fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 542 مشترک است و جایگاه 8 329 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 179 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 542 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 03 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 31 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.36% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.21% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 097 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 520 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 542
مشترکین
-124 ساعت
-167 روز
+3130 روز
آرشیو پست ها
photo content
+9

Mechanical Eng. Applicants

Control and Instrumental
+1
Control and Instrumental

Civil Eng. Applicants
+4
Civil Eng. Applicants

photo content
+1

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

Electrical Eng. Applicants

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪካል ኢንጂነር 1ኛ፤ በሲቪል ኢንጂነር 1ኛ፤ በሜካኒካል ኢንጂነር 1ኛ፤ በኮንትሮል እና ኢንስትሩሜንቴሽን ኢንጂነር 1ኛ እና በሀይድሮሎጂስት 1ኛ የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 13 እና ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ (AASTU) የፅሑፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ለሲቪልኢንጂነር 1ኛ፤ ለሜካኒካል ኢንጂነር 1ኛ፤ ለኮንትሮል እና ኢንስትሩ ሜንቴሽን ኢንጂነር 1ኛ እና ሀይድሮሎጂስት 1ኛ የስራ መደቦች ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ለኤሌክትሪካል ኢንጂነር 1ኛ የስራ መደብ ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ (AASTU) እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

መምሪያው 5 ነጥብ 25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማዳኑን ገለጸ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሥራ ዘርፍ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 5 ነጥብ 25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚያድን የግንባታ ሥራ ማከናወኑንና ለተቋሙ 11 ነጥብ 46 ሚሊዮን ብር ገቢ የሚያስገኝ ሥራ መስራቱን ገለፀ። በበጀት ዓመቱ የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለጹት በዘርፉ ካሉት ስድስት የሥራ ክፍል አንዱ በሆነው በራስ ኃይል የግንባታ መምሪያ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤቱ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ የስራ ክፍሉ በተጠናቀቀው በጀት 11 የሲቪል ግንባታ ፕሮጀክቶችን ፣ሁለት የኤሌክትሮ ሜካኒካል ፕሮጀክቶችን እና አራት የሲቪል ጥገና ስራ ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ለአገልግሎት ማብቃቱ ተብራርቷል፡፡ ቢሮው በሰሜኑ ሀገራችን ከጦርነት ነጻ በወጡ አካባቢዎች በወደሙት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ጥገና ላይ በስፋት መሳተፉ እና የሱሉልታ ደብረ ማርቆስና ጊቤ 3 ሰኮሩ ባለ 400 ኪሎ ቮልተረ የማስተላለፊያ መስመር ጥገና በስኬት ማከናወኑ በግምገማው ወቅት በጥንካሬ ተነስቷል ፡፡ ይሁንና የወሰን ማስከበርና የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት በበጀት ዓመቱ ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነ በግምገማው ላይ ተነስቷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ረጅም ዓመታት የቆሙ ዩኒቶችን ወደ ስራ በማስገባት እና የተጎዱ መስመሮችን በመጠገን ውጤታማ ስራ ማከናወኑ ተገለፀ ........////...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት በተለያዩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለረጅም ዓመታት የቆሙ ዩኒቶችን ጠግኖ ወደ ሥራ በማስገባት ውጤታማ ስራ ማከናወኑን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ጽ/ቤት አስታወቀ። የስራ ክፍሉ የ2014 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሲገመገም እንደተገለፀው ተቋሙ በጢስ አባይ 2ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለ8 ዓመታት ያህል በብልሽት የቆመ 36 ሜጋ ዋት መጫን የሚችል አንድ ዩኒት በራስ አቅም በመጠገን ወደ ሥራ እንዲገባ አድርጓል፡፡ በቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ ለ10 ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ቆሞ የነበረን አንድ ዩኒት በመጠገን ወደ ሥራ አስገብቷል፡፡ በግልገል ጊቤ 2ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በራስ አቅም የሁለት ዩኒቶችን የኖዝል ጥገና በማከናወን በሙሉ አቅማቸው 210 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ እንዲያመነጩ ከማስቻሉም በተጨማሪ ተቋሙ ለውጭ ባለሞያ ያወጣ የነበረውን እስከ 650 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ማስቀረት መቻሉ ተብራርቷል፡፡ በግልገል ጊቤ 1ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመጠባበቂያ ዲዝል ጀኔሬተር ተከላ እና በጊቤ 3ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ ሳሊኒና ዴክ ከተሰኙ ድርጅቶች ጋር በተፈጠረው ስምምነት መሰረት የግድብ ሊኬጅ ጥገና ተከናውኗል፡፡ በጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድቡን ከኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚያገናኘው የግንኙነት ስርዓት (communication system) ብልሽት በመጠገን በዋነኛነት በግሪድ ሥርዓቱ ላይ ኃይል ሲቋረጥ መልሶ ለማገናኘት የሚያስችለውን የብላክ ስታርት ሞድ ወደ ነበረበት ለመመለስ መቻሉም ተብራርቷል፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ከጥገናው በተጨማሪ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለማስተካከል የሚረዱ አሰራሮችን ሲሰራ መቆየቱ ተገልጿል፡፡ በ2014 በጀት ዓመት በራስ አቅም የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የዘርፉ ሰራተኞችን አቅምና በራስ መተማመን ከማሳደጉም በተጨማሪ ተቋሙ ለውጭ ባለሞያ ያወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጭ ማዳን ተችሏል፡፡ በተያያዘም በኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ስራዎች በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀው የህወኃት ቡድን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የፈፀመውን ጉዳት የመጠገን ስራ መሰራቱ ተገምግሟል። የኔትወርክ ቁጥጥር እና ክትትል እንዲሁም ኤሌክትሪክ ጠፍቶ የሚቆይበትን ጊዜ ለመቀነስ የተሰሩት ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ፣ በተጨማሪም የማከፋፈያ ጣቢያዎችና መስመሮች ጥገና እና ፍተሻ ስራ የኤሌክትሪክ መቋረጥን በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱም በጠንካራ ጎን ተነስቷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እና የፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል ........////....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2014 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ (OPGW) ኪራይ ከ15 ነጥብ 79 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን በተቋሙ የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ። የበጀት ዓመቱ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ህይወት እሸቱ እንደገለፁት ከሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ፣ ከኃይል ኤክስፖርት እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ 15 ነጥብ 79 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ20 ነጥብ 75 ቢሊየን ብር በላይ ሽያጭ በማከናወን የእቅዱን 107 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡ የተቋሙ የፋይናንስ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ከሽያጩ ውስጥ ከ14 ነጥብ 44 ቢሊዮን ብር በላይ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ፣ ከ834 ነጥብ 16 ሚሊዮን ብር በላይ ከከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች፣ ከ418 ነጥብ 57 ሚሊዮን ብር በላይ ለኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ከቀረበ የኃይል ሽያጭ የተገኘ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም 94 ሚሊዮን ብሩ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያና ዌብስፕሪክስ አይሲቲ ሶሉሽን የተባሉ ኩባንያዎች ከተጠቀመበት የፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ የተገኘ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥ አገልግሎት የሚውል 13 ሺህ 262 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ታቅዶ 10 ሺህ 325 ኪሎ ዋት ሰዓት በማቅረብ የእቅዱን 77 ነጥብ 8 በመቶ ማሳካት መቻሉ በግምገማው ላይ ተነስቷል። በበጀት ዓመቱ የተሰበሰበውን ገቢ ለማግኘት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 9 ሺህ 472 ነጥብ 2 ኪሎ ዋት ሰዓት፣ ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች 7 መቶ 44 ነጥብ 5 ኪሎ ዋት እንዲሁም ለኢትዮ- ጂቡቲ ምድር ባቡር 108 ነጥብ 9 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ ተችሏል፡፡ ተቋሙ በ2014 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ የሰበሰበው ገቢ ከ2013 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 98 ቢሊዮን ብር በላይ ወይም የ11.16 በመቶ ብልጫ ያለው ነው ፡፡ እንደ አቶ ደመረ አሰፋ ገለፃ ተቋሙ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ አማራጮቹን በማስፋት በበጀት ዓመቱ ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያና ዌብስፕሪክስ አይሲቲ ሶሉሽን ለተባሉ ኩባንያዎች የፋይበር ኦፕቲክስ በማከራየት ተጨማሪ ከ4 ነጥብ 95 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ችሏል። ይህም ለተቋሙ የገቢ አፈጻጸም ማደግ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር ጊቨርስ (ሞግዚት) የስራ መደብ ባለሙያዎችን ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች
+3
ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር ጊቨርስ (ሞግዚት) የስራ መደብ ባለሙያዎችን ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሜክሲኮ በሚገኘው ኬ ኬር ህንፃ ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ 20ኛ /ሃያኛ ፎቅ/ የፅሑፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል አድሃ- አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡ ኢድ ሙባረክ

photo content
+4

በፖወር ኢንጂነሪንግ የትምህርት መስክ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሰራተኞች ተመረቁ ……///……. በጅማ ዩኒቨርሲቲ በፓወር ኢንጂነሪንግ የትምህርት መስክ የሁለተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የግልገል ጊቤ 1 እና 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ስድስት ሠራተኞች ሰኔ 25 ቀን 2014 ዓ.ም ተመርቀዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጅ ኢንስትቲዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ኤፍሬም ዋቅጅራ እንደተናገሩት ለምረቃ የበቁ ሠራተኞች በስራ ገበታቸው ላይ በመሆን ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ነበር፡፡ በስራ ቦታቸው ላይ ላይ በመሆን ትምህርታቸውን በመከታተላቸው እውቀታቸውንና የስራ ልምዳቸውን ለተቋሙ በአግባቡ እንዲያውሉና የሠው ኃይል እጥረት እንዳይከሰት በማድረግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ምህንድስና ትምህርት ክፍል ዲን አቶ ብርሃኑ በለጠ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ዕድልን በቀላሉ ወደማያገኙ የስራ ቦታዎች በመሄድ ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ሠራተኞች ከሥራቸው ሳይስተጓኮሉ ማስመረቅ መቻሉን ገልፀዋል፡፡ አሁን ከተመረቁት በተጨማሪ 23 የግልገል ጊቤ 1 ሠራተኞች የሁለተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ እንደሚገኙ እና የመመረቂያ ጽሁፋቸውን ያላቀረቡ አራት ተማሪዎች ደግሞ ጽሑፋቸውን አጠናቀዉ በቅርብ ቀን ሊመረቁ እንደሚችሉ አስታውቀዋል፡፡ ከተቋሙ ጋር ያለውን የጋራ ትብብር ለማጠናቀር በቀጣይ ጊቤ 2 እኛ 3 መሰል የመማር ማስተማር ስራዎችን ለመጀመር ከተቋሙ ጋር እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል በኃይል ማመንጫዎች ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የክላስተር አንድ ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ዘለቀ እንደተናገሩት ትምህርቱን በወቅቱ ለማጠናቀቅ በግልገል ጊቤ 2 የተከሰተው አደጋና ሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ፈተና ሆነው ነበር ብለዋል፡፡ ይሁንና ይህን ፈተና በማለፍ መመረቅ በመቻላቸው እንደተደሰቱ በመግለጽ እርሳቸውን ጨምሮ ሌሎች ሠራተኞች ተቋሙ ከሚያከናውነው የስራ ጸባይ ጋር በሚገናኝ የትምህርት ዘርፍ መማራቸው ተቋሙ እያከናወነ ላለው የለውጥ ስራ የራሱን አስተዋጽዖ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡ በማመንጫ ጣቢያዎች የሠራተኛ ፍልሰትን ለመቀነስ ተቋሙ ማመንጫ ጣቢያዎቹ ባሉበት አካባቢ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተቋማዊ የሆነ ስምምነት በማድረግ ሠራተኞች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልፀዋል፡፡ ሌሎች ተመራቂዎች በበኩላቸው ትምህርቱን በመከታተል ላይ እያሉ በግልገል ጊቤ 2 ተከስቶ በነበረው የመኪና አደጋ ምክንያት ደርሶባቸው ከነበረው አካላዊና የስነ ልቦና ቀውስ ወጥተው ትምህርቱን ማጠናቀቅ በመቻላቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ ተመራቂዎቹ ተቋሙ ላደረገላቸው ድጋፍ አመስግነው ያስተማራቸውን ተቋም ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 27 ቀን 2014 ዓ.ም