fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 540 مشترک است و جایگاه 8 340 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 161 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 540 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 1 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.98% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.34% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 882 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 539 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 540
مشترکین
-424 ساعت
-147 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በሊጉ ነጥብ ተጋርቷል ………///……. በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ትናንት በተከናወነው ጨዋታ የምድቡ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪነቱን ማጠናከር የሚችልበትን አጋጣሚ ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡ ከሃላባ ከተማ ጋር በሐዋሳ የተጫወተው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያለምንም ጎል ባዶ ለባዶ ተለያይቷል፡፡ በጋለ የጨዋታ ስሜት በጀመረው በዚህ ጨዋታ ሀላባ ከተማ በመጀመሪያዎቹ አስር ደቂቃዎች የጨዋታ ብልጫ መውሰድ የቻለ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በበኩሉ መሪነቱን ለማጠናከር በመልሶ ማጥቃት በጥሩ ኳስ ቅብብል ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ ክልል ሲገቡ ተስተውሏል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ44ኛው ደቂቃ በአቤል ሀብታሙ አማካኝነት አደገኛ ሙከራ ያደረገ ሲሆን ከመስመር የተሻገረውን ኳስ በግንባሩ ገጭቶ ለማስቆጠር ያደረገውን ሙከራ የግቡ አግዳሚ መልሶበታል። ከዕረፍት መልስ ኢትዮ ኤሌክትሪክ የሀላባን ቁጥር ማነስ በመጠቀም ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ መድረስ ቢችልም ሙሉ በሙሉ ሲከላከል የዋለውን የሀላባን ተከላካይ መስመር አልፎ ግብ ማስቆጠር አልቻለም። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ምንም እንኳ ነጥብ ቢጥልም በ32 ነጥብ ከተከታዩ አዲስ አበባ ከተማ በስድስት ነጥብ ርቆ የከፍተኛ ሊጉን እየመራ ይገኛል፡፡ የሃላባ ተጫዋች የሆነው አብዱልከሪም ራህማቶ በአቤል ሀብታሙ ላይ በሰራው ከባድ ጥፋት በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ተወግዷል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

የፕሮጀክቱን ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ……....///…….... የደብረታቦር ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ እንደተናገሩት የፕሮጀክቱ ግንባታ ሥራ አጠቃላይ አፈፃፀም 45 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል። የስዊችያርድ ዕቃዎች፣ የመቆጣጠሪያ ክፍል፣ የትራንስፎርመር ማስቀመጫና የሽቦዎች መቅበሪያ ጉድጓዶች የመሠረት ሥራዎች እንዲሁም ትራንስፎርመር የማስቀመጥ፣ የብረት ተከላና የአጥር ሥራዎች መጠናቀቃቸውን አቶ ቴዎድሮስ ገልፀዋል። የመቆጣጠሪያ ክፍል የኮንክሪት ሙሌት፣ የባዝባር ዝርጋታ፣ የኢንሱሌተር ማስቀመጥ እና የመኖሪያ ቤት ግንባታዎችንም ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል። የ4 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች የቁፋሮ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው 100 ነጥብ 8 ሜጋ ዋት ኃይል የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች፣ 10 ባለ 15 እና 10 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት አቶ ቴዎድሮስ ገልፀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሪዚደንት መሐንዲስ አቶ ሀብታሙ ተሾመ በበኩላቸው ከ80 በመቶ በላይ የማከፋፈያ ጣቢያ ዕቃዎችን የማምረት ሥራ ተጠናቆ ከ60 በመቶ በላይ ሳይት ላይ መድረሱን ተናግረዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለደብረታቦር ከተማና በአቅራቢዋ ላሉት ከተሞች አስተማማኝ ኤሌክትሪክ እንደሚያቀርብ አቶ ቴዎድሮስ ጠቅሰዋል። ፕሮጀክቱ ከፀጥታና ከዕቃ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ችግሮች እያጋጠሙት ቢሆንም በከፍተኛ የሥራ ተነሳሽነትና ሞራል በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የደብረታቦር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከ160 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በጣቢያው የኃይል ምርትን አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……...///…….. የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫን የኃይል ምርቱን አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጣቢያው የጥገና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ሐፍቱ እንደገለፁት በተያዘው በጀት ዓመት ደረጃቸውን የጠበቁ የቅድመ መከላከል የጥገና ሥራ ለማከናወንየሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቷል። በጣቢያው ሳምንታዊና ወርሃዊ የፍተሻና ጥገና ሥራዎችን በተሻለ አፈፃፀም ለመከወን የሚያስችሉ የአሰራር ሥርዓቶች መዘርጋታቸውንም ነው አቶ መብራቱ የጠቆሙት። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የእያንዳንዱን የተርባይን ዩኒት ችግሮችን ለመለየትና ሶፍትዌሮችን በመጠቀም መፍትሔዎችን ለመስጠት የሚያግዙ የትግበራ ዕቅዶች በማዘጋጀት ዘመናዊ የጥገና አሰራሮችን ለመከተል እየተሞከረ ነው። በአሁኑ ወቅት በጣቢያው የአብዛኛው ዩኒት መቆጣጠሪያ ፕሮግራም የመሙላት፣ ከአገልግሎት ውጪ የነበሩ የሲስተም ካርዶችን ለዩኒቶቹ በሚያመች መልኩ ወደ ሥራ የማስገባት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። ለዓመታት በንፋስ ማመንጫ ተርባይኖችና በማከፋፈያ ጣቢያው መካከል ተቋርጦ የቆየውን የኮሙዩኒኬሽን ኔትወርክ በመጠገን ዳግም ወደ ሥራ እንዲገባ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል። ጣቢያው በየደረጃው ለሚገኙ ሠራተኞች የተለያዩ የክህሎት ማሳደጊያ መርሃግብሮችን በማዘጋጀት የሥራ ላይ ሥልጠናዎችን በመስጠት ላይ እንደሚገኝም ነው አቶ መብራቱ የገለፁት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 02 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ………..///…….... የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን የማመንጨት አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን የጣቢያው የጥገና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ተወካይ ኃላፊ አቶ ፀጋይ አፅብሃ እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በሁለት ዩኒቶች 120 ሜጋ ዋት እያመነጨ ነው። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የኦፕሬሽን፣ የጥገና እና የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት በርካታ ሥራዎች እየሰሩ እንደሆነም ተናግረዋል። ጣቢያው ተቋሙ በዘረጋው ኤስ.ኤ.ፒ በተባለ ዘመናዎ ሥርዓት አማካይነት የጥገናና የኦፕሬሽን መተገበሪያ ሞጁል ለመጠቀም እንቅስቃሴ መጀመሩን የጠቆሙት ተወካዩ የማመንጫ ዩኒቶችን የኦፕሬሽን አቅም ለማዘመን የሚያስችሉ ተግባራት ከቻይናው ዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ኩባንያ ጋር በጥምረት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በጣቢያው የቅድመና ድህረ ጥገና ሥራዎች እየተካሔዱ ቢሆንም የማመንጫ ዩኒቶቹ በተደጋጋሚ ብልሽት ስለሚያጋጥማቸው በጥገና ሠራተኞች ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠሩ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ባለፉት 8 ወራት በኃይል ማመንጫው ዩኒት አንድ፣ ሁለት እና አራት ላይ የጥገና ሥራዎችን በማከናወን ዳግም ወደ ኦፕሬሽን የመመለስ ሥራዎች ቢሰሩም በአሁኑ ወቅት ግን ሁለት ዩኒቶች ብቻ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የመልሶ ግንባታ ሥራዎች በቅርቡ ይከናወናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው ተወካይ ኃላፊው ያስታወቁት። ጣቢያው የሚያጋጥሙትን የመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት ለመቅረፍ በሂደት ላይ መሆኑን የገለፁት አቶ ፀጋይ የተበላሹ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በሀገር ውስጥ እንዲጠገኑ በማድረግ የወጪ ቅነሳ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም አብራርተዋል። የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአራት ዩኒቶች 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ባለ ጥምር ቅስት ቅርፅ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 02 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

የንፋስ ኃይል ማመንጫው ከ3 ዓመት በኋላ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል ………...///…….... የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከሦስት ዓመት በኃላ ዳግም ኤሌክትሪክ ማመንጨት መጀመሩን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ካህሰ ፀሐይ እንደገለፁት በአካባቢው ተከስቶ በነበረው የእርስበርስ ግጭት ሳቢያ የንፋስ ኃይል ማመንጫው ላለፉት ሦስት ዓመታት ሙሉ በሙሉ ኤሌክትሪክ ሳያመርት ቆይቷል። በዚህ የተነሳ የንፋስ ኃይል ማመንጫው ዩኒቶች ባለፉት ሦስት ዓመታት አገልግሎት ባለመስጠታቸው የተርባይን ዩኒት ባትሪዎችና ዋና የመቆጣጠሪያ ክፍል (Galileo) ዕቃዎች፣ የማከፋፈያ ጣቢያ ባትሪ ቻርጀር፣ የዘይትና ግሪስ ፈሳሾች ላይ ጉዳት መድረሱን አቶ ካህሰ ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በጣቢያው ላይ እየተከናወኑ በሚገኙ የጥገና ሥራዎች ሳቢያ በአማካይ እስከ 24 ነጥብ 4 ሜጋ ዋት ድረስ ማመንጨት መቻሉን ኃላፊው ጠቁመዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያው 54 ባለ ሦስት እና 30 ባለ ሁለት ክንፍ የንፋስ መቅዘፊያ ያላቸው ተርባይኖች እንዳሉት የጠቆሙት አቶ ካህሰ በ22 የባለ ሦስት ክንፍ የንፋስ መቅዘፊያ ተርባይኖች ላይ የጥገና ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት ተጨማሪ 5 የባለ ሦስት ክንፍ የንፋስ መቅዘፊያ ተርባይኖችን ወደ ሥራ ለማስገባት የፍተሻና የጥገና ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አመላክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የመለዋወጫ ዕቃዎች በግዥ ሒደት ላይ መዘግየታቸው፣ የሰው ኃይልና የተሽከርካሪ እጥረት ማጋጠሙ እንዲሁም የውሃ አቅርቦት ችግር መፈጠሩ በኦፕሬሽና ጥገና ሥራዎች ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደራቸውን ተናግረዋል። እንደ ኃላፊው ገለፃ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት እንዲችል የተቋሙ ሥራ አመራርና የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል። የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 120 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ የተደረገውም በ2006 ዓ.ም ነበር። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ለተቋምና ለሀገር ዕድገት ሴቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ተጠየቀ ---------//-------- በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን ዘርፍ የማዕከላዊ 1 ሪጅን ሠራተኞች ዓለም ዓቀፉን የሴቶች ቀን በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አከበሩ፡፡ ዕለቱ “ሴቶችን እናብቃ፣ ልማትና ሰላም እናረጋግጥ” በሚል መሪ ቃል ሲከበር የተቋሙ የሴቶች እና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሌንሴ ኤዴኤ ባስተላፉት መልክዕክት ሴቶች ሦስት ተደራራቢ ኃላፊነት ቢኖርባቸውም እችላለሁ በሚል መንፈስ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ ሴቶች ራሳቸውን ለማብቃት በመጣር የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡም አሳስበዋል። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወ/ማርያም በበኩላቸው ሴቶች ራሳቸውን በማብቃት እና ተወዳዳሪ ሠራተኛ በመሆን ለተቋምና ለሀገር ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሴት ሠራተኞች ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የተገኘው የዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤታማ ነው ……..///……… ከአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እየተገኘ ያለው የዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግግር ውጤታማ መሆኑን በፕሮጀክቱ የተሳተፉ የሥራ ኃፊዎችና ሠራተኞች ተናገሩ፡፡ የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪጅ አቶ ፍቃዱ አብርሃም እንደተናገሩት የተቋሙ ሠራተኞች ከሥራ ተቋራጩ ባለሙያዎች ጋር አብረው እንዲሰሩ በማድረግ እና ስልጠናዎችን በማመቻቸት የዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እየተደረገ ነው፡፡ በፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ተቆጣጣሪ አቶ ደረጀ ጣሰው በበኩላቸው የኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች ከሥራ ተቋራጩ ባለሙያዎች ጋር አብረው በመስራታቸው በተርባይን መትከያ የመሠረት ሥራዎችና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ልምድ እንደቀሰሙ አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የንፋስ ተርባይኖቹ የመሰረት ግንባታ ሥራ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች እየተከናወነ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት፡፡ የፕሮጀክቱ የመሰረት ግንባታ ሥራ በራስ አቅም መከናወኑ የተቋሙን ሠራተኞች ክህሎትና ልምድ ለማጎልበት ከማገዙም ባለፈ በቀጣይ በቴክኖሎጂ በመታገዝ በራስ አቅም የተርባይን ተከላ የሚያከናውኑ ሠራተኞችን ለማፍራት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ንዑስ ሥራ ተቋራጭ የራማ ኮንስትራክሽን ፎርማን የሆኑት አቶ ወደፊት ፀሐዩ በግንባታ የሥራ ዘርፍ ላይ ከ20 ዓመታት በላይ መስራታቸውን ገልፀው የዚህ ሥራ በአሰራርና በቴክኖሎጂ እስካሁን ከሰሩት የተለየ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ወደፊት ገለፃ እስካሁን ከተከናወኑ የመሰረት ሥራዎች ሁለቱ ከሥራ ተቋራጩ ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት የተሰሩ ሲሆን ቀሪዎቹ 13ቱ የመሠረት ግንባታ ሥራዎች ግን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያዊያን የተከናወኑ ናቸው፡፡ ፕሮጀክቱ በሚገነባበት የአጤ አንዶዴ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑትና በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት አቶ ሙላት ይገዙ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በንፋስ ኃይል ማመንጫ ማማ የመሰረት ግንባታ ምንም ልምድ እንዳልነበራቸው አንስተዋል፡፡ ይሁንና ከሥራ ተቋራጩ ባለሙያዎች ጋር በመስራታቸው በዘርፉ ያገኙት ዕውቀትና ልምድ በቀጣይ ለሚከናወኑ ሥራዎች አቅም እንደፈጠረላቸው ገልፀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የሸዋ ሮቢት ኮምቦልቻ መስመር ተጠግኖ ወደ አገልግሎት ተመልሷል ……..///…….. የደብረ ብርሃን 2 - ሸዋ ሮቢት - ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ ማምሻውን ሥራ መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንዳስታወቁት በሸዋ ሮቢት አቅራቢያ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገኑ ካለፈው እሁድ ጀምሮ ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ የአፋር መዲና ሠመራን ጨምሮ በሰሜን ምሥራቅ የሚገኙ ከተሞች ዳግም ኃይል አግኝተዋል። በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የሪል ታይም ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት እንግዳ በበኩላቸው በአሁኑ ሰዓት ኤሌክትሪክ ተቋርጦባቸው የቆዩት ሁሉም የሰሜን ምሥራቅ ከተሞች ኤሌክትሪክ ዳግም ማግኘታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የሦስት የንፋስ ተርባይኖች ተከላ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል ……..///…….. በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከሚተከሉ 29 ተርባይኖች መካከል የሦስቱ ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ፍቃዱ አብርሃም እንደገለፁት 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 465 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 ተርባይኖች አሉት፡፡ 50 በመቶ የሚሆኑት የንፋስ ተርባይንና የጀነሬተር አካላት እንዲሁም 99 በመቶ ለማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ የሚያስፈልጉ ዕቃዎች ሳይት መድረሳቸውን አቶ ፍቃዱ አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ ፍቃዱ ገለፃ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ 48 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው 4 ነጥብ 9 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን አጠቃላይ አፈፃፀሙ ደግሞ 50 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ተቆጣጣሪ አቶ ደረጄ ጣሰው በበኩላቸው የ12 የንፋስ ተርባይን ማማ መትከያ የመሰረት ሥራዎች የኮንክሪት ሙሌት ሲጠናቀቅ የሦስቱ የብረት ሥራ ተጠናቆ ለኮንክሪት ሙሊት ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አንድ የመሰረት ሥራ ለማጠናቀቅ 32 ሺ ኪሎ ግራም ብረት እና ከ120 ሺ ኪሎ ግራም በላይ ሲሚንቶ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡ እንደ ተቆጣጣሪ መሀንዲሱ ገለፃ የአንድ ምሰሶ የመሰረት ሥራ ለማከናወን ከሰባት እስከ 12 ቀናት የሚወስድ በመሆኑ ቀሪ የመሰረት ሥራዎች በቀጣዮቹ አስር ወራት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ በኢተያ ከተማ አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ሀገሪቱ ከንፋስ የምታገኘውን የኤሌክትሪክ ኃል ወደ 544 ሜጋ ዋት ያሳድገዋል፡፡ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የግንባታ ሥራ ሲመንስ ጋሜሳ በተሰኘ ኩባንያ በመከናወን ላይ ሲሆን ለግንባታው 145 ሚሊዮን ዩሮ በጀት ተይዞለታል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የክለቡ አባላት የህፃናት ልብ ህክምና ማዕከልን ለመርዳት ቃል ገቡ ………///……… የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚገኘውን የኢትዮጵያ ህፃናት ልብ ህክምና ማዕከልን ጎብኝተዋል። የክለቡ አባላት ማዕከሉ ለህክምና አገልግሎት የሚጠቀምባቸውን የፅኑ ህሙማን ክፍል፣ የራጅ እና ኤሲጂ፣ የቀዶ ጥገናና የደም ባንክ ክፍሎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። በህክምና ላይ የሚገኙ ህፃናትን የጠየቁት የቡድኑ አባላት ህፃናቱ በቶሎ አገግመው ወደ ጤናማ ኑሯቸው እንዲመለሱ በመመኘት አበረታተዋቸዋል። መላው የቡድኑ አባላትበ 6710 የአጭር መልዕክት መላኪያ ቁጥር መልዕክት በመላክ በየቀኑ አስተዋፅኦ ማድረግ ጀምረዋል። የአንድ ህፃን የልብ ቀዶ ህክምና በትንሹ እስከ 3 መቶ ሺ ብር ወጪ እንደሚጠይቅ የተገነዘቡት የቡድኑ አባላት ሌሎችንም በማስተባበር የአንድ ህፃን የልብ ቀዶ ጥገና ወጪ ሙሉ በሙሉ ለመሸፈን ቃል ገብተዋል። የልብ ህፃናት ማዕከሉ በስመ ጥሩ ዶክተር በላይ አበጋዝ በ1984 ዓ.ም የተመሠረተ ሲሆን በእስካሁኑ ጉዞው የበርካታ ህፃናትን ህይወት መታደግ ችሏል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም