fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 781 مشترک است و جایگاه 1 694 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 459 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 781 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 125 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 34.57% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.80% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 764 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 177 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 781
مشترکین
-324 ساعت
+47 روز
+12530 روز
آرشیو پست ها
በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው ፡፡ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ። የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል። እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው። እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት  የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል። በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡ በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል። በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል። ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል። በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤ በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል። በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል። በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል። በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል። መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን!

ደሎ ሰብሮ - ጃራ - ሼይኽ  ሑሴን መንገድ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው   ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (ኢመአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ባሌ ዞን የታሪካዊው ድሪ ሼይኽ ሑሴን መካነ - ቅርስ መዳረሻ የሆነውን የደሎ - ሰብሮ - ጃራ - ሼይኽ ሑሴን መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው። 77 ነጥብ 48 ኪሎሜትር የሚሸፍነው ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት መነሻውን ደሎ ሰብሮ  ከተማ አድርጎ እስከ ሼህ ሁሴን  የሚዘልቅ ነው። ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 58.82 በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ  ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።   ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን 1,592,270,000.00 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ዘጠና ሁለት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ሺህ) ብር የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው ።    የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ዠይጂያንግ ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ቡድን  ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ አይዲኮን ኢንፍራስትራክቸር ዴቬሎፕመንት ኮንሰልታንት ኃላ.የተ.የግ ማኅበር  እያከናወነው ይገኛሉ።    ቀደም ሲል በጸጥታ ሁኔታ ፣ በወሰን ማስከበር ችግሮች እና በተቋራጭ ለውጥ ምክንያት የግንባታ ሂደቱ መዘግየት አጋጥሞት የነበረ ቢሆንም፤ በኢመአ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ጥረት ፕሮጀክቱ አሁን ላይ በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል።  የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች አዎንታዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ለውጥን ያመጣል።   የጊኒር እና ጎሎልቻ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካታ አጓራባች ቀበሌዎችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማስተሳሰር የሕዝብ ለሕዝብ መስተጋብሩን ይበልጥ ያጠናክራል።    የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መጠናቀቅ  ቀደም ሲል ይወስድ የነበረውን የ3 ሰዓታት የጉዞ ጊዜ ወደ 1ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል።   የመንገድ ፕሮጀክቱ በተለይም በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች እንደሚጎበኙት የሚነገርለት የታሪካዊው የድሪ ሼይኽ ሑሴን ባሌ መዳረሻ እንደመኾኑ፣  ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለጎብኝዎች ምቹ ሁኔታ ይፈጠራል። ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን 21 ሺህ የሚጠጉ ችግኞችን በጋራ ተከለ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (ኢመአ) ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ ብሔራዊ መርሃ-ግብር ላይ አሻራውን አኑሯል። አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 800,000 ችግኞችን ለመትከል አቅዶ በዋና መሥሪያ ቤትና የመንገድ ፕሮጀክቶች ባሉበት ቦታዎች ሁሉ ለመትከል በያዘው ዕቅድ መሠረት፤ ከሳምንት በፊት 3,000 ችግኞችን መትከሉ ይታወቃል። የዛሬው ተሳትፎም የዚሁ አጠቃላይ የክረምት መርሃ-ግብር አካል ሲሆን፤ አስተዳደሩ ከተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ጋር በመሆን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ልዩ ስሙ «ገበያ» በሚባለው ስፍራ ወደ 21 ሺህ የሚጠጉ ችግኞችን በጋራ ተክሏል። ይህ ተቋማዊ የተቀናጀ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ከተሞች ይስተዋሉ የነበሩ የጥራት፣ የእቅድ እና የተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭነት ችግሮችን ለመቅረፍ የተያዘውን ሀገራዊ ራዕይ ለማገዝ የተከናወነ መሆኑ ተገልጿል። በመረሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል አብዛኞቹ የሀገሪቱ ከተሞች በዝቅተኛ ጥራት የተገነቡ እና ለጎርፍ አደጋ የተጋለጡ በመሆናቸው ለዜጎች ምርታማ ህይወት አመቺ አልነበሩም። ሆኖም ላለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጁ የአረንጓዴና ተፋሰስ ልማት ፕሮጀክቶች ለከተሞች ሳንባ የሚሆኑ አረንጓዴ ቦታዎችን ማስፋፋት፣ ወንዞችን መታደግና የጎርፍ ተጋላጭነትን በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ ተችሏል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ባለፉት 5 ዓመታት ብቻ ከ40 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለው የ90 በመቶ የጽደቅ ስኬት የተመዘገበ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የደን ሽፋን እ.አ.አ በ2018 ከነበረበት 17.2% በ2023 ወደ 23.6% አሳድጎታል። በተመሳሳይ መልኩ የዋና ከተማዋ የአዲስ አበባ የደን ሽፋን ከ11% ወደ 20% ማደጉን ያነሱት ክብርት ሚኒስትሯ፤ እኚህ ስራዎች የተፈጥሮ መልክዓ ምድሮች የከተማ እና የመሠረተ ልማት እቅድ አካል ወደሆኑበት ሥነ ምኅዳራዊ (ecological) የከተማ ንድፍ እየተደረገ ላለው ሽግግር ሕያው ማሳያዎች መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና የሌሎች ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች በዕቅዳቸው መሠረት የክረምት መርሃ-ግብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ፤ የተተከሉትን ችግኞች በቀጣይነት የመንከባከብ ሥራን በማጠናከር እንዲሁም የመንገድ መሠረተ ልማቶች የአካባቢን ስነ-ምህዳር ባገናዘበ መልኩ እንዲገነቡ በማስቻል ከተሞችን ለመኖር ምቹ የማድረግ ራዕይን ለማሳካት ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሠራተኞች እና አመራሮች አረንጓዴ እሻራቸውን አኖሩ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20/2018 (ኢመአ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሠራተኞች እና አመራሮች 75አመታት ኢትዮጵያን በመንገድ ያስተሳሰረ ጉዞ በሚል መሪ ቃል ዛሬ ለስምንተኛ ጊዜ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል። ተቋማችን የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት በተለያዩ መርሃ-ግብሮች እያከበረ መሆኑ ይታወቃል። የዛሬው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብርም የዚሁ ክብረ-በዓል አካል ነው። የዋናው መስሪያ ቤት ፤ የዓለም ገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት የቃሊቲ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞች እና  አመራሮች በጋራ በመሆን በጣፎ አደባባይ -ለገዳዲ -ኩራጅዳ (15ኪሜ) የመንገድ ፕሮጀክት ላይ አሻራቸውን አሳርፈዋል። በተመሳሳይ ተቋማችን ባሉት 11 ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላት እንዲሁም በ25ቱ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች ችግኞች ተተክለዋል። ተቋማችን የተመሠረተበትን 75ተኛ ዓመት በማስመልከት በዘንድሮ ዓመት በሁሉም አካባቢ ከ75 ሺህ በላይ ችግኞችን መትከሉ ለተቋሙ ልዩ መርሐግብር ሆኗል ። ኢመአ ባለፋት ስምንት ዓመታት ሀገራዊ አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የተቋሙን መላውን ሰራተኛ በማሳተፍ  ሀላፊነቱን መወጣቱን ቀጥሏል። የተቋሙ ሰራተኞች  አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ መሆኑን ተረድተው ሀገራዊ ባህል ተሳትፎና ንቃታቸው በማደጉ ደስተኞች መሆናቸውን የተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ገልፀዋል ። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።እንደ ተቋም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች  የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግ ግብረ -ሀይል በመቋቋሙምም የመጽደቅ ምጣኔው አጥጋቢ ውጤት እንዲገኝ ማስቻሉ ተገልጿል። በተለይም የመንገድ ግንባታን ተከትሎ በደኖች ላይ ጉዳት እንዳይከሰት መጠንቀቅ መቻሉ ፤ የዲዛይን ስራዎችን ታሳቢ አድርጎ ቀድሞ መስራቱ እንዲሁም ተቋራጮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የችግኝ ተከላ መርሃ -ግብርን አጠናክረው መቀጠላቸው በአካባቢ ጥበቃ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር እንደሆነ ተገልጿል ። ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ባለፉት ሰባት አሥርተ ዓመታት ውስጥ ተቋሙ የኢትዮጵያን ገጠር ከከተማ፣ አምራቹን አርሶ አደር ከገበያ በማስተሳሰር ረገድ የከፈለው በዋጋ የማይተመን መሥዋዕትነትና የጀግንነት ታሪክ የታየበት ነው። በም
ባለፉት ሰባት አሥርተ ዓመታት ውስጥ ተቋሙ የኢትዮጵያን ገጠር ከከተማ፣ አምራቹን አርሶ አደር ከገበያ በማስተሳሰር ረገድ የከፈለው በዋጋ የማይተመን መሥዋዕትነትና የጀግንነት ታሪክ የታየበት ነው። በምስረታው ወቅት ከነበረበት ውስን አቅም ተነስቶ ዛሬ ላይ የሀገራችንን ገጽታ የሚቀይሩና ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ታላላቅ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የማከናወን ብቃት ላይ መድረሱ የሁላችንም ኩራት ነው። ጫልቱ ሳኒ የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚኒስትር

“የዛሬው ክብረ በዓል መንገድ መሠረተ ልማታችን ከየት ተነስቶ የት ደረሰ የምንቃኝበት ብቻ ሳይሆን፤ የወደፊቱን የመንገድ ልማት አቅጣጫ የምንወስንበትም ነው።” ዶ/ር እዮብ ተካልኝ የኢትዮጵያ መንገዶች
“የዛሬው ክብረ በዓል መንገድ መሠረተ ልማታችን ከየት ተነስቶ የት ደረሰ የምንቃኝበት ብቻ ሳይሆን፤ የወደፊቱን የመንገድ ልማት አቅጣጫ የምንወስንበትም ነው።” ዶ/ር እዮብ ተካልኝ የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የቦርድ ሰብሳቢ

"በቀጣዮቹ ዓመታት ትኩረታችን መንገዶችን በብዛት መገንባት ብቻ ሳይሆን፣ በጥራት፣ በዘላቂነት፣ በደኅንነት፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በዘመናዊ የንብረት አሥተዳደር መርሆዎች ላይ በተመሠረተ የመንገድ ልማት
"በቀጣዮቹ ዓመታት ትኩረታችን መንገዶችን በብዛት መገንባት ብቻ ሳይሆን፣ በጥራት፣ በዘላቂነት፣ በደኅንነት፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በዘመናዊ የንብረት አሥተዳደር መርሆዎች ላይ በተመሠረተ የመንገድ ልማት ላይ ያተኮረ ይሆናል።" :- ኢንጅነር መሐመድ አብዱራሕማን የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ዋና ዳይሬክተር

የ75 ዓመታት የፅናት ጉዞ በምስል መነፅር የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የ75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን አስመልክቶ በዋናው መሥሪያ ቤት ልዩ ታሪካዊ የፎቶ አውደርዕይ በይፋ ተከፈተ። ​ይህ አውደርዕይ ተቋሙ "የአውራ ጎዳና ባለሥልጣን" ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 75 ዓመታት በመንገድ ልማት ያለፈባቸውን ውጣ ውረዶች በምስል የሚያሳይ ነው። ተቋሙ ሥራውን በጀመረበት ወቅት ሀገሪቱ ከነበራት አነስተኛ የመንገድ ርዝማኔ ተነስቶ ዛሬ ላይ የደረሰበትን የዘመናዊ ፈጣን መንገዶች፣ የድልድዮችና የሜጋ ፕሮጀክቶች የምህንድስናን ከፍታ የሚያሳዩ በርካታ  ታሪካዊ ፎቶግራፎችን በማቅረብ ያለፈበትን የዕድገት ጎዳና ለታዳሚዎቹ ያሳያል። በዝግጅቱ ላይ የአስተዳደሩ ቁልፍ የሥራ ዘርፎች የሆኑት የማሠልጠኛ ተቋማት፣ የምርምር ማዕከል፣ የፕላኒንግ፣ የዲዛይ እና ግንባታ ፣ የመንገድ ሀብት እና የድልድዮች ግንባታ ክፍሎች የየራሳቸውን ተቋማዊ የሥራ ክንዋኔዎችና ውጤቶች እንዲሁም ያለፉበትን ዓመታት ለጎብኚዎች በስፋት አቅርበዋል። ​መርሐ-ግብሩን በይፋ የከፈቱት የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ሲሆኑ፣ የኢመአ የቦርድ አባላት፣ የከተማ፣ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው ተቋማት ኃላፊዎች፣ የቀድሞ የኢመአ ዋና ዳይሬክተሮች  የቀረቡትን ታሪካዊ ሁነቶች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ​በዕለቱም ለረጅም ዘመን ተቋሙን በታማኝነትና በፅናት ያገለገሉ፣ በጡረታ ላይ የሚገኙ አንጋፋ ሠራተኞች ተሳትፈዋል። በሀገሪቱ ወጣ ገባ መልከዓ-ምድሮች ውስጥ በታላቅ ሀገራዊ ፍቅርና መስዋዕትነት መንገድ ለመክፈት ይከፈል የነበረውን ታላቅ ዋጋ ያሳየ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ከዚህም ባለፈ ይህ የፎቶ አውደርእይ  የታሪክ ማስታወሻ ብቻ ሳይሆን፣ ለአዲሱ ትውልድ  የአገልግሎት ፅናትንና ሙያዊ ሥነ-ምግባርን የሚማርበት፣ የትውልድ ቅብብሎሽ በተግባር የታየበት ድልድይ ሆኗል። ​አስተዳደር መ/ቤቱ የመንገድ መሠረተ ልማቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ይህ አውደርዕይ በቀጣይም ለሁለት ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ እያከበረ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16/2018 (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ባለፉት 75 ዓመታት የተጓዘበትን ታሪካዊ የመንገድ ልማት አሻራዎች በማስታወስ፣ የተቋሙን ስኬቶች በመዘከር እና ለነገው አዲስ የልማት ምዕራፍ ቃል ኪዳን በመግባት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት እያከበረ ይገኛል። በዝግጅቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቀድሞ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የልማት አጋር ተቋማት፣ የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የመስሪያ ቤቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተገኝተዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንደገለጹት፤ ይህ የ75ኛው ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል ተቋሙ ባለፉት ሰባት አሥርተ ዓመታት ያከናወናቸውን ታላላቅ ሥራዎች የሚዘክርበት ብቻ ሳይሆን ወደፊት የሚጠብቁትን ሀገራዊ ግቦች ለማሳካትም አዲስ ቃል የሚገባበት ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሯ አክለውም ተቋሙ በምስረታው ወቅት ከነበረው ውስን አቅም ተነስቶ ዛሬ የሀገሪቱን ገጽታ የሚቀይሩና ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ታላላቅ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የማከናወን ብቃት ላይ መድረሱ የሚያኮራ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። ከዚህም በተጨማሪ የመንገድ መሠረተ ልማት ለኢንዱስትሪ ዕድገት፣ ለግብርና ምርታማነትና ለቱሪዝም መስፋፋት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል በመሆኑ የተቋሙ የወደፊት ጉዞ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በዲጂታል አሠራር የታገዘ እንዲሆን የሚደረጉ የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ በበኩላቸው፣ በዓሉ ተቋሙ ባለፉት 75 ዓመታት ከአንደኛው የሀገሪቱ ጫፍ እስከ ሌላኛው ጫፍ ሕዝቦችን በማገናኘት ያከናወናቸውን ሥራዎች የሚያደንቅበት ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራዊ ራዕይን ዕውን ለማድረግና የተጀመሩ የልማት ምዕራፎችን ለማጠናከር አዲስ ጉልበት እንደሚሰጥ ተናግረዋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራሕማን የኢመአ የ75 ዓመታት ጉዞ ባለፉት ዓመታት ብዛት ብቻ የሚለካ ሳይሆን በራዕይ፣ በቁርጠኝነት፣ በሙያዊ ብቃትና በትውልዶች ትጋት የተገነባ ታሪክ መሆኑን ገልጸዋል። በተቋሙ ምስረታ ወቅት የነበረው የሀገሪቱ የመንገድ አውታር 6, ሺህ 400 ኪሎ ሜትር ብቻ እንደነበር ጠቅሰው፣ ዛሬ ግን 182 ሺህ 232 ኪሎ ሜትር የደረሰ ሰፊ የመንገድ አውታር መገንባቱን ጠቁመዋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ ቀድሞ ከነበሩት የአውራ ጎዳና ፕሮግራሞች ተነስቶ እስከ መንገድ ሴክተር፣ እንዲሁም ከ1989 ዓ.ም ወዲህ በተተገበሩ ተከታታይ የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሞች አማካኝነት የተከናወኑ የመንገድ ግንባታና ጥገና፣ የድልድይ ልማት፣ የመንገድ ንብረት አስተዳደር፣ የመንገድ ደኅንነትና የተቋማዊ አቅም ግንባታ ላይ ከፍተኛ እመርታ ተመዝግቧል። በቀጣይም ተቋሙ በጥራት፣ በዘላቂነት፣ በደኅንነት፣ በአካባቢ ጥበቃና በዘመናዊ የንብረት አስተዳደር መርሆዎች ላይ በመመሥረት የመንገድ ልማቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። ለሦስት ቀናት በሚቆየው በዚህ የበዓል መርሃ-ግብር ፣ የተቋሙን የ75 ዓመታት የመንገድ ልማት ጉዞ የሚያሳዩ የፎቶና የሰነድ ኤግዚቢሽኖች፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማሳያዎች እንዲሁም የውይይት መድረኮች ይከናወናሉ። ከዚህም በተጨማሪ የእውቅና አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓቶችና የባሕል ዝግጅቶችን ጨምሮ የተለያዩ ይዘት ያላቸው ፕሮግራሞች የዚሁ ሁነት አካል ናቸው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads