fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 739
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+27 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምርቶች እና አገልግሎቶች ጥራት የማረጋገጥ ስራ ዓለም አቀፍ አሰራር ስርዓትን መሰረት በማድረግ ለአምራቾች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች፣ ለላኪዎች፣ ለአስመጪዎች፣ ለተ
+7
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምርቶች እና አገልግሎቶች ጥራት የማረጋገጥ ስራ ዓለም አቀፍ አሰራር ስርዓትን መሰረት በማድረግ ለአምራቾች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች፣ ለላኪዎች፣ ለአስመጪዎች፣ ለተቆጣጣሪ መስሪያ ቤቶች፣ ለምርምር ተቋማት እና በአጠቃላይ ለሸማቹ ማህበረሰብ የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎትን የሚሠጥ መንግስታዊ ድርጅት ነው። ‎ ‎በድሬዳዋ አካባቢ ለሚገኙ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ ነፃ የንግድ ቀጣና እንዲሁም የደረቅ ወደብን መሰረት በማድረግ ቀደም ብሎ ይሰጡ ከነበሩ የጥራት ማረጋገጫ  አገልግሎቶች በተጨማሪ በምግብ ዘይት፣ ፔትሮሊዬም ወይም የነዳጅ ምርት፣ የተለያዩ የምግብ ምርቶች፣ የማስዋቢያና የዲተርጀንት ምርቶች፣ የተለያዩ የኮንስትራክሽን ምርቶችንና ግብዓቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አዲስ  የፍተሻ ላቦራቶሪ በማደራጀት አገልግሎቱን ተደራሽ አድርጓል ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያደረጉት ጉብኝት፡-

ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ በውስጡ 10 ተቋማት ይዞ 73 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ለዜጎች በመስጠት ላይ ይገኛል። አንድ ማዕከሉ ተገልጋዬችን የሚያስተናግዱ 96 ካውንተሮች እንዲኖሩት ተደርጎ
+6
ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ በውስጡ 10 ተቋማት ይዞ 73 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ለዜጎች በመስጠት ላይ ይገኛል። አንድ ማዕከሉ ተገልጋዬችን የሚያስተናግዱ 96 ካውንተሮች እንዲኖሩት ተደርጎ የተደራጀ ነው። ማዕከሉ ስራ ከጀመረበት ስድስት ወራቶች ውስጥ በአጠቃላይ ከ23 ሺ በላይ ተገልጋዮችን አስተናግዷል። ከፍ ብሎ የተጀመረውን  የተቀላጠፈ የዲጅታል አገልግሎት ይበልጥ ለማስፋት አቅዶም እየሠራ ነው።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ከሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር በኢንዱስትሪው ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ የምክክር መድረክ አካሄደ:: በመድረኩን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ እንዱስትሪውን ከመደገፍ አኳያ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ታልሞ በሚዘጋጀው ጥናት ላይ ከኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ ተካሂዷል:: በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ትኩረት ተደርጎባቸው ከሚከናወኑ ቁልፍ ተግባራት መካከል ኢኮኖሚውን የሚያንቀሳቅሱ የአምራች እንዱስትሪዎችን አቅም ማጎልበት አንደኛው መሆኑን የጠቀሱት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ በዚህም በሰለጠነ የሰው ሀይል፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ላይ በኢንዱስትሪው ፍላጎት መሰረት በዘላቂነት ድጋፍ ለማድረግ እንዲቻል የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ቡድን በማዋቀር በተቋም ደረጃ ጥናት እያካሄድን እንገኛለንም ብለዋል:: በመድረኩ ለፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ውይይቱ መነሻ የሚሆን ሰንድ በጥናት ቡድኑ አማካኝነት ለባለ ድርሻ አካላቱ ገለፃ የተደረገ ሲሆን በተጨማሪም ኢንዱስትሪዎችን በዘርፍ በመክፈል በቡድን እንዲወያዩ ማድረግ ተችሏል:: በተካሄደው የቡድን ውይይት ወቅትም ኢንዱስትሪዎች በሰለጠነ የሰው ሀይል፣ ተኪ በሆኑ ቴክኖሎጂዎች እና በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ላይ ያሏቸውን ፍላጎቶች ለይተው በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን በቀጣይ በቅንጅት መስራት በሚቻልበት እግባብ ላይም አመርቂ ውይይቶችን በማድረግ ለጥናቱ አስፈላጊ ግብዓቶች የተገኙበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካቲት 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሙ የ10 አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ለባለ ድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ። በመድረኩ በዋናነት የኮሌጁ የቀጣይ 10 አመት ስትራቴጂ እቅድ እንዲሁም የተቋሙ የሰው ሀይል ልማት ረቂቅ ሰነድ ለኮሌጁ አድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላትና ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይቶች ተካሂደዋል:: ኮሌጁን በቀጣይ አመታት ግልፅ በሆነ ስትራቴጂ ለመምራት የሚያስችል አቅም የሚፈጥር የ10 አመት ስትራቴጂክ እቅድ መዘጋጀቱን ያስታወቁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ ይህ የ10 አመት ስትራቴጂክ እቅድም ሰፊና ብዙ ጉዳዮችን በውስጡ የያዘ ከመሆኑም በተጨማሪ መጪውን ዘመንም ታሳቢ በማድረግ የተዘጋጀ በመሆኑ መሪ እቅዱን ለባለድርሻ አካላት ለማስተዋወቅ ያለመ መድረክ መሆኑንም ገልፀዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ከፌደራል በተሰጠን ተልዕኮ መሰረት አዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂክ እቅድ ለህብረተሰቡና ለኢንዱስትሪው እንዲወርድ አቅጣጫ መሰጠቱን አስታውሰው የዘርፉን እስትራቴጂ በተቋም ደረጃ ስናወርድ ምን ምን ተግባራት ይከናወናሉ የሚለውንም የሚመልስ እስትራቴጂክ እቅድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በቀጣይ የዘርፉን እስትራቴጂክ እቅድ ከተቋማችን የ10 ዓመት እስትራቴጂክ እቅድ ጋር የምናስተዋውቅ ይሆናል ብለዋል:: በመድረኩ የኮሌጁን የ10 አመት እስትራቴጂክ እቅድ በኮሌጁ የእቅድና በጀት ዝግጅት ባለሙያ በሆኑት አቶ አለማየሁ ብርሃኑ እማካኝነት ለባለድርሻ አካላት የቀረበ ሲሆን በዚህም ኮሌጁ እንደ አንድ የትምህርትና ስልጠና ተቋም ከተሰጠው ተልዕኮ አንፃር በቀጣይ 10 አመታት በትኩርት የሚያከውናቸውን ቁልፍ ጉዳዮች በዝርዝር ለመድረኩ ተሳታፊዎች ገለፃ ማድረግ ተችሏል:: በቀረቡት ረቂቅ ሰነዶች ላይ ከባለ ድርሻ አካላት ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶባቸው ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገ ሲሆን በዚህም የስትራቴጂክ እቅዱ ከኢንዱስትሪው አኳያ ታሳቢ ያልተደረጉና መካተት ይገባቸዋል ያሉዋቸውን ገንቢ ሀሳቦችም በመድረኩ አንስተዋል:: በቀጣይ የኮሌጁ የ10 አመት ስትራቴጂክ እቅድ ላይ የተገኙ ግብዓችን አካቶ ለኮሌጁ ቦርድ አቅርቦ በማፀደቅ ወደ ትግበራ እንደሚገባም በመድረኩ ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካቲት 26/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና ስራ ሂደቶች የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወር የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብር ማካሄድ ጀመረ:: በኮሌጁ ዲን በሚመራው በዚህ የድጋፍና ክትትል በድጋፍና ክትትል ቡድኑ በተዘጋጀው ቼክሊስት መሰረት ትምህርትና ስልጠና ክፍሎች፣ ዋና ስራ ሂደቶችና የስራ ክፍሎች በግማሽ አመቱ በእቅድ አፈፃፀም፣ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በስልጠና ጥራት፣ በመረጃ አደረጃጀት፣ በሀብት ማፍራትና ግብዓት አጠቃቀም ላይ ባተኮሩ ነጥቦች መነሻነት ሂደቶችና ክፍሎች ያሉበትን ቁመና የሚገመግም የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብር መሆኑም ተገልጿል:: የዚህ ድጋፍና ክትትል ዋና አላማ በተቋሙ የሚገኙ ስራ ሂደቶችና ክፍሎች ከተሰጣቸው ተልዕኮ አንፃርና ካስቀመጡት ግብ አኳያ ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ ክትትል ለማድረግና በአፈፃፀም ክፍተት የሚታይባቸውን ተግባራቶች ተለይተው ክፍተቶች እንዲሞሉ ድጋፍ የማድረግ ሲሆን በተጨማሪም የተሻለ አፈፃፀም ለታየባቸው ስራ ሂደቶችና ክፍሎች እውቅና በመስጠት ለሌሎች ሞዴል እንዲሆኑ ማስቻል እንደሆነው ተገልፇል:: በድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብሩ እስካሁን የአውቶሞቲቭ፣ የማኑፋክቸሪንግ፣ የአይ.ሲ.ቲ፣ የውድ ዎርክ እና የኮስትራክሽ ትምህርትና ስልጠና ክፍሎችን ማካሄድ የተቻለ ሲሆን በቀጣይ ቀናትም በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የድጋፍና ክትትሉ የሚቀጥል መሆኑም ታውቋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካቲት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ከደረጃ 5 ወደ 8፤ የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ አዲስ ምዕራፍ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የአምራች ኢንዱስትሪውን ፍላጎት መለየት የሚያስችል የውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ:: ከተማችን ድሬደዋ የኢንዱስትሪ ማዕከል ከመሆኗ ጋር ተያይዞ አምራች ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ብቁና የሰለጠን የሰው ሀይል በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ አሰልጥኖ ለማቅረብ ታሳቢ ያደረግ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናትና የምክክር መድረክ ከኮልጁ የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ አካላት ጋር ማካሄድ ተችሏል:: የምክክር መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው "ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ወጣቶች ከረጅም ጊዜ ስልጠና ይልቅ ወቅቱ ሚጠይቀውን የአጫጭር ሙያ ስልጠናዎች ላይ ትኩረት በማድረጋቸው አምራች ኢንዱስትሪው በሚፈልገው ልክ የበቃ የሰው ሀይል የማቅረብ ውስነት እንዲስተዋል እድርጎታል ያሉ ሲሆን ይህን ክፍተት በዘላቂነት ለመቅረፍ የአምራች ኢንዱስትሪውን የሙያ ፍላጎት መሰረት ያደረገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም መቅረፅ አስፈላጊ በመሆኑ ከኢንዱስትሪ አድቫይዘሪግ ቦርድ አባላት ጋር ለመወያየት ይህ መድረክ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል:: በEASE ፕሮጀክት ትኩረት ተደርጎባቸው ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ለኢንዱስትሪው ግብዓት የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን የማፍራቱን ሂደት መደገፍ አንደኛው መሆኑን ያስታወሱት የፕሮጀክቱ ኮርዲኔተር ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ የፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ከትምህርትና ስልጠና ዘርፉ ጋር በመቀናጀት በሚያዘጋጁት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደርገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ላይ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግም ገልፀዋል:: የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት አስፈላጊነት ዝርዝር ዓላማ እንዲሁም የአጫጭር ስልጠና ሞጁሉን በማዘጋጀት ሂደት ውስጥ የሚያካተቱ ዝርዝር ተግባራትን በተመለከተ በኮሌጁ ም/ል ዲን እና የትምህርትና ስልጠው ዋና ሀላፊ በሆኑት አቶ ኤሊያስ አህመድ አማካኝነት ለባለ ድርሻ አካላት ግንዛቤ መስጠትም ተችሏል:: በመድረኩ በነበረው ውይይት ኢንዱስትሪውን ወክለው የተገኙ ተስታፊዎች አምራች ኢንዱስትሪዎች ከበቃ የሰው ሀይል አኳያ ያላቸው ፍላጎት ለጥናት ቡድኑ በዝርዝር አቅርበው ሰፊ ውይይት የተካሄደት ሲሆን ለፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችም የተገኙበት መድረክ ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካቲት 21/6/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት በተቋሙ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት
+4
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት በተቋሙ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የስልጠና ዘመኑ የአንደኛ ተርም መጠናቀቁን ተከትሎ በተርሙ የተከናወኑ የትግበራ አፈፃፀም እና የሁለተኛ ተርም ማስጀመሪያ የውይይት መድረክ ተካሂዷል:: የውይይት መድረኩ የመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው እንደግለፁት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የትምህርትና ስልጠናው የመጀመሪያ ተርም ተጠናቆ ሁለተኛውን ተርም ምንጀምርበት ወቅት ላይ እንደመሆናችን የነበሩ ክፍተቶችን በሚገባ ለይቶ መፍትሄ ለማበጀትና በሁለተኛው ተርም ላይ ማስተካከያ ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑንም ገልፀዋል:: በመድረኩ ተሳታፊ ከነበሩት አሰልጣኝ መምህራንም የመጀመርያውን ተርም የትምህርትና ስልጠና ሂደቱን አስመልክቶ የተስተዋሉ ጠንካራና ጎኖችና ያጋጠሙ ትግዳሮቶችን በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን አያይዘውም የመፍትሄ ሀሳብ ይሆናሉ ያሏቸውንም በመድረኩ አቅርበዋል:: በመጨረሻም ከመድረኩ በተገኙ ግብዓቶችና አጠቃላይ በተነሱ ሀሳቦች ላይ በመወያየት ሰፊ ማብራርያና ምላሽ የተሰጠባቸው ሲሆን በተጨማሪም በቀጣይ በተቋምና አገር አቀፍ ምዘና ሰልጣኝ ተማሪዎችን ማብቃት፣ፕሮጀክት መሰረት ያደረገ ስልጠና፣የትብብር ስልጠና፣ የዲጂታል ስልጠና አገልግሎት እና አሰልጣኝ መ/ራንን በረጅም ጊዜ የማሰልጠን ስነዘዴ ማብቃት ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የጋራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካቲት 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ