ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 464 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 734,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 494 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 464 名订阅者。
根据 27 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 198,过去 24 小时变化为 15,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 35.35%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 756 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 28 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 464
订阅者
+1524 小时
+847 天
+19830 天
帖子存档
13 471
የፊቅ-ሰገግ የአስፋልት መንገድ /DBST/ ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15/2018 (ኢመአ):- በሶማሌ ክልል ውስጥ የሚገኘው እና 90 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው የፊቅ - ሰገግ - ገርቦ - ደናን፡¬- ክፍል 1 የፊቅ-ሰገግ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት 75 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ግንባታውን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን ፊቅ ከተማ ላይ አድርጎ እስከ ሰገግ የሚዘልቅ ነው።
ከአጠቃላይ የግንባታ ስራው አሁን ላይ 75.60% በመቶ የተጠናቅቀቀ ሲሆን የ33.24 ኪ.ሜ DBST ፣የ49.28 ኪ.ሜ ቤዝ ኮርስ ፣ የ71.57 ኪ.ሜ ሰብ ቤዝ፣ የ79.49% የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ 59 የተጠናቀቀ አና 32 በሂደት ላይ ያሉ የማፋሸሻ ቱቦ ፣ 2 የተጠናቀቀ አና 4 በሂደት ላይ ያሉ የድልድይ ግንባታ፣ 67.1% ጠጠር መፍጨት (ቤዝ ኮርስ እና የአስፋልት ጠጠር) እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,488,968,324.58 (አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰማንያ ስምንት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ሶስት መቶ ሀያ አራት ብር ከሃምሳ ስምንት ሳንቲም) ብር የሚሸፈነው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ።
የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ ሥራ - ተቋራጭ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ቫልዩ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማ እያከናወነው ይገኛል።
የዚህ መንገድ መገንባት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ በDBST ደረጃ እየተገነባ ይገኛል::
የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ በፊቅ በኩል ጎዴ ለመጓዝ ቀድሞ ይፈጅ የነበረውን 1ሺህ 170 ኪሎ ሜትር መንገድ በ150 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል፡፡
ከጎዴ-ጅጅጋ-ሐረር ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ እና የትራፊክ መጨናነቅ ይቀንሰዋል፡፡
በአካባቢው ለሚገኙ አርብቶ አደሮችና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡
የአካባቢው ማህበረሰብ በአብዛኛው አርብቶ አደር በመሆኑ የቤት እንሰሳቶች በማርባትና በመሸጥ የሚተዳደር በመሆኑ በቀላሉ ወደ ገቢያ አውጥቶ በመሸጥ የተሻለ የገቢ እንዲያገኝ ያደርገዋል፡፡
መንገዱ አቋርጧቸው የሚሄድባቸው ከተሞች እና ቀበሌዎችን ለትራንስፖርት ምቹ ከማድረጉም ባለፈ የህብረተሰቡን አገልግሎት የትምህርት ፣ የጤና ተቋማት እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ይደግፋል።
ከመነሻው ፊቅ ተነስቶ ሰገግ ለመድረስ ቀደም ሲል ከ4 ሰዓት በላይ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ዝቅ ያደርገዋል።
የመንገድ ግንባታው በከተማ 19 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ።
የዚሁ መንገድ ፕሮጀክት ኮሪደር ቀጣይ ክፍል የሆነው ክፍል ሁለት፦ ሰገግ-ገርቦ-ዮአለ አስፋልት መንገድ በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 471
የሻሸመኔ - ሃላባ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየተከናወነለት ነው
ሻሸመኔ፣ መጋቢት 09/ 2018 (ኢ መ አ):- ወደ ደቡብ እና ማዕከላዊ የሀገራችን ክፍል የሚደረገውን የትራንስፖርት ፍሰት የሚያቀላጥፈው የሻሸመኔ - ሃላባ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየተከናወነለት ነው
የመንገድ ፕሮጀክቱ 68 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ የምዕራብ አርሲ ዞንን ከሃላባ ዞን ጋር ያገናኛል።
አሁን ላይ የ16 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል። ከዚሁ ጎን ለጎን የጠረጋ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው።
ለፕሮጀክቱ መጓተት ምክንያት የነበረው የወሰን ማስከበር ችግር አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ በመቀረፉ፣ ግንባታውን ለማፋጠን በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታውን ቻይና ሬይልዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ በማከናወን ላይ ነው። ኤስ ጂ ኮንሰልቲንግ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ይሠራል።
ለመንገድ ፕሮጀክቱ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግሥት በጀት ተይዞለታል።
መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ኾኖ የ4 ድልድዮች ግንባታ ያካትታል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ኦሮሚያ ክልልን ከማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ጋር በማገናኘት ሁለንተናዊ መስተጋብሩን ያጠናክራል።
ከዋናው የሞጆ - ሐዋሳ ፍጥነት መንገድ ጋር ስለሚገናኝ ወደ ደቡብ ኢትዮጲያ ክፍል የሚኖረውን የትራንስፖርት እና ንግድ በከፍተኛ ሁኔታ ያሳልጣል።
የጤና፣ የትምህርት እና መሰል የትምህርት ተቋማት ተደራሽነት ይጨምራል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 471
13 471
በጋሼና - ላሊበላ - ብልባላ ሰቆጣ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 09/2018 (ኢ መ አ):-በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞንን ከዋግኽምራ ዞን ጋር በሚያስተሳስረው በጋሼና - ላሊበላ እና የላሊበላ ተለዋጭ መንገድ እንዲሁም የብልባላ - ሰቆጣ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጀምሯል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በሁለት ኮንትራቶች ተከፋፍሎ የሚገነባ ሲኾን፥ ኮንትራት-1 የጋሼና - ብልባላ እና የላሊበላ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ ያካትታል። ኮንትራት-2 ከብልባላ - ሰቆጣ ያለውን መንገድ ይሸፍናል።
ከዚህ አብዛኛው የመንገዱ ክፍል በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ከመቋረጡ በፊት በአስፋልት ደረጃ ተጠናቅቆ የነበረ ሲኾን፤ ከቀሪው 23 ነጥብ 32 ኪሎሜትር ውስጥ 10 ነጥብ 27 በመቶውን ማጠናቀቅ ተችሏል።
ከአስፋልት ሥራው ጎን ለጎን የጠረጋ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የመንገድ አካፋይ፣ እንደዚሁም የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በሰቆጣ፣ ላሊበላ እና ጋሼና ከተማዎች ውስጥ በመከናወን ላይ ናቸው።
በዚህ ዓመትም የፕሮጀክቱን አፈጻጸም አጠናክሮ በማስቀጠል በሰቆጣ እና በላሊበላ ከተሞች ያለውን የአስፋልት ሥራ እንዲሁም የ1 ነጥብ 2 ኪሎሜትር የሪጅድ ፔቭመንት (ሲሚንቶ ኮንክሪት) ሥራ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።
ለፕሮጀክቱ 5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግሥት በጀት ተይዞለታል። ግንባታውን ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ጋር በጣምራ በማከናወን ላይ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ የሰቆጣ -ላሊበላ እንዲሁም ከጋሸና - ወልድያ- ደሴ ያለውን የትራንስፖርት ፍሰት ያቀላጥፋል። የላሊበላ አብያተ-ክርስቲያናት ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ በኩል አዎንታዊ ሚና ይወጣል።
ከዚህ በተጨማሪም የዋድላ፣ መቄት፣ ላስታ፣ ጋዝጊብላ እንደዚሁም የሰቆጣ ወረዳዎችን ማኅበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ መስተጋብር ያጠናክራል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 471
መንገድ ካልታከመ ይሞታል!"
ቢሾፍቱ፣ መጋቢት 7፣ 2018 ዓም (ኢመአ): የመንገድ ኤጀንሲዎች የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በቢሾፍቱ ተካሄደ
"መንገድ ካልታከመ ይሞታል" በሚል መሪ ቃል፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (ኢ.መ.አ) የመንገድ ፈንድ ዳይሬክቶሬትና የክልል መንገድ ኤጀንሲዎች የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ከመጋቢት 4-5 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ ከአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋና ከሁሉም ክልሎች የተወከሉ የክልል መንገድ ኤጀንሲዎች ተገኝተው የ6 ወራት የሥራ ሪፖርታቸውን አቅርበዋል።
ሪፖርቶቹ በዋናነት በፊዚካልና በፋይናንሺያል አፈጻጸም ላይ ያተኮሩ ሲሆን፤ የተከናወኑ ወቅታዊ፣ መደበኛና ከባድ የጥገና ሥራዎች፣ የከተማ አስፋልት ግንባታ፣ የድልድይ ጥገናና ድንገተኛ የጥገና ሥራዎች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የክልል ተወካዮች በሪፖርታቸው ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦
የመንገድ ጥገና በጀት እጥረትና ተጨማሪ በጀት አስፈላጊነት፤
ያረጁ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ጥገናና አዳዲስ ማሽነሪዎችን የመግዛት አስፈላጊነት፤
ከዋናው መሥሪያ ቤት (ኢ.መ.አ) የሚጠበቁ የቴክኒክና የድጋፍ ፍላጎቶች ይገኙበታል።
በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የኢ.መ.አ የመንገድ ፈንድ ዳይሬክቶሬት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ ዳይሬክቶሬቱ ከመንገድ ፈንድ ምስረታ ጀምሮ ከኢ.መ.አ ጋር እስከመዋሃድ ድረስ ያለውን ሂደት፣ የገቢ ምንጮችን እንዲሁም ለኤጀንሲዎች የሚሰጠውን ድጎማ የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎችን አቅርቧል።
በመጨረሻም በሪፖርቶቹ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በኢ.መ.አ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮችና በመንገድ ፈንድ ዳይሬክተሩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 471
የወራቤ - ቦዠባር አስፋልት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 75 በመቶ ደረሰ
ወራቤ፣ መጋቢት 04/2018 (ኢመአ):- የስልጤ ዞንን ከጉራጌ ዞን ጋር የሚያገናኘው የወራቤ - ቦዠባር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 75 በመቶ ደርሷል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ መነሻውን ከወራቤ ከተማ አሥተዳደር በማድረግ በዋናነት አልቾውሪሮ እና ቅበት ወረዳዎችን የሚያስተሳስር ሲኾን፥ 41 ነጥብ 34 ኪሎሜትር ይሸፍናል።
አሁን ላይ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 14 ኪሎሜትሩን በአስፋልት የማልበስ ሥራ ተሠርቷል። ከዚሁ ጎን ለጎን እየተከናወኑ ከሚገኙ በርካታ የግንባታ ሥራዎች መካከል፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የውኃ መፋሰሻ፣ የሰብቤዝ እንዲሁም የቤዝኮርስ ሥራዎች ይጠቀሳሉ።
ከመንገድ ወሰን ማስከበር እንዲሁም ከግንባታ ግብዓት አቅርቦት ጋር የተያያዙ ችግሮች በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ፈጥረው የነበረ ቢኾንም፤ ተቋማችን ባደረገው የተቀናጀ ጥረት ችግሮቹን መቅረፍ ተችሏል።
በመኾኑም ፕሮጀክቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተሻለ ቁመና ላይ ይገኛል። በቀጣይ ዓመት ታኅሣሥ ወር ለማጠናቀቅ ታቅዶም በትኩረት በመሠራት ላይ ነው።
ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከፌደራል መንግሥት በተመደበ 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ኤስ ጂ ኮንስትራክሽን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን በመሥራት ላይ ነው።
የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ከወራቤ ከተማ ተነስቶ ቦዠባር ከተማ ለመድረስ ይወስድ የነበረውን የ2 ሰዓት ተኩል ጉዞ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ወደ ወልቂጤ እና ጅማ ለመጓዝ በቡታጅራ በኩል የሚደረገውን አድካሚ እና ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ ያስቀራል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 471
የነቀምት ቡሬ ፡ ክፍል 3: አጋምሳ -ቡሬ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
መጋቢት 3፣ 2018 (ኢመአ)፦ 84.55 ኪሎ ሜትርን የሚሸፍነው የነቀምት ቡሬ ፡ ክፍል 3: አጋምሳ -ቡሬ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን አጋምሳ ከተማ አድርጎ እስከ ቡሬ የሚዘልቅ ነው።
ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 66.8 በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 2,291,551,346.32 (ሁለት ቢሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ ሶስት መቶ አርባ ስድስት ብር ከሰላሳ ሁለት ሣንቲም) ብር የሚሸፈነው በአለም ባንክ ነው ።
የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ቾንግኪንግ ኢንተርናሽናል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኩንሃ ኢንጅንሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስዌይ ኮርፖሬሽን በትብብር እንዲሁም ኢትዮ ኢንፍራ እንጅንሪንግ ኃላ/የተ/የግ ኩባንያ ጋር በጣምራ በመሆን እያከናወኑት ይገኛሉ።
ቀደም ሲል በጸጥታ ሁኔታ፣ በወሰን ማስከበር ችግሮች እና በተቋራጭ ለውጥ ምክንያት የግንባታ መዘግየት አጋጥሞት የነበረ ቢሆንም፤ በኢመአ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ጥረት ፕሮጀክቱ አሁን ላይ በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል።
ቀደም ሲል ከ4 ሰዓት በላይ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ዝቅ ያደርገዋል።
አርሶ አደሮች ምርታቸውን ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ እና የውጭ ገበያ በማውጣት አምራችና እና ሸማቾችን በቀላሉ በማገናኘት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡
መንገዱ ግንባታው በከተማ 21.5 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
