ኦርቶዶክስ ሃይማኖታችን
رفتن به کانال در Telegram
✞የኦርቶዶክስ ቻናል✞ > የየዕለቱ ስንክሳር >ኦርቶዶክሳዊ ጥያቄዎች ከነመልሱ > በቅርብ የጀመረው አስተማሪ ታሪኮች > መንፈሳዊ ዝማሬዎች > የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ > መንፈሳዊ ፊልሞች > መንፈሳዊ ትምህርቶችና የተለያዩ ፁፎች #ሁሉም_በየእለቱ
نمایش بیشتر940
مشترکین
-224 ساعت
+17 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
🕊
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
[ ✞ እንኳን ለአባቶቻችን ቅዱሳን ፲፪ [ 12 ] ቱ ደቂቀ ነቢያት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]
🕊 ✞ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት ✞ 🕊
ነቢይ ማለት ከእግዚብሔር ተመርጦ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን] : መጻዕያትን [ለወደፊቱ የሚደረገውን] የሚያውቁ ሰዎች ሲሆኑ ሕዝቡን እንዲመሩ: እንዲገስጹም ይላካሉ:: ሕይወታቸውም በቅድስና የተለበጠ ነው:: ነቢያትን በቁጥር መግለጽ ከባድ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን እንድንረዳቸው እንዲህ ትከፍላቸዋለች::
=> በኩረ ነቢያት አዳም
=> ሊቀ ነቢያት ሙሴ
=> ርዕሰ ነቢያት ኤልያስ
=> ልበ አምላክ ዳዊት
=> ፲፭ [15] ቱ ነቢያት [ከአዳም ጀምሮ እስከ ሳሙኤል]
=> ፬ [4] ቱ ዐበይት ነቢያት [ኢሳይያስ: ኤርምያስ: ሕዝቅኤልና ዳንኤል]
፲፪ [12] ቱ ደቂቀ ነቢያት ደግሞ ከሆሴዕ እስከ ሚልክያስ ያሉት ናቸው:: በዚህች ቀን ታዲያ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት በአንድነት ይታሠባሉ:: እነዚህም :-
፩. ቅዱስ ሆሴዕ [ኦዝያ]
፪. ቅዱስ አሞጽ
፫. ቅዱስ ሚክያስ
፬. ቅዱስ ኢዩኤል
፭. ቅዱስ አብድዩ
፮. ቅዱስ ዮናስ
፯. ቅዱስ ናሆም
፰. ቅዱስ እንባቆም
፱. ቅዱስ ሶፎንያስ
፲. ቅዱስ ሐጌ
፲፩. ቅዱስ ዘካርያስ እና
፲፪. ቅዱስ ሚልክያስ ናቸው::
ቅዱሳኑ ደቂቀ ነቢያት የተባሉት
፩. የነቢያት ልጆች በመሆናቸው
፪. የጻፏቸው ሐረገ ትንቢቶች በንጽጽር ከዐበይቱ [ከነኢሳይያስ] ስለሚያንስ ነው::
በምግባር: በትሩፋት: በአገልግሎት ግን ያው ናቸው:: ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እሊህን ነቢያት "እለ አውኀዙ ተነብዮ በእንተ ስመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ" ይሏቸዋል:: [ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መውረድ: መወለድና የማዳን ሥራ የትንቢት ጐርፍን ያፈሰሱ እንደ ማለት ነው ::]
ቅዱሳኑ ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ባሻገር ዓለማችን ላይ ከነበሩበት ዘመን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሊደረጉ ያላቸውን ነገሮችም ተናግረዋል:: የነበሩበት ዘመን በአማካኝ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ፱ መቶ [900] እስከ ፭ [500] ነው:: በትንቢት ደረጃም እንደነ ሆሴዕና ዘካርያስ ፲፬ [14] ምዕራፎችን: እንደነ አብድዩም አንዲት ምዕራፍ ብቻም የጻፉ አሉ::
በሕይወታቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ያሻቸው ናቸውና በየጊዜው ከእግዚአብሔር ጋር እየተነጋገሩ የእርሱን ድምጽ ለእሥራኤል [አንዳንዴም ለአሕዛብ] ያደርሱ ነበር:: ፊት አይተው የማያዳሉ ናቸውና ሕዝቡንም ሆነ ነገሥታቱን ስለ ኃጢአታቸው ይገሰጹ ነበር:: በዚህም ምክንያት ከነገሥታቱና ከሕዝቡ አለቆች መከራ ደርሶባቸዋል:: አልፎም ያለ አበሳቸው ሕዝቡ በኃጢአቱ ሲማረክ አብረውት ወርደዋል::
በመጨረሻ ሕይወታቸውም አንዳንዶቹን ክፉዎች ሲገድሏቸው አንዳንዶቹ ደግሞ በመልካም ሽምግልና ዐርፈዋል:: ዛሬ ነቢያት ከእነርሱ ባሕርይ በተገኘችና ብዙ ትንቢትን በተናገሩላት በእመቤታችን ምክንያት ክርስቶስ ድኅነትን ፈጽሞላቸው በተድላ ገነት ይኖራሉ:: ስለ እኛም ይማልዳሉ::
" ናጥሪ እንከ ትሕትና ዘምስለ ንጽሕና"
[ እንግዲህ እንደ ነቢያት ትሕትናን ከንጽሕና ጋር ገንዘብ እናድርግ ]
"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ"
[ ነቢያት መንፈስን ንጹሕ በማድረግ እግዚአብሔርን አይተውታልና: ፊት ለፊትም ተያይተዋልና ]
/ቅዳሴ ማርያም/
ከአባቶቻችን ቅዱሳን ነቢያት በረከት ይክፈለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፬ [ 4 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. "12ቱ" ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት
፪. ቅዱስ ሶፎንያስ ነቢይ [ዕረፍቱ]
፫. ቅዱሳን ሰማዕታት አቡቂርና ዮሐንስ [ቅዳሴ ቤታቸው]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጉዋድ [ወንጌላዊው]
፪. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ [ሰማዕት]
" ለእናንተም ስለሚሰጠው ጸጋ ትንቢት የተናገሩት ነቢያት ስለዚህ መዳን ተግተው እየፈለጉ መረመሩት:: በእነርሱም የነበረ የክርስቶስ መንፈስ ስለ ክርስቶስ መከራ ከእርሱም በሁዋላ ስለሚመጣው ክብር አስቀድሞ እየመሠከረ በምን ወይም እንዴት ባለ ዘመን እንዳመለከተ ይመረምሩ ነበር:: " [፩ዼጥ.፩፥፲]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🍒 🍒
🕊 ም ክ ረ ቅ ዱ ሳ ን 🕊
═══════════════
▷ ❝ ባ ዶ ነ ት ! ! ❞
[ 💛 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💛 ]
🕊 🍒 🕊
❝ ከእናንተ ዘንድ በአንዱ ስንኳ እንዳንከብድበት ፥ ሌሊትና ቀን በድካምና በጥረት እየሠራን እንኖር ነበር እንጂ ፥ ከማንም እንጀራን እንዲያው አልበላንም። ❞ [ ፪ተሰ.፫፥፰ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
👇
🕊 🌺 🕊
💛 [ ዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ] 💛
🕊 🌺 🕊
❝ † ሰላም ለቄርሎስ ወልደ አንበሳ ጽኑዕ ፤
ነባቢ ምስጢረ ሥላሴ ቅድስት ፤
ዘተናገረ ላዕለ መለኮት። ❞ [ ተአምኆ ቅዱሳን ]
[ በመለኮት ላይ የተናገረ ፤ የቅድስት ሥላሴን ምስጢርን ተናጋሪ ፤ ብርቱ [ ጠንካራ ] ለኾነ ለአንበሳው ልጅ ለቄርሎስ ሰላምታ ይገባል። ]
❝ የማኅበር አለቃ ኾኖ ቴዎፍሎስ ካሳደገው በኋላ የመጻሕፍትን ቃል የተከተለ ለኾነ ለቄርሎስ ሰላምታ ይገባል ፤ የንስጥሮስን የክሕደት እምነት ለመቃወም መለኮትን ቀለም በሸፈነው ጸምር ፤ ትስብእትንም እሳት ባጋለው በብረት መሰለ። ❞ [ ተአምኆ ቅዱሳን ]
🕊
[ † እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
🕊 💖 🕊
ጸሎቱና በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
🕊 🌺 🕊
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
🕊 🌺 🕊
[ † እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
🕊 💖 🕊
ይኽ ቅዱስ ቄርሎስ ብዙ መጻሕፍትን የጻፈ ሲኾን ከእነዚኽ ውስጥ ፦
❖ ፲፪ አንቀጽ ያለው ነገረ ሥጋዌን የሚተነትኑ ደብዳቤዎችን
❖ የብሉይ ኪዳን ትርጓሜን
❖ ስለ አርዮስ የስሕተት ትምህርት
❖ የዮሐንስ እና የሉቃስ ወንጌል ትርጓሜን
❖ በምስጢረ ሥላሴ ላይ ምላሽን
❖ የእግዚብሔር መቅደስ ስለመኾን
❖ በንስጥሮስ የኑፋቄ ትምህርት ላይ ዐምስት ታላላቅ ጽሑፎች
❖ ክርስቶስ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አንድያ ስለመኾኑ
❖ ስለ ወልድ ዋሕድ ሥጋዌ
❖ በተርሴሱ ዴዎዶር እና በሞፕሴዪስቲያው ቴዎዶርን ተቃውሞ
❖ ጁልያንን ተቃውሞ የጻፈው ወዘተርፈ ይገኙበታል፡፡
ይኽም ቅዱስ አባት የቀናች ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነትን በጽሑፉ በትምህርቱ እያስጠበቀ በመንበረ ማርቆስ ላይ ሠላሳ ኹለት ዓመት ከኖረ በኋላ መልካም ሥራውን ፈጽሞ ሐምሌ ፫ በ፬፻፵፬ ዓ.ም. በሰላም ዐርፏል፡፡
🕊
ቅዱስ ቄርሎስ በከበረች ጸሎቱ : በአማላጅነቱ አይለየን። በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
🕊
[ † እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †
🕊 † ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ † 🕊
† ቅዱስ ቄርሎስን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን " ዓምደ ሃይማኖት የሃይማኖት ምሰሶ" ይሉታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ሊቁ የተወለደው በእስክንድርያ [ግብጽ] በ፬ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: እናቱ የወቅቱ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎፍሎስ እህቱ ነበረችና አጎቱ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ወስዶ አሳድጐታል:: ገና በልጅነቱ ወደ አባ ሰራብዮን ገዳም ገብቶ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ገዳማዊ ሕይወትን ተምሯል:: በጾም: በጸሎትና በትሕትና የታሸ ነውና ሲማር አንድ ጊዜ ካነበበው በሕሊናው ተስሎ ይቀር ነበር::
ቅዱስ ቴዎፍሎስ "ምዕመናንን አስተምርልኝ" ብሎ ወደ ከተማ አመጣው:: መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ሲያስተምር ወይ ደግሞ መጻሕፍትን ሲያነብ ከምዕመናን ወገን ስንኩዋን የሚያወራና የሚንቀሳቀስ ቀርቶ የሚቀመጥም አልነበረም:: ጣዕመ ስብከቱም ብዙዎችን ለወጠ::
ከዚያም በ፬፻፲፪ [412] ዓ/ም አጎቱ የነበረው ፓትርያርክ አባ ቴዎፍሎስ ሲያርፍ ዻዻሳትና ሊቃውንት በአንድነት ቅዱስ ቄርሎስን መረጡ:: የእስክንድርያም ፳፬ [24] ኛ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሾመ:: በዘመኑ ቤተ ክርስቲያን አበራች:: በቅድስናው: በሊቅነቱ: በስብከቱ: በድርሰቶቹና በትጋቱ በፍጹም አገለገላት::
በወቅቱ ስመ ክፉ መናፍቅ ንስጥሮስ ተነስቶ የእስያ አብያተ ክርስቲያናትን አወካቸው:: ትምሕርቱ ክርስቶስን "2 አካል: ባሕርይ ነው" [ሎቱ ስብሐት!] የሚል ነበር:: በእውነት እንየው ከተባለ ግን ጠቡና ጥላቻው ከድንግል ማርያም ጋር ነበር:: ምክንያቱም ጌታችንን ወደ ፪ የከፈለው እመቤታችንን የአምላክ እናት አይደለሽም ለማለት ነው:: [ላቲ ስብሐት!]
ነገሩን ቅዱስ ቄርሎስ በሰማ ጊዜ ወዳለበት ሒዶ ቢመክረውም ንስጥሮስ ሊሰማ አልፈለገም:: በዚህ ምክንያት በትንሹ ቴዎዶስዮስ [የቁስጥንጥንያ ንጉሥ] ትዕዛዝ በኤፌሶን ታላቅ ጉባኤ እንዲሰበሰብ ሆነ:: ይህ ጉባዔ በቤተ ክርስቲያናችን የመጨረሻው የተቀደሰ ጉባዔ ነው:: በ፬፻፴፩ [431] ዓ/ም በኤፌሶን ከተማ የመናፍቃኑን ጥርቅም ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና ፪፻ [200] ቅዱሳን ሊቃውንት ተገኙ::
የሚገባው ጸሎትና ሱባዔ ከተፈጸመ በሁዋላ ጉባዔው ተጀመረ:: አፈ ጉባዔው ሊቀ ማሕበር ማር [ቅዱስ] ቄርሎስ ነበርና በጉባዔ ፊት ንስጥሮስን ተከራክሮ ረታው:: ምላሽም አሳጣው:: ከቅዱሳት መጻሕፍት ክርስቶስ አንድ ባሕርይ መሆኑን: ድንግል ማርያምም ወላዲተ አምላክ መሆኗን እየጠቀሰ: በምሳሌም እያሳየ አስረዳ::
የሰይጣን ማደሪያ ንስጥሮስ ግን እንቢ: አላምንም በማለቱ ተወግዞ ተለየ:: ቅዱሳን ሊቃውንቱም በቅዱስ ቄርሎስ አርቃቂነት ፲፪ [12] አንቀጾችን አዘጋጅተው ወደ ዓለም ሁሉ ላኩ:: እሊህ አንቀጾች ዛሬም በሊቃውንቱ እጅ አሉ:: ይነበባሉ: ይተረጎማሉ::
† ከእነዚህም አንዱ ድንግል ማርያም "ታኦዶኮስ [የእግዚአብሔር እናቱ] ናት" የሚል ነው:: እመቤታችንን :-
¤ የአምላክ እናት:
¤ ዘላለማዊት ድንግል:
¤ ፍጽምት:
¤ ንጽሕትና አማላጅ ብሎ ማመን ለሰማያዊ ርስት የሚያበቃ በጐ ሃይማኖት ነውና::
ጉባዔው ከተጠናቀቀ በሁዋላ ቅዱስ ቄርሎስ ንስጥሮስን ጠርቶ "በድንግል ማርያም እመን:: እርሷ ከልጇ ታስታርቅሃለች" ቢለው በድጋሚ "እንቢ" አለው:: ያን ጊዜ ሊቁ "ለአምላክ እናት ያልታዘዘ ምላስህ ላንተም አይታዘዝህ" ብሎ ረገመው:: ወዲያው ምላሱ ተጐልጉሎ ወጥቶ ደረቱ ላይ ወደቀ::
እንደ ውሻ እየተዝረከረከ ሒዶ ከወዳጆቹ ጋር ቁሞ ሳለ መሬት ተከፍታ ውጣዋለች:: ቅዱስ ቄርሎስ ግን ለ፴፪ [32] ዘመናት በመንበሩ ላይ አገልግሎ: ፍሬ ትሩፋት አፍርቶ: ብዙ ድርሰቶችንም ደርሶ በ፬፻፵፬ [444] ዓ/ም በዚህች ቀን ዐርፏል:: ከድርሰቶቹም ቅዳሴው: ድርሳነ ቄርሎስና ተረፈ ቄርሎስ ይጠቀሳሉ::
† ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቶቻችን ጸሎት ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቅልን:: ከሊቁም በረከቱን ይክፈለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፫ [ 3 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ [ዓምደ ሃይማኖት]
፪. ቅዱስ ክልስቲያኖስ ዘሮሜ [ታላቅ ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት]
፫. አባ ሉቅያስ ኤዺስ ቆዾስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
፪. ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
፫. ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው [ዘካርያስና ስምዖን]
፬. አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
፭. አቡነ ዜና ማርቆስ
፮. አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል
† " የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ:: የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው:: ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ: እስከ ዘለዓለምም ያው ነው:: ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምሕርት አትወሰዱ:: ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም:: በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና:: " † [ዕብ.፲፫፥፯]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊 💖 🕊
[ 🕊 ድንግል ሆይ ፦ 🕊 ]
🕊 💖 🕊
❝ ድንግል ሆይ ፦ እታመንሻለሁ ከተሠወረው መከራ በግልጽም ከሚመጣብኝ ጥፋት ሁሉ በዚህ ዓለም እንድታድኝኝ ፤ በሚመጣውም ዓለም ከገሃነመ እሳት ጥርስ ማፏጨት ፥ ጽኑ ልቅሶም ካለበት ከሚያስጨንቅ መቅሠፍት ትሠውሪኝ ዘንድ ፤ እኔም ባንቺ አማላጅነት በልጅሽም ምሕረት የታመንሁ ነኝ፡፡
በፈረሰኞች ሰልፍ በሠረገላም መንኰራኩር የምታመን አይደለሁም፡፡ ባንቺና በልጅሽ ብቻ እታመናለሁ እንጂ፡፡ ❞ [ አርጋኖን ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
