fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 744
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከታች የተቀመጠውን መስፈርት ለሚያሟሉ ትምህርትና ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ ከሰኞ 16/09/2013 ዓ.ም ጀምሮ ምዝገባ የሚጀምር መሆኑን በደስታ ይገልፃል።

ፎቶ ሳይነሳ ያመለጠው አስከ ማታ ፎቶ አላዛር ሄዶ መነሳት ይቻላል አድራሻ: አማን ሆቴል ቁ-2 ስጋ ቤት አጠገብ።

………………………………… የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1442ኛው የኢድ-አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል። #ኢድ_ሙባረክ

…………………………………………… የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራር አባላት የእስልምና እምነት ተከታይ በሆነው የስራ ባልደረባቸው መኖርያ ቤት በመገኘት በጋራ የአፍጥር ስነ-ስርዓት ላይ በመካፈል አብሮነታቸውን አሳይተዋል።

ለ አሰልጣኝ መምህራን እና አስተዳደር ሰራተኞች:: ለመታወቂያ የሚሆን መረጃ እየተሰበሰበ ስለሆነ በየ ዲፓርትመንት እና በየስራ ክፍላችው እድትሞሉ በትህትና እንጠይቃለን።

………………………………………………… የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የቴክኖሎጂና ክህሎት ውድድር ላይ ኮሌጃችንን ብሎም አስተዳደሩን ወክለው በመሳተፍና ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ተቋሙን እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩን ላኮሩት አሰልጣኝ መምህራኖች እና ሰልጣኝ ተማሪዎች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ኘሮግራም በማዘጋጀት ጀግኖቹን አመስግኗል። ተሸላሚዎችም ለተደረገላቸው እውቅናና ሽልማት በማመስገን እንዲ አይነት ማበረታቻዎች በቀጣይ በበለጠ ጠንክረው እንዲሰሩና ከዚህም የላቀ ውጤት ለማምጣት የሞራል ስንቅ እንደሚሆናቸው ገልፀዋል።

የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ ይላል። #መልካም_የፋሲካ_በዓል

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ …………………… ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተሰናዳው የቴክኖሎጂ እና ቴክኒካል ክህሎት ውድድር ላይ ድሬዳዋን እንዲሁም ተቋማችንን በመወከል የተወዳደረው አሰልጣኝ መምህር #ስንታየሁ_ቀጭኔ በተወዳደረበት ዘርፍ(CNC) ከመላው ኢትዮጵያ ከመጡ ተወዳዳሪዎች 1ኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳልያ እና የ30ሺህ ብር ተሸላሚ መሆን ችሏል። በዚህም አሰልጣኝ መምህራችን ያስመዘገበው ላቅ ያለ ውጤት የተቋማችንን እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደርን ስም በክብር ያስጠራ በመሆኑ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተገኘው ድል ደስታውን እየገፀ ለአሰልጣኝ መምህር #ስንታየሁ_ቀጭኔ ላቅ ያለ ክብርና ምስጋና ያቀርባል።👏👏👏

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ …………………… ▶በ 2013 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የቴክኖሎጂ እና ክህሎት ውድድር ላይ ኮሌጃችንን እንዲሁም ድሬዳዋን ወክለው የተሳተፉ የተቋማችን አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ በድል ተመልሰዋል። ▶በዚህ በተገኘው አኩሪ ውጤትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንኳን ደስስስ አላችሁ እንኳን ደስስ አለን ማለት ይወዳል። ▶በውድድሩ ውጤት ያስመዘገቡ የኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች:- 💥አሰልጣኝ መምህር #ስንታየሁ_ቀጭኔ በተወዳደሩበት ዘርፍ 1ኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ። 💥አሰልጣኝ መምህር #ደረጀ_ሽፈራው በተወዳደሩበት ዘርፍ 3ኛ በመውጣት የነሀስ ሜዳልያ ተሸላሚ። 💥አሰልጣኝ መምህር #ብሩክ_አንለይ በተወዳደሩበት ዘርፍ 3ኛ በመውጣት የነሀስ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆነዋል። በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን።👏👏👏