fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 692 مشترک است و جایگاه 8 014 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 155 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 692 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 145 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 31.28% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.96% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 909 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 661 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 31 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 692
مشترکین
+224 ساعت
+187 روز
+14530 روز
آرشیو پست ها
በበጀት ዓመቱ ውሳኔ ካገኙ የፍትሀብሔርና የሥራ ክርክሮች ከ806 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ‎………///…… ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ስድስት ወራት በፌዴራልና በክልል ፍርድ ቤቶች
በበጀት ዓመቱ ውሳኔ ካገኙ የፍትሀብሔርና የሥራ ክርክሮች ከ806 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ‎………///…… ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ስድስት ወራት በፌዴራልና በክልል ፍርድ ቤቶች ክርክር ካካሄደባቸው የፍትሀብሔርና የሥራ ክርክር መዝገቦች ከ806 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን ገለፀ፡፡ ‎ ‎በተቋሙ የሕግ አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ መስከረም በቀለ እንደገለፁት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በተቋሙ ውስጥ ግልጽ እና ወጥ የአሰራር ሥርዓት እንዲዘረጋ በማድረግ እንዲሁም ክስ የመርታት አቅምን በማሳደግ የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል፡፡  ‎  ‎በዚህም በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ደረጃ ላይ የሚገኙ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር የገንዘብ መጠን ያላቸው 244 የፍትሀብሔር መዝገቦች ላይ ክትትል ሲደረግ መቆየቱንና 73 መዝገቦች ላይ ውሳኔ መሰጠቱን አንስተዋል፡፡ https://www.eep.com.et/?amh-news=በበጀት-ዓመቱ-ውሳኔ-ካገኙ-የፍትሀብሔርና&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተሰራ ነው .......///....... በደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች እና በዙሪያቸው ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጥያቄ በዘላቂነት ለመመለስ እየተሰራ መሆ
+5
የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተሰራ ነው .......///....... በደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች እና በዙሪያቸው ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጥያቄ በዘላቂነት ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጂኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደተናገሩት በሪጅኑ ውስጥ አምስት ባለ 132 እና ሦስት የባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 973 ነጥብ 68 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮች ይገኛሉ፡፡ በሪጅኑ በደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች እና አካባቢያቸው ያለው  የኃይል ፍላጎት ከፍተኛ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦት-ጥያቄዎችን-ለመመለስ-እ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የኒውክሌር ኮሚሽንን ለማጠናከር የሚያስችል ድጋፍ እያደረገ ነው .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተቋቁሞ ወደ ሥራ የገባውን የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽንን ለማጠናከር የሚያስችል የገንዘብ እና የዓይነት ድጋፍ ማድረጉን በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ገለፀ፡፡ የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት ኮሚሽኑ የሚያከናዉነው ሥራ እንደ ሀገር ብሎም ተቋም ያለውን የኢነርጂ ፍላጎት ለማሟላት ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ ኮሚሽኑ ለሚያከናውነው ሥራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅበት በመንግስት አቅጣጫ መሰጠቱን ያነሱት አቶ ደመረ ይህን ተከትሎም ተቋሙ ለኮሚሽኑ ሥራ መነሻ የሚሆን የዓይነትና የገንዘብ ድጋፎችን ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ ተቋሙ ምንም እንኳን ከፍተኛ ፕሮጀክቶችን እየመራና እያስተዳደረ የሚገኝ ቢሆንም በቀጣይ የሚገኘውን ጥቅም ለማስጠበቅ የፋይናንስ አቅሙን ባገናዘበ መልኩ የግማሽ ቢሊየን ብር እና ከ67 ነጥብ 21 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገዙ ሁለት ዘመናዊ ተሸከርካሪዎችን ድጋፍ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡ የገንዘብ ድጋፉ ከዚህ በፊት ለኮሚሽኑ የተሰጠ ሲሆን ተሸከርካሪዎችን ደግሞ በትላንትናው ዕለት ማስረከብ ተችሏል ነው ያሉት፡፡ እንደ አቶ ደመረ ገለፃ ተቋሙ የፋይናንስ ችግሩን ተቋቁሞ ለኮሚሽኑ ያደረገው ድጋፍ ኮሚሽኑ የሚያከናውናቸውን ሥራዎች በማሳለጥ የተቋቋመበትን ዓላማ ከማሳካት ባለፈ እንደ ሀገር ያለውን የኢነርጅ ፍላጎት ለማሟላት ያግዛል፡፡ በቀጣይ ተቋሙ የፋይናንስ አቅሙን መሰረት ባደረገ መልኩ ለኮሚሽኑ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑንም ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አረጋግጠዋል። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጷጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምርቃ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር “ኢትዮጵያ የህዳሴን ግድብ የሚተካከል ለሰላማዊ ዓላማ ብቻ የሚውል የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ በቅርቡ ሥራ ትጀምራለች” ማለታቸው ይታወሳል፡፡ ዕቅዱን ለማሳካትም ከሩሲያ ጋር ከተደረገው የኒውክሌር ኃይል የድርጊት መርሃ ግብር ስምምነት በተጨማሪ ከኒውክሌር ኃይል የማመንጫ ሥራ የዓለም አቀፍ የህግ እና የቁጥጥር ማዕቀፎችን በተከተለ መልኩ እንዲፈፀም ለማድረግ የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን በቅርቡ ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወቃል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

የማከፋፈያ ጣቢያው ለኢንዱስትሪዎች መመስረት እና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የጎላ ሚና አለው …….///……. የኮምቦልቻ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ እና በአካባቢው ለሌሎ
+6
የማከፋፈያ ጣቢያው ለኢንዱስትሪዎች መመስረት እና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የጎላ ሚና አለው …….///……. የኮምቦልቻ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ እና በአካባቢው ለሌሎች ኢንዱስትሪዎች መመስረት እንዲሁም ለሥራ ዕድል ፈጠራ መሰረት የጣለ መሆኑን የኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙስጠፋ ጀማል እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው ለፋብሪካው የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በመገንባቱ ፋብሪካው እና ማከፋፈያ ጣቢያዉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ ፋብሪካዉ በተለያየ ጊዜያት የማስፋፊያ ሥራ ባከናወነበት ወቅት የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከጣቢያው ሲያገኝ መቆየቱን በመጠቆም አሁን ላይም 6 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ኃይል እየተጠቀመ እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያው-ለኢንዱስትሪዎች-መመ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያው ለኢንዱስትሪዎች መመስረት እና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የጎላ ሚና አለው …….///……. የኮምቦልቻ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ እና በአካባቢው ለሌሎ
+6
የማከፋፈያ ጣቢያው ለኢንዱስትሪዎች መመስረት እና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የጎላ ሚና አለው …….///……. የኮምቦልቻ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ እና በአካባቢው ለሌሎች ኢንዱስትሪዎች መመስረት እንዲሁም ለሥራ ዕድል ፈጠራ መሰረት የጣለ መሆኑን የኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙስጠፋ ጀማል እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው ለፋብሪካው የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በመገንባቱ ፋብሪካው እና ማከፋፈያ ጣቢያዉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ ፋብሪካዉ በተለያየ ጊዜያት የማስፋፊያ ሥራ ባከናወነበት ወቅት የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከጣቢያው ሲያገኝ መቆየቱን በመጠቆም አሁን ላይም 6 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ኃይል እየተጠቀመ እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያው-ለኢንዱስትሪዎች-መመ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግደብን ስትገነባ ምንም ዓይነት የውጭ እርዳታም ሆነ ብድር አልወሰደችም ……..///……. ኢትዮጵያ የታላቁ ኢትዮጵ ህዳሴ ግደብን ስትገነባ ምንም ዓይነት የውጭ እርዳታም ሆነ ብድር አለመውሰዷን የኢፌዲሪ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር አረጋገጡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሲሰጡ እንደተናገሩት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግደብ ግንባታ ኢትዮጵያ ምንም ዓይነት የውጭ እርዳታም ሆነ ብድር አልወሰደችም፡፡ በቅርቡ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ለግድቡ ማን እንደከፈለ ታውቃላችሁ? ዩናይትድ ስቴትስ” ሲሉ በዋይት ሐውስ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ስልጣን የመጡበትን አንደኛ አመት አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት መናገራቸው ይታወሳል፡፡ በዛሬው ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ታዲያ ”በህዳሴ ላይ አንድም ብር እርዳታ፣ አንድም ብር ብድር ኢትዮጵያ አልወሰደችም” ብለዋል፡፡  ”በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ቁርጠኛ አቋም በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም ያሉ ኢትዮጵያውያን በቁርጠኝነት ጨክነው በጋራ ቆመው ስለሰሩ የተከወነ ፕሮጀክት ነው” ሲሉም አክለዋል:: ”ህዳሴን ካለ አንድ ብር እርዳታ፣ ካለ አንድ ብር ብድር ያሳካ መንግስት ፕሮጀክት አይሰራም ሊባል አይችልም ግፍ ነው” ሲሉ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሌሎች ትልልቅ ፕሮጀክቶችም እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

በኢትዮጵያ በመንግስት እና የግል አጋርነት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሊገነቡ ነው …...///…... በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመንግሥትና የግል አጋርነት ዘርፍ (Public- Private Par
በኢትዮጵያ በመንግስት እና የግል አጋርነት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሊገነቡ ነው …...///…... በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመንግሥትና የግል አጋርነት ዘርፍ (Public- Private Partnership) የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ሊከናወን ነው። ‎የኢትዮጵያ መንግስት ከዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት ጋር ሁለት የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ለመገንባት የ400 ሚሊዮን ዶላር ሥምምነት ተፈራርሟል። ‎ሥምምነቱ 198 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የሁርሶ- አይሻ ባለ 400 ኪሎ ቮልት እና 206 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን የደገሃቡር- ቀብሪድሃር ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ለመገንባት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በኢትዮጵያ-በመንግስት-እና-የግል-አጋርነ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ከማከፋፈያ ጣቢያው የሚፈልገውን ኃይል እያገኘ መሆኑን ፋብሪካው ገለፀ .......///........ ከኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለምርት ሂደቱ የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑ
+9
ከማከፋፈያ ጣቢያው የሚፈልገውን ኃይል እያገኘ መሆኑን ፋብሪካው ገለፀ .......///........ ከኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለምርት ሂደቱ የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን የአማር ቁጥር አንድ የከረጢትና ፕላስቲክ ማምረቻ ፋብሪካ አስታወቀ፡፡ የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ እንየው ጌትነት (ዶ/ር) እንደተናገሩት ፋብሪካው የፕላስቲክና የአግሮ ባግ ከረጢቶችን እያመረተ ይገኛል፡፡ ፋብሪካው ለብቻው በተዘረጋለት መስመር በቀጥታ ከማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ እንደተቀረፈ ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… ‎https://www.eep.com.et/?amh-news=ከማከፋፈያ-ጣቢያው-የሚፈልገውን-ኃይል-እ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዕድገት በጋራ ማደግ መርህ ላይ የተመሰረተ ነው _ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ....///.... የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዕድገት ጎረቤት ሀገራትን የሚጎዳ ሳይሆን በጋራ የማደግ መርህ ላይ የተመሠረተ መሆኑን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒሰትር  ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍን በመረቁበት ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ  የምትገነባው የአረንጓዴ ኢነርጂ አካባቢን የማይጎዳ እና ለመላው አፍሪካ የመጣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ብስራት ነው። ከ21ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በኋላ የኤሌክትሪክ  ኃይል ዕድገትን  ያረጋገጡ ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ቢያመጡም በነበረው የኢነርጂ አመራረት ችግር ምክንያት በተፈጥሮ ላይ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ ያለፈ ዕድገት እንደነበራቸው አንስተዋል። በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ ዕድገት እንዲመጣ ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ ንጹህ ኢነርጂ ማምረት እንደሚገባ በአፅንኦት ተናግረዋል። ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ ግርማ ሞገስና የመቻል ተምሳሌት መሆኑን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ህዝቦች ከፈለጉና ከወደዱ እንዲሁም ከተደመሩ ግዙፍ ሥራ ጀምረው መጨረስ እንደሚችሉ ያሳየ የንፁህ ኢነርጂ ፕሮጀክት ነው ብለዋል ። ግድቡ በኢትዮጵያውያን ታስቦ በኢትዮጵያውያን ሀብት ብቻ የተገነባ ለመላው አፍሪካ የምሳሌነት ምልክት እንደሆነም ነው የገለጹት  ። ኢትዮጵያ ከተለያዩ የታዳሽ ኃይል ምንጮች የምትገነባቸው ፕሮጀክቶች የወደፊቱን የአፍሪካ ዘመን ዕድገት ለማረጋገጥ አብዛኛው በንጹህ ኢነርጂ ላይ ያተኮረ መሆን እንዳለበት ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የምታካሂዳቸው የንጹህ ኢነርጂ ኢንቨስትመንቶች ኮፕ 2032 በኢትዮጵያ እንዲዘጋጅና ዓለም አቀፍ እውቅና እንድታገኝ መታሰቡ በአረንጓዴ አሻራ እና በአካባቢ ደህንነት በምትከተለው ፖሊሲ የተገኘ ውጤት መሆኑን አመልክተዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 24 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

‎የኢነርጂ ደህንነት የሀገር ደህንነት ጉዳይ ነው!  ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎....///..... ‎የኢነርጂ ደህንነት የሀገር ደህንነት ጉዳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ። ‎ ‎የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በዛሬው ዕለት በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቋል፡፡ ‎ ‎በዚህ ወቅት ኢንጂነር አሸብር እንደገለጹት ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገር የነበረውን 4 ሺህ ሜጋ ዋት ከእጥፍ በላይ በማሳደግ ከ9 ሺህ 700 ሜጋ ዋት በላይ ማድረስ ተችሏል። ‎ ‎ለዚህም የለውጡ መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረትና የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ድርሻቸው ከፍተኛ ነበር ብለዋል። ‎ ‎የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ መጠናቀቅ እንደ ሀገር የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል በመሆን ቀጣናውን በኤሌክትሪክ ለማስተሳሰር የተያዘውን ግብ አመላካች መሆኑን ገልፀዋል። ‎ ‎ከአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ በተጨማሪ 350 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የሚያስችል ፕሮጀክት ለመገንባት እየተሰራ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር በመንግሥትና በግል አጋርነት 300 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ውል ተፈርሞ ለግንባታ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። ‎ ‎በምስራቁ የአይሻ ኮሪደር ከንፋስ እስከ 9 ሺ ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም መኖሩንም አስገንዝበዋል። ‎ ‎በአሁኑ ወቅት ለኬኒያ፣ ጅቡቲና ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል እየቀረበ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በቀጣይ ከደቡብ ሱዳንና ከሶማሊያ ጋር የኃይል ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎ተቋሙ እንደ አዲስ ከተቋቋመ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱንና የውጭ ምንዛሬ ግኝቱም 247 ሚሊዮን ዶላር መድረሱን ተናግረዋል። ‎ ‎ይህም የአይሻ ሁለት የንፋስ እና የኮይሻ የውሃ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎችን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በፋይናንስ ለመደገፍ እንዳስቻለው ጠቁመዋል። ‎ ‎ክቡር ጠ/ሚኒስትሩ የኢነርጂ ሴክተሩን በማሳደግ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማማ ለማድረግ ለሚሰጡት ቆራጥ አመራር፣ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ ለተሳተፉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

በዛሬው እለት ታሪካዊ የሆነውን የአይሻ-2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በይፋ መርቀን ለአገልግሎት አብቅተናል። በሶማሌ ክልል የሚገኘው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የኃይል ዋስትና የማረጋገጥ ስትራቴጂያችን አንድ የማዕዘን ድንጋይ ነው። ፕሮጀክቱ ዓመታዊ ኃይል የማመንጨት አቅሙ 467 ጊጋ ዋት በሰዓት (GWh) ሲሆን፤ ዘመናዊ የSCADA እና SVG ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለተረጋጋ የኃይል አቅርቦት እና ለቴክኖሎጂ-መራሽ ኢኮኖሚ ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ የአይሻ ስትራቴጄያዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የንፋስ ኮሪደርነቱ ያለፈ ጠቀሜታ አስገኝቶለታል። ለጎረቤት ሀገራት ያለው ቅርበት ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ንግድ ማዕከል ለማድረግ ለተቀመጠው ግብ መሳካት በተግባር የተረጋገጠ ትልቅ እመርታ ነው። በመደመር መርህ የኢትዮጵያን ሰፊ የተፈጥሮ ጸጋ ወደ የጋራ ሐብት በመለወጥ የአፍሪካ ቀንድን  በአካል እና በኢኮኖሚ ይበልጥ ለማስተሳሰር ቁርጠኞች ነን። "ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)"

‎የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ ‎…...///….... ‎ከአዲስ አበባ በ700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሶማሌ ክልል አይሻ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በይፋ ተመረቀ፡፡ ‎ ‎በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣የጅቡቱ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የፌደራል መንግስትና የክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ ‎ ‎የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ከ257 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በ2009 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረ ሲሆን በፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የ32 ተርባይኖች ተከላ፣  30 የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶችና የስዊች ያርድ እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። ‎ ‎በዛሬው ዕለት የተመረቀው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በ32 ተርባይን 80 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ‎ ‎የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ሲጠናቀቅ  የዛሬውን ጨምሮ 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ይኖረዋል። ‎ ‎በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ታሪክ የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዩኒት በአማካሪነት ለመጀመሪያ ጊዜ በአይሻ ቁጥር 2 የንፋስኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ላይ ተሳትፎ አድርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

‎የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ ‎…...///….... ‎ከአዲስ አበባ በ700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሶማሌ ክልል አይሻ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በይፋ ተመረቀ፡፡ ‎ ‎በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣የጅቡቱ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የፌደራል መንግስትና የክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ ‎ ‎የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ከ257 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በ2009 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረ ሲሆን በፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የ32 ተርባይኖች ተከላ፣  30 የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶችና የስዊች ያርድ እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። ‎ ‎በዛሬው ዕለት የተመረቀው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በ32 ተርባይን 80 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ‎ ‎የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ሲጠናቀቅ  የዛሬውን ጨምሮ 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ይኖረዋል። ‎ ‎በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ታሪክ የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዩኒት በአማካሪነት ለመጀመሪያ ጊዜ በአይሻ ቁጥር 2 የንፋስኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ላይ ተሳትፎ አድርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ የኢነርጂ ፕሮጀክት ተብሎ ተመረጠ .......///........ ‎ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአፍሪካ የንግድ ምክር ቤት የ2026 የዓመቱ "የኢንዱስትሪ ኢነርጂ ፕሮጀክት" (Industrial Energy Project of the Year) ተብሎ ተመረጠ።  ‎ የዕውቅና ሥነ-ሥርዓቱ ጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ማታ በጋና አክራ ኬምፐንስኪ ጎልድ ኮስት ሆቴል ተካሂዷል። ‎ ዕውቅናው የታላቁ ህዳሴ ግድብ አህጉራዊ ፋይዳ ያለው ታላቅ የኢንዱስትሪ ኢነርጂ ፕሮጀክት መሆኑን ለመመስከር ያለመ ነው። የዕውቅና ሽልማቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን በመወከል በጋና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተጠባባቂ የሚሲዮን መሪ  የሆኑት ክቡር                                                                                       አምባሳደር አሣየ ዓለማየሁ (ዶ/ር) ተቀብለዋል። በእውቅና ሽልማቱ ፕሮግራም ላይ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችና ተቋማት ኃላፊዎች፣ ኣምባሳደሮች እና ሌሎች ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል፡፡ ‎በአፍሪካ የንግድ ምክር ቤት የአፍሪካ የንግድ ሽልማት ዳይሬክተር መሀሙዱ ሃያቱ እንደገለፁት ምክር ቤቱ ፕሮጀክቱን ለመሸለም የወሰነው ግድቡ ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ ለቀጣናዊ የንግድና የኤሌክትሪክ ትስስር እያበረከተ ያለውን የጎላ አስተዋጽኦ እና የፕሮጀክት አመራር ሚና ዕውቅና ለመስጠት ነው። ‎ ግድቡ በኃይል ማመንጨት አቅምና ዋስትና እንዲሁም በረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ ሽግግር ላይ የተደረገ ትልቅ ኢንቨስትመንት መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ‎ ግድቡ ለከፍተኛ ማኑፋክቸሪንግ፣ ለግብርና ማቀነባበሪያ እና ለኢንዱስትሪ የእሴት ሰንሰለቶች መሠረት የጣለ መሆኑን የጠቆሙት ሚስተር መሀሙዱ ለቀጣናዊ የኃይል ትስስር እና ለዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል። ‎ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ዕውቅናው በአፍሪካ ንግድ ሽልማት ቋሚ ተቋማዊ መዝገብ ላይ የሚሰፍር ይሆናል። ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በኤምባሲው በኩል ዕውቅናውን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት ሽልማቱ የአፍሪካን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ሀገራት በራሳችን ሀብትና ጥረት ለመገንባት ያለንን የጋራ ምኞት የሚያሳይ ነው ብለዋል።‎ ‎ግድቡ ግዙፍ፣ ውስብስብ እና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በአፍሪካውያን ታስበው፣ ተገንብተው እና ተመርተው ለአፍሪካውያን የጋራ ብልፅግና ሊውሉ እንደሚችሉ ማረጋገጫ የሰጠ ነው። ‎ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ወደ አረንጓዴ ኢነርጂ-መር የልማት ጎዳና የምታደርገውን ስልታዊ ሽግግር የሚያሳይ ህያው ምስክር  ነው ብለዋል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በመልዕክታቸው። ኢትዮጵያ ታዳሽ የውሃ ኃይልን በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና የአካባቢ ጥበቃ ተደጋግፈው የሚሄዱ ጉዳዮች መሆናቸውን እያስመሰከረች እንደምትገኝ አብራርተዋል። ‎ግድቡ በአሁኑ ወቅት ፋብሪካዎችን በማንቀሳቀስ፣ የዲጂታል ሽግግርን በማገዝ እና በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ገንዳ (Eastern Africa Power Pool) በኩል ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ትስስርን በማጠናከር እንደ አህጉራዊ የኃይል ማዕከል እያገለገለ መሆኑን ጠቅሰዋል። ‎ ዕውቅናው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ስኬት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን በማንሳት ፕሮጀክቱ አፍሪካ በራሷ ኃይል ኢንዱስትሪዎቿን የማንቀሳቀስ አቅም እንዳላት ለዓለም ያበሰረ ክስተት ሆኖ መመዝገቡን በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም