fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 307 مشترک است و جایگاه 1 759 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 546 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 307 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 88 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 40.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.41% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 352 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 050 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 17 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 16 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 307
مشترکین
+224 ساعت
+297 روز
+8830 روز
آرشیو پست ها
የአዲስ  - ሰበታ  - ሆለታ  የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን ለማፋጠን እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2018 (ኢመአ) :- አዲስ  አበባን ከተለያዩ  የክልል  ከተሞች ጋር የሚያገናኙ ዋና መግቢያ እና መውጫ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች  መካከል አንዱ  የሆነው  የአዲስ  - ሰበታ -ሆለታ  50 ነጥብ 2  ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን ለማፋጠን እየተሰራ  ይገኛል። በኢትዮጵያ  መንግስት  በ 9 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር  እየተከናወነ የሚገኘው  ይህ የመንገድ ግንባታ፤ በብሪጅ ኮንስትራክሽን፣ በመሳይ ኦሊ  እና  በፋል  ጠቅላላ የሥራ ተቋራጮች ጥምረት በመከናወን ላይ ነዉ። የፕሮጀክቱን  የማማከርና  የቁጥጥር  ሥራ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ እና  ፎርትረስ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ በጋራ  እየሰሩት ይገኛሉ። የተሸከርካሪዎችን ፍሰት  በዘላቂነት  የሚያቀላጠፈው ይህ መንገድ፤ የአዲስ-ሰበታ፣ የሰበታ-ሆለታ እና የሱባ መናፈሻ ፓርክን የሚያገናኙ ሦስት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅትም ከፍተኛ የትራንስፖርት ጫና የሚስተዋልበትን የመጀመሪያ ምዕራፍ  የአዲስ- ሰበታ 11 ነጥብ  9 ኪሎ ሜትር  ግንባታ  በተያዘው  ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ለአገልግሎት ለማብቃት  እየተሠራ ነው። ቀደም ሲል መንገዱ የነበረው 10 ሜትር የጎን ስፋት የትራንስፖርት እንቅስቃሴውን አስቸጋሪ አድርጎት ቆይቷል። ይኸው የመንገድ ክፍል፤ አሁን ላይ በግራና በቀኝ አራት የመኪና  መተላለፊያዎችን፣ የእግረኛና የሳይክል መንገዶችን እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን በማካተት በ 50 ሜትር የጎን ስፋት እየተገነባ ነው። ይህንኑ የግንባታ ሂደት ለማፋጠን በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የቁፋሮ፣ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ቀበራ እንዲሁም የድጋፍ ግንብ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በሦስት ዓመት ውስጥ የሚጠናቀቀው የአዲስ -ሰበታ  -ሆለታ የመንገድ ፕሮጀክት በተለይም ከአዲስ አበባ ወደ ወልቂጤ፣ ጅማ እና ጋምቤላ የሚደረገውን የትራንስፖርት ፍሰት የሚያቀላጥፍ ሲሆን፤ ከዚህም ጎን ለጎን የደቡብ ሸዋና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞኖችን፣ የሸገርና የሆለታ ከተማ አስተዳደሮችን እንዲሁም የሰበታ ሀዋስና የወልመራ ወረዳዎችን በቅርበት  ያስተሳስራል። ግንባታው ሲጠናቀቅ የአካባቢውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርግ ከመሆኑም ባለፈ የጉዞ ጊዜን፣ ወጪንና እንግልትን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል። በተጨማሪም የግብርና ምርቶች በፍጥነት ለገበያ እንዲቀርቡና እንደ ሱባ ፓርክ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች በቀላሉ እንዲጎበኙ በማስቻል ለአካባቢው ዕድገት የላቀ ፋይዳ ይኖረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጅማ - አጋሮ - ዴዴሳ ወንዝ የመንገድ ግንባታ 85 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2018 (ኢመአ):- የጅማ - አጋሮ - ዴዴሳ ወንዝ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 85 በመቶ ደርሷል፡፡ 79.74 ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው በዚህ የመንገድ ፕሮጀክት እስካሁን ድረስ 53.28 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። በአሁኑ ወቅት የ71.20 ኪሎ ሜትር የአፈር ጠረጋና ሙሌት እንዲሁም የ61.66 ኪሎ ሜትር የሰብቤዝ ሥራ ተጠናቋል። ከዚህም በተጨማሪ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ 87.36 በመቶ፣ የተለያዩ የስትራክቸር ሥራዎች ደግሞ 77.56 በመቶ አፈጻጸም ላይ ደርሰዋል፡፡ በፌደራል መንግሥት ከ 2.29 ቢሊዮን ብር እየተገነባ የሚገኘው የጅማ - አጋሮ ዴዴሳ ወንዝ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በቻይና ሬልዌይ 21 ግሩፕ የሥራ ተቋራጭ አማካኝነት በመከናወን ላይ ሲሆን የፕሮጀክቱን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ኦሜጋ ኢንጂነሪንግ አማካሪ ከፕሮም አማካሪ ጋር በመተባበር እየሰሩት ይገኛሉ። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በግንባታ ሂደቱ የታዩ ችግሮችን በመፍታትና ለትራፊክ ደህንነት ምቹ የሆኑ የዲዛይን ማሻሻያዎችን በማካተት፤ የፕሮጀክቱን ጥራትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ነው። የአዲስ አበባ – ወሊሶ – ጅማ – አጋሮ – ዴዴሳ ወንዝ ድልድይ - በደሌ – መቱ – ጋምቤላ ዋና የመንገድ አካል የሆነው ይህ ፕሮጀክት ከጅማ ከተማ ተነስቶ ዴዴሳ ወንዝ ድልድይ ድረስ የሚዘልቅ ሲሆን፤ በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ 19 ሜትር እንዲሁም በዞን 22 .5 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ የጉዞ ጊዜን በእጅጉ በማሳጠር ለማህበረሰቡ ምቹ፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ የትራንስፖርት ትስስር ይፈጥራል። ይህም ጊዜን ለመቆጠብና የጉዞ ደህንነትን ከማረጋገጡም በላይ የአካባቢውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ይበልጥ እንዲቀላጠፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ከዚህ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ባሻገር የውጭ ምንዛሪ ምንጭ የሆኑትን የቡና እና ልዩ ልዩ የጥራጥሬ፣ የቅመማ ቅመም እንዲሁም ሌሎች የግብርና ውጤቶችን በፍጥነት ወደ ገበያ እንዲደርሱ በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይጨምራል። በተጨማሪም ወደ አባ ጅፋር ቤተ-መንግሥት በቀላሉ ለመጓዝ ከማስቻሉ ጎን ለጎን የጅማና የአጋሮ ከተሞችን የኑሮ ደረጃ የሚያሻሽሉ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በማካተቱ ፤ የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴና ሁለንተናዊ ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ ያፋጥናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የለሚ - ጀማ ወንዝ መንገድ ወደ ግንባታ ሊሸጋገር ነው አዲስ አበባ፣ ጥር 25/2018 ዓ.ም (ኢመአ)፦ የለሚ - ጀማ ወንዝ የ20 ኪሎ ሜትር መንገድን የሚያከናውነው የሥራ ተቋራጭ በመለየት ወደ ግንባታ ምዕራፍ ሊሸጋገር ነው፡፡ በ 5.1 ቢሊየን ብር በጀት የሚገነባው ይህ መንገድ ለአካባቢው ህብረተሰብና ለመንገዱ ተጠቃሚዎች ምቹ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ ከማስቻሉ ባሻገር የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን ለማውጣት ብሎም የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ምርቶችን ወደ ተለያዩ የገበያ ማእከላት ለማድረስ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን አማካኝነት የሚገነባው ይህ መንገድ በአሁኑ ወቅት ወደ ሥራ ለመግባት የሚያስችለውን የዝግጅት ምዕራፍ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል። መንገዱ በሲሚንቶ ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ሆኖ በገጠር ከ 8-10 ሜትር እንዲሁም በከተማ ደግሞ 15 ሜትር ስፋት ይኖረዋል። ግንባታው በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ ከጀማ ወንዝ - ዓለም ከተማ የሚዘልቀው የመንገድ ግንባታ በአካባቢው በነበረው የፀጥታና አለመረጋጋት ችግር ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱ ይታወሳል። በዚህም ረገድ ዋና የግንባታ ሥራው እስከሚጀመር ድረስ ኅብረተሰቡ የተሻለ የትራንስፖርት አገልግሎት ማግኘት እንዲችል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በራስ ኃይል የጥገና ሥራውን ለማከናወን የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ የጥገና ሥራ በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ውስጥ የሚጀመር ሲሆን በሚጠናቀቅበት ወቅት ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያስችል ይሆናል፡፡ የዚሁ መንገድ የመጀመሪያው ክፍል የሆነው የሙከጡሪ - ኮከብ መስክ 59 ኪሎሜትር የሚሸፍነው የመንገድ ግንባታ ቀደም ብሎ ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የደባርቅ - ጃናሞራ መንገድ ግንባታ ለማፋጠን እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ጥር 22/2018 (ኢመአ):- በሰሜን ጎንደር ዞን 63 ኪሎሜትር የሚሸፍነው የደባርቅ - ጃናሞራ መንገድ ግንባታ ለማፋጠን እየተሰራ ነው። በመንገድ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ በመከናወን ላይ ነው። ቀደም ሲል በተለያዩ የሥራ ተቋራጮች ሲከናወን የቆየው ይኸው መንገድ በደካማ አፈጻጸም፣ ከዲዛይን ለውጦች እና ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ግንባታው ዘግይቶ እንደነበር ይታወሳል። አሁን ላይ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅ ፕሮጀክቱን ተረክቦ በግንባታ ሂደት ላይ ነው። አይዲኮን ኢንፍራስትራክቸር ዴቨሎፕመንት ኮንሰልታንስ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በመሥራት ላይ ይገኛል። ለመንገድ ግንባታው 4.174 ቢሊዮን (አራት ቢሊዮን አንድ መቶ ሰባ አራት ሚሊዮን) ብር በጀት ተይዞለታል። ወጪው በፌደራል መንግሥት ይሸፈናል። አሁን ላይ ከአስፋልት ሥራው ጎን ለጎን የአፈርና የአለት ቆረጣ፣ ሙሌት እንዲሁም የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የተጀመረው የአስፋልት ንጣፍ ሥራ አጠናክሮ ለማስቀጠል አስፈላጊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቅቀዋል። መንገዱ ሲጀመር በድርብ-አስፋልት (DBST) ደረጃ ሊገነባ ታቅዶ የነበረ ቢኾንም፥ ሥፍራው ካለው ዘርፈ-ብዙ ፋይዳዎች እና ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት አንጻር ወደ አስፋልት ኮንክሪት እንዲያድግ ተደርጓል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በፊት ከደባርቅ - ጃናሞራ ለመጓዝ ይወስድ ይነበረውን የጉዞ ጊዜ ከ4 ሰዓት ወደ 1 ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል። በሥፍራው የሚገኙ ከተሞችን ከበለስ እና ወይና ቀበሌ እንዲሁም ከመካነ-ብርሃን ከተማ ጋር በማስተሳሰር የንግድ እንቅስቃሴውን ያቀላጥፋል። የሰሜን ብሔራዊ ፓርክን ለውጭ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ምቹ እንዲሆን ያስችላል። ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጨረቲ - ጎሮቦከክሳ - ጎርዳሞሌ: ሎት 3 ቁንዲ - ጎሮዳሞሌ - ጅብሪል የአስፋልት መንገድ ግንባታን ፕሮጀክት በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ጥር 20 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ መ አ)፦ የሶማሌ እና ኦሮሚያ ክልሎችን በአስፋልት መንገድ የሚያስተሳስረው ሎት 3 ቁንዲ - ጎሮዳሞሌ - ጅብሪል የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት 77.8 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍን ሲሆን በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ ስራ የተለዋዋጭ መንገድ ፣የጠረጋ ፣የማፋሰሻ ቱቦ እና የፋካ ስራዎች፣አፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣የካፒንግ ፣እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ይህም እንቅስቃሴውን 44.7 % በመቶ እንዲደርስ አስችሎታል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን ቁንዲ ከተማ (192+000) አድርጎ እስከ ጅብሪል ከተማ (269+800) ድረስ የሚዘልቅ ነው። ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 3,811,899,916.93 (ሶስት ቢሊዮን ስምንት መቶ አስራ አንድ ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ አስራ ስድስት ከዘጠና ሶስት ሳንቲም) ብር የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው ። የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ኤምሲጂ ኮንስትራክሽን ኃ/የ/ማ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኮር አማካሪ መሀንዲሶች አ.ማ እያከናወኑት ይገኛሉ። ፕሮጀክቱ ደረጃውን በጠበቀ አስፋልት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አቋርጧቸው የሚሄዱ ከተሞች፣ ወረዳዎች እና ቀበሌዎችን በአስፋልት መንገድ ከማገናኘቱም ባለፈ የትራንስፖርት ተደራሽነት እና ተጠቃሚነትን ከፍ ያደርገዋል፤ በተጨማሪም ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከቁንዲ ከተማ እስከ ጅብሪል ከተማ በተሽከርካሪ ለማጓዝ ይወስድ የነበረውን የ8፡00 ሰዓት ጉዞ ወደ 1:30 ከማሳጠሩም ባለፈ ለትራንስፖርት ተጠቃሚዎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። የመንገድ ግንባታው በከተማ 19 ሜትር የጎን ስፋት ሲኖረው በገጠር 8 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ነው የሚገኘው ። የዚህ መንገድ አካል የሆኑት የጨረቲ - ሀገረመቆር ክፍል -1 እና የሀገረመቆር - ቁንዲ ክፍል ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ቀደም ብሎ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ይታወሳል ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ባለፉት 6 ወራት የ237 ኪሎሜትር የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ፣ 133 ኪሎ ሜትር ነባር መንገዶች ማጠናከርና ደረጃ ማሻሻል እና 6 ሺህ 577 ኪሎሜትር የሚሸፍኑ የጥገና ሥራዎች ተከናወኑ አዲስ አበባ፣ ጥር 19/2018 (ኢ መ አ):- በበጀት ዓመቱ ባለፉት 6 ወራት 237 ኪሎሜትር የሚሸፍኑ የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ፣ 133 ኪሎ ሜትር ነባር መንገዶች ማጠናከርና ደረጃ ማሻሻል እና 6 ሺህ 577 ኪሎሜትር ልዩ ልዩ የጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል። ተቋማችን የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ አጋማሽ ዕቅድ አፈጻጸም እና የቀጣይ ወራት ዕቅድ አስመልክቶ በዓለምገና ኢንጅነሪንግ እና ማኔጅመንት ማሠልጠኛ ማዕከል አጠቃላይ ውይይት አካሂዷል። በዚሁ ወቅት በቀረበው ሪፖርት መሰረት የመንገዶች ግንባታ፣ ማጠናከርና ማሻሻል የእቅዱን 81 በመቶ፤ የመንገዶች ከባድ ጥገና የእቅዱን 80 በመቶ፤ ወቅታዊ የመንገዶች ጥገና የእቅዱን 71 በመቶ እንዲሁም መደበኛ ጥገና የእቅዱን 86 በመቶ አፈጻጸም ተመዝግቧል፡፡ በሌላ በኩል በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት በምህንድስና ግዥ፣ በዲዛይን ፕሮጀክቶች፣ በግንባታ እና በልዩ ልዩ የጥገና ሥራዎች እንዲሁም በተቋም አቅም ግንባታ ስራዎች በተሰጣቸው ክብደት መሰረት በተቋም ደረጃ ሲጠቃለል የዕቅዱን 81 በመቶ ማሳካቱ ተገልጿል። ተቋማችን በተያዘው በጀት ዓመት 314 የግንባታ፣ 50 የከባድ ጥገና ፣ 73 ወቅታዊ ጥገና፣ 56 መደበኛ ጥገና ፣ 184 የምህንድስና ግዥ እና 35 የዲዛይን ጥናት ፕሮጀክቶች ጨምሮ በአጠቃላይ 712 ፕሮጀክቶችን እያከናወነ እንደሚገኝ ሪፖርቱ አመላክቷል። የኢተያ - አርሲ ሮቤ፣ እስቴ - ስማዳ ፣ የድሬዳዋ ሽንሌ እና የድሬዳዋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ፣ የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ እንዲሁም ሳውላ - ቃቆ መንገድ ፕሮጀክቶች በዚህ በጀት ዓመት የተጠናቀቁ መሆኑም ተገልጿል። በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻም የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ከ16 ሺህ 976 ኪሎሜትር በላይ የሚሸፍኑ የመንገድ ግንባታ እና ልዩ ልዩ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ግብ ተቀምጦ እየተሠራ ይገኛል። ከዚሁ ጎን ለጎን ተቋማችን የመንገድ ግንባታውን የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ውጤቶች ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ የምርምር ሥራዎችን የሚያከናውን ሲሆን፣ የዚሁ ጥረት ውጤት የሆነውን ያገለገሉ የተሽከርካሪ ጎማዎችን ከአስፋልት ጋር በማዋሀድ ለመንገድ ንጣፍ በመጠቀም የአገልግሎት ጊዜን አራዝሞ ለጥገና የሚወጣውን ወጪ ለመቀነስ የሚያስችል የቴክኖሎጂ ውጤት በተሞክሮነት አቅርቧል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሀገራችን  አጠቃላይ የመንገድ አውታር ከ182 ሺህ በላይ ደርሷል:- ሚንስትር ደኤታ የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር) ምሥራቅ ጉራጌ ዞን፣ ጥር 17/2018 (ኢ መ አ): የሀገራችን አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን ከ182 ሺህ በላይ መድረሱን የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር የትምጌታ አሥራት ገልጸዋል። ሚንስትር ደኤታው ይኽንን የገለጹት የቱሉ ቦሎ - ኬላ መንገድ ፕሮጀክት ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኅላፊዎች በተገኙበት የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ በተካሄደበት ወቅት ነው። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተማን ብቻ ሳይሆን ገጠሩ እና የቆላማ የአርብቶ አደሩን አካባቢ ያካተተ ፍትሃዊ የመሠረተ-ልማት ስርጭት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ሥንሠራ ቆይተናል ያሉት ሚንስትር ደኤታው፥ በዚህም በየዓመቱ በአማካኝ 7 ሺህ ኪሎሜትር የሚደርስ አዳዲስ የመንገድ ግንባታ በማካሄድ የሀገራችንን የመንገድ አውታር ከ182 ሺህ በላይ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። ይህንን የመንገድ ርዝመት በሚቀጥሉት 2 ዓመታት በሚሠሩ ሥራዎች ከ200 ሺህ ብላይ ለማድረስ እንደዚሁ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ደግሞ ከ245 ሺህ በላይ ለማድረስ እንደ መንግሥት በቁርጠኝነት እየተሠራ እንደኾነ ገልጸዋል። "መንግሥት የመሠረተ-ልማት እና የከተማ ልማትን ቁልፍ የልማት መሳሪያ፣ የሥልጣኔ መገለጫ፣ የብልጽግና መንገድ እና ዋና መዳረሻ አድርጎ ይወስዳል" ያሉት የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር)፥ የመንገድ ግንባታም በሀገራችን ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው የመሠረተ-ልማቶች አንዱ እንደኾነ ጠቁመዋል። ዛሬ በይፋ የተመረቀው መንገድም የንግድ እና የልማት በሮችን በመክፈት መንግሥት ከተማን እና ገጠርን እንደዚሁም ከተሞችን እርስ በእርስ በማስተሳሰር የኢትዮጵያን የብልጽግና ራዕይ ዕውን ለማድረግ የጀመረውን ጉዞ ጉልህ ማሳያ እንደኾነ ተናግረዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፥ የመንገዱ መገንባት የተለያዩ የምርት ውጤቶችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ብሎም የተለያዩ ሸቀጦችን በአጭር ሰዓት ወደ ክልሉ በማምጣት ነዋሪው ተጠቃሚ እንዲኾን ያስችላል ብለዋል። አካባቢው ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ እንደመኾኑ፣ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በክልል ደረጃ የተያዘውን ራዕይ በማሳካት በኩል ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መኾኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ም/ዋና ዳይሬክተር ብርሃኑ ተስፋዩ (ኢንጅነር)፣ የቱሉቦሎ - ኬላ መንገድ ግንባታ የትራንስፖርት ፍሰት በከፍተኛ ሁኔታ ከማሳለጡም በላይ፤ ለማኅበረሰቡ አስተማማኝና ዘላቂ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል ደረጃ የተከናወነ ነው ብለዋል። ተቋማችን የዛሬውን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ነባር እና አዲስ የመንገድ ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ ለአገልግሎት ለማዋል እና የሕዝባችንን ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየሠራ ነው ያሉት ም/ዋና ዳይሬክተሩ፥ ለዚህም ከፍተኛ የዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መኾናቸውን ጠቁመዋል። የመንግድ መሠረተ-ልማት በከፍተኛ ሀብትና በባለሙያዎቻችን ጥረት የተገነባ የልማት ውጤት በመኾኑ፣ ዘላቂ አገልግሎት መስጠት እንዲችል መላው ኅብረተሰብ በባለቤትነት ስሜት በመላበስ አስፈላጊውን ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርግለት ም/ዋና ዳይሬክተሩ ብርሃኑ ተስፋዩ (ኢንጅነር) አሳስበዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሀገራችን አጠቃላይ የመንገድ አውታር ከ182 ሺህ በላይ ደርሷል:- ሚንስትር ደኤታ የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር) ምሥራቅ ጉራጌ ዞን፣ ጥር 17/2018 (ኢ መ አ): የሀገራችን አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን ከ182 ሺህ በላይ መድረሱን የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር የትምጌታ አሥራት ገልጸዋል። ሚንስትር ደኤታው ይኽንን የገለጹት የቱሉ ቦሎ - ኬላ መንገድ ፕሮጀክት ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኅላፊዎች በተገኙበት የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ በተካሄደበት ወቅት ነው። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተማን ብቻ ሳይሆን ገጠሩ እና የቆላማ የአርብቶ አደሩን አካባቢ ያካተተ ፍትሃዊ የመሠረተ-ልማት ስርጭት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ሥንሠራ ቆይተናል ያሉት ሚንስትር ደኤታው፥ በዚህም በየዓመቱ በአማካኝ 7 ሺህ ኪሎሜትር የሚደርስ አዳዲስ የመንገድ ግንባታ በማካሄድ የሀገራችንን የመንገድ አውታር ከ182 ሺህ በላይ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። ይህንን የመንገድ ርዝመት በሚቀጥሉት 2 ዓመታት በሚሠሩ ሥራዎች ከ200 ሺህ ብላይ ለማድረስ እንደዚሁ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ደግሞ ከ245 ሺህ በላይ ለማድረስ እንደ መንግሥት በቁርጠኝነት እየተሠራ እንደኾነ ገልጸዋል። "መንግሥት የመሠረተ-ልማት እና የከተማ ልማትን ቁልፍ የልማት መሳሪያ፣ የሥልጣኔ መገለጫ፣ የብልጽግና መንገድ እና ዋና መዳረሻ አድርጎ ይወስዳል" ያሉት የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር)፥ የመንገድ ግንባታም በሀገራችን ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው የመሠረተ-ልማቶች አንዱ እንደኾነ ጠቁመዋል። ዛሬ በይፋ የተመረቀው መንገድም የንግድ እና የልማት በሮችን በመክፈት መንግሥት ከተማን እና ገጠርን እንደዚሁም ከተሞችን እርስ በእርስ በማስተሳሰር የኢትዮጵያን የብልጽግና ራዕይ ዕውን ለማድረግ የጀመረውን ጉዞ ጉልህ ማሳያ እንደኾነ ተናግረዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፥ የመንገዱ መገንባት የተለያዩ የምርት ውጤቶችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ብሎም የተለያዩ ሸቀጦችን በአጭር ሰዓት ወደ ክልሉ በማምጣት ነዋሪው ተጠቃሚ እንዲኾን ያስችላል ብለዋል። አካባቢው ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ እንደመኾኑ፣ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በክልል ደረጃ የተያዘውን ራዕይ በማሳካት በኩል ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መኾኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ም/ዋና ዳይሬክተር ብርሃኑ ተስፋዩ (ኢንጅነር)፣ የቱሉቦሎ - ኬላ መንገድ ግንባታ የትራንስፖርት ፍሰት በከፍተኛ ሁኔታ ከማሳለጡም በላይ፤ ለማኅበረሰቡ አስተማማኝና ዘላቂ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል ደረጃ የተከናወነ ነው ብለዋል። ተቋማችን የዛሬውን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ነባር እና አዲስ የመንገድ ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ ለአገልግሎት ለማዋል እና የሕዝባችንን ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየሠራ ነው ያሉት ም/ዋና ዳይሬክተሩ፥ ለዚህም ከፍተኛ የዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መኾናቸውን ጠቁመዋል። የመንግድ መሠረተ-ልማት በከፍተኛ ሀብትና በባለሙያዎቻችን ጥረት የተገነባ የልማት ውጤት በመኾኑ፣ ዘላቂ አገልግሎት መስጠት እንዲችል መላው ኅብረተሰብ በባለቤትነት ስሜት በመላበስ አስፈላጊውን ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርግለት ም/ዋና ዳይሬክተሩ ብርሃኑ ተስፋዩ (ኢንጅነር) አሳስበዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads