቀረን ካንሰር መሆኑን ጠቅሰው የተቋሙ ሰራተኛ በየትኛውም የስራ እንቅስቃሴው ሁሉ ሙስናን የሚጠይፍ ማህበረሰብ መሆን እንደሚገባውም አሳስበዋል::
መድረኩ ቀጥሎም በአለም አቀፍ እንዲሁም በሀገራችን ደረጃ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ የሚዳስስ ሰነድ በአቶ አድማሱ ዳምጤ አማካኝነት ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎችም ሙስና በጋራ ለመታገል ቃል በመግባት መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ህዳር 30/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
ADRA ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በፕሮጀክቱ አፈፃፀም ላይ በየጊዜው የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ከባለድርሻ እካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
በመድረኩ የመጀመርያ ዙር ተመራቂ ሰልጣኞችን በማደራጀት ሂደት ውስጥ ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች ለመለየት እና የመፍትሄ አቅጣጫ ለማስቀመጥ በአስተዳደሩ ከከተማና ከገጠር የተወጣጡ አራት ክላስተሮች በተገኙበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል::
በእለቱ ባለድርሻ አካላቱን ያወያዩት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊና የኤጀንሲው ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጥፋ ለተሳታፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት ዘርፉ አዲስ ከመሆኑ አኳያ ብዙ ያልተነኩ የስራ ዕድሎችን መፍጠር የሚያስችል በመሆኑ እንዲሁም በእስተዳደሩ በሚገኙ ገጠር ወረዳዎች ውስጥ ከተወሰኑት በቀር የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ እለመደረጉን እስታውሰው ይህን ሁሉ አጋጣሚ በእጃችን ይዘን ሰልጣኞቹን ለማደራጀትና ወደ ስራ ለማስገባት ምክንያት ምንደረድር ከሆን ችግሩ ያለው እኛው ጋር ነውም ብለዋል::
በዘርፉ የገጠሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ሰፋ ያለ ውይይትም የመጀመርያ ዙር ሰልጣኞች በገጠርም ሆነ በከተማው በአፋጣኝ ወደ ስራ የሚገቡበት ሁኔታ ምችችት እንዲደረግና ለዚህም ጉዳዩን በባለቤትነት የያዙት ባለድርሻ አካላት ተቀዳሚ ተግባራቸው አድርገው ሊወስዱትና ጉዳዩንም ከዳር ሊያደርሱት እንደሚገባ ተገልፇል::
በተጨማሪም ሰልጣኞች የወሰዱት የሙያ ክህሎት ወደ ሀብት እንዲለወጥ እንዲሁም ያሰለጠንናቸው ወጣቶች ወደ ስራ መሰማራታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ዘርፉ ላይ ያለውን የሀብት ብክነት እንደሚታደግ የተገለፀ ሲሆን ሁሉም የባለድርሻ አካላት በመረባረብ የስልጠናውን ውጤት ማሳየት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል::
በመጨረሻም ለሁለተኛ ዙር ስልጠና በተደረገው የሰልጣኝ የምልመላ ሂደት ላይ እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮች በመድረኩ በዝርዝር ተነስተው ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በገጠሩ ያሉ ወጣቶችን በምልመላው መስፈርት መሰረት ተመልምለው ለክላስተር ሀላፊዋች ወደ ስልጠናው እንዲገቡ ጠንከር ያለ መልእክትም ተላልፏል።
በመድረኩ ማገባደጃም በአስተዳደሩ ከሚገኙ የከተማ እና የገጠር አራት ክላስተሮች የተወጣጡ የአንድ ማዕከል ባለሞያዎች እና ሀላፊዎች የጋራ ውይይት አካሂደዋል::
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 29/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ ዓመት በተቋሙ ለሚጀመረው የEASE ፕሮጀክት SIP Validation እና የፕሮጀክት ማስጀመርያ መድረክ አካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የስልጠና መርሀ-ግብር SIP(Strategic Investment Plan) ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በእለቱ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም ይህን የEASE ፕሮጀክት ትግበራ ላይ ሲውል የከተማና የገጠር ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ መሆን እንደሚገባው ተናግረው አያይዘውም መሰል ፕሮጀክቶች በአግባቡ ካልተመሩ እና በትክክል ለተቀመጠላቸው አላማ ማይውሉ ከሆነ ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው እንደሚያመዝን ጠቅሰው ኮሌጁ ከሌሎች ትምህርት በመውሰድ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት እቅድ መሰረት እንዲመራና የሚፈለገውን ግብ እንዲመታ አደራ ብለዋል::
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ እሰፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም ይህ ፕሮጀክት የኮሌጁ የፈንድ ራይዚንግ ክፍል የመጀመርያ ስራ የሆነው የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀክት መሆኑን አስታውሰው በብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ታልፎና ብዙ ኮሚትመንት ተጨምሮበት ዛሬ ለደረስንበት ደረጃ መብቃቱን ጠቅሰው በነበረው ሂደት ላይም ቀላል ማይባሉ እድካሚና እሰልቺ መንገዶች ታልፈው እዚህ እንደደረሰ በመግለፅ ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ትልቁን ሚና ለተወጡት የፕሮጀክት አስተባባሪዎች ትልቅ ምስጋና አቅርበዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ 5 አመታት ውስጥ አንድ የራሱን አሻራ አሳርፎ የሚያልፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀው ዛሬ ይህ ፕሮጀክት ለሰራተኛው ሲቀርብም በተቻለ መጠን የሰራተኛውን ተሳትፎና የሁሉንም ሰው ርብርብ እንደሚጠይቅ ግንዛቤ ለመፍጠር ሲሆን የፕሮጀክት ውጤታማነት የሚለካውም በሁሉም የጋራ ተሳትፎ መሆኑንም አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል::
በመድረኩ የEASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀርት ሰነድ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለተቋሙ ሰራተኛ የቀረበ ሲሆን በዚህም ይህ ፕሮጀክት ከምን ተነስቶ እንደተጀመረና አላማውስ ምንድነው ከሚለው ጀምሮ የፕሮጀክቱን ዋና ሰነድ በዝርዝር አቅርበዋል::
በመጨረሻም የፕሮጀክቱን SIP(Strategic Investment Plan) እንዲሁም ከፕሮጀክቱ የሚጠበቁ ውጤቶችን በተመለከት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ በሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን አጠቃላይ በመድረኩ በቀረቡ ሰነዶች ላይ ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጎበታል::
ፕሮጀክቱ በዋናነት የስራ እድል ትስስርን ይፈጥራል የተባለ ሲሆን ይህም በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካቶችን የሞያ ክህሎትን በማሰልጠን ከገበያው ጋር የሚያስተሳስር መሆኑም ተገልፇል።
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 28/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ወጣቶችን የስራ እድል ትስስርን የሚፈጥር ኘሮጀክት በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስትራቴጂክ ፕላን ቀርቦ ውይይት ተካሄዶል::
የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የስልጠና መርሀ-ግብር ስትራቴጂክ ፕላን ቀርቦ ውይይት ተካሔደ። ይህ ፕሮጀክት ለአምስት አመት እንደሚቆይ ተገልጿል።
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7 ሚልየን ዶላር EASE Education and Skills for Employ Ability (EASE) ኢዱኬሽን ኤንድ ስኪል ፎር ኢምፑሊቲ ፕሮጀክትን የማስጀመር መርሀ-ግብር ተካሒዷል።
ፕሮጀክቱ በዋናነት የስራ እድል ትስስርን ይፈጥራል ይህም በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካቶችን የሞያ ጥበብን ወይም ስኪልን በማሰልጠን ከገበያው ጋር ያስተሳስራል።
በዚህ EASE ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተው መርሀ-ግብሩን ያስጀመሩት በድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ባስተላለፉት መልእክት ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ጠንካራ አመራር ሰጪነት ወሳኝ እንደሆነ ገልፀው ለታለመለት አላማም መሰረት አድርጎ መከናወን እንዳለበት አሳስበዋል።
ኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በማኒፋክቸሪንግ ፣ በኤሌክትሮ ቴክኖሎጂና በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ የስልጠና መስኮች ከመማርና ማስተማር ጋር ያሉ የትምህርት ጥራትን አካቶ ተወዳዳሪነትን የሚጨምሩ የኢንዱስትሪ ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ የስልጠና መስኮችን ለመቅረፅ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው ሲሉ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ ተናግረዋል።
ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዚህ በፊት በመደበኛ ከሚሰጠው ስልጠና ይህ EASE ፕሮጀክት ዋና አላማ አካታች የሆነ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠናው ይሰጣል ሲሉ የፕሮጀክቱ ዋና ኮርድኔተር አቶ ፋሲል ማዘንጊያሽ ገልጸዋል።
ይህ EASE Education and Skills for Employ Ability ፕሮጀክት ኮሌጁ ከአምስት አመት በኋላ አሁን ካለበት ስልጠና የመስጠት አቅም በቴክኖሎጂ የተደገፈ መሰረተ ልማት የተሟላለት ኮሌጅ እንዲሆን ያስችለዋል ተብሏል።
#DGC ህዳር 26/2017
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
