fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 743
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
"Laminated Managerial Table" ======================== ✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የዉድ ወርክ ቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት በድሬዳዋ አቀፍ በተካሄደ የቴክኖሎጂ ውድድር ላይ በመሳተፍ "Laminated Managerial Table" በመስራት ከአቻ ኮሌጅ ዲፓርትመንት በመላቅ አንደኛ መውጣት ችሏል፤ ✍️ ይህም ቴክኖሎጂ በዋናነት ከውጭ ሀገር ወደ ሀገር ውስጥ በከፍተኛ ገንዘብ የሚገባውን እንዲሁም እዚሁ በማምረት የውጭ ምንዛሬን የሚያስቀር ሀገራዊ ፋይዳው ቀላል የማይባል ስራ ነው፤ ከዚህ በተጨማሪ ዲፓርትመንቱ የተለያዩ የፈርኒቸር ውጤቶችን በጥራት በመስራት ላይ ይገኛል፤ ✍️ በሌላ በኩል ጥያቄዎችን ተቀብሎ በጊዜ ሰርቶ ከማስረከብ አንጻር የሚነሱ ቅሬታዎችንም ለመፍታት ከሰው ሃይል፤ ከማቴሪያል አቅርቦትና ግዢ፤ እንዲሁም አጠቃላይ አሰራር ላይ የኮሌጁ ምርትና አገልግሎት መመሪያ ተሻሽሎ ተግባራዊ ከመሆኑ ሂደት የሚያመጣው ማሻሻያ ጎን ለጎን ከሚመለከታቸው ሂደቶች እና የስራ ክፍሎች ጋር በመናበብ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ የዲፓርትመንቱ ተጠሪ አሰልጣኝ መምህር ዮሴፍ እንዳልካቸው ለኮምንኬሽን ክፍላችን ገልጸዋል። ድሬዳዋ ሚያዚያ 06/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን

photo content
+5

"የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች ቅኝት" ======================= ✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ተልዕኮዎች ውስጥ ችግር ፈቺና አዋጪ የሆነ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስልጠና ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዞች በማቅረብና ኢንተርኘራይዞችን በማሰልጠን ቴ/ጂዎችን ለማሸጋገርና ብቃቱ የተረጋገጠ ኢንተርኘራይዝ መፍጠር ጥራት ያለው ተወዳዳሪ የሆነ ምርት በማምረት ራሳቸውም ማህበረሰቡንም በመጥቀም ምርትና ምርታማነታቸውን በማሳደግ ሀብት ማፍራት እንዲችሉ ማድረግ ሲሆን በዚህ ቴክኖሎጂ ተሳታፊና በቴክኖሎጂው በመጠቀም የራሳቸውን ሀብት፤ እውቀት፣ ቴክኖሎጂን100 ፐርሰንት የመቅዳት አቅም ከፍ ያደርጋሉ ተብሎ ይታመናል፡፡ ✍️ በአስተዳደሩ የሚገኙ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ገበያን መሠረት ያደረጉ እና በጥራት፣ በምርታማነት፣ በጊዜና በዋጋ ተወዳዳሪ የሆኑ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ማቅረብ እንዲችሉ ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ማመቻቸት የግድ ይላል፤ ለዚህም ኮሌጁ የማህበረሰቡን ችግር ሊፈታ የሚችል ቴክኖሎጂ የመስራት አቅሙን ከፍ ለማድረግና ብቃቱ የተረጋገጠ ቴክኖሎጂን ማለትም የዳቦ ማሽን ሙሉ ፓኬጅን የያዘ ይህም የማቡኪያ፤ማኮፈሻና የመጋገሪያውን ናሙና እና የፕላስቲክ ተረፈ ምርትን ወደ ምርትነት የሚቀይር ማሽን በመስራት ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዞች በማሸጋገር ምርታማነታቸው እንዲጨምርና ሀብት እንዲያፈሩ አላማው በማድረግ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወስ ነው፡፡ ✍️ በዚህም አሰልጣኝ መምህራን በዚህ ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ሲሳተፉ ቴክኖሎጂውን 100 ፐርሰንት የመቅዳት አቅም ከፍ ያደርጋሉ ተብሎ ይታመናል፤ በትግበራው ያገኙትን ዕውቀት ክህሎት በመጠቀም በገበያ ተወዳዳሪ አዳዲስ የሆኑ ምርቶችን በማቅረብ ማህበረሰቡን እንዲሁም እራሳቸውን ወደ ተሻለ ቴክኖሎጂ መግባትና መጠቀም አንዲችሉ ያስችላል፤ ተፈትሾ ጥራታቸው የተረጋገጠ ቴክኖሎጂዎች ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዞች በማሸጋገር ምርታማነታቸው እንዲጨምርና ሀብት እንዲያፈሩ ማድረግ ስለሚያስችል እንዲሁም የማህበረሰቡን ችግር በመፍታት ተቋሙን እና አሰልጣኝ መምህሩን በሃገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን የኮሌጁ ኮምንኬሽን ክፍል የቴክኖሎጂ ስራዎቹም አሁናዊ ሁኔታ ቅኝት በማድረግ ስራዎቹ የደረሱበትን ደረጃ ለመመልከት ችሏል፡፡ ድሬዳዋ ሚያዚያ 04/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

የኮሌጅ የቦርድ አመራር __ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከረጅም ጊዜ በኋላ የኮሌጁ የቦርድ አመራር በአዲስ መልክ ተዋቅሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድና ኢንደስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ሰብሳቢነት በኮሌጁ ስማርት የመሰብሰቢያ ክፍል የመጀመሪያውን ስቡሰባ አድርጓል በዚህም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለቦርዱ አባላት እንደ ከተማ አስተዳደር በኮሌጁ ትኩረት ሊያገኙ እና ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን አቅርበው ውይይት ማድረግ ተችሏል። ድሬዳዋ ሚያዚያ 01/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

photo content
+5

የኮሌጅ የቦርድ አመራር __________ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከረጅም ጊዜ በኋላ የኮሌጁ የቦርድ አመራር በአዲስ መልክ ተዋቅሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድና ኢንደስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ሰብሳቢነት የመጀመሪያውን ስብሰባ በኮሌጁ ስማርት የመሰብሰቢያ ክፍል የመጀመሪያውን ስቡሰባ አድርጓል በዚህም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለቦርዱ አባላት እንደ ከተማ አስተዳደር በኮሌጁ ትኩረት ሊያገኙ እና ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን አቅርበው ውይይት ማድረግ ተችሏል። ድሬዳዋ ሚያዚያ 01/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

photo content
+2

የአገልግሎት ማሻሻያ ጥናቶች ላይ ውይይት ተደረገ ==================================== በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2014 ዓ.ም ትኩረት የተሰጠበት ስራዎች በዋናነት የሚሰጡ አገልግሎቶችን አሰራርና መመሪያዎችን በማሻሻል ለትግበራ አመቺ የሚሆኑበትን መንገድ ቀይሶ ይህንንም ለማስፈጸም በኮሌጁ የሚገኙ የA ደረጃ መምህራንና የሚመለከታቸውን በማዋቀር የተለያዩ ጥናቶች እንዲጠኑ መወሰኑ የሚታወስ ሲሆን በዚህም መሠረት የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አገልግሎቶችን ለማሻሻል የተጠኑ ጥናቶች በተጨማሪም የምርትና አገልግሎት መመሪያ ለኮሌጁ አመራር ፑል ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል በዚህም ውይይት ላይ ተሳታፊዎች ቢታይ እና ቢሻሻል ያሏቸውን ሀሳብና አስተያያት ያነሱ ሲሆን በቀጣይም ጥናቶቹ ዳብረው የሚጠናቀቁበት አቅጣጫ ማስቀመጥ ተችሏል። ድሬዳዋ መጋቢት 30/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

photo content
+5

ተማሪዎች በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ ====================== በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቀደም ሲል ከተለያዩ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረገው ውይይትና በተደረሰው የጋራ መገባባትና በተዘጋጀው ዕቅድ መሰረት የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ ማለትም(STEM) ግንዛቤ ለማስጨበጥ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዓ.ም ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በዚህም ተማሪዎቹ የተግባር ስልጠና የሚሰጥባችውን የትምህርት ክፍል(workshop) በመጎብኘት ስለቴክኒክና ሙያና በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ (STEM) ግንዛቤ ማስጨበጥ ተችሏል፡፡ እንዲሁም ተማሪዎቹ የማኑፋክቸሪግ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል፤ የአውቶሞቲቭ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል፤ የውድ ቴክኖሎጂ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል እና የኤሌክትሪክና ኢሌክትሮኒክስ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል አሰልጣኝ መምህራን ለጉብኝት ለመጡት ተማሪዎቹ የተግባር ስልጠና የሚስጥበትን ክፍሎች(workshops) በማስጎብኘት ተማሪዎቹን ግንዛቤ እንዲጨብጡ አድርገዋል፡፡ ድሬዳዋ መጋቢት 30/2014 የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

photo content
+5

በኮሌጁ የሚገኙ ቦታዎችን የማልማት እንቅስቃሴ ================================ ✍️ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሚታወቅበትን ጽዱ እና አረንጓዴያማ ገጽታውን ወደነበረበት ለመመለስ አልፎም ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ኮሌጁ አቅዶ እየሰራበት ይገኛል፤ ✍️ ከዚሁ ጎን ለጎን አንዳንድ ዲፓርትመንቶች እና ክፍሎች ቀድመው ወደ እንቅስቃሴ የገቡ እንዳሉ መመልከት ችለናል በተለይም በኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት አሰልጣኝ መምህራን እና ወርክሾፕ ባለሙያ ወርክሾፓቸው አካባቢ እና በኮሌጁ የጥበቃ ሰራተኞች መግቢያው በር አካባቢ እያደረጉ ያሉት ለምግብነት የሚውሉ አትክልቶችን የማልማት ተግባር በሌሎችም ዲፓርትመንቶችና የስራ ክፍሎች ተሞክሮው ሊሰፋ ይገባል፤ ✍️ በቀጣይ የሌሎች ዲፓርትመንቶችና የስራ ክፍሎችን እንቅስቃሴ እየተከታተልን የምናጋራችሁ ይሆናል። የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን መጋቢት 07/2014 ዓ.ም ድሬዳዋ