EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 542 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 329,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 179 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 542 名订阅者。
根据 03 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 31,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.36%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.21% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 097 次浏览,首日通常累积 2 520 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 04 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 542
订阅者
-124 小时
-167 天
+3130 天
帖子存档
15 542
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪካል ኢንጂነር 1ኛ፤ በሲቪል ኢንጂነር 1ኛ፤ በሜካኒካል ኢንጂነር 1ኛ፤ በኮንትሮል እና ኢንስትሩሜንቴሽን ኢንጂነር 1ኛ እና በሀይድሮሎጂስት 1ኛ የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 13 እና ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ (AASTU) የፅሑፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ለሲቪልኢንጂነር 1ኛ፤ ለሜካኒካል ኢንጂነር 1ኛ፤ ለኮንትሮል እና ኢንስትሩ ሜንቴሽን ኢንጂነር 1ኛ እና ሀይድሮሎጂስት 1ኛ የስራ መደቦች ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30
ለኤሌክትሪካል ኢንጂነር 1ኛ የስራ መደብ ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ (AASTU) እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
15 542
መምሪያው 5 ነጥብ 25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማዳኑን ገለጸ
.......///.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሥራ ዘርፍ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 5 ነጥብ 25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚያድን የግንባታ ሥራ ማከናወኑንና ለተቋሙ 11 ነጥብ 46 ሚሊዮን ብር ገቢ የሚያስገኝ ሥራ መስራቱን ገለፀ።
በበጀት ዓመቱ የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለጹት በዘርፉ ካሉት ስድስት የሥራ ክፍል አንዱ በሆነው በራስ ኃይል የግንባታ መምሪያ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤቱ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
የስራ ክፍሉ በተጠናቀቀው በጀት 11 የሲቪል ግንባታ ፕሮጀክቶችን ፣ሁለት የኤሌክትሮ ሜካኒካል ፕሮጀክቶችን እና አራት የሲቪል ጥገና ስራ ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ለአገልግሎት ማብቃቱ ተብራርቷል፡፡
ቢሮው በሰሜኑ ሀገራችን ከጦርነት ነጻ በወጡ አካባቢዎች በወደሙት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ጥገና ላይ በስፋት መሳተፉ እና የሱሉልታ ደብረ ማርቆስና ጊቤ 3 ሰኮሩ ባለ 400 ኪሎ ቮልተረ የማስተላለፊያ መስመር ጥገና በስኬት ማከናወኑ በግምገማው ወቅት በጥንካሬ ተነስቷል ፡፡
ይሁንና የወሰን ማስከበርና የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት በበጀት ዓመቱ ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነ በግምገማው ላይ ተነስቷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም
15 542
ተቋሙ ረጅም ዓመታት የቆሙ ዩኒቶችን ወደ ስራ በማስገባት እና የተጎዱ መስመሮችን በመጠገን ውጤታማ ስራ ማከናወኑ ተገለፀ
........////......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት በተለያዩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለረጅም ዓመታት የቆሙ ዩኒቶችን ጠግኖ ወደ ሥራ በማስገባት ውጤታማ ስራ ማከናወኑን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ጽ/ቤት አስታወቀ።
የስራ ክፍሉ የ2014 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሲገመገም እንደተገለፀው ተቋሙ በጢስ አባይ 2ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለ8 ዓመታት ያህል በብልሽት የቆመ 36 ሜጋ ዋት መጫን የሚችል አንድ ዩኒት በራስ አቅም በመጠገን ወደ ሥራ እንዲገባ አድርጓል፡፡
በቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ ለ10 ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ቆሞ የነበረን አንድ ዩኒት በመጠገን ወደ ሥራ አስገብቷል፡፡
በግልገል ጊቤ 2ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በራስ አቅም የሁለት ዩኒቶችን የኖዝል ጥገና በማከናወን በሙሉ አቅማቸው 210 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ እንዲያመነጩ ከማስቻሉም በተጨማሪ ተቋሙ ለውጭ ባለሞያ ያወጣ የነበረውን እስከ 650 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ማስቀረት መቻሉ ተብራርቷል፡፡
በግልገል ጊቤ 1ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመጠባበቂያ ዲዝል ጀኔሬተር ተከላ እና በጊቤ 3ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ ሳሊኒና ዴክ ከተሰኙ ድርጅቶች ጋር በተፈጠረው ስምምነት መሰረት የግድብ ሊኬጅ ጥገና ተከናውኗል፡፡
በጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድቡን ከኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚያገናኘው የግንኙነት ስርዓት (communication system) ብልሽት በመጠገን በዋነኛነት በግሪድ ሥርዓቱ ላይ ኃይል ሲቋረጥ መልሶ ለማገናኘት የሚያስችለውን የብላክ ስታርት ሞድ ወደ ነበረበት ለመመለስ መቻሉም ተብራርቷል፡፡
ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ከጥገናው በተጨማሪ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለማስተካከል የሚረዱ አሰራሮችን ሲሰራ መቆየቱ ተገልጿል፡፡
በ2014 በጀት ዓመት በራስ አቅም የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የዘርፉ ሰራተኞችን አቅምና በራስ መተማመን ከማሳደጉም በተጨማሪ ተቋሙ ለውጭ ባለሞያ ያወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጭ ማዳን ተችሏል፡፡
በተያያዘም በኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ስራዎች በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀው የህወኃት ቡድን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የፈፀመውን ጉዳት የመጠገን ስራ መሰራቱ ተገምግሟል።
የኔትወርክ ቁጥጥር እና ክትትል እንዲሁም ኤሌክትሪክ ጠፍቶ የሚቆይበትን ጊዜ ለመቀነስ የተሰሩት ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ፣ በተጨማሪም የማከፋፈያ ጣቢያዎችና መስመሮች ጥገና እና ፍተሻ ስራ የኤሌክትሪክ መቋረጥን በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱም በጠንካራ ጎን ተነስቷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም
15 542
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እና የፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል
........////.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2014 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ (OPGW) ኪራይ ከ15 ነጥብ 79 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን በተቋሙ የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ።
የበጀት ዓመቱ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ህይወት እሸቱ እንደገለፁት ከሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ፣ ከኃይል ኤክስፖርት እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ 15 ነጥብ 79 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ20 ነጥብ 75 ቢሊየን ብር በላይ ሽያጭ በማከናወን የእቅዱን 107 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡
የተቋሙ የፋይናንስ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ከሽያጩ ውስጥ ከ14 ነጥብ 44 ቢሊዮን ብር በላይ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ፣ ከ834 ነጥብ 16 ሚሊዮን ብር በላይ ከከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች፣ ከ418 ነጥብ 57 ሚሊዮን ብር በላይ ለኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ከቀረበ የኃይል ሽያጭ የተገኘ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም 94 ሚሊዮን ብሩ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያና ዌብስፕሪክስ አይሲቲ ሶሉሽን የተባሉ ኩባንያዎች ከተጠቀመበት የፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ የተገኘ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥ አገልግሎት የሚውል 13 ሺህ 262 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ታቅዶ 10 ሺህ 325 ኪሎ ዋት ሰዓት በማቅረብ የእቅዱን 77 ነጥብ 8 በመቶ ማሳካት መቻሉ በግምገማው ላይ ተነስቷል።
በበጀት ዓመቱ የተሰበሰበውን ገቢ ለማግኘት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 9 ሺህ 472 ነጥብ 2 ኪሎ ዋት ሰዓት፣ ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች 7 መቶ 44 ነጥብ 5 ኪሎ ዋት እንዲሁም ለኢትዮ- ጂቡቲ ምድር ባቡር 108 ነጥብ 9 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ ተችሏል፡፡
ተቋሙ በ2014 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ የሰበሰበው ገቢ ከ2013 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 98 ቢሊዮን ብር በላይ ወይም የ11.16 በመቶ ብልጫ ያለው ነው ፡፡
እንደ አቶ ደመረ አሰፋ ገለፃ ተቋሙ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ አማራጮቹን በማስፋት በበጀት ዓመቱ ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያና ዌብስፕሪክስ አይሲቲ ሶሉሽን ለተባሉ ኩባንያዎች የፋይበር ኦፕቲክስ በማከራየት ተጨማሪ ከ4 ነጥብ 95 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ችሏል። ይህም ለተቋሙ የገቢ አፈጻጸም ማደግ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም
15 542
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር ጊቨርስ (ሞግዚት) የስራ መደብ ባለሙያዎችን ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሜክሲኮ በሚገኘው ኬ ኬር ህንፃ ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ 20ኛ /ሃያኛ ፎቅ/ የፅሑፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
15 542
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል አድሃ- አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡
ኢድ ሙባረክ
15 542
በፖወር ኢንጂነሪንግ የትምህርት መስክ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሰራተኞች ተመረቁ
……///…….
በጅማ ዩኒቨርሲቲ በፓወር ኢንጂነሪንግ የትምህርት መስክ የሁለተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የግልገል ጊቤ 1 እና 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ስድስት ሠራተኞች ሰኔ 25 ቀን 2014 ዓ.ም ተመርቀዋል፡፡
በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጅ ኢንስትቲዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ኤፍሬም ዋቅጅራ እንደተናገሩት ለምረቃ የበቁ ሠራተኞች በስራ ገበታቸው ላይ በመሆን ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ነበር፡፡
በስራ ቦታቸው ላይ ላይ በመሆን ትምህርታቸውን በመከታተላቸው እውቀታቸውንና የስራ ልምዳቸውን ለተቋሙ በአግባቡ እንዲያውሉና የሠው ኃይል እጥረት እንዳይከሰት በማድረግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡
በዩኒቨርሲቲው የኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ምህንድስና ትምህርት ክፍል ዲን አቶ ብርሃኑ በለጠ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ዕድልን በቀላሉ ወደማያገኙ የስራ ቦታዎች በመሄድ ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ሠራተኞች ከሥራቸው ሳይስተጓኮሉ ማስመረቅ መቻሉን ገልፀዋል፡፡
አሁን ከተመረቁት በተጨማሪ 23 የግልገል ጊቤ 1 ሠራተኞች የሁለተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ እንደሚገኙ እና የመመረቂያ ጽሁፋቸውን ያላቀረቡ አራት ተማሪዎች ደግሞ ጽሑፋቸውን አጠናቀዉ በቅርብ ቀን ሊመረቁ እንደሚችሉ አስታውቀዋል፡፡
ከተቋሙ ጋር ያለውን የጋራ ትብብር ለማጠናቀር በቀጣይ ጊቤ 2 እኛ 3 መሰል የመማር ማስተማር ስራዎችን ለመጀመር ከተቋሙ ጋር እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል በኃይል ማመንጫዎች ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የክላስተር አንድ ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ዘለቀ እንደተናገሩት ትምህርቱን በወቅቱ ለማጠናቀቅ በግልገል ጊቤ 2 የተከሰተው አደጋና ሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ፈተና ሆነው ነበር ብለዋል፡፡
ይሁንና ይህን ፈተና በማለፍ መመረቅ በመቻላቸው እንደተደሰቱ በመግለጽ እርሳቸውን ጨምሮ ሌሎች ሠራተኞች ተቋሙ ከሚያከናውነው የስራ ጸባይ ጋር በሚገናኝ የትምህርት ዘርፍ መማራቸው ተቋሙ እያከናወነ ላለው የለውጥ ስራ የራሱን አስተዋጽዖ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡
በማመንጫ ጣቢያዎች የሠራተኛ ፍልሰትን ለመቀነስ ተቋሙ ማመንጫ ጣቢያዎቹ ባሉበት አካባቢ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተቋማዊ የሆነ ስምምነት በማድረግ ሠራተኞች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልፀዋል፡፡
ሌሎች ተመራቂዎች በበኩላቸው ትምህርቱን በመከታተል ላይ እያሉ በግልገል ጊቤ 2 ተከስቶ በነበረው የመኪና አደጋ ምክንያት ደርሶባቸው ከነበረው አካላዊና የስነ ልቦና ቀውስ ወጥተው ትምህርቱን ማጠናቀቅ በመቻላቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
ተመራቂዎቹ ተቋሙ ላደረገላቸው ድጋፍ አመስግነው ያስተማራቸውን ተቋም ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሰኔ 27 ቀን 2014 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
