es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 696 suscriptores, ocupando la posición 8 017 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 152 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 696 suscriptores.

Según los últimos datos del 31 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 142, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 30.85%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 842 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 578 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 696
Suscriptores
+224 horas
+237 días
+14230 días
Archivo de publicaciones
‎የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ ዝግጁ ሆኗል ‎.....///..... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለምርቃት ዝግጁ መሆኑን የጀነሬሽን ቢዝነስ ዩኒት ገለጸ። ‎ ‎በቢዝነስ ዩኒቱ የዕቅድና ክትትል ባለሙያ አቶ ሰለሞን ተረፈ እንደገለጹት የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ የተጀመረው በየካቲት 2016 ዓ.ም ነበር። ‎ 32 ተርባይኖች የተተከሉበት የግንባታው የመጀመሪያው ምዕራፍ፣  30 የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶች ግንባታና የስዊች ያርድ የግንባታ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለምርቃት ዝግጁ ሆነዋል። ‎ በመጀመሪያው የግንባታ ምዕራፍ ጣቢያው ሲጠናቀቅ ማመንጨት ከሚችለው 120 ሜጋ ዋት ውስጥ 80 ሜጋ ዋት እያመነጨ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ‎ ‎የቀሪው 16 ተርባይኖች ሥራ በ69 ሚሊዮን ዶላር ወጭ በምዕራፍ ሁለት ሥር ተካቶ ግንባታው እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ‎ ‎አሁን ላይ የስምንቱ ተርባይኖች ምርት ተጠናቆ ከቻይና የማጓጓዝ ሥራ መጀመሩንና በ45 ቀናት ውስጥ ሳይት ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አብራርተዋል። ‎ ‎የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ወጪ 257 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር መሆኑንና ከዚህ ውስጥ ተቋሙ 15 በመቶውን ማለትም 38 ሚሊዮን ዶላሩ በኢትዮጵያ ብር ከፍሎ ማጠናቀቁን አስረድተዋል። ‎ ‎ሆኖም 85 በመቶውን የሚሸፍነው አበዳሪው የቻይና ኤግዚም ባንክ 114 ሚሊዮን ዶላር ከከፈለ በኋላ ቀሪውን በውሉ መሠረት ክፍያዎቹን ለሥራ ተቋራጩ መክፈል በማቋረጡ ምክንያት የፕሮጀክቱ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ አለመጠናቀቁን አቶ ሰለሞን ጠቁመዋል። አሁን ላይ የሁለተኛውን ምዕራፍ የግንባታ ፋይናንስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመሸፈን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ‎ ‎ፕሮጀክቱ በንፋስ ኃይል የተሻለ የማምረት አቅም ያለው በመሆኑን ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ለምስራቁ ግሪድ የሲስተም መረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ገልጸዋል። ‎ ‎የፕሮጀክቱ አማካሪ የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዩኒት ሬዝዴንት ኢንጂነር አቶ እንድሪስ ገዙ በበኩላቸው አበዳሪው ባንክ የተወሰነውን ገንዘብ መልቀቅ ባይቻልም የሥራ ተቋራጩ የምዕራፍ አንድን የግንባታ ሥራዎች ማጠናቀቁን ገልጸዋል። ‎ ‎የምዕራፍ ሁለት የፕሮጀክቱን ሥራዎች ተቋሙ በራሱ ፋይናንስ ለማድረግ ከስምምነት ተደርሶ የቀሪ 16 ተርባይኖች የሲቪል ሥራ መጠናቀቁን አብራርተዋል። ‎ እንደ አቶ እንድሪስ ገለጻ ‎ተርባይኖቹ ሳይት እንደደረሱም የተከላ ሥራው እንደሚጀመርና ፕሮጀክቱን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል። ‎ ‎በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ታሪክ የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዩኒት በአማካሪነት ሲሳተፍ የአይሻ ቁጥር 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ የመጀመሪያ መሆኑን ያወሱት አቶ እንድሪስ ይህም የተቋሙ ከፍተኛ ወጭ ከማዳኑም ባሻገር የባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አስገንዝበዋል። ‎ ፕሮጀክቱ ‎ከአዲስ አበባ 700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሶማሌ ክልል አይሻ ከተና አቅራቢያ የሚገኝ ሲሆን ዶንግ ፋንግ ኤሌክትሪክ ኮርፖሬሽን የተባለ የቻይና ሥራ ተቋራጭ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 48 ተርባይኖች የሚኖሩት ሲሆን እያንዳንዳቸው 2 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት በድምሩ 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አላቸው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎ጣቢያው በሩብ ዓመቱ ከ34 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አምርቷል ‎......//...... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2018 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ34 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ ገለጹ። ‎ ‎ኃላፊው  አቶ ዮሐንስ አስማረ እንደገለጹት ጣቢያው በሩብ ዓመቱ በ32 ተርባይኖች 39 ነጥብ 72 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት አቅዶ 34 ነጥብ 67 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ያመረተ ሲሆን ይህም የዕቅዱን 87 ነጥብ 2 በመቶ ነው። ‎ ‎በተወሰኑ ተርባይኖች ላይ ከጀነሬተሩ የመነጨውን ኃይል ወደ ዩኒት ትራንስፎርመር በሚልከው ኮንዳክተር ላይ ባጋጠመ ቴክኒካል ችግር እና በዓመታዊ ጥገና ምክንያት ተርባይኖች ይቆሙ ስለነበር አፈፃፀሙ ዝቅ ማለቱን ተናግረዋል። ‎ ‎አሁን ላይ ያጋጠመው ቴክኒካዊ ችግር በመፈታቱና ዓመታዊ የጥገና ሥራዎች እየተጠናቀቁ በመሆኑ እንዲሁም ዓመታዊ የንፋስ አቅጣጫውና ፍጥነቱ እየጨመረ በመሆኑ በቀጣይ ጊዜያት የተሻለ ኃይል በማምረት ዓመታዊ ዕቅዱን ማሳካት እንደሚቻል ገልጸዋል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ ጣቢያውን ከኢትዮጵያ ወደ ጅቡቲ ከተዘረጋው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ጋር በማገናኘት ከጣቢያው የመነጨውን ኃይል ለጅቡቲ በቀጥታ ለመስጠት የሚያስችለውን የተሳካ የሙከራ ሥራ ማካሄዱንም ተናግረዋል። ‎ ‎በጣቢያው ከፍተኛ ንፋስና አቧራ በመኖሩ ተርባይኖቹን በየጊዜው ለማጽዳትና አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ የፍተሻና የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን የሠው ኃይል እጥረት መኖሩን ጠቁመዋል። ‎ ‎በተጨማሪም በኮንትራት ሥምምነቱ መሠረት ለሦስት ዓመት ጥገና ሥራው የሚከናወነው በሥራ ተቋራጮቹ ድጋፍ መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎ከአዳማ 1 እና 2 እንዲሁም ከአሸጎዳ በመቀጠል በአራተኛነት የተገነባው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት 436 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

የጽሁፍ ፈተና ውጤትንና ለቃል ፈተና የተጠሩ አመልካቾችን ስለማሳወቅ ……..///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮይሻ የውሃ ኃ/ማ/ፕሮጀክት (Civil engineer I) ሲቪል መሐንዲስ I (ፔ
+4
የጽሁፍ ፈተና ውጤትንና ለቃል ፈተና የተጠሩ አመልካቾችን ስለማሳወቅ ……..///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮይሻ የውሃ ኃ/ማ/ፕሮጀክት (Civil engineer I) ሲቪል መሐንዲስ I (ፔአር1) ፣ (Geologist I) ጂኦሎጂስት I (ፒአር1) እና (Geothechnical Lab Technician I) ጂኦተክኒካል ላብ ቴክኒሻን I (ኤስፒ 1) የስራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 10 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መስፈርቱን አሟልታችሁ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም የተሰጠው ፈተና ውጤት ከዚህ በላይ የተገለፀው መሆኑን እያሳወቅን በቀጣይም ለቃል ፈተና የተጠራችሁ ሐሙስ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት ጀነሬሽን ኮንስትራክሽን ቢሮ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

ጣቢያው ለምርታማነት ማደግ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገለፀ ……..///………. የደብረብርሃን ቁጥር 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በደብረብርሃን ከተማ እና ዙሪያው ለሚገኙ በርካታ ፋብሪካዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ለምርታማነት ማደግ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስታወቀ። የጣቢያው ኃላፊ አቶ ዳኜ ይታገሱ እንደገለፁት ጣቢያው 33  እና 15 ኪሎ ቮልት አቅም ባላቸው 15 ወጪ መስመሮች አማካኝነት ለደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ዞንና ለሌሎች ግዙፍ ፋብሪካዎች ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ በጣቢያው ባሉት 15 ወጪ መስመሮች በቀን በአማካኝ ከ110 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝም ነው ኃላፊው የተናገሩት። እንደ አቶ ዳኜ ገለፃ ጣቢያው በተጨማሪም በ230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በቀን በአማካኝ 50 ሜጋ ዋት ኃይል በማቅረብ ላይ ነው። ለፋብሪካዎች ከሚያቀርበው ኃይል ባሻገር ጣቢያው ለደብረብርሃን ከተማ እና በአቅራቢያው ለሚገኙ እነዋሪ፣ ሸኖ፣ ሀገረማርያም፣ ይናገር፣ ጫጫ፣ ደነባ፣ መንዲዳ እና ፅጌረዳ ከተሞች ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል። የካቲት 2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ጣቢያ የኃይል አቅርቦቱን የሚያሳልጡ ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች እና ሁለት ፓወር ትራንስፎርመሮች አሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ሪጅኑ የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እየገመገመ ነው   ........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ አንድ ሪጅን የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ገዛኸኝ እንደገለፁት የግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። በሩብ ዓመቱ አስተማማኝ ኃይል ለደንበኞች ለማቅረብ እንዲቻል በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ መጠነ ሰፊ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡  ለሦስት ቀናት በሚቆየው ግምገማ ላይ ሪጅኑ በሩብ ዓመቱ የዕቅድ ክንውን ላይ የታዩ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች፣ መልካም አጋጣሚዎች እና ተግዳሮቶች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ይካሔድባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በሪጅኑ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጆች እንደገለፁት ከደንበኞችና ኢንዱስትሪዎች ጋር የነበረው ግንኙነት መሻሻሉን፣ የኃይል መቆራረጥ ችግር ላይ አፋጣኝ መፍትሄ እየሰጡ መሆኑን እንዲሁም የሚወገዱ ንብረቶችን በአግባቡ የመለየት ሥራ በአግባቡ መስራታቸዉን አብራርተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጆቹ ገለፃ በሩብ ዓመቱ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም በማከናወን ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

የማህበሩ አጠቃላይ ካፒታል  ከ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ደረሰ ‎…..…///……. የኢትዮ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/የሕ/ሥራ ማህበር በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ ካፒታሉ ከ 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን የማህበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ገለጹ፡፡ ሰብሳቢው አቶ አንበሴ ግዛቸው ይህን የገለጹት ‎የሕብረት ሥራ ማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የሥራ አመራር ቦርዱን 2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ነው፡፡ የማህበሩ ካፒታል በመጋቢት 2014 በጀት ዓመት ከነበረበት 995  ሚሊዮን 754 ሺህ 689 ብር በ2017 በጀት ዓመት ወደ 1 ቢሊዮን 925 ሚሊዮን 137 ቪህ 79 ብር  ማሳደግ  መቻሉን አመልክተዋል፡፡ በበጀት አመቱ ከተሰበሰበው ብር 815 ሚሊዮን 77 ሺህ 102 ብር ከ17 ሳንቲም ውስጥ  ለ1 ሺህ 70 አዲስ ብድር ጠያቂ አባላት 372 ሚሊዮን 388 ሺህ 204 ብር ከ19 ሳንቲም ብድር መስጠቱን ተናግረዋል። በተመሳሳይ በብድር ላይ ብድር ለጠየቁ 1 ሺህ 6 አባላት 423 ሚሊዮን 341 ሺህ 242 ብር ብድር መሰጠቱን ገልጸዋል ፡፡ በዚህም ማህበሩ በበጀት ዓመቱ በድምሩ 795 ሚሊዮን 729 ሺህ 446 ብር ከ21 ሳንቲም ለአባላት ብድር ሰጥቷል ብለዋል፡፡ በጀት ዓመቱ 1 ሺህ 763 አዲስ አባላትን ማፍራት የተቻለ ሲሆን በልዩ ልዩ ምክንያት ከማህበሩ 922 አባላት መልቀቃቸውን አብራርተዋል፡፡ ጠቅላለ ጉባኤው በቆይታው የብድር ምጣኔ ጣሪያውን ከነበረበት 800 ሺህ ወደ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር የማሳደግ እና የብደር መክፈያ ጊዜውን ከ15 ዓመት ወደ 10 ዓመት ዝቅ እንዲል ወስኗል። በተጨማሪም የሥራ አመራር ቦርዱ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ማሻሻያን ጨምሮ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ አጽድቋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

በተቋሙ የሚከናወኑ ሥራዎች ግልጽነትና ተጠያቂነትን ማረጋገጥ አለባቸው ‎.....///..... ‎በተቋሙ የሚከናወኑ ሥራዎች ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ያረጋገጡና የተቋሙን ጥቅም ያስጠበቁ እንዲሆኑ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት፣ የኮርፖሬት ገቨርናንስና ኮምፕሊያንስ፣ የውስጥ ኦዲት እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፎች የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ በሪፖርቱ ‎የተቋሙን አሰራሮች በማዘመን ሀብቱን ከመጠበቅና ገጽታውን ከመገንባት ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን ከማስፈን እንዲሁም የሴቶችን ተሳትፎ ከማሳደግ አንጻር የተከናወኑ ሥራዎች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ቀርበዋል፡፡ በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያዎችና ምላሾች ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ‎በግምገማው ማጠቃለያ እና የሥራ አቅጣጫ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በሩብ ዓመቱ በዘርፎቹ የተከናወኑ ሥራዎች ክፍተቶች የታየባቸውና ትኩረት የሚፈልጉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይም ተቋሙ የሚሰራቸውን ሥራዎች ከማስተዋወቅና ከገጽታ ግንባታ አንጻር ከመረጃ አያያዝ ጀምሮ የሚስተዋሉ ችግሮች በአስቸኳይ መታረም እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ የውስጥ ኦዲት ሪፖርቶች በኦፕሬሽንና በፕሮጀክቶች ላይ አላግባብ የሚወጡ ወጪዎችን መቆጠብ የሚያስችል ምክረ ሀሳብ ለተቋሙ አመራር በሚያቀርብ መልኩ መዘጋጀት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። ‎ ‎ጊዜው የመፍጠንና የመፍጠር በመሆኑ የተቋሙን አሰራሮች ወደ ዲጂታል እንዲቀየሩ እና የሪፎርም ሥራዎች ወደ መሬት እንዲወርዱ ሁሉም አመራር በትብብርና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው ጠቁመዋል፡፡ ‌‎ከመረጃ አያያዝ፣ ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ፣ ከፕሮጀክት አፈጻጸም፣ ከክትትልና ቁጥጥር ጋር የተያያዙ ተግዳሮቶች መኖራቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው እነዚህንና ሌሎች ችግሮች በጥናት ተለይተው መፍትሔ አምጪ ምክረ ሀሳቦች እንዲቀርቡ የፓወር አካዳሚ ሚና ከፍተኛ ሊሆን እንደሚገባም ነው የገለፁት። በሩብ ዓመቱ ‎ያልተሰሩት ሥራዎች በአጭር ጊዜ የድርጊት መርሀ ግብር ተዘጋጅቶ መከናወን እንዳለባቸውና ይሄን በማያደርጉ የሥራ ክፍሎችና አመራሮች ላይ ተጠያቂነት እንደሚኖር አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

‎በዕቅድ እና ሪፖርት አቀራረብ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም ይገባል ~አሸብር ባልቻ ‎.....///...... ‎በተቋሙ ከዕቅድ እና ሪፖርት አቀራረብ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። ‎ ‎የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የ2018 በጀት የመጀመሪያውን ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በሥራ አስፈፃሚው አቶ ሕይወት እሸቱ ቀርቧል። ‎ ‎ዘርፉ ለተቋሙ አዋጭ የሆኑ ሣይንሳዊ መንገዶችን በመጠቀም የአጭር፣ መካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን ማዘጋጀት፣ መከታተልና መገምገም እንዲሁም ምክረ ሀሳብ እንደሚያቀርብ ገልፀዋል። ‎ ‎እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ ክፍሉ የአዋጭነት፣ የአካባቢ ደህንነትና የመልክዓ ምድር ጥናቶች እየሰራ ይገኛል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ በራስ አቅም የሲስተም ማሻሻያ እና የግሪድ አቅምን ለማሳደግ የሚያስችሉ ጥናቶች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎በተጨማሪም የሁለት ፕሮጀክቶችን የዋጋ ጥናት እና የሦስት ከተሞችን የኃይል ፍላጎት ትንበያ ሥራዎች ማከናወናቸውን አብራርተዋል። ‎ ‎ታዳሽ፣ የተቀናጀ፣ ዘላቂ ኃይልና ዲጂታላይዜሽን ፕሮግራም ዕቅድ መጽደቁንም ነው አቶ ሕይወት የጠቆሙት። ‎ ‎በፕሮጀክት አስተዳደር ላይ የሚታዩ መዘግየቶች መንስዔዎቻቸውን ለመለየትና የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያስችል ጥናት ለመዘጋጀት መረጃ የማሰባሰብ ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም ተናግረዋል። ‎ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው የክትትልና የድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከር የተቋሙን ዋና ዋና ጉዳዮች የያዘ የተደራጀ፣ የተቀናጀና የተናበበ ዕቅድና ሪፖርት መዘጋጀት እንዳለበት ገልጸዋል። ‎ ‎የፕላኒንግ ዘርፍ የተቋሙን መነሻና መዳረሻ የምንወስንበት በመሆኑ አደረጃጀቱን በማስተካከልና በሠለጠነ የሠው ኃይል በማሟላት መልሶ ማደራጀት እንደሚገባ ተናግረዋል። ‎ ‎እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ አንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት የሚለውን የመንግሥት አቅጣጫ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የተቋሙ አመራር በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቅበታል። ‎ ‎የተቋሙን ሥጋቶችና በባለድርሻ አካላት የሚሰጡ ግበረ መልሶችን በዕቅድ አካቶ ከመስራት አንጻር ክፍተቶች እንደሚስተዋሉም ጠቁመዋል። ‎ ‎ዘርፎች ወደ ኮርፖሬት ፕላኒግ የሥራ ክፍል የተጠናቀቀና መግባባት ላይ የተደረሰበት ጥራት ያለው ዕቅድና ሪፖርት በተቀመጠው ጊዜ በመላክ በዕቅድ እና በሪፖርት አቀራረብ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም እንደሚገባ አሳስበዋል። ‎ ‎ዕቅድና ሪፖርት አዘጋጅቶ ማቅረብ የሁሉም ሥራ ኃላፊዎች ግዴታ መሆኑን የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር በወቅቱ ምላሽ በማይሰጡ የሥራ ዘርፎች ላይ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ዘርፉ በሩብ ዓመቱ የገቢ አሰባሰብ እና ወጪ ቅነሳ ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል ‎.......///........ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ በ2018 በጀት በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በገቢ አሰባሰብ እና ወጪ ቅነሳ ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱን ገለፀ። ‎ ‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት በሩብ ዓመቱ የነዳጅ አጠቃቀምን በጂፒኤስ የአሰራር ሥርዓት በመታገዝ፣ የብቃት ምዘናና ሥልጠናን በራስ አቅም በማከናወን፣ የሠራተኞችን የሰረቪስ ኪራይ በማስቀረት እና የቢሮ መገልገያ ዕቃዎችን ቅድመ ጥገና በማከናወን ወጪ መቀነስ ተችሏል። ‎ ‎ተቋሙ የዕውቅና ሽልማት እንዲያገኙ ዘጠኝ ሠራተኞችን በፈጠራ ሥራ እና 19 በቡድን ሥራ እንዲሁም በሥራ አፈፃፀማቸው ዕውቅና የሚሰጣቸው ሠራተኞችን ለይቶ ለውሳኔ ማቅረቡን ገልፀዋል። ‎ ‎በኢትዮጵያ የትራንስፖርት ዘርፍ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ዕድገት እያሳየ መምጣት በግሪድ ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ የገመገመ የመጀመሪያ የጥናት ረቂቅ ማውጣት መቻሉንም ነው የተናገሩት። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሥልጠና ከወሰዱ 37 የሥራ መሪዎች መካከል 16ቱ ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀት ሲያገኙ 15ቱ በሒደት ላይ እንዲሁም 6ቱ ውጤት ሳይመጣላቸው መቅረቱን አስረድተዋል። ‎ ‎በራስ አቅም የሚከናወኑ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ ስትራቴጂካዊ አመራር መስጠት፣ የተቋሙን የአደረጃጀትና የአሰራር ሥርዓት ማሻሻያ ትግበራ ማጠናቀቅ እና የሰው ኃይል ስብጥር ምጣኔን ማሻሻል እንዲሁም የተቋሙን ስትራቴጂክ ዕቅድ መሰረት ያደረገ የሰው ኃይል ልማት ዕቅድ ማዘጋጀትና መተግበር ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውን አብራርተዋል። ‎ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆንና ትርፋማ ተቋም ለመፍጠር እንዲቻል አመራሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ መስራት አለበት። ‎ ‎ከተቋሙ ገቢ፣ ከሠራተኞች እርካታና ለሥራ መሰጠት፣ ከአመራር ቁርጠኝነት እና ከመረጃ ጥራት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም እንደሚገባ አሳስበዋል። ‎ ‎እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ የተቋሙን ገቢ ከማሳደግ አንፃር የኃይል ሽያጭ የሜትር ንባብን ከሰው ንክኪ የፀዳና በዘመናዊ የአውቶሜሽን ሥርዓት የታገዘ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎችን በየጊዜው መፈተሽ ይገባል። ‎ ‎ከአበል እና ነዳጅ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የሚታዩ የአሰራር ክፍተቶችን ለማረም ዘርፉ አፋጣኝ እርምጃዎችን መውሰድ እንዳለበት ተናግረዋል። ‎ ‎የተቋሙ ሠራተኞች በቁርጠኝነትና በጊዜ የለኝም ስሜት እንዲሰሩ ለማስቻል አመራሩ የክትትልና ድጋፍ ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል አለበት ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎ዘርፉ በሩብ ዓመቱ የታዩ ክፍተቶችን በማረም የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ለማሻሻል ይሰራል ‎......///..... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የታዩ ክፍተቶችን በማረም የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ለማሻሻል እንደሚሰራ ገለፀ። ‎ ‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ የዘርፉን አፈጻጸም ሲያቀርቡ እንደተናገሩት የኃይል ማመንጫ፣ ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመሮች እንዲሁም የሲቪል ሥራዎች ዲዛይን ላይ የተሻለ አፈጻጸም ተመዝግቧል። ‎ ‎በሩብ ዓመቱ የበቆጂ፣ የደብረ ታቦር፣ የደጀን-ደብረ ማርቆስ የማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ እንዲሁም የአሸጎዳ ማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር ቤይ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ እንደነበርም ገልጸዋል። ‎ ‎ለተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች የመዝጊያ ሪፖርት መስራት መቻሉንም ነው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው የጠቆሙት። ‎ ይሁንና ‎በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት አንድ ሥር የሚገኙ ሰባት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ፕሮጄክቶች ግንባታ ላይ ዝቅተኛ አፈጻጸም መመዝገቡን ኢንጂነር ውድነህ ገልጸዋል። ‎ ‎እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍም ዘርፉ የፕሮጀክቶችን መሰረታዊ ችግሮች በመለየት የፋይናንስ እና የፊዚካል አፈጻጸሞችን መገምገሙን ተናግረዋል። ‎ ‎ዘርፉ በሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ላይ የፋይናንስ ወጪን ያገናዘበ የሥራ ጥራት እና ቅልጥፍና መለያዎቹ እንዲሆኑ ግንዛቤ መፍጠርና ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ መቻሉንም አብራርተዋል። ‎ ‎በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ሥር የሚገኙ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ትርፋማ እና ውጤታማ ሆነው እንዲቀጥሉ እንዲሁም ከነባር ፕሮጀክቶች ተንከባለው የመጡ የፋይናንስ ችግሮችን መፍታት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውንም አንስተዋል። ‎ ‎በቀጣይም ዘርፉ በሩብ ዓመቱ የታዩ መልካም ጅምሮችን በማጠናከር እና ክፍተቶቹን በማረም ዓመታዊ ዕቅዱን እንዲያሳካና ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ፣ ጥራት እና ወጪ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ ኢንጂነር ውድነህ አረጋግጠዋል። ‌‎ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ተቋሙ ከዲዛይን ጀምሮ እስከ ፕሮጀክት ትግበራ የሚታዩ ችግሮችን በቅርበት በመፍታት እንዲሁም የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን በማጠናከር የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል እንዲችል ዘርፉን በአዲስ መልክ አዋቅሮ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ ‎ ‎በዘርፉ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት እና በውጭ የሥራ ተቋራጮች የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቁ የሚያስችሉ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በመስራት የኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲቀላጠፉ ለማድረግ ዘርፉ በትኩረት መስራት አለበት ብለዋል። ‎ ‎ዘርፉ ወደ ፊት የተሟላ ሥራ ተቋራጭ ለመሆን ከያዘው ዕቅድ አንፃር ትርፋማ መሆን እንዳለበትና ለዚህም የተቋሙ ከፍተኛ አመራር ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3