ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 793 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 694,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 463 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 793 名订阅者。
根据 27 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 135,过去 24 小时变化为 10,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 34.74%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.66% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 791 次浏览,首日通常累积 2 160 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 28 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 793
订阅者
+1024 小时
+147 天
+13530 天
帖子存档
13 793
የኦሞራቴ–ኛንጋቶም የ63.5 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ 85 በመቶ ደረሰ
ጂንካ፣ ነሐሴ 03/2018 (ኢ መ አ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገነባውና ኦሞራቴን ከኛንጋቶም ወረዳ መስተዳድር ካንጋተን ጋር የሚያገናኘው የ63 ነጥብ 52 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 85 በመቶ ደርሷል።
965 ሚሊዮን ብር (ብር 900,000,000.00) የሚፈጀው ይህ ፕሮጀክት ግንባታው በኤን.ኬ.ኤች (NKH) ኮንስትራክሽን እየተከናወነለት የሚገኝ ሲሆን፣ የሳውንድ ኢንጅነሪንግ ሶሊሽን እና ፒዩር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ጥምረት ደግሞ በአማካሪነት እየሰሩበት ይገኛል።
እስካሁን በተከናወነው ስራ 32.45 ኪሎ ሜትር አስፋልት የመንጠፍ፣ 62.97 ኪሎ ሜትር የአፈር ሙሌት፣ 155 አነስተኛ እንዲሁም 38 መካከለኛ የውሃ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ግንባታ ተጠናቋል። በቀጣይም ቀሪ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በትኩረት እየተሰራ ነው።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በስራ ሂደቱ ላይ ከታችኛው የኦሞ ስምጥ ሸለቆ መካነ-ቅርስ ጥበቃ ጋር በተያያዘ የወሰን ማስከበር፣ የድንጋይና የአፈር ማውጫ ቦታዎች እንዲሁም የመተላለፊያ መስመሮች ለውጥ ያጋጠሙ ችግሮች ናቸው። ይህንን ችግር ለመፍታት ከባህልና ቱሪዝም ባለሙያዎች ጋር በመመካከር የቅርስ ሁኔታን የሚያጠና ባለሙያ ተቀጥሮ መፍትሄ እንዲያገኝ ተደርጓል። በተጨማሪም በኦሞራቴ ከተማ የነበረው የወሰን ማስከበር የካሳ ክፍያ መዘግየት ችግር በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ተፈቷል።
ከዚህ ቀደም አካባቢዎቹን የሚያገናኝ ቀጥተኛ የመኪና መንገድ ባለመኖሩ፣ ነዋሪዎች በቱርሚ ከተማ በኩል ከ140 ኪሎ ሜትር በላይ ተጨማሪ ርቀት ለመጓዝና ከ4 ሰዓታት በላይ ለማባከን ይገደዱ ነበር። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ይህንን እንግልት በእጅጉ ከመቀነሱም በላይ የትራንስፖርት እንቅስቃሴውን ያቀላጥፋል። ከዚህ ባለፈም የኦሞራቴ እና የኛንጋቶም ማህበረሰቦችን በማገናኘት፣ የአካባቢውን የእንስሳት ሀብት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ፣ የንግድ ፍሰቱን ለማሳደግ እና የታችኛው የኦሞ ስምጥ ሸለቆ መካነ-ቅርስን የቱሪዝም ተደራሽነት ለማሳደግ ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል።
ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት
መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን!
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 793
በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከ1 ሺህ 534 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ጥገና ሥራዎች ተከናወኑ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 01/2018 (ኢ መ አ)፦ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ አውታር አሥተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከ1 ሺህ 534 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የመንገድ ጥገና በማከናወን ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም አስመዝግቧል።
በበጀት ዓመቱ ከተከናወኑ ጠቅላላ ሥራዎች ውስጥ 1 ሺህ 431 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትሩ መደበኛ የመንገድ ጥገና ሲሆን፣ ቀሪው 102 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ደግሞ ወቅታዊ የመንገድ ጥገና ነው። እነዚህ ተግባራት የመንገዶቹን የጉዳት መጠንና ዓይነት መሠረት በማድረግ በወቅታዊ፣ በመደበኛ እና በከባድ የጥገና ዘርፎች የተከፋፈሉ ሲሆን፣ ሥራዎቹም በጽሕፈት ቤቱ ራስ-ኃይል፣ በመንግሥትና በግል ሥራ ተቋራጮች አማካኝነት ተከናውነዋል።
በበጀት ዓመቱ ከተከናወኑ ዋና ዋና ፕሮጀክቶች መካከል የሚከተሉት በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ፦
· ደንገጎ-ሐረር (ማያ ከተማ) አስፋልት ማንጠፍ
· አዋሽ-ሚሌ መደበኛ ጥገና
· ሐረር-ቦንባስ ወቅታዊ ጥገና ፕሮጀክቶች
የእነዚህ ቁልፍ የትራንስፖርት መስመሮች በመጠገናቸው የተጠቃሚዎችን የጉዞ ጊዜና ወጪ በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ የተቻለ ሲሆን፣ አስተማማኝ የመንገድ ደኅንነትና ምቾትም ተፈጥሯል። ከዚህ በተጨማሪም የሀገሪቱ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ እንዲሆን የጎላ አስተዋጽዖ አድርጓል።
ጽሕፈት ቤቱ ከዋናው የጥገና ሥራ ጎን ለጎን የመሬት መንሸራተት መከላከልና የድንገተኛ አደጋ ምላሽ አሰጣጥን ጨምሮ መጠነ-ሰፊ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በአዲሱ የ2019 በጀት ዓመትም የማሽነሪ፣ የማቴሪያልና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት የመንገድ ጥገና ሥራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛል።
ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት
መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን!
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 793
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 793
መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው ፡፡
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት
መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን!
13 793
ደሎ ሰብሮ - ጃራ - ሼይኽ ሑሴን መንገድ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው
ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (ኢመአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ባሌ ዞን የታሪካዊው ድሪ ሼይኽ ሑሴን መካነ - ቅርስ መዳረሻ የሆነውን የደሎ - ሰብሮ - ጃራ - ሼይኽ ሑሴን መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው።
77 ነጥብ 48 ኪሎሜትር የሚሸፍነው ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት መነሻውን ደሎ ሰብሮ ከተማ አድርጎ እስከ ሼህ ሁሴን የሚዘልቅ ነው።
ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 58.82 በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን 1,592,270,000.00 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ዘጠና ሁለት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ሺህ) ብር የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው ።
የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ዠይጂያንግ ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ቡድን ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ አይዲኮን ኢንፍራስትራክቸር ዴቬሎፕመንት ኮንሰልታንት ኃላ.የተ.የግ ማኅበር እያከናወነው ይገኛሉ።
ቀደም ሲል በጸጥታ ሁኔታ ፣ በወሰን ማስከበር ችግሮች እና በተቋራጭ ለውጥ ምክንያት የግንባታ ሂደቱ መዘግየት አጋጥሞት የነበረ ቢሆንም፤ በኢመአ በኩል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ጥረት ፕሮጀክቱ አሁን ላይ በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች አዎንታዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ለውጥን ያመጣል።
የጊኒር እና ጎሎልቻ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካታ አጓራባች ቀበሌዎችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማስተሳሰር የሕዝብ ለሕዝብ መስተጋብሩን ይበልጥ ያጠናክራል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መጠናቀቅ ቀደም ሲል ይወስድ የነበረውን የ3 ሰዓታት የጉዞ ጊዜ ወደ 1ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በተለይም በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች እንደሚጎበኙት የሚነገርለት የታሪካዊው የድሪ ሼይኽ ሑሴን ባሌ መዳረሻ እንደመኾኑ፣ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለጎብኝዎች ምቹ ሁኔታ ይፈጠራል።
ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት
መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን!
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 793
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን 21 ሺህ የሚጠጉ ችግኞችን በጋራ ተከለ
ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (ኢመአ) ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ ብሔራዊ መርሃ-ግብር ላይ አሻራውን አኑሯል። አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 800,000 ችግኞችን ለመትከል አቅዶ በዋና መሥሪያ ቤትና የመንገድ ፕሮጀክቶች ባሉበት ቦታዎች ሁሉ ለመትከል በያዘው ዕቅድ መሠረት፤ ከሳምንት በፊት 3,000 ችግኞችን መትከሉ ይታወቃል። የዛሬው ተሳትፎም የዚሁ አጠቃላይ የክረምት መርሃ-ግብር አካል ሲሆን፤ አስተዳደሩ ከተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ጋር በመሆን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ልዩ ስሙ «ገበያ» በሚባለው ስፍራ ወደ 21 ሺህ የሚጠጉ ችግኞችን በጋራ ተክሏል።
ይህ ተቋማዊ የተቀናጀ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ከተሞች ይስተዋሉ የነበሩ የጥራት፣ የእቅድ እና የተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭነት ችግሮችን ለመቅረፍ የተያዘውን ሀገራዊ ራዕይ ለማገዝ የተከናወነ መሆኑ ተገልጿል። በመረሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል አብዛኞቹ የሀገሪቱ ከተሞች በዝቅተኛ ጥራት የተገነቡ እና ለጎርፍ አደጋ የተጋለጡ በመሆናቸው ለዜጎች ምርታማ ህይወት አመቺ አልነበሩም። ሆኖም ላለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጁ የአረንጓዴና ተፋሰስ ልማት ፕሮጀክቶች ለከተሞች ሳንባ የሚሆኑ አረንጓዴ ቦታዎችን ማስፋፋት፣ ወንዞችን መታደግና የጎርፍ ተጋላጭነትን በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ ተችሏል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ባለፉት 5 ዓመታት ብቻ ከ40 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለው የ90 በመቶ የጽደቅ ስኬት የተመዘገበ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የደን ሽፋን እ.አ.አ በ2018 ከነበረበት 17.2% በ2023 ወደ 23.6% አሳድጎታል። በተመሳሳይ መልኩ የዋና ከተማዋ የአዲስ አበባ የደን ሽፋን ከ11% ወደ 20% ማደጉን ያነሱት ክብርት ሚኒስትሯ፤ እኚህ ስራዎች የተፈጥሮ መልክዓ ምድሮች የከተማ እና የመሠረተ ልማት እቅድ አካል ወደሆኑበት ሥነ ምኅዳራዊ (ecological) የከተማ ንድፍ እየተደረገ ላለው ሽግግር ሕያው ማሳያዎች መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና የሌሎች ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች በዕቅዳቸው መሠረት የክረምት መርሃ-ግብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ፤ የተተከሉትን ችግኞች በቀጣይነት የመንከባከብ ሥራን በማጠናከር እንዲሁም የመንገድ መሠረተ ልማቶች የአካባቢን ስነ-ምህዳር ባገናዘበ መልኩ እንዲገነቡ በማስቻል ከተሞችን ለመኖር ምቹ የማድረግ ራዕይን ለማሳካት ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል።
13 793
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሠራተኞች እና አመራሮች አረንጓዴ እሻራቸውን አኖሩ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20/2018 (ኢመአ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሠራተኞች እና አመራሮች 75አመታት ኢትዮጵያን በመንገድ ያስተሳሰረ ጉዞ በሚል መሪ ቃል ዛሬ ለስምንተኛ ጊዜ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
ተቋማችን የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት በተለያዩ መርሃ-ግብሮች እያከበረ መሆኑ ይታወቃል። የዛሬው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብርም የዚሁ ክብረ-በዓል አካል ነው።
የዋናው መስሪያ ቤት ፤ የዓለም ገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት የቃሊቲ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በመሆን በጣፎ አደባባይ -ለገዳዲ -ኩራጅዳ (15ኪሜ) የመንገድ ፕሮጀክት ላይ አሻራቸውን አሳርፈዋል።
በተመሳሳይ ተቋማችን ባሉት 11 ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላት እንዲሁም በ25ቱ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች ችግኞች ተተክለዋል።
ተቋማችን የተመሠረተበትን 75ተኛ ዓመት በማስመልከት በዘንድሮ ዓመት በሁሉም አካባቢ ከ75 ሺህ በላይ ችግኞችን መትከሉ ለተቋሙ ልዩ መርሐግብር ሆኗል ።
ኢመአ ባለፋት ስምንት ዓመታት ሀገራዊ አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የተቋሙን መላውን ሰራተኛ በማሳተፍ ሀላፊነቱን መወጣቱን ቀጥሏል።
የተቋሙ ሰራተኞች አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ መሆኑን ተረድተው ሀገራዊ ባህል ተሳትፎና ንቃታቸው በማደጉ ደስተኞች መሆናቸውን የተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ገልፀዋል ።
የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።እንደ ተቋም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግ ግብረ -ሀይል በመቋቋሙምም የመጽደቅ ምጣኔው አጥጋቢ ውጤት እንዲገኝ ማስቻሉ ተገልጿል።
በተለይም የመንገድ ግንባታን ተከትሎ በደኖች ላይ ጉዳት እንዳይከሰት መጠንቀቅ መቻሉ ፤ የዲዛይን ስራዎችን ታሳቢ አድርጎ ቀድሞ መስራቱ እንዲሁም ተቋራጮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የችግኝ ተከላ መርሃ -ግብርን አጠናክረው መቀጠላቸው በአካባቢ ጥበቃ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር እንደሆነ ተገልጿል ።
ኢትዮጵያን የማገናኘት 75 ዓመታት
መንገዳችን፤ ኃላፊነታችን!
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 793
ባለፉት ሰባት አሥርተ ዓመታት ውስጥ ተቋሙ የኢትዮጵያን ገጠር ከከተማ፣ አምራቹን አርሶ አደር ከገበያ በማስተሳሰር ረገድ የከፈለው በዋጋ የማይተመን መሥዋዕትነትና የጀግንነት ታሪክ የታየበት ነው። በምስረታው ወቅት ከነበረበት ውስን አቅም ተነስቶ ዛሬ ላይ የሀገራችንን ገጽታ የሚቀይሩና ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ታላላቅ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የማከናወን ብቃት ላይ መድረሱ የሁላችንም ኩራት ነው።
ጫልቱ ሳኒ
የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚኒስትር
13 793
“የዛሬው ክብረ በዓል መንገድ መሠረተ ልማታችን ከየት ተነስቶ የት ደረሰ የምንቃኝበት ብቻ ሳይሆን፤ የወደፊቱን የመንገድ ልማት አቅጣጫ የምንወስንበትም ነው።”
ዶ/ር እዮብ ተካልኝ
የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የቦርድ ሰብሳቢ
13 793
"በቀጣዮቹ ዓመታት ትኩረታችን መንገዶችን በብዛት መገንባት ብቻ ሳይሆን፣ በጥራት፣ በዘላቂነት፣ በደኅንነት፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በዘመናዊ የንብረት አሥተዳደር መርሆዎች ላይ በተመሠረተ የመንገድ ልማት ላይ ያተኮረ ይሆናል።" :-
ኢንጅነር መሐመድ አብዱራሕማን
የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ዋና ዳይሬክተር
