fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 305 مشترک است و جایگاه 1 758 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 550 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 305 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 88 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 40.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.41% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 352 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 050 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 17 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 307
مشترکین
+224 ساعت
+297 روز
+8830 روز
آرشیو پست ها
በጋሼና - ላሊበላ - ብልባላ ሰቆጣ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጀመረ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 09/2018 (ኢ መ አ):-በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞንን ከዋግኽምራ ዞን ጋር በሚያስተሳስረው በጋሼና - ላሊበላ እና የላሊበላ ተለዋጭ መንገድ እንዲሁም የብልባላ - ሰቆጣ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጀምሯል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በሁለት ኮንትራቶች ተከፋፍሎ የሚገነባ ሲኾን፥ ኮንትራት-1 የጋሼና - ብልባላ እና የላሊበላ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ ያካትታል። ኮንትራት-2 ከብልባላ - ሰቆጣ ያለውን መንገድ ይሸፍናል። ከዚህ አብዛኛው የመንገዱ ክፍል በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ከመቋረጡ በፊት በአስፋልት ደረጃ ተጠናቅቆ የነበረ ሲኾን፤ ከቀሪው 23 ነጥብ 32 ኪሎሜትር ውስጥ 10 ነጥብ 27 በመቶውን ማጠናቀቅ ተችሏል። ከአስፋልት ሥራው ጎን ለጎን የጠረጋ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የመንገድ አካፋይ፣ እንደዚሁም የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በሰቆጣ፣ ላሊበላ እና ጋሼና ከተማዎች ውስጥ በመከናወን ላይ ናቸው። በዚህ ዓመትም የፕሮጀክቱን አፈጻጸም አጠናክሮ በማስቀጠል በሰቆጣ እና በላሊበላ ከተሞች ያለውን የአስፋልት ሥራ እንዲሁም የ1 ነጥብ 2 ኪሎሜትር የሪጅድ ፔቭመንት (ሲሚንቶ ኮንክሪት) ሥራ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል። ለፕሮጀክቱ 5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግሥት በጀት ተይዞለታል። ግንባታውን ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ጋር በጣምራ በማከናወን ላይ ይገኛል። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ የሰቆጣ -ላሊበላ እንዲሁም ከጋሸና - ወልድያ- ደሴ ያለውን የትራንስፖርት ፍሰት ያቀላጥፋል። የላሊበላ አብያተ-ክርስቲያናት ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ በኩል አዎንታዊ ሚና ይወጣል። ከዚህ በተጨማሪም የዋድላ፣ መቄት፣ ላስታ፣ ጋዝጊብላ እንደዚሁም የሰቆጣ ወረዳዎችን ማኅበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ መስተጋብር ያጠናክራል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መንገድ ካልታከመ ይሞታል!" ቢሾፍቱ፣ መጋቢት 7፣ 2018 ዓም (ኢመአ): የመንገድ ኤጀንሲዎች የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በቢሾፍቱ ተካሄደ "መንገድ ካልታከመ ይሞታል" በሚል መሪ ቃል፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (ኢ.መ.አ) የመንገድ ፈንድ ዳይሬክቶሬትና የክልል መንገድ ኤጀንሲዎች የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ከመጋቢት 4-5 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ከአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋና ከሁሉም ክልሎች የተወከሉ የክልል መንገድ ኤጀንሲዎች ተገኝተው የ6 ወራት የሥራ ሪፖርታቸውን አቅርበዋል። ሪፖርቶቹ በዋናነት በፊዚካልና በፋይናንሺያል አፈጻጸም ላይ ያተኮሩ ሲሆን፤ የተከናወኑ ወቅታዊ፣ መደበኛና ከባድ የጥገና ሥራዎች፣ የከተማ አስፋልት ግንባታ፣ የድልድይ ጥገናና ድንገተኛ የጥገና ሥራዎች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። የክልል ተወካዮች በሪፖርታቸው ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦ የመንገድ ጥገና በጀት እጥረትና ተጨማሪ በጀት አስፈላጊነት፤ ያረጁ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ጥገናና አዳዲስ ማሽነሪዎችን የመግዛት አስፈላጊነት፤ ከዋናው መሥሪያ ቤት (ኢ.መ.አ) የሚጠበቁ የቴክኒክና የድጋፍ ፍላጎቶች ይገኙበታል። በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የኢ.መ.አ የመንገድ ፈንድ ዳይሬክቶሬት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ ዳይሬክቶሬቱ ከመንገድ ፈንድ ምስረታ ጀምሮ ከኢ.መ.አ ጋር እስከመዋሃድ ድረስ ያለውን ሂደት፣ የገቢ ምንጮችን እንዲሁም ለኤጀንሲዎች የሚሰጠውን ድጎማ የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎችን አቅርቧል። በመጨረሻም በሪፖርቶቹ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በኢ.መ.አ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮችና በመንገድ ፈንድ ዳይሬክተሩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የወራቤ - ቦዠባር አስፋልት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 75 በመቶ ደረሰ ወራቤ፣ መጋቢት 04/2018 (ኢመአ):- የስልጤ ዞንን ከጉራጌ ዞን ጋር የሚያገናኘው የወራቤ - ቦዠባር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 75 በመቶ ደርሷል። የመንገድ ፕሮጀክቱ መነሻውን ከወራቤ ከተማ አሥተዳደር በማድረግ በዋናነት አልቾውሪሮ እና ቅበት ወረዳዎችን የሚያስተሳስር ሲኾን፥ 41 ነጥብ 34 ኪሎሜትር ይሸፍናል። አሁን ላይ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 14 ኪሎሜትሩን በአስፋልት የማልበስ ሥራ ተሠርቷል። ከዚሁ ጎን ለጎን እየተከናወኑ ከሚገኙ በርካታ የግንባታ ሥራዎች መካከል፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የውኃ መፋሰሻ፣ የሰብቤዝ እንዲሁም የቤዝኮርስ ሥራዎች ይጠቀሳሉ። ከመንገድ ወሰን ማስከበር እንዲሁም ከግንባታ ግብዓት አቅርቦት ጋር የተያያዙ ችግሮች በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ፈጥረው የነበረ ቢኾንም፤ ተቋማችን ባደረገው የተቀናጀ ጥረት ችግሮቹን መቅረፍ ተችሏል። በመኾኑም ፕሮጀክቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተሻለ ቁመና ላይ ይገኛል። በቀጣይ ዓመት ታኅሣሥ ወር ለማጠናቀቅ ታቅዶም በትኩረት በመሠራት ላይ ነው። ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከፌደራል መንግሥት በተመደበ 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ኤስ ጂ ኮንስትራክሽን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን በመሥራት ላይ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ከወራቤ ከተማ ተነስቶ ቦዠባር ከተማ ለመድረስ ይወስድ የነበረውን የ2 ሰዓት ተኩል ጉዞ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ወደ ወልቂጤ እና ጅማ ለመጓዝ በቡታጅራ በኩል የሚደረገውን አድካሚ እና ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ ያስቀራል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የነቀምት ቡሬ ፡ ክፍል 3: አጋምሳ -ቡሬ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው መጋቢት 3፣ 2018 (ኢመአ)፦ 84.55 ኪሎ ሜትርን የሚሸፍነው የነቀምት ቡሬ ፡ ክፍል 3: አጋምሳ -ቡሬ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን አጋምሳ ከተማ አድርጎ እስከ ቡሬ የሚዘልቅ ነው። ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 66.8 በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 2,291,551,346.32 (ሁለት ቢሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ ሶስት መቶ አርባ ስድስት ብር ከሰላሳ ሁለት ሣንቲም) ብር የሚሸፈነው በአለም ባንክ ነው ። የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ቾንግኪንግ ኢንተርናሽናል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኩንሃ ኢንጅንሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስዌይ ኮርፖሬሽን በትብብር እንዲሁም ኢትዮ ኢንፍራ እንጅንሪንግ ኃላ/የተ/የግ ኩባንያ ጋር በጣምራ በመሆን እያከናወኑት ይገኛሉ። ቀደም ሲል በጸጥታ ሁኔታ፣ በወሰን ማስከበር ችግሮች እና በተቋራጭ ለውጥ ምክንያት የግንባታ መዘግየት አጋጥሞት የነበረ ቢሆንም፤ በኢመአ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ጥረት ፕሮጀክቱ አሁን ላይ በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል። ቀደም ሲል ከ4 ሰዓት በላይ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ዝቅ ያደርገዋል። አርሶ አደሮች ምርታቸውን ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ እና የውጭ ገበያ በማውጣት አምራችና እና ሸማቾችን በቀላሉ በማገናኘት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡ መንገዱ ግንባታው በከተማ 21.5 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መጋቢት 1፣ 2018 (ኢመአ)፦ የጅግጅጋ - ቱሊ - ሎዋንጃ - ዱልአድ - ሰመካብ - ሐርሙከሌ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክትን በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማን ከጅቡቲ ወደብ ጋር በአቋራጭ የሚያገናኘው የጅግጅጋ - ቱሊ - ሎዋንጃ -ዱልአድ - ሰመካብ - ሐርሙከሌ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክትን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው የመንገድ ፕሮጀክቱ 104 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትርን የሚሸፍን ሲሆን፥ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 80.08 በመቶው ተጠናቅቋል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ጅማሮውን ከጅግጅጋ ከተማ አድርጎ በድሬደዋ ደወሌ መንገድ በሃርሙካሌ ቀበሌ ላይ ያልቃል። በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ 93.17 %( 96.47 ኪሜ) የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣73.74% የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ፣92.39% የከፍተኛ ድልድይ (ብዛት -06) ፣78.46 ኪ ሜ የሰብቤዝ ንጣፍ ፣66.37 ኪሜ) የቤዝ ኮርስ ንጣፍ ፣ 66.37 ኪሜ የአሰፋልት ንጣፍ ፣እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,551,507,344.53 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባት ሺህ ሶስት መቶ አርባ አራት መቶ ብር ከሃምሳ ሳንቲም) ብር የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው ። የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንትራክሽን ኮርፖሬሽን (CCECC) ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ስታዲያ የምህንድስና ስራዎች አማካሪ ኃ.የተ.የግ.ማ እያከናወኑት ይገኛሉ። የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የጅቡቲን ወደብ ከጅግጅጋ ከተማ ጋር በአቋራጭ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማገናኘት የቀጠናውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስሮችን ያጎለብታል፤ የአካባቢው ማህበረሠብ በአብዛኛው አርብቶ አደር በመሆኑ የቁም ከብቶችን እና ተጓዳኝ የግብርና ውጤቶችን በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገባያ እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፤ ከጅግጅጋ ተነስቶ በሐረር - ድሬደዋ - ጅቡቲ ለመድረስ ቀድሞ 475 ኪሎ ሜትር ይወስድ የነበርውን ርዝመት በ99ኪሜ የሚያሳጥረው ሲሆን ይህም ከጅግጅጋ-ጅቡቲ ለመድረስ ይወስድ የነበረውን ጉዞ በ2 ሰዓት ይቀንሳል። ለአካባቢው ማህበረሰብ የረዥም ግዜ የመንገድ ጥያቄን ከመመለስ ባሻገር የመንገድ ተደራሽነትን ያሳድጋል፤ የከተሞችን እድገት ያፋጥናል፤ የመንገድ ግንባታውን ተከትሎ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል። የመንገድ ግንባታው በከተማ 22ሜትር ሜትር የጎን ስፋት ሲኖረው በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መጋቢት 1፣ 2018 (ኢመአ)፦ የጅግጅጋ - ቱሊ - ሎዋንጃ - ዱልአድ - ሰመካብ - ሐርሙከሌ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክትን በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማን ከጅቡቲ ወደብ ጋር በአቋራጭ የሚያገናኘው የጅግጅጋ-ቱሊ-ሎዋንጃ-ዱልአድ-ሰመካብ-ሐርሙከሌ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክትን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው የመንገድ ፕሮጀክቱ 104 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትርን የሚሸፍን ሲሆን፥ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 80.08 በመቶው ተጠናቅቋል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ጅማሮውን ከጅግጅጋ ከተማ አድርጎ በድሬደዋ ደወሌ መንገድ በሃርሙካሌ ቀበሌ ላይ ያልቃል። በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ 93.17 %( 96.47 ኪሜ) የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣73.74% የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ፣92.39% የከፍተኛ ድልድይ (ብዛት -06) ፣78.46 ኪ ሜ የሰብቤዝ ንጣፍ ፣66.37 ኪሜ) የቤዝ ኮርስ ንጣፍ ፣ 66.37 ኪሜ የአሰፋልት ንጣፍ ፣እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,551,507,344.53 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባት ሺህ ሶስት መቶ አርባ አራት መቶ ብር ከሃምሳ ሳንቲም) ብር የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው ። የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንትራክሽን ኮርፖሬሽን (CCECC) ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ስታዲያ የምህንድስና ስራዎች አማካሪ ኃ.የተ.የግ.ማ እያከናወኑት ይገኛሉ። የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የጅቡቲን ወደብ ከጅግጅጋ ከተማ ጋር በአቋራጭ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማገናኘት የቀጠናውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስሮችን ያጎለብታል፤ የአካባቢው ማህበረሠብ በአብዛኛው አርብቶ አደር በመሆኑ የቁም ከብቶችን እና ተጓዳኝ የግብርና ውጤቶችን በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገባያ እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፤ ከጅግጅጋ ተነስቶ በሐረር - ድሬደዋ - ጅቡቲ ለመድረስ ቀድሞ 475 ኪሎ ሜትር ይወስድ የነበርውን ርዝመት በ99ኪሜ የሚያሳጥረው ሲሆን ይህም ከጅግጅጋ-ጅቡቲ ለመድረስ ይወስድ የነበረውን ጉዞ በ2 ሰዓት ይቀንሳል። ለአካባቢው ማህበረሰብ የረዥም ግዜ የመንገድ ጥያቄን ከመመለስ ባሻገር የመንገድ ተደራሽነትን ያሳድጋል፤ የከተሞችን እድገት ያፋጥናል፤ የመንገድ ግንባታውን ተከትሎ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል። የመንገድ ግንባታው በከተማ 22ሜትር ሜትር የጎን ስፋት ሲኖረው በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads