fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 542 مشترک است و جایگاه 8 329 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 179 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 542 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 03 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 31 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.36% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.21% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 097 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 520 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 542
مشترکین
-124 ساعت
-167 روز
+3130 روز
آرشیو پست ها
በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ተጨማሪ የብር እና የነሀስ ሜዳልያ አግኝተናል። ወርቅውሀ ጌታቸው በ8:54.61 በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ መቅደስ አበበ ደግሞ በ8:56.08 በሶስተኛነት
+2
በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ተጨማሪ የብር እና የነሀስ ሜዳልያ አግኝተናል። ወርቅውሀ ጌታቸው በ8:54.61 በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ መቅደስ አበበ ደግሞ በ8:56.08 በሶስተኛነት ውድድሯን ጨርሳለች። እንኳን ደስ አለን! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም

ኢትዮ ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ክለብ የብር ሜዳልያ አሸናፊ መሆኑን አረጋገጠ ……..//////………. በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮ ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ክለብ ሁለት ጨዋታ እየቀረው ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ መሆኑን አረጋግጧል። ክለቡ የዓመቱን የፕሪሜርሊግ ዋንጫ ለማሸነፍ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር እስከመጨረሻው የተፎካከረ ቢሆንም ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። ይህ ውጤት በኢትዮ ኤሌክትሪክ በሴቶች እግር ኳስ ታሪክ ከፍተኛ ውጤት ሲሆን የክለቡ ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቧል። ክለቡ በዚህ ዓመት ካደረጋቸው 22 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች መካከል 16 ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ በአራቱ አቻ፣ በሁለት ጨዋታዎች ደግሞ ሽንፈት ገጥሞት በድምሩ 55 ነጥብ መያዝ ችሏል። በዚህ የውድድር ዓመት ኢትዮ ኤሌክትሪክ 55 ጎሎችን በተቃራኒ ቡድን መረብ ላይ በማሳረፍ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀጥሎ ብዙ ጎል ያስቆጠረ ክለብ ሆኗል። በዚህ ውድድር ዓመት 19 ተከታታይ ጨዋታዎችን ሳይሸነፍ በመጓዝም ለራሱ ያለመሸነፍ ክብረወሰን ማስመዝገብ ችሏል። በአዳማ ከተማ እየተካሔደ የሚገኘው የ2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሜርሊግ በሚቀጥለው ሳምንት ፍፃሜውን ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+5

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተቋሙ በራስ አቅም የገነባቸውን 17 ፕሮጀክቶች ማጠናቀቅ ችሏል …….////…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ስር በሚገኙ ሦስት የስራ ክፍሎች ሲከናወኑ የነበሩ 17 የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ መቻሉን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ ጽ/ቤቱ እንዳስታወቀው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመምሪያው ስር በሚገኙ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ፣ ሲቪል ሰራዎች ግንባታ እና ሲቪል ሥራዎች ጥገና ቢሮዎች ሲከናወኑ የነበሩ 17 የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት በቅተዋል፡፡ በመምሪያው በመከናወን ላይ ከሚገኙት 37 የተለያዩ ፕሮጀክቶች መካከል 20 ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ 17 ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውና የተቀሩት ሦስት ፕሮጀክቶች ግን በሲሚንቶ አቅርቦት ችግርና በማሽነሪ ብልሽት ምክንያት በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሰረት አለመጠናቀቃቸውን ጽ/ቤቱ አስታውቋል፡፡ ከተጠናቀቁት ፕሮጀክቶች መካከል ሁለቱ በኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ ቢሮ፣ 11 በሲቪል ሥራዎች ግንባታ ቢሮ አራቱ ደግሞ በሲቪል ሥራዎች ጥገና ቢሮ የተከናወኑ መሆናቸውን ጽ/ቤቱ አመልክቷል፡፡ በመምሪያው ከሚከናወኑት ፕሮጀክቶች መካከል አስሩን በ2015 በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ለማከናወን ከያዛቸው ፕሮጀክቶች መካከል 23ቱ በሲቪል ግንባታ ቢሮ፣10 በሲቪል ጥገና ቢሮ እንዲሁም 4ቱ በኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ ቢሮ የሚከናወኑ ናቸው፡፡ መምሪያው ለማከናወን በእቅድ ከያዛቸው ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ከጦርነት ነፃ በወጡ አካባቢዎች የወደሙትን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን የጥገና ስራ እና የደብረ ዘይት አየር ኃይል ግቢ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ እና የማስዋብ ስራን አከናውኗል፡፡ የፕሮጀክቶች የግንባታ ስራ በራስ ኃይል መከናወኑ የሀገር በቀል አቅምን በማሳደግ እና ወጪን በመቀነስ በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ሲሆን በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት መምሪያው ባከናወናቸው ስራዎችም 5 ነጥብ 25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማዳን መቻሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በራስ ኃይል መገንባት የጀመረው በ1973 ዓ.ም በባለ 45 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+7

ከተማ አስተዳደሩ ተቋሙ ለሚያከናውነው ሥራ አስፈላጊውን ድጋፍ አደርጋለሁ አለ ………////……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን መምሪያ በድሬዳዋ ከተማ ለማስገንባት ላቀደው G+7 ህንፃ የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳድር ከንቲባ አረጋገጡ፡፡ ከንቲባው ከድር ጁዋር የሪጅኑን ቢሮ እና የሥራ እንቅስቃሴ ከጎበኙ በኋላ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጠቅላላ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት እና ከትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ከተውጣጣ ቡድን ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይቱም በከተማ አስተዳደሩ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ስላለው የንብረት አጠቃቀም፣ በድሬዳዋ ከተማዋ ውስጥ ሊገነባ በታቀደው G+7 የምስራቅ ሪጅን መምሪያ ዋና ቢሮ ግንባታ ዕቅድ እና ከከተማ አስተዳደሩ በሚፈለጉ ድጋፎች ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ የቡድኑ መሪ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋሲሊቲ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ እንደገለጹት በሪጅኑና በከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም በሪጅኑና በሌሎች የመንግስት መ/ቤቶች መካከል ተቀራርቦ የመስራት ሰፊ ክፍተት አለ፡፡ በመሆኑም ክፍተቶቹን መሙላት በሚቻልበት እና የከተማዋ አገልግሎት ሰጪ መስሪያ ቤቶች ሪጅኑን መደገፍ በሚችሉበት ሁኔታ በቅርበት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ስራ አስፈጻሚን ወክለው በስፍራው የተገኙት የኦፕሬሽን ሰርቪስ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ እስማኤል ሙዘይን በበኩላቸው የድሬዳዋ ቁጥር 1 እና የድሬዳዋ ቁጥር 3 ኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥበቃና የደህንነት ጉዳዮች ላይ እንዲሁም የድሬዳዋ ቁጥር 1 - ሐሮማያ 66ኪቮ ፕሮጀክት መጀመር በሚችልበት ሁኔታ ገለፃ በማድረግ የከተማ አስተዳደሩን ድጋፍ ጠይቀዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳድር ከንቲባ ከድር ጁዋር እንደገለፁት መስተዳድራቸው ተቋሙ ለሚያከናውነው ሥራ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማው የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም የሱፍ ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ ሪጅኑ ለድሬዳዋ ከተማ ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ ኢትዮጵያ ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን እንደተገነዘቡ ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም የሪጅኑ የስራ ኃላፊዎች ከህዝብና ከመንግስት ተቋማት ጋር ጠንካራ ግንኙነት በመፍጠር ተቀራርበው እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡ ማዕከሉን በድሬዳዋ ከተማ ያደረገው የምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን መምሪያ ከአዋሽ ጀምሮ በምዕራብና ምስራቅ ሐረርጌ ዞኖች፣ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር፣ በሐረሪ እና በሶማሌ ክልሎች ከ1ሺህ አምስት መቶ ኪሎ ሜትሮች በላይ የሚሸፍኑ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የመጠገንና የኦፕሬሽን ሥራዎችን ይሰራል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+4

ኃይል የማስተላለፍና የማከፋፈል ስራውን አስተማማኝ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሰራ ነበር ……///….. የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ያልተቆራረጠ፣ ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ ለማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የፍተሻና ጥገና ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን አስታወቀ፡፡ የዘርፉ የ2014 ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት እንደሚያሳየው አስተማማኝ የሆነ የኃይል አቅርቦት እንዲኖርና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት በ37 ሺህ 580 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ላይ የፍተሻ ሥራ ለመሥራት እቅድ ተይዞ በ30 ሺህ 481 ኪሎ ሜትር ላይ ፍተሻ ተከናውኗል፡፡ ከፍተሻ ሥራው በተጓዳኝ የ24 ሺህ 122 ኪሎ ሜት የማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሥራ ለማከናወን ታቅዶ በ21 ሺህ 514 ኪሎ ሜርት ላይ ጥገና በማከናወን የዕቅዱን 89.19% መሳካቱን ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡ በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ ለአስቸኳይ ጥገና ክስተቶች ምላሽ በመስጠት ውጤታማ የሆኑ የጥገና ስራዎች መከናወናቸውም በሪፖርቱ ተዘርዝሯል፡፡ በአንዳንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የስማርት ቆጣሪ ተከላ፣ ፍተሻና የኮሚሽኒንግ ስራዎችን፤ የአቅም ማሳደግ፣ የመልሶ ግንባታና የኢንሱሌተር መቀየር ስራዎችን በራስ አቅም በማከነወን እንዲሁም የትርፍ ሰዓት ክፍያ ከ10 በመቶ በላይ እንዳይሆን በማድረግ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መቀነስ መቻሉም ተጠቅሷል፡፡ ለስራ ዘርፉ ከተሰጠው ኃላፊነት በተጨማሪ በስሩ የሚገኙ ሠራተኞችን በማስተባበር ከ1 ነጥብ 14 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብና በዓይነት የተለያዩ ድጋፎችን ማድረግ መቻሉን ተችሏል፡፡ ሀገር አቀፍ የኃይል መቆራረጥ መቀነስ መቻሉ፣ የአቅም ማሳደግና መልሶ ግንባታ ስራዎችን በራስ አቅም ማከናወን መጀመሩ፣ በጦርነት የወደመውን የሰሜን ኢትዮጵያን መሰረተ ልማት መልሶ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውስጥ ማከናወን መቻሉ የበጀት ዓመቱ ጠንካራ ጎኖች ተደርገው ተለይተዋል፡፡ በአንፃሩ የመለዋወጫ ዕቃዎችና የፍተሻና የጥገና መሳሪያዎች በተፈለገው መጠንና ጊዜ አለመቅረብ፣ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ስርቆቶች መበራከትና ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ችግሮች በወቅቱ መፍትሄ አለማግኘታቸው በድክመት የሚጠቀሱ መሆናቸው በሪፖርቱ ላይ ተመልክቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

በአሜሪካ ኦሪጎን እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ እስካሁን ስድስት ሜዳሊያዎችን በማግኘት በደረጃ ሰንጠረዡ ከዓለም በሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። አትሌቶቻችን እስ
በአሜሪካ ኦሪጎን እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ እስካሁን ስድስት ሜዳሊያዎችን በማግኘት በደረጃ ሰንጠረዡ ከዓለም በሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። አትሌቶቻችን እስካሁን በውድድሩ ሶስት ወርቅ እና ሶስት ብር ያገኙ ሲሆን ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ እየመራች ትገኛለች። እንኳን ደስ አለን!!!

ተቋሙ በ2014 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2015 ዕቅድ ላይ ከሰራተኞች ጋር ተወያየ ……..///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በ2014 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2015 በጀት ዓመት ዋና ዋና ዕቅዶች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ በዋናነት በሰው ኃይል አደረጃጀት፣ በፋይናንስ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ በማመንጫ፣በማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ እና የጥገና ሥራዎች እንዲሁም በሪፎርም እና በሌሎችም ተግባራት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ስለተከናወኑ ሥራዎች ገለጻ ተደርጓል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ልደት ዘርይሁን እንዳብራሩት ኃይል በማመንጨት በበጀት ዓመቱ የማያቋርጥ እና አስተማማኝ የኢነርጂ ምርት ለማምረት የሚያስችሉ ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ወጪን በመቀነስ እና ገቢን በማሳደግ ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግ በተከናወነው ሥራ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ከቀረበው ኃይል እንዲሁም ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ተቋሙ 20 ነጥብ 94 ቢሊዮን ብር ሽያጭ ማከናወኑን በሪፖርቱ ገልጸዋል፡፡ በተቋሙ እየተገነቡ የሚገኙትን ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች በቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት እና በ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ግልጽ አይደሉም ባሏቸው ሀሳቦች ላይ ጥያቄዎችን በማንሳት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 11 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ15 ሺህ 4 መቶ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨት ተችሏል ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2014 በጀት ዓመት 15 ሺህ 487 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨቱን የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ ጽ/ቤቱ እንደገለፀው በ2014 በጀት ዓመት 17 ሺህ 953 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ 15 ሺህ 487 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ተችሏል፡፡ በበጀት ዓመቱ ማመንጨት ከተቻለው ውስጥ 14 ሺህ 9 መቶ ነጥብ 27 ጌጋ ዋት ሰዓት ወይም 96 ነጥብ 2 በመቶ ከውሃ፣ 557 ነጥብ 66 ጌጋ ዋት ሰዓት ከንፋስ እንዲሁም 29 ነጥብ 2 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከእንፋሎት በማመንጨት የዕቅዱን 86 በመቶ ማሳካቱን ጽ/ቤቱ ገልጿል ፡፡ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ባጋጠመው የፀጥታ ችግር ምክንያት በመሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰ ጉዳት የኃይል ተጠቃሚ ቁጥር በማነሱ በዕቅዱና በአፈፃፀሙ መካከል የ2 ሺህ 466 ጌጋ ዋት ሰዓት ወይም የዕቅዱን 14 በመቶ ልዩነት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ተብሏል፡፡ በበጀት ዓመቱ በተከዜና በአሸጎዳ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ከፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ እንዲሁም በገናሌ ዳዋ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በካሳ ክፍያ ጥያቄ ምክንያት የታቀደውን ያህል ኢነርጂ ማምረት እንዳልተቻለ ነው ጽ/ቤቱ ያስታወቀው፡፡ የ2014 በጀት ዓመት የኢነርጂ ምርት ከ2013 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ300 ጌጋ ዋት ሰዓት ወይም 1 ነጥብ 9 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱም ተገልጿል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በስራ ላይ ከሚገኙት 19 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ውስጥ ጊቤ 3ኛ፣ መልከ ዋከና፣ ፣ ፊንጫ፣ ጢስ አባይ 2ኛ፣ አዋሽ 2ኛ እና 3ኛ እንዲሁም አዳማ 2 የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያዎች ከታቀደላቸዉ በላይ ኃይል አመንጭተዋል። በአንፃሩ አመርቲ ነሼ፣ ጊቤ 1 እና 2፣ ጣና በለስ፣ ቆቃ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና አዳማ 1 የንፋስ ማመንጫ ጣቢያ ያመነጫሉ ተብሎ ከታቀደላቸው በታች ካመነጩ ጣቢያዎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 11 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ከጎፈሬ የትጥቅ አምራች ኩባንያ ጋር የስፖንሰርሺፕ ሥምምነት ተፈራረመ ...........////.............. የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ከጎፈሬ የትጥቅ አምራች ኩባንያ ጋር የ3 ዓመት የስፖንሰርሺፕ ሥምምነት ተፈራረመ። የስፖንሰርሺፕ ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮ- ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ፕሬዚዳንት አቶ ጫላ አማን እና የጎፈሬ ትጥቅ አምራች ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሳሙኤል መኮንን ናቸው። የስፖንሰርሺፕ ሥምምነቱ በቅርቡ ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ለተቀላቀለው የወንዶች የእግርኳስ ቡድን የልምምድ እና የውድድር ትጥቆችን ማቅረብ እንደሆነ ተገልጿል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ፕሬዚዳንት አቶ ጫላ አማን በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ስፖንሰርሺፑ ሃገር በቀል ምርቶችን ከማበረታታት አንፃር ሚናው የጎላ ነው። ትጥቅ አምራች ኩባንያው የክለቡን ታሪክ የሚመጥኑ ትጥቆችን በጊዜ እና በጥራት አምርቶ ማቅረብ እንዳለበት አቶ ጫላ ተናግረዋል። የጎፈሬ ትጥቅ አምራች ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሳሙኤል መኮንን በበኩላቸው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የእግርኳስ ክለብ በኢትዮጵያ የስፖርት ታሪክ አንጋፋ በመሆኑ በጋራ በመስራታችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል። እንደ አቶ ሳሙኤል ገለጻ ሶስት ዓመት በሚቆየው የስፖንሰርሺፕ ፕሮግራም ላይ ክለቡ የጎፈሬ ትጥቆችን በመጠቀም የማስተዋወቅ ሥራ ይሰራል። ለሴቶች እና ለተስፋ የእግር ኳስ ቡድኖችም የልምምድ እና የውድድር ትጥቆችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ሥምምነት ላይ ተደርሷል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው 10 ሺህ የደጋፊ ማሊያዎችን ለመግዛት ሥምምነት ላይ መድረሱንም ነው ለማወቅ የተቻለው። በተያያዘ ዜና ክለቡ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተናን ውል ማራዘሙን አስታውቋል። በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳትፎ ለማድረግ በዝግጅት ላይ የሚገኘው የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የአሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተናን ውል ለተጨማሪ አንድ ዓመት ማራዘሙን በፊርማ ሥምምነቱ ላይ ገልጿል። ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ እጅጉ እና ዋና አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ናቸው። በሥምምነቱ ወቅት አሰልጣኝ ክፍሌ እንደተናገሩት በቀጣይ ዓመት ክለቡን ተፎካካሪ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የእግር ኳስ ቡድኑ በ2015 የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ተጠናክሮ ለመቅረብ ከወዲሁ የአዳዲስ ተጫዋቾችን ዝውውር ለማከናወን በሒደት ላይ መሆኑንም ዋና አሰልጣኙ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

Civil eng applicant

photo content

Hydrologist
Hydrologist

photo content
+4