fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 555 مشترک است و جایگاه 8 397 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 165 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 555 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 21 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 10 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.74% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 14.94% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 003 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 323 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 555
مشترکین
+124 ساعت
+87 روز
+1030 روز
آرشیو پست ها
photo content
+2

የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎች ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ደሴ ገቡ ‎……..///…….. ‌‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ የተመራ የልዑካን ቡድን ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ደሴ ከተማ ገብቷል። ‎ ‎ኢንጂነር አንዱዓለም እና ልዑካቸው ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ አሊ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ‎ ‎ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው እና ልዑካቸው በአንድ ቀን የሥራ ጉብኝታቸው የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት እንቅስቃሴን ጨምሮ የችግኝ ተከላ እና የአቅመ ደካማ ቤቶች ዕድሳት እንዲሁም ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ሁሉም  የሥራ መሪ ለተቋሙ ስኬት በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለፀ …….///……. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ለሁለንተናዊ  ዕድገት ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን በመረዳት መላው የተቋሙ የሥራ መሪዎች በዘርፉ የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። በግሪድ ስትራቴጂ፣ በሰው ሀብት ልማት፣ በስነምግባር እና በለውጥ ሥራ አመራር ላይ በማተኮር ለተቋሙ የስራ መሪዎች ለሁለተኛ ዙር እየተሰጠ ያለው ስልጠና ማጠናቀቂያ መርሃግብር ላይ የተገኙት ኢንጂነር አሸብር የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የበጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በስኬት አጠናቀን በምረቃ ዋዜማ ላይ የምንገኝበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። በዚህ ስኬት ይበልጥ በመነሳሳት የ2018 በጀት ዓመት በሁሉም የሥራ ዘርፎች ያቀድናቸውን ግቦች ለማሳካት በቁርጠኝነት ሌት ተቀን ልንሰራ ይገባል ብለዋል። በዚህ በጀት ዓመት ከባለፉት ዓመታት የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅ ያሳሰቡት ኢንጂነር አሸብር ሁሉም የሥራ መሪ መተማመንን መሠረት ያደረገ የቡድን ሥራ በተቀናጀ መልኩ ማከናወን እንደሚኖርበት አሳስበዋል። የተቋሙ የሰው ሀብት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው የተቋም መዋቅር በሥራ ላይ የሚውለው የተቋሙን ዓላማ ለማሳካት መሆኑን ገልፀዋል። በመዋቅር ትግበራ ወቅት የታዩ ክፍተቶች በቀጣይ በተግባር ሂደት አስፈላጊነታቸው እየተገመገመ ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረዋል። የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ ሁሉም የሥራ መሪ ኃላፊነት በተሞላበት እና በተጠያቂነት መንፈስ ሥራውን ሊያከናውን እንደሚገባ አሳስበዋል። የተቋሙን ውጤታማነት ለማሳደግ በተነሱ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ላይ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎች ምላሽ ሰጥተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

የ2018 በጀት ዓመት በኤሌክትሪክ ዘርፍም የማንሰራራት ዓመት ይሆናል ........///...... በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ ያለውን የማንሰራራት ዘመን በኃይል ዘርፉም እውን ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተናግሩ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት እና የኤሌክትሪክ ኃይል ልማት በእጅጉ የተቆራኙ በመሆናቸው የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል የኃይል መሠረተ ልማት መገንባት ያስፈልጋል። ለተቋሙ የሥራ መሪዎች ለሁለተኛ ዙር እየተሰጠ በሚገኘው ሥልጠና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ኢንጂነር አሸብር ሀገሪቱ የምትፈልገውን የኃይል ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል፤ የተቋሙን ራዕይ እና ተልዕኮ በውል የተረዳ የሥራ መሪ ያስፈልጋል ብለዋል። የሁሉም ዘርፍ የሥራ መሪዎች ራሳቸውን በእውቀት እና ክህሎት በማብቃት በስራ ክፍላቸው የሚገኙ ሠራተኞችን ማብቃት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ .....….///…...... የደጀን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ አስታወቀ። በትራንስሚሽን ቢዝነስ የፕሮጀክት ማኔጅመንት 2 ሥራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር እንዳስታወቁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከ90 ሜጋ ዋት በላይ የመሸከም አቅም ያላቸው አንድ ባለ 63 እና አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ ጣቢያው ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥንድ ገቢ መስመር እና አምስት ባለ 33 እንዲሁም አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት ተናግረዋል። እንደ አቶ መሐመድ ገለፃ የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በአካባቢው ይስተዋል ለነበረው የኤሌክትሪክ አቅርቦት ችግር መፍትሔ በመስጠት የግሪድ ሥርዓቱን ከማጠናከሩም ባሻገር  በደጀን እና አካባቢው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ በተቋሙ የደጀን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተቆጣጣሪ አቶ ግርማ ብርሃኑ በበኩላቸው እንደገለፁት ጣቢያው ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ግንባታው ሲከናወን ቆይቷል። የፕሮጀክቱ ሙሉ የፋይናንስ ወጪ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሸፈኑን የገለፁት አቶ ግርማ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በይፋ ሥራ መጀመር ለተቋሙና ለአካባቢው ማህበረሰብ እፎይታ የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። የደጀን- ደብረማርቆስ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የደብረ ማርቆስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ ከሁለት ሳምንት በፊት ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውንም ነው ያስታወሱት። የደጀን-ደብረ ማርቆስ የኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ በተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ የተከናወነ ሲሆን በዕቃ አቅርቦቱ በኩል ደግሞ ፓወር ቻይና የተባለ ኩባንያ ተሳትፎ ማድረጉ ተገልጿል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

አመራሩ ተቋማዊ ለውጡን በብቃት የመምራት የወል ኃላፊነት አለበት - ‎ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎.....///.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በየደረጃው የሚገኙ ‎አመራሮች ተቋማዊ ለውጡን በብቃት በመምራት ህዳሴን የመሰሉ ዘመን ተሻጋሪ ሥራዎችን የመስራት የወል ኃላፊነት እንዳለበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። ‎ ‎በተቋሙ የስትራቴጅክ ዕቅድ፣ በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና፣ በለውጥ ሥራዎች እንዲሁም በስትራቴጅክ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዙሪያ ለሥራ አመራሩ የተሰጠው የሁለት ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጠናቋል። ‎ ‎በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ሠልጣኝ አመራሮቹ ከመዋቅር፣ ከሥራ ልምድ አያያዝና ከዕድገት፣ ከቅንጅታዊ አሰራር፣ ከኮሙዩኒኬሽን፣ ከብልሹ አሰራር፣ ከግምገማ እና ከተጠያቂነት፣ ከሥራ አፈፃፀም እንዲሁም ከጥቅማ ጥቅም ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል። ‎ ‎ሥልጠናው አመራሩ ሚናውን አውቆ የውሳኔ አሰጣጡን በማሳደግ ተቋሙን የሚያሻግሩ ተግባራትን በህብረት ለመስራት የሚያነሳሳ ነው ብለዋል። ‎ ‎መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች በአመራሩ መካከል ያለውን መግባባትንና ቅንጅታዊ አሰራርን የሚያሳድግ በመሆኑ ቀጣይነት ባለው መልኩ በዕቅድ ተይዞ መሰራት እንዳለበትም አንስተዋል። ‌‎ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲዓ አመራሩ ለተቋሙ ስኬትና ድክመት ኃላፊነት እንዳለበት አውቆ በቁርጠኝነት በመተጋገዝና በመተጋገል መንፈስ መስራት አለበት ብለዋል፡፡ በተቋሙ የሚከናወኑ ሥራዎች በማስተዋወቅ፣ የአገልግሎት አሰጣጣጡን በማዘመን እና በሥሩ ያሉ ሠራተኞችን በአርያነት በመምራት በኩል ሁሉም አመራር ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡ የሰው ሀብት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ መዋቅሩ ሥራን ማዕከል ባደረገ መልኩ ተቋማዊ ውጤታማነት ለማሳደግ፣ ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም ታስቦ መሰራቱንና ጥያቄዎች ካሉ በሂደት እንደሚታዩ አንስተዋል፡፡ አመራሩ ሠራተኞችን በተሠጣቸው የሥራ ዕቅድና ደረጃ መሠረት በአግባቡ የመመዘን፣ ሌሎችን የማብቃት እንዲሁም ለሥራ የተሰጠውን ሀብት በአግባቡ የማስተዳደርና የመጠቀም ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡም ጠይቀዋል፡፡ ‎የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን ሠራተኞችና የሥራ ክፍሎችን ለማበረታታት የሽልማት እና የእውቅና ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው እንደገለጹት የ2018 በጀት ዓመት የተቋሙ የግሪድ ስትራቴጂ ትግበራ የመጨረሻው ዘመን መሆኑን ታሳቢ በማድረግ አመራሩ ሥራ ቆጥሮ አቅዶ መስራት አለበት፡፡ ‎ አመራሩ ህዳሴን መሰል ዘመን ተሻጋሪ አሻራዎችን ለመስራት ‎በጊዜ የለኝም መንፈስ በመግባባት እንዲሁም የተቋሙን ጥቅም በማስቀደም እና ሥራን ማዕከል በማድረግ ተጠያቂነትን በማስፈን ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ ሥራዎቻችንን በአግባቡ ኮሙዩኒኬት ማድረግ አለመቻል አመራሩ ለተቋሙ ያለው የእኔነት ስሜት ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር አመራሩ በሥሩ ያለውን ሀብትና ሠራተኛ በብቃት በመጠቀምና በመምራት ለተቋሙ ዘብ መቆም እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ በተቋሙ የተፈጠሩ የኮሙዩኒኬሽን ፕላትፎርሞች ሥራን ማዕከል በማድረግ በአግባቡና በሥርዓት መጠቀም አስፈላጉ በመሆኑ ያለው ክፍተት መታረም እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ አመራሩ ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ተቋማዊ ለውጡን በብቃት የመምራት የወል ኃላፊነት አለበት ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው መሰል ስልጠናዎችን በማጠናከርና ሕግን የተከተለ አሳታፊ የግምገማ ሥርዓት በመዘርጋት ለተሻለ ውጤት እንዲተጋ ጥሩ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

አመራሩ የስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብን ተገንዝቦ ለውጤታማነት መስራት ይጠበቅበታል .......///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ውጤታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኘው የሥራ መሪ የስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብንና ለተቋም የሚኖረውን ሚና ተገንዝቦ መስራት እንደሚጠበቅበት በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ አሳሰበ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ስለ ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብና አስፈላጊነት እንዲሁም በተቋም ላይ ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ምን መምሰል እንዳለበት ለተቋሙ የሥራ መሪዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዳይሬክተሩ በማብራሪያቸው የተቋሙ የኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት ከርዕይ፣ ተልዕኮ እና ዓላማዎቹ ጋር የተያያዘ መሆን እንዳለበት እና ምን አይነት መረጃ ለማን፣ መቼና ለምን ማስተላለፍ እንደሚገባ ቀድሞ መለየት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ተቋሙን ለማስተዋወቅና ገፅታውን ለመገንባት ከማገዙም ባለፈ ውስጣዊ ግንኙነትን ለማጠናከር፣  በተቋሙ ላይ የኢንዱስትሪ ሰላምን ለማስፈን፣ ከደንበኞች ጋር መልካም ግንኙነትን ለመፍጠር፣ አስተሳሰብን ለመቅረፅ እና ሠራተኛው በተቋሙ በሚተላለፈው መልዕክት ላይ ድርሻ እንዳለው ለማሳወቅ እንደሚረዳ ተናግረዋል። ተቋሙ የሚፈልገው ለውጥ ላይ እንዲደርስ ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ከፍተኛ ሚና እንዳለው የተናገሩት አቶ ሞገስ አመራሩም  ሚናውን በመረዳት ማንኛውን ነገር ስልታዊ በሆነ አግባብ ኮሙዩኒኬት ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል። በተቋሙ ውስጥ ውጤታማ የሆነ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ ለማከናወን መረጃ በወቅቱ የሚገኝበት ሥርዓት ያለመጠናከሩ፣ ከሥራ ክፍሎች፣ ከሚዲያና ባለድርሻ አካላት ጋር  ወጥ ግንኙነት ያለመፈጠሩ፣ ሙያዊ ለሆኑ አንዳንድ ቃላት አቻ ትርጉም ለማግኘት አስቸጋሪ መሆኑ፣ የአመራሮች የሚዲያ አጠቃቀም ግንዛቤ ክፍተት መኖርና የመሳሰሉት ችግሮቹ  እንዳሉ አብራርተዋል። የተቋም የኮሙዩኒኬሽን ሥራ የአንድ ክፍል ብቻ ባለመሆኑ ችግሮቹን በመቅረፍ ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የሥራ መሪ የስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብንና ለተቋም የሚኖረውን ሚና ተገንዝቦ በጋራና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚኖርበት ዳይሬክተሩ አሳስበዋል። በዕለቱም ከተቋም ገፅታ ግንባታና ማስተዋወቅ፣ ከተቋሙ ሠራተኞች የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና ተጠያቂነት ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከተሳታፊዎች ቀርበዋው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ ሀሳብ የሰጡት የኮርፖሬት ገቨርናንስና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዱጉማ ነዳ በበኩላቸው ተቋሙን ለማስተዋወቅና ገፅታውን ለመገንባት የተቋሙን ስያሜ እስከመቀየር ያሉ የመፍትሔ ሀሳቦች መቅረባቸውን አስታውቀዋል። ሁሉም አመራር የኮሙዩኒኬሽን ሥራ የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት የሚኖረውን ሚና ተገንዝቦ መረጃ ከመስጠት ጀምሮ ክፍሉን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

በተቋሙ የሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተከተሉ መሆን አለባቸው ‎.....///..... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚከናወኑ ተግባራትና የሚሰጡ ውሳኔዎች ሙያዊ ሥነ-ምግባርን የተከተሉ መሆን እንዳለባቸው የተቋሙ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ ገለጸ። ‎ ‎መምሪያው በ “ሥራ ቦታ ሥነ-ምግባር” (Ethics in the work place) ዙሪያ ለተቋሙ የሥራ መሪዎች በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ላይ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ደረጀ አጥናፌ እንደገለጹት ተቋሙ ከፍተኛ በጀት በመመደብ ሕዝባዊ ጠቀሜታና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸውን ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ይገነባል። ‎ ‎ሥልጠናው አመራሩ በተቋሙ የሚስተዋሉ ከሥነ-ምግባር ያፈነገጡ አሰራሮችን እና አስተሳሰቦችን በመቅረፍ ፕሮጀክቶችን ውጤታማ በሆነ መንገድ በመፈፀም ብሩህ ኢትዮጵያን ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል። ‎የራስን ጥቅም በማስቀደም በተቋሙ ጥቅም ላይ መደራደር፣ የተቋሙን ምስጢር አሳልፎ መስጠት፣ የተቋሙን ሀብትና ንብረት አላግባብ መጠቀም፣ የሥራ ሰዓትን አለማክበር የመሳሰሉት የኢ-ሥነ-ምግባርዊ አሰራሮች መገለጫ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል። ‎ ‎በመሆኑም ተቋሙ ከብክነት በፀዳ መልኩ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣትና ርዕዩን ለማሳካት በየደረጃው የሚገኘው አመራር ከሥነ-ምግባር ያፈነገጡ ችግሮችን ለመከላከል በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት ገልፀዋል። ‎ ይህም የተቋሙን መልካም ሥም ለመጠበቅ፣ ስጋቶችን ለመቀነስ፣ አቅም ያላቸውን ባለሙያዎች ለመሳብ፣ የሠራተኞችን እርካታ ለማሳደግ እና ጥሩ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር ይረዳል ብለዋል። ‎ ‎የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ በበኩላቸው በተቋሙ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ለማረጋገጥ የአመራሩ ሚና የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል። ‎ ‎አመራሩ በተቋሙ የሚስተዋሉ ሥነ-ምግባራዊ ጥሰቶችን በማስወገድ ተቋማዊ የሥራ ባህል ለውጥ ለማምጣት የወል ኃላፊነት እንዳለበትም አንስተዋል። ‎ ‎በመሆኑም በተቋሙ የወጡ ፖሊሲዎችን፣ ደንቦችና ሕጎች እንዲሁም የሥነ-ምግባር መርሆችን በማከበር እና በማስከበር በኩል አመራሩ በባለቤትነት ስሜት ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ‎ ‎ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሥልጠናው በተቋሙ ከሚስተዋሉ የሥነ-ምግባር ችግሮች አንፃር ራሳቸውን ማየታቸውንና በቀጣይ በሥራ ቦታ ሥነ-ምግባራዊ መርሆችን በማረጋገጥ ተቋሙ የጣለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋማዊ አደረጃጀቱ ውጤታማነትን ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ መቀረጹ ተገለፀ ........///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያካሄደ ያለው የአደረጃጀት ማሻሻያ ከተቋሙ የኮርፖሬት ስትራቴጂ ጋር የተጣጣመ እና ውጤታማነትን ለማሳደግ በሚያስችል መልኩየተቀረፀ መሆኑን በተቋሙ የሰው ሀብት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ አታላይ አበበ በአደረጃጀት ማሻሻያው አስፈላጊነትና አተገባበር እንዲሁም አመራሩ ተቋማዊ ለውጡን በአግባቡ ለመተግበር ስለሚኖረው ሚና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ተቋማትን ውጤታማ ለማድረግ ግልፅ የሆነ ተቋማዊ ስትራቴጂና አደረጃጀት፣ የተሟለ የሠው ኃይል እንዲሁም የተሻለ የአሰራር ስርዓት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል። አደረጃጀቱ  ተቋማዊ ውጤታማነት ለማሳደግ፣ ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀሞ፣ ወጥ የሆነ የአሰራር ስርዓት ለመተግበር፣  በሥራ ክፍሎች መካከል  ያለውን የሥራ ድግግሞሽ ለመቀነስ እንዲሁም ኃላፊነትን በአግባቡ ለመወጣት በሚያስችል መልኩ መቀረፁን ሥራ አስፈጻሚው አስረድተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ለተቋሙ አስፈላጊ የሆኑ አዲስ የሥራ ክፍሎችን ለማቋቋም፣ በሥራ ክፍሎች መካከል ትበብርን ለመፍጠርና የሥራ ጫና ለማመጣጠን፣ ግልፅነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ከተቋሙ ተልዕኮ ጋር የተጣጣመ የሰው ኃይል ስብጥር እንዲኖር ለማድረግ እንደሚያስችል አብራርተዋል። የሥራ መሪዎቹ  የተቋሙን ርዕይ፣ ተልዕኮና ስትራቴጂክ ግቦችን የማወቅ፣ በተለያዩ መንገዶች ለሠራተኛው አርዓያ የመሆን፣ ሠራተኞችን በተሠጣቸው የሥራ ዕቅድና ደረጃ መሠረት በአግባቡ የመመዘን፣ ሌሎችን የማብቃት እንዲሁም ለሥራ የተሰጠውን ሀብት በአግባቡ የማስተዳደርና የመጠቀም ኃላፊነት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። አቶ አታላይ እንዳሉት ተቋማዊ ለውጡን ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ ለለውጥ ራሱን የማዘጋጀት፣ የሥራ ጊዜውን በአግባቡ የመጠቀም፣ ሥራውን ለማከናወን የሚያስችሉ ፖሊሲዎችንና አሰራሮችን በማዘጋጀት  ወደ ሥራ የመግባት እንዲሁም የሠራተኞችን የሥራ መዘርዝር የመከለስ ሚና እና ኃላፊነት አለበት። ተቋማዊ አደረጃጀት በየጊዜው ሊሻሻል የሚችል ጉዳይ ነው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው በቀጣይም ጊዜውንና የተቋሙን ዕድገት መሠረት ባደረገ መልኩ ሊሻሻል እንደሚችል ጠቁመዋል። በተቋሙ የፖሊሲ፣ ፕሮሰስ እና የለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ በበኩላቸው በተቋሙ እየተካሄደ ያለውን የመዋቅር ማሻሻያ ተከትሎ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣት እየተሰራ ነው ብለዋል። ውጤትን መሠረት ያደረገ ተቋማዊ ባህል ለመገንባት የሥራ ባህልን መቀየር፣ የዲጅታላይዜሽን ሥርዓት መዘርጋት፣ የአሰራር ስርዓቶችን ማሻሻል እና ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚገባ የተናገሩት ዳይሬክተሩ ለውጡን በአግባቡ ለመተግበርም ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጣ ኮሚቴ መዋቀሩን ጠቅሰዋል። በተቋሙ ለመተግበር የታሰቡ የለውጥ ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አመራሩ ለሁለንተናዊ ለውጥ ራሱን ማዘጋጀት እንዳለበት አቶ አንዱዓለም አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የተቋሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ አመራሩ ሚናውን በአግባቡ መወጣት ይኖርበታል .........///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠውን ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ ሚናውን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። በየደረጃው ለሚገኙ የተቋሙ የሥራ መሪዎች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ የተሳትፎ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ስልጠናውን በንግግር ሲከፍቱ እንደገለፁት መንግስትና ህዝብ ከተቋሙ  የሚጠብቀውን ነገር በአግባቡ ለመፈፀም ብቃት ያለው አመራር  ያስፈልጋል። በዚህም የአመራሩን አቅም ማሳደግ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እየተካሄዱ ይገኛሉ ብለዋል። የተቋሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኘው አመራር ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር  አመራሩ የተቋሙን ግብ፣ ርዕይ፣ ተልዕኮና እሴቶች  ተገንዝቦ ወደ ውጤት መቀየር እንደሚጠበቅበትም ተናግረዋል። አመራሩ ከስልጠናው የሚያገኘውን ግንዛቤ ወደ ሠራተኛው በማውረድ  በተቋሙ ስትራቴጅና የለውጥ ሥራዎች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር እንደሚኖርበት ዋና ሥራ አስፈፃሚው አስገንዝበዋል። የተቋሙን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ተተኪ አመራርና ሠራተኛ ማፍራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት መሠራት ይኖርበታል ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው። የተቋሙን ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም በየደረጃው የሚገኝ አመራር በትብብር መስራት  እንደሚጠበቅበትም አሳሰበዋል። የአመራሩን አቅም ለማሳደግ በቀጣይ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኢንጂነር አሸብር አረጋግጠዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ተቋሙ የያዘውን ዕቅድ በአግባቡ ለማሳካት የአመራሩን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ስልጠናው የአመራሩን ተሳትፎ በማጎልበት የተቋሙን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ብቃት ያለው፣ ሥነ ምግባር  የተላበሰ  እንዲሁም ለለውጥ አርአያ  የሆነና ግንባር ቀደም አመራር ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ አስረድተዋል። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ በተቋሙ ስትራቴጅክ ዕቅድ፣ በሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ፣ በሰው ሀብት አስተዳደርና ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲሁም በለውጥ ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል። ለቀሪ የሥራ መሪዎች መሰል ስልጠና በቀጣይ ሳምንት እንደሚሰጥም አቶ  ሙላት ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የተቋሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ አመራሩ ሚናውን በአግባቡ መወጣት ይኖርበታል .........///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠውን ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ ሚናውን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። በየደረጃው ለሚገኙ የተቋሙ የሥራ መሪዎች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ የተሳትፎ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ስልጠናውን በንግግር ሲከፍቱ እንደገለፁት መንግስትና ህዝብ ከተቋሙ  የሚጠብቀውን ነገር በአግባቡ ለመፈፀም ብቃት ያለው አመራር  ያስፈልጋል። በዚህም የአመራሩን አቅም ማሳደግ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እየተካሄዱ ይገኛሉ ብለዋል። የተቋሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኘው አመራር ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር  አመራሩ የተቋሙን ግብ፣ ርዕይ፣ ተልዕኮና እሴቶች  ተገንዝቦ ወደ ውጤት መቀየር እንደሚጠበቅበትም ተናግረዋል። አመራሩ ከስልጠናው የሚያገኘውን ግንዛቤ ወደ ሠራተኛው በማውረድ  በተቋሙ ስትራቴጅና የለውጥ ሥራዎች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር እንደሚኖርበት ዋና ሥራ አስፈፃሚው አስገንዝበዋል። የተቋሙን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ተተኪ አመራርና ሠራተኛ ማፍራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት መሠራት ይኖርበታል ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው። የተቋሙን ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም በየደረጃው የሚገኝ አመራር በትብብር መስራት  እንደሚጠበቅበትም አሳሰበዋል። የአመራሩን አቅም ለማሳደግ በቀጣይ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኢንጂነር አሸብር አረጋግጠዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ተቋሙ የያዘውን ዕቅድ በአግባቡ ለማሳካት የአመራሩን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ስልጠናው የአመራሩን ተሳትፎ በማጎልበት የተቋሙን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ብቃት ያለው፣ ሥነ ምግባር  የተላበሰ  እንዲሁም ለለውጥ አርአያ  የሆነና ግንባር ቀደም አመራር ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ አስረድተዋል። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ በተቋሙ ስትራቴጅክ ዕቅድ፣ በሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ፣ በሰው ሀብት አስተዳደርና ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲሁም በለውጥ ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል። ለቀሪ የሥራ መሪዎች መሰል ስልጠና በቀጣይ ሳምንት እንደሚሰጥም አቶ  ሙላት ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም