fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 290 مشترک است و جایگاه 1 761 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 559 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 290 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 09 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 135 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.75% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.16% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 555 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 148 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 290
مشترکین
+1624 ساعت
+317 روز
+13530 روز
آرشیو پست ها
የድሬዳዋ- ሸነሌ የመንገድ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ ሱማሌ፣ ሸነሌ፣ ሚያዚያ 28 2018 ዓ.ም (ኢመአ):- ድሬዳዋ ከሸነሌ ከተማ ጋር የሚያገናኘው የድሬዳዋ- ሸነሌ የመንገድ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራ፣ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር  አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ፣ የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ደኤታ የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሃመድ አብዱራህማን (ኢንጅነር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል የመንግሥት የሥራ ኅላፊዎች ተገኝተዋል። በሸነሌ ከተማ በተካሄደው የምረቃ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ክቡር አቶ አደም ፋራህ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት፤ ዛሬ የድሬዳዋ – ሸነሌ መንገድ መጠናቀቅ በክልሉ ልማት ታሪካዊ ምዕራፍ እንደተከፈተ ግልጽ ማሳያ ያሉ ሲሆን መንገዶች አንድ ላይ ሲገናኙ የኢኮኖሚን እና የማህበራዊ  እንቅስቃሴን በስፋት እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል። አያይዘውም ከመንገድ ባሻገር  በክልሉ ውስጥ ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች እየተሰሩ መሆኑን ገልፀው ኢትዮጵያ በተግባር የተገነባ የትስስር እና የኢኮኖሚ ኮሪደር ስርዓት በመዘርጋት ወደፊት እየተጓዘች መሆኑን ተናግረዋል። የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ዛሬ በሱማሌ ክልል የምናየው ልማት የተለየ ነው።  ይህ የድሬዳዋ – ሸነሌ መንገድ ምርቃት በቃል ሳይሆን በተግባር የተፈጠረ ለውጥ ምስክር ነው ያሉ ሲሆን ይህ መንገድ ከተሞችን ብቻ አያገናኝም፤ ህዝብን ከህዝብ ጋር ያገናኛል፣ ንግድን ያበረታታል፣ እንዲሁም የኢኮኖሚ እድገትን ያፋጥናል። አርብቶ አደሩም ሆነ ገበሬው ምርታቸውን ወደ ገበያ ማድረስ ያስችላል፣ ለወጣቶቻችን ዕድል ይፈጥራል፣ ለሕዝባችን አገልግሎትን ያቀርባል ብለዋል። መንገዱ የድሬዳዋ እና የሸነሌን ህዝቦች በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ግንኙነት ይበልጥ በማስተሳሰር በሁለቱ ከተማዎች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና አብሮነት ከማጠናከሩም ባለፈ አንዱ አካባቢ ከሌላው ሳይነጠል በጋራ የማደግ ፍልስፍናችንን በተግባር የሚያሳይ ስኬታማ የመንገድ ልማት ነው  ያሉት የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ዲኤታ ዶ/ር የትምጌታ  አስራት  አክለውም የሃገራችን ከተሞች ለነዋሪዎቻቸው ምቹ ለኢንቨስትመንት ሳቢ እና ለንግድ እንቅስቃሴ ቀልጣፋ እንዲሆኑ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን በበኩላቸው ይህ ስኬት መንግስታችን ለመሠረተ-ልማት ግንባታ የሰጠውን ልዩ ትኩረትና የማይለወጥ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያረጋግጥ እንደሆነ ተናግረዋል። ይህ ከፍተኛ የመንግስት መዋዕለ-ነዋይ ወጪ የሆነበት መንገድ ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ይችል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካል ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያደርግለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የድሬዳዋ–ሽነሌ እና የድሬዳዋ ባይፓስ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ያካተተ ሲሆን፣   ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በፌደራል መንግሥት ወጪ ተደርጎበታል።  የድሬዳዋ አስተዳደርን ከሽነሌ ከተማ ጋር የሚያገናኘው ይኸው መንገድ  10.5 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው መንገዱ 7.5 ኪ.ሜ በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ውስጥ ሲገኝ፣ ቀሪው ክፍል በድሬዳዋ አስተዳደር ስር ይገኛል ዓለም - አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የመንገዱን ግንባታ ያካሄደው ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራው በቤዛ ኢንጂነሪንግ ኬንያ ሊሚትድ ተከናውኗል። መንገዱ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያለው ሲሆን ከድሬዳዋ ተነስቶ ሽንሌን በማቋረጥ ሰፊውን የሶማሌ ክልል ከሀገራዊ የንግድ መረብ ጋር የሚያስተሳሰር ወሳኝ የልማት ድልድይ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ ጅዳ መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21/ 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማን ከክልል ከተሞች ጋር ከሚያገናኙ አምስት ዋና ዋና መግቢያና መውጫዎች መካከል አንዱ የሆነው የጣፎ አደባባይ - ለገዳዲ - ኩራ ጅዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል። 15 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህ የመንገድ  ሥራ በኢመአ የራስ ኃይል (ዓለም ገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት) ፣በአሰር ኮንስትራክሽን እንዲሁም በዋይብ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ጥምረት ነው እየተከናወነ የሚገኘው። የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ  የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የትራንስፖርት ሴክተር እየሰራው ሲሆን ለመንገዱ ግንባታ የሚውለውን 19 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በፌዴራል መንግሥት የተሸፈነ ነው። መንገዱ  በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እና በሸገር  ከተማ አስተዳደር ውስጥ  የሚገኙትን  ኤካ ጣፎ እና ኩራ ጅዳ ወረዳዎችን አቋርጦ ያልፋል። ቀደም ሲል የነበረው  7 ሜትር  የጎን ስፋት የነበረው መንገድ አሁን ላይ  በግራና በቀኝ 4 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ በሚችል መልኩ ወደ 28 ሜትር ስፋት እንዲያድግ ተደርጓል። የፕሮጀክቱ ግንባታ የትራፊክ ፍሰቱን ከማሳለጥ ባለፈ 4 ሜትር የአረንጓዴ ስፍራ እንዲሁም 14 ሜትር የእግረኛና የሳይክል መንገዶችን ያካተተ ነው። መስመሩ ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ሲና፣ ኮምቦልቻ እና ደሴ ለሚደረግ ጉዞ ዋነኛ መተላለፊያ በመሆኑ የትራፊክ መጨናነቅ በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል። ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው ከሚገኙ የኢንዱስትሪ ዞኖች የሚወጡ የኤክስፖርት ምርቶችን እንቅስቃሴ ከማሳለጡም በላይ የግብርና እና የወተት ውጤቶች ያለምንም መጓተት ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ረገድ የላቀ ፋይዳ ይኖረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የመክፈቻ ዝግጅት ተካሄደ አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 12/2018(ኢመአ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገሪቱ የመንገድ መሠረተ ልማት ግንባታ የ75 ዓመታት ጉዞ የሚዘክርበትን የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል በተሰናዳ የመክፈቻ ሥነ-ስርዓት ተካሄዷል። ይህንን በማስመልከት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን፤ ኢመአ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ውስጥ ያለፈባቸውን አስቸጋሪና ስኬታማ የሥራ እንቅስቃሴዎች በዝርዝር አብራርተዋል። ዋና ዳይሬክተሩ "ይህ በዓል ያለፈውን ታሪካዊ ስኬት የምናደንቅበት ብቻ ሳይሆን፣ የወደፊቱን የልማት ግቦች የምንቃኝበትና አዳዲስ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን ለማስተግበር ቃል የምንገባበት ጭምር ነው" በማለት ሁሉም በጋራ በመቆም የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በስኬት እንደሚያስቀጥሉ ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር የትምጌታ አሥራት በበኩላቸው ተቋሙ የሀገሪቱን የኢኮኖሚና ማህበራዊ ትስስር በማጠናከር ረገድ እየተወጣ ያለውን ሚና አድንቀዋል። የመንገድ ልማት ሥራዎችን በጥራትና በፍጥነት ከማከናወን ጎን ለጎን፣ የመንገድ ግንባታ ሥራ እንቅስቃሴዎችን በቅርበት በመከታተልና የአሠራር ውጤታማነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባም በአፅንኦት አሳስበዋል። የክብረ በዓሉ አንዱ አካል ሆኖ በልዩ ሁኔታ በቀረበው አውደ-ርዕይ፤ ተቋሙ በኢትዮጵያ ተራራማና አስቸጋሪ መልክዓ-ምድር ውስጥ መንገዶችን ለመገንባት የከፈለውን መሥዋዕትነት የሚያሳዩ ሥራዎችን አካቶ ለታዳሚው ቀርቧል። ዘመናዊ መሣሪያዎች ባልነበሩበት ወቅት የነበረውን አድካሚ የሥራ ሂደት ህያው አድርገው የሚያሳዩት እነዚህ የታሪክ አሻራዎች፤ ተቋሙ ያለፈበትን ጥንካሬና ለዛሬው የዕድገት መሠረት መሆናቸውን ማሳየት ተችሏል ። በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት አንጋፋ አመራሮችም፣ ተቋሙ በየዘመኑ የነበሩበትን ተግዳሮቶች እንዴት በፅናት እንደተወጣና አሁን ላለው ደረጃ እንደደረሰ የሚያሳይ ዘመን ተሻጋሪ የሥራ ተሞክሮአቸውን ለታዳሚው አካፍለዋል። በዕለቱ የኢመአ የ75 ዓመታት ጉዞ ውስጥ የተከናወኑ ታላላቅ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም ለተሳታፊዎች ቀርቧል። በዛሬው እለት የተካሄደው የአልማዝ ኢዮቤልዩ የመክፈቻ ሥነ -ሥርዓት ሲሆን በቀጣይም በዋናው መስሪያቤት እንዲሁም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ዲስትሪክቶች እና የፕሮጀክት ፅ/ቤቶች በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር ይሆናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

“ኢትዮጵያ ትገነባለች!”፦ የመጀመሪያው ሀገራዊ የኮንስትራክሽንና መሰረተ ልማት ሳምንት በታላቅ ድምቀት ተከፈተ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 9/2018 ዓ.ም (ኢመአ): በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማትና የኮንስትራክሽን ሳምንት፤ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና በከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በይፋ ተጀመረ። “ኢትዮጵያ ትገነባለች!” በሚል መሪ ቃል በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የተዘጋጀውና እስከ ሚያዝያ 12 ቀን የሚቆየው ይህ ታላቅ መድረክ፤ የዘርፉ ተዋናዮችና ባለድርሻ አካላት ልምድ የሚለዋወጡበትና ለሀገር ግንባታ የጋራ ራዕይ የሚሰንቁበት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል። የዕለቱ ክብር እንግዳ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዘርፉ የታዩ ሀገራዊ ስኬቶችንና የቴክኖሎጂ አማራጮችን የሚያሳየውን አውደ-ርዕይ መርቀው የከፈቱ ሲሆን፣ ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ጉብኝት አድርገዋል። አቶ ተመስገን በመክፈቻው ባስተላለፉት መልእክት፤ መሰረተ ልማት ለሀገር እድገት ያለውን ወሳኝ ሚና አብራርተዋል። ኩነቱ አዳዲስ የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን ለማስተዋወቅ፣ የሀገር በቀል አቅምን ለማሳደግና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች አገልግሎታቸውን ለዓለም አቀፍ ገበያ እንዲያስተዋውቁ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተመልክቷል። በቀጣዮቹ ቀናትም በዘርፉ ስኬቶችና የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮሩ የፓናል ውይይቶች እንደሚካሄዱና ልዩ ልዩ ሰነዶች እንደሚቀርቡ ታውቋል። በኤግዚቢሽኑ ላይ የተለያዩ የግንባታ ግብዓቶች፣ ግዙፍ ማሽነሪዎች እና ዲጂታል የግንባታ ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ ቀርበዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

"ኢትዮጵያ ትገነባለች!" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ሀገራዊ የኮንስትራክሽንና መሰረተ ልማት ሳምንት ነገ ይጀምራል የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማትና የኮንስትራክሽን ሳምንት ነገ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (CMC) በይፋ ይጀምራል። እስከ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚቆየው ይህ መድረክ፣ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማሳየትና የቀጣይ የልማት አቅጣጫዎችን ለመጠቆም ያለመ መሆኑ ተገልጿል። መርሐ ግብሩ "ኢትዮጵያ ትገነባለች! ፈጠራ፣ ፍጥነት እና ጥራት ለመሠረተ ልማት እምርታ" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የሚሳተፉበት ይሆናል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ቀደም ብለው በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፣ ይህ ሳምንት በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስተዋወቅና የሀገር በቀል አቅምን ለማሳደግ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል። በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት የተገነቡ 40 ሺህ ኪሎ ሜትር የሚጠጉ አዳዲስ መንገዶችና የአዲስ አበባን ገጽታ የቀየሩ የኮሪደር ልማት ውጤቶች በመድረኩ በዝርዝር እንደሚቀርቡ ይጠበቃል። በኤግዚቢሽኑ ላይ፦ የግንባታ ግብዓቶች፣ ግዙፍ ማሽነሪዎች እና ዲጂታል የግንባታ ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ ይቀርባሉ። የ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ አፈጻጸም ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል። በዘርፉ ከፍተኛ አፈጻጸም ላሳዩ ተቋራጮች፣ አማካሪዎችና ባለሙያዎች ዕውቅና ይሰጣል። ይህ ሳምንት የኢትዮጵያን የ67 ቢሊዮን ዶላር የኮንስትራክሽን ገበያ ለዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በማስተዋወቅ ረገድም ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው ተመልክቷል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መልካም በዓል
መልካም በዓል

For the fastest 24/7 updates and analysis on the Iran war, join @geopolitics_prime.

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለፉት ስምንት ዓመታት • የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (ኢ.መ.አ) ክልሎችን እርስ በርስ የሚያገናኝና ሀገራዊ የንግድ ኮሪደሮችን የሚያጠናክር ጠንካራ የፌዴራል የመንገድ መረብ የመዘርጋት ተልዕኮውን ወደ ተግባር በመለወጥ ረገድ ያስመዘገበው አሀዛዊ መረጃ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ያሳያል። • በ2010 ዓ.ም የነበረው የ126,773 ኪሎ ሜትር አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን በ2018 ዓ.ም አጋማሽ ወደ 180,232 ኪሎ ሜትር በማደጉ፣ ከ53 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ አዲስ መንገድ ለሀገሪቱ ተጨምሯል። • የመንገድ ጥግግቱ በየ1000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ከ115.2 ወደ 157 ኪሎ ሜትር አድጓል። • ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ ብቻ 182 ፕሮጀክቶች ወደ ግንባታ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን፣ 71 ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ሆነዋል። • ተቋሙ የመንገድ ጥራትን ከመጠበቅ አንጻርም 80,037 ኪሎ ሜትር መደበኛ ጥገና እና 3,035 ኪሎ ሜትር ከባድ ጥገና በማከናወን የሀገሪቱን የመንገድ ሀብት የመንከባከብ ስራ በትኩረት ሰርቷል። • የውጤቱ ሌላኛው ማሳያ ሀገራችንን የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል የሚያደርጉ ግዙፍ የፍጥነት መንገዶች እውን መሆናቸው ነው። • ከለውጡ በፊት የነበረው 84.7 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ ብቻ ሲሆን፣ ዛሬ ግን የሞጆ-መቂ-ባቱ-አርሲ ነገሌ (151 ኪ.ሜ) እና የድሬዳዋ-ደዋሌ (220 ኪ.ሜ) የፍጥነት መንገዶች ተጠናቅቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። • ከዚህ በተጨማሪ ተቋሙ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ፣ ጅማ፣ ደብረ ማርቆስ እና ነቀምቴ የሚዘልቁ አራት አዳዲስ የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት የአዋጭነት ጥናት እያጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያን በ10 ዓመታት ውስጥ የ1,600 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ባለቤት ለማድረግ ለተያዘው ግብ ትልቅ እርምጃ ነው። • ሌላኛው ትልቅ ስኬት ኢትዮጵያን ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያገናኙ ግዙፍ መንገዶች እውን መሆናቸው ነው። • ተቋማዊ አደረጃጀትን በማዘመንና ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት ረገድም በለውጡ ማግስት ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል። • ቀደም ሲል ተነጥለው የነበሩ የመንገድ ጥገና ዲስትሪክቶችና ሴክሽኖች ወደ ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እንዲመለሱ ተደርጓል። • በተጨማሪም በሀገሪቱ በተለያዩ ክፍሎች የግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤቶች ተከፍተው ስራ እንዲጀምሩ በመደረጉ፣ የፕሮጀክቶች ክትትልና ድጋፍ በመንገድ ግንባታው ስፍራ ቅርብ እንዲሆኑ አስችሏል። • የመንገድ ሀብቱን ለመጠበቅና የከባድ ተሽከርካሪዎችን ጫና ለመቆጣጠር የሚረዱ የሚዛን ጣቢያዎች ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በማስፋፋት እና ያሉትን ዲጂታላይዝ እንዲሆኑ ተደርገዋል። • ይህ የዲጂታላይዜሽን ስራ የተሽከርካሪዎችን ክብደት ከሰው እጅ ንክኪ ነጻ በሆነ መልኩ በመመዝገብ፣ የአሰራር ግልጽነትን በማስፈንና የመንገድ ብልሽትን በመቀነስ ረገድ የላቀ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። • በመንገድ ምርምር ረገድም የተቋሙን የምርምርና ላቦራቶሪ ማዕከል አቅም በማሳደግ የመንገድ ግንባታ ግብአቶችን ጥራት በሳይንሳዊ መንገድ ለመፈተሽ የሚያስችሉ ስራዎች ተሰርተዋል። • የዘርፉን አቅም ለመገንባትም በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ወጪ የተደረገባቸው በርካታ ዘመናዊ ለመንገድ ግንባታ የሚውሉ ማሽነሪዎች ግዢ መፈጸሙ እና ሌሎችም በርካታ ተግባራት ተከናውነውል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

NOTICE OF INVITATION FOR BIDS CAPACITY BUILDING ROAD PROJECTS

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የተጠሪ ተቋማትን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ገመገመ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ/ም (ኢመአ)፡ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን እና የግንባታ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄዱ። በመድረኩ የተቋማቱ ጥንካሬና ድክመቶች የተፈተሹ ሲሆን፣ በቀጣይ መወሰድ ስላለባቸው ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በግምገማው አፈጻጸማቸውን ካቀረቡት ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የዕቅዱን 78 በመቶ ማሳካቱ ገልጿል። አስተዳደሩ በአሁኑ ወቅት ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ፕሮጀክቶችን እየመራ ሲሆን፣ ዓመታዊ የመንገድ ግንባታ የማጠናቀቅ አቅሙን ከ800 ኪሎ ሜትር ወደ 1,600 እና 2,000 ኪሎ ሜትር ማሳደግ እንደሚገባው አጽንኦት ተሰጥቶበታል። መድረኩን የመሩት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር የትምጌታ አስራት በተለያዩ ምክንያቶች የተቋረጡ ፕሮጀክቶችን በመለየት መፍትሄ እንዲቀመጥላቸውና በመንገድ ጥገና ሥራዎች ላይ ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን (ECA) በበኩሉ፣ የኮንስትራክሽን ግብዓቶች የዋጋ መረጃ ሥርዓት የመዘርጋት እንዲሁም በምዝገባ፣ በፈቃድ አሰጣጥና በቁጥጥር ሥራዎች በኢንዱስትሪው ላይ ተጨባጭ ለውጥ የማምጣት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ተጠቁሟል። በተመሳሳይ የግንባታ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት (CMI) ለሚገነባው የልህቀት ማዕከል ግልጽ የሥራ መመሪያ (Roadmap) እንዲያዘጋጅና ከመንግሥት በጀት ጥገኝነት ወጥቶ ገቢ የሚያመነጩ የኢንተርፕርነርሺፕ ሥራዎች ላይ እንዲያተኩር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የዋጋ ንረት፣ የነዳጅና የአቅርቦት እጥረት በፕሮጀክቶች ላይ ተጨማሪ ወጪና መጓተት እያስከተሉ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ማጠቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር የትምጌታ አስራት እነዚህን ተግዳሮቶች ለመወጣት በተጠሪ ተቋማቱ መካከል ያለው ቅንጅት መጠናከር እንዳለበትና ሁሉም ተቋማት ከወዲሁ የ2019 ዓ.ም የቅድመ ዝግጅት ዕቅድ ማውጣት እንዲጀምሩ መመሪያ ሰጥተዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads