fa
Feedback
ኦርቶዶክስ ሃይማኖታችን

ኦርቶዶክስ ሃይማኖታችን

رفتن به کانال در Telegram

✞የኦርቶዶክስ ቻናል✞ > የየዕለቱ ስንክሳር >ኦርቶዶክሳዊ ጥያቄዎች ከነመልሱ > በቅርብ የጀመረው አስተማሪ ታሪኮች > መንፈሳዊ ዝማሬዎች > የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ > መንፈሳዊ ፊልሞች > መንፈሳዊ ትምህርቶችና የተለያዩ ፁፎች #ሁሉም_በየእለቱ

نمایش بیشتر
940
مشترکین
-224 ساعت
+17 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
[ ስንክሳር ሐምሌ - ፬ - ] .mp37.06 MB

🕊 ✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞ [ ✞ እንኳን ለአባቶቻችን ቅዱሳን ፲፪ [ 12 ] ቱ ደቂቀ ነቢያት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ] 🕊 ✞ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት ✞ 🕊 ነቢይ ማለት ከእግዚብሔር ተመርጦ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን] : መጻዕያትን [ለወደፊቱ የሚደረገውን] የሚያውቁ ሰዎች ሲሆኑ ሕዝቡን እንዲመሩ: እንዲገስጹም ይላካሉ:: ሕይወታቸውም በቅድስና የተለበጠ ነው:: ነቢያትን በቁጥር መግለጽ ከባድ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን እንድንረዳቸው እንዲህ ትከፍላቸዋለች:: =>  በኩረ ነቢያት አዳም =>  ሊቀ ነቢያት ሙሴ =>  ርዕሰ ነቢያት ኤልያስ =>  ልበ አምላክ ዳዊት =>  ፲፭ [15] ቱ ነቢያት [ከአዳም ጀምሮ እስከ ሳሙኤል] => ፬ [4] ቱ ዐበይት ነቢያት [ኢሳይያስ: ኤርምያስ: ሕዝቅኤልና ዳንኤል] ፲፪ [12] ቱ ደቂቀ ነቢያት ደግሞ ከሆሴዕ እስከ ሚልክያስ ያሉት ናቸው:: በዚህች ቀን ታዲያ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት በአንድነት ይታሠባሉ:: እነዚህም :- ፩. ቅዱስ ሆሴዕ [ኦዝያ] ፪. ቅዱስ አሞጽ ፫. ቅዱስ ሚክያስ ፬. ቅዱስ ኢዩኤል ፭. ቅዱስ አብድዩ ፮. ቅዱስ ዮናስ ፯. ቅዱስ ናሆም ፰. ቅዱስ እንባቆም ፱. ቅዱስ ሶፎንያስ ፲. ቅዱስ ሐጌ ፲፩. ቅዱስ ዘካርያስ እና ፲፪. ቅዱስ ሚልክያስ ናቸው:: ቅዱሳኑ ደቂቀ ነቢያት የተባሉት ፩. የነቢያት ልጆች በመሆናቸው ፪. የጻፏቸው ሐረገ ትንቢቶች በንጽጽር ከዐበይቱ [ከነኢሳይያስ] ስለሚያንስ ነው:: በምግባር: በትሩፋት: በአገልግሎት ግን ያው ናቸው:: ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እሊህን ነቢያት "እለ አውኀዙ ተነብዮ በእንተ ስመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ" ይሏቸዋል:: [ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መውረድ: መወለድና የማዳን ሥራ የትንቢት ጐርፍን ያፈሰሱ እንደ ማለት ነው ::] ቅዱሳኑ ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ባሻገር ዓለማችን ላይ ከነበሩበት ዘመን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሊደረጉ ያላቸውን ነገሮችም ተናግረዋል:: የነበሩበት ዘመን በአማካኝ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ፱ መቶ [900] እስከ ፭ [500] ነው:: በትንቢት ደረጃም እንደነ ሆሴዕና ዘካርያስ ፲፬ [14] ምዕራፎችን: እንደነ አብድዩም አንዲት ምዕራፍ ብቻም የጻፉ አሉ:: በሕይወታቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ያሻቸው ናቸውና በየጊዜው ከእግዚአብሔር ጋር እየተነጋገሩ የእርሱን ድምጽ ለእሥራኤል [አንዳንዴም ለአሕዛብ] ያደርሱ ነበር:: ፊት አይተው የማያዳሉ ናቸውና ሕዝቡንም ሆነ ነገሥታቱን ስለ ኃጢአታቸው ይገሰጹ ነበር:: በዚህም ምክንያት ከነገሥታቱና ከሕዝቡ አለቆች መከራ ደርሶባቸዋል:: አልፎም ያለ አበሳቸው ሕዝቡ በኃጢአቱ ሲማረክ አብረውት ወርደዋል:: በመጨረሻ ሕይወታቸውም አንዳንዶቹን ክፉዎች ሲገድሏቸው አንዳንዶቹ ደግሞ በመልካም ሽምግልና ዐርፈዋል:: ዛሬ ነቢያት ከእነርሱ ባሕርይ በተገኘችና ብዙ ትንቢትን በተናገሩላት በእመቤታችን ምክንያት ክርስቶስ ድኅነትን ፈጽሞላቸው በተድላ ገነት ይኖራሉ:: ስለ እኛም ይማልዳሉ:: " ናጥሪ እንከ ትሕትና ዘምስለ ንጽሕና" [ እንግዲህ እንደ ነቢያት ትሕትናን ከንጽሕና ጋር ገንዘብ እናድርግ ] "እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ" [ ነቢያት መንፈስን ንጹሕ በማድረግ እግዚአብሔርን አይተውታልና: ፊት ለፊትም ተያይተዋልና ] /ቅዳሴ ማርያም/ ከአባቶቻችን ቅዱሳን ነቢያት በረከት ይክፈለን:: 🕊 [ † ሐምሌ ፬ [ 4 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. "12ቱ" ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት ፪. ቅዱስ ሶፎንያስ ነቢይ [ዕረፍቱ] ፫. ቅዱሳን ሰማዕታት አቡቂርና ዮሐንስ [ቅዳሴ ቤታቸው] [ †  ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጉዋድ [ወንጌላዊው] ፪. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ ፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት ፬. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ [ሰማዕት] " ለእናንተም ስለሚሰጠው ጸጋ ትንቢት የተናገሩት ነቢያት ስለዚህ መዳን ተግተው እየፈለጉ መረመሩት:: በእነርሱም የነበረ የክርስቶስ መንፈስ ስለ ክርስቶስ መከራ ከእርሱም በሁዋላ ስለሚመጣው ክብር አስቀድሞ እየመሠከረ በምን ወይም እንዴት ባለ ዘመን እንዳመለከተ ይመረምሩ ነበር:: " [፩ዼጥ.፩፥፲] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖

[ + ባዶነት + ] .mp35.72 MB

🍒 🍒 🕊 ም ክ ረ ቅ ዱ ሳ ን 🕊 ═══════════════ ▷ ❝ ባ ዶ ነ ት ! ! ❞ [ 💛 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💛 ] 🕊 🍒 🕊 ❝ ከእናንተ ዘንድ በአንዱ ስንኳ እንዳንከብድ
🍒                                               🍒      🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊 ═══════════════ ▷     ❝  ባ  ዶ  ነ  ት  !  !  ❞ [ 💛  በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💛  ] 🕊                        🍒                       🕊 ❝ ከእናንተ ዘንድ በአንዱ ስንኳ እንዳንከብድበት ፥ ሌሊትና ቀን በድካምና በጥረት እየሠራን እንኖር ነበር እንጂ ፥ ከማንም እንጀራን እንዲያው አልበላንም። ❞ [ ፪ተሰ.፫፥፰ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y🕊                        💖                       🕊                              👇

ተዋህዶ_መሸሸጊያ_ኦርቶዶክስ_መጠለያዬ256k.mp35.96 MB

🕊 🌺 🕊 💛 [ ዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ] 💛 🕊 🌺 🕊 ❝ † ሰላም ለቄርሎስ ወልደ አንበሳ ጽኑዕ ፤ ነባቢ ምስጢረ ሥላሴ ቅድስት ፤ ዘተናገረ ላዕለ መለኮት። ❞ [ ተአምኆ ቅዱሳን
🕊                        🌺                       🕊 💛 [  ዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ  ] 💛     🕊                        🌺                       🕊 ❝ † ሰላም ለቄርሎስ ወልደ አንበሳ ጽኑዕ ፤ ነባቢ ምስጢረ ሥላሴ ቅድስት ፤ ዘተናገረ ላዕለ መለኮት። ❞ [ ተአምኆ ቅዱሳን ] [ በመለኮት ላይ የተናገረ ፤ የቅድስት ሥላሴን ምስጢርን ተናጋሪ ፤ ብርቱ [ ጠንካራ ] ለኾነ ለአንበሳው ልጅ ለቄርሎስ ሰላምታ ይገባል። ] ❝ የማኅበር አለቃ ኾኖ ቴዎፍሎስ ካሳደገው በኋላ የመጻሕፍትን ቃል የተከተለ ለኾነ ለቄርሎስ ሰላምታ ይገባል ፤ የንስጥሮስን የክሕደት እምነት ለመቃወም መለኮትን ቀለም በሸፈነው ጸምር ፤ ትስብእትንም እሳት ባጋለው በብረት መሰለ። ❞ [ ተአምኆ ቅዱሳን ] 🕊 [  † እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ] 🕊                        💖                     🕊 ጸሎቱና በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊

+1
ጻድቃን_ሰማእታት_በሙሉ(256k).mp33.91 MB

🕊 🌺 🕊 [ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ] 🕊 🌺 🕊 [ † እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ] 🕊 💖 🕊 ይኽ ቅዱስ ቄርሎ
🕊                        🌺                       🕊          [  🕊   ቅዱስ ቄርሎስ   🕊 ]       🕊                        🌺                       🕊 [  † እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ] 🕊                        💖                     🕊 ይኽ ቅዱስ ቄርሎስ ብዙ መጻሕፍትን የጻፈ ሲኾን ከእነዚኽ ውስጥ ፦ ❖ ፲፪ አንቀጽ ያለው ነገረ ሥጋዌን የሚተነትኑ ደብዳቤዎችን ❖ የብሉይ ኪዳን ትርጓሜን ❖ ስለ አርዮስ የስሕተት ትምህርት ❖ የዮሐንስ እና የሉቃስ ወንጌል ትርጓሜን ❖ በምስጢረ ሥላሴ ላይ ምላሽን ❖ የእግዚብሔር መቅደስ ስለመኾን ❖ በንስጥሮስ የኑፋቄ ትምህርት ላይ ዐምስት ታላላቅ ጽሑፎች ❖ ክርስቶስ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አንድያ ስለመኾኑ ❖ ስለ ወልድ ዋሕድ ሥጋዌ ❖ በተርሴሱ ዴዎዶር እና በሞፕሴዪስቲያው ቴዎዶርን ተቃውሞ ❖ ጁልያንን ተቃውሞ የጻፈው ወዘተርፈ ይገኙበታል፡፡ ይኽም ቅዱስ አባት የቀናች ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነትን በጽሑፉ በትምህርቱ እያስጠበቀ በመንበረ ማርቆስ ላይ ሠላሳ ኹለት ዓመት ከኖረ በኋላ መልካም ሥራውን ፈጽሞ ሐምሌ ፫ በ፬፻፵፬ ዓ.ም. በሰላም ዐርፏል፡፡ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ በከበረች ጸሎቱ : በአማላጅነቱ አይለየን። በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊

[ ስንክሳር ሐምሌ - ፫ - ] .mp39.06 MB

🕊 [ † እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ] †  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን † 🕊   †  ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ  †    🕊 †  ቅዱስ ቄርሎስን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን " ዓምደ ሃይማኖት የሃይማኖት ምሰሶ" ይሉታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- ሊቁ የተወለደው በእስክንድርያ [ግብጽ] በ፬ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: እናቱ የወቅቱ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎፍሎስ እህቱ ነበረችና አጎቱ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ወስዶ አሳድጐታል:: ገና በልጅነቱ ወደ አባ ሰራብዮን ገዳም ገብቶ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ገዳማዊ ሕይወትን ተምሯል:: በጾም: በጸሎትና በትሕትና የታሸ ነውና ሲማር አንድ ጊዜ ካነበበው በሕሊናው ተስሎ ይቀር ነበር:: ቅዱስ ቴዎፍሎስ "ምዕመናንን አስተምርልኝ" ብሎ ወደ ከተማ አመጣው:: መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ሲያስተምር ወይ ደግሞ መጻሕፍትን ሲያነብ ከምዕመናን ወገን ስንኩዋን የሚያወራና የሚንቀሳቀስ ቀርቶ የሚቀመጥም አልነበረም:: ጣዕመ ስብከቱም ብዙዎችን ለወጠ:: ከዚያም በ፬፻፲፪ [412] ዓ/ም አጎቱ የነበረው ፓትርያርክ አባ ቴዎፍሎስ ሲያርፍ ዻዻሳትና ሊቃውንት በአንድነት ቅዱስ ቄርሎስን መረጡ:: የእስክንድርያም ፳፬ [24] ኛ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሾመ:: በዘመኑ ቤተ ክርስቲያን አበራች:: በቅድስናው: በሊቅነቱ: በስብከቱ: በድርሰቶቹና በትጋቱ በፍጹም አገለገላት:: በወቅቱ ስመ ክፉ መናፍቅ ንስጥሮስ ተነስቶ የእስያ አብያተ ክርስቲያናትን አወካቸው:: ትምሕርቱ ክርስቶስን "2 አካል: ባሕርይ ነው" [ሎቱ ስብሐት!] የሚል ነበር:: በእውነት እንየው ከተባለ ግን ጠቡና ጥላቻው ከድንግል ማርያም ጋር ነበር:: ምክንያቱም ጌታችንን ወደ ፪ የከፈለው እመቤታችንን የአምላክ እናት አይደለሽም ለማለት ነው:: [ላቲ ስብሐት!] ነገሩን ቅዱስ ቄርሎስ በሰማ ጊዜ ወዳለበት ሒዶ ቢመክረውም ንስጥሮስ ሊሰማ አልፈለገም:: በዚህ ምክንያት በትንሹ ቴዎዶስዮስ [የቁስጥንጥንያ ንጉሥ] ትዕዛዝ በኤፌሶን ታላቅ ጉባኤ እንዲሰበሰብ ሆነ:: ይህ ጉባዔ በቤተ ክርስቲያናችን የመጨረሻው የተቀደሰ ጉባዔ ነው:: በ፬፻፴፩ [431] ዓ/ም በኤፌሶን ከተማ የመናፍቃኑን ጥርቅም ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና ፪፻ [200] ቅዱሳን ሊቃውንት ተገኙ:: የሚገባው ጸሎትና ሱባዔ ከተፈጸመ በሁዋላ ጉባዔው ተጀመረ:: አፈ ጉባዔው ሊቀ ማሕበር ማር [ቅዱስ] ቄርሎስ ነበርና በጉባዔ ፊት ንስጥሮስን ተከራክሮ ረታው:: ምላሽም አሳጣው:: ከቅዱሳት መጻሕፍት ክርስቶስ አንድ ባሕርይ መሆኑን: ድንግል ማርያምም ወላዲተ አምላክ መሆኗን እየጠቀሰ: በምሳሌም እያሳየ አስረዳ:: የሰይጣን ማደሪያ ንስጥሮስ ግን እንቢ: አላምንም በማለቱ ተወግዞ ተለየ:: ቅዱሳን ሊቃውንቱም በቅዱስ ቄርሎስ አርቃቂነት ፲፪ [12] አንቀጾችን አዘጋጅተው ወደ ዓለም ሁሉ ላኩ:: እሊህ አንቀጾች ዛሬም በሊቃውንቱ እጅ አሉ:: ይነበባሉ: ይተረጎማሉ:: † ከእነዚህም አንዱ ድንግል ማርያም "ታኦዶኮስ [የእግዚአብሔር እናቱ] ናት" የሚል ነው:: እመቤታችንን :- ¤ የአምላክ እናት: ¤ ዘላለማዊት ድንግል: ¤ ፍጽምት: ¤ ንጽሕትና አማላጅ ብሎ ማመን ለሰማያዊ ርስት የሚያበቃ በጐ ሃይማኖት ነውና:: ጉባዔው ከተጠናቀቀ በሁዋላ ቅዱስ ቄርሎስ ንስጥሮስን ጠርቶ "በድንግል ማርያም እመን:: እርሷ ከልጇ ታስታርቅሃለች" ቢለው በድጋሚ "እንቢ" አለው:: ያን ጊዜ ሊቁ "ለአምላክ እናት ያልታዘዘ ምላስህ ላንተም አይታዘዝህ" ብሎ ረገመው:: ወዲያው ምላሱ ተጐልጉሎ ወጥቶ ደረቱ ላይ ወደቀ:: እንደ ውሻ እየተዝረከረከ ሒዶ ከወዳጆቹ ጋር ቁሞ ሳለ መሬት ተከፍታ ውጣዋለች:: ቅዱስ ቄርሎስ ግን ለ፴፪ [32] ዘመናት በመንበሩ ላይ አገልግሎ: ፍሬ ትሩፋት አፍርቶ: ብዙ ድርሰቶችንም ደርሶ በ፬፻፵፬ [444] ዓ/ም በዚህች ቀን ዐርፏል:: ከድርሰቶቹም ቅዳሴው: ድርሳነ ቄርሎስና ተረፈ ቄርሎስ ይጠቀሳሉ:: † ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቶቻችን ጸሎት ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቅልን:: ከሊቁም በረከቱን ይክፈለን:: 🕊 [ † ሐምሌ ፫ [ 3 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ [ዓምደ ሃይማኖት] ፪. ቅዱስ ክልስቲያኖስ ዘሮሜ [ታላቅ ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት] ፫. አባ ሉቅያስ ኤዺስ ቆዾስ †  ወርኀዊ በዓላት   ] ፩. በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ፪. ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ፫. ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው [ዘካርያስና ስምዖን] ፬. አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ ፭. አቡነ ዜና ማርቆስ ፮. አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል † " የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ:: የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው:: ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ: እስከ ዘለዓለምም ያው ነው:: ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምሕርት አትወሰዱ:: ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም:: በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና:: " † [ዕብ.፲፫፥፯] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖

[ + ምስለ ፍቁር ወልዳ + ] .mp37.72 MB

🕊 💖 🕊 [ 🕊 ድንግል ሆይ ፦ 🕊 ] 🕊 💖 🕊 ❝ ድንግል ሆይ ፦ እታመንሻለሁ ከተሠወረው መከራ በግልጽም ከሚመጣብኝ ጥፋት ሁሉ በዚህ ዓለም እንድታድኝኝ ፤ በሚመጣውም ዓለም ከገሃነመ እ
🕊                        💖                       🕊       [   🕊 ድንግል ሆይ ፦  🕊    ]   🕊                        💖                       🕊 ❝ ድንግል ሆይ ፦ እታመንሻለሁ ከተሠወረው መከራ በግልጽም ከሚመጣብኝ ጥፋት ሁሉ በዚህ ዓለም እንድታድኝኝ ፤ በሚመጣውም ዓለም ከገሃነመ እሳት ጥርስ ማፏጨት ፥ ጽኑ ልቅሶም ካለበት ከሚያስጨንቅ መቅሠፍት ትሠውሪኝ ዘንድ ፤ እኔም ባንቺ አማላጅነት በልጅሽም ምሕረት የታመንሁ ነኝ፡፡ በፈረሰኞች ሰልፍ በሠረገላም መንኰራኩር የምታመን አይደለሁም፡፡ ባንቺና በልጅሽ ብቻ እታመናለሁ እንጂ፡፡ ❞ [  አርጋኖን   ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y🕊                        💖                       🕊

[ + ከጨለማ የመውጫ በር + ] .mp35.59 MB