fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 567 مشترک است و جایگاه 8 356 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 162 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 567 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 24 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 24 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 19 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.91% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.83% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 035 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 465 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 25 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 567
مشترکین
+1924 ساعت
+197 روز
+2430 روز
آرشیو پست ها
photo content
+8

ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ዕውቅና ተሰጣቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በተቋሙ ባላቸው የአመራርነት ሚና እና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ላበረከቱት አስተዋፅኦ የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ በሚል ዕውቅናና ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር በኢነርጂ ዘርፍ ላይ በፈጠራና በአስተዳደር እንዲሁም በልዩ ልዩ ደረጃዎች ተፅዕኖ ለፈጠሩ ሴቶች ዕውቅና ለመስጠት እና በኢነርጂ ዘርፍ ላይ የተሳተፉ ተቋማትና ድርጅቶች ምርታቸውንና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት አውደ ርዕይ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል፡፡ በዕለቱም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤን ጨምሮ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለሆኑ ተጨማሪ ሁለት ሴቶች ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ዕውቅናውን የሰጡት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት የኢነርጂ ዘርፍ ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል፡፡ ዘርፉን ለማሳደግ ብቃት ያለው እና በሁሉም ጾታዎች የተመጣጠነ ባለሙያ እንደሚያስፈልግ ገልፀው ሚኒስቴሩም ሴቶችን ወደ ዘርፉ ለማምጣት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ ማህበሩ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ያለውን የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እና ብቃት ያለው ባለሙያ ለመፍጠር እየሰራ ካለው ሥራ ጎን ለጎን በዘርፉ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ሴቶችን ዕውቅና ለመስጠት የሚያደርገውን ጥረት አመስግነው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለማህበሩ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር ፕሬዚዳንት እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ የሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር ቢሮ ሪዚደንት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሪት አደይ ጌታቸው በበኩላቸው ማህበሩ ባለፉት ሦስት ዓመታት በኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለሆኑ ዘጠኝ ሴቶች ዕውቅና መስጠቱን አስታውሰዋል፡፡ በዛሬው ዕለት በተካሄደው መርሃ ግብር ከቀረቡ አስር ተወዳዳሪዎች መካከል ለሦስት የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች ዕውቅናና ሽልማት መሰጠቱንም ጠቁመዋል፡፡ ዕውቅናዉ ሴት ባለሙያዎች በኢነርጂ ዘርፍ የሚያደርጉትን አስተዋጽዖ ለማስተዋወቅ፣ ለማበረታታት እና ለማክበር እንዲሁም ወጣት ሴቶች በዘርፉ እንዲሰማሩና ለሌሎች ዓርአያ እንዲሆኑ ለማድረግ እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡ በዕለቱ ዕውቅና ከተሰጣቸው መካከል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ማህበሩ ላበረከተላቸው ዕውቅና አመስግነው ዕውቅናው በተቋሙ ባላቸው የአመራርነት ሚና፣ የተቋሙን ሴት ሠራተኞች ጫና ለማቃለል እና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ላበረከቱት አስተዋፅኦ እንደተሰጣቸውም ተናግረዋል:: ዓላማን ለማሳካት ዛሬ ከትላንት የተሻለ እንደሆነ በመገንዘብና ምቹ ሁኔታዎችን በመጠቀም በትጋት መስራት እንደሚጠበቅ የተናገሩት ወ/ሮ ሌንሴ የተሻለ ነገር ለማግኘት ሴቶች ያላቸውን አቅም አሟጠው መጠቀም እንደሚገባቸውም አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር (EWiEN) በኢነርጂ ዘርፍ ያለውን የሥርዓተ-ፆታ ክፍተት ለማመጣጠን በማሰብ በአምስት ሴት ባለሙያዎች የተመሠረተ ለትርፍ ያልተቋቋመና መንግሥታዊ ያልሆነ ማህበር ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ የእድሳት ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው .........//........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር የሚያስችሉ የእድሳት ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የጣቢያው የአስተዳደር፣ ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ተሻገር እንደተናገሩት ጣቢያው ከ37 ዓመት በላይ እድሜ ያስቆጠረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመዝናኛ ሥፍራዎችና የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ እድሳት እየተደረገ ነው። አስር መኖሪያ ቤቶችንና ባለ አንድ ፎቅ የእንግዳ ማረፊያ ቤት ላይ የእድሳት ስራ መጠናቀቁን የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ የቀሪ መኖሪያ ቤቶችን እድሳት ሙሉ በሙሉ በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ አቅደው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። የቤት እድሳት ሥራው ቀለም የመቀባትና የኮርኒስ እንዲሁም ያረጁ የቤት ውስጥ እቃዎችን የግዢ ሂደቱን ጠብቆ የመቀየር ሥራንም የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸዋል። የሠራተኞች ክበብ፣ መናፈሻ፣ የመዋኛ ገንዳ እድሳት፣ የክሊኒክ ጥገና እና የመኪና ማቆሚያ እንዲሁም ጋራዥ ሥራ በራስ አቅም እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተጨማሪም ከሠራተኛ መኖሪያ ቤት እስከ ኃይል ማመንጫ ቤቱ ድረስ ያለውን 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ የጥገና ሥራ ለማካሄድ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ሠራተኛው የዕረፍት ጊዜውን የሚያሳልፍባቸው የዲ ኤስ ቲቪ፣ የፑል፣ የኳስ ሜዳና እና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮች በግቢው ውስጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የሠራተኞችና የአካባቢው ልጆች የሚማሩበት ከቅድመ መደበኛ እስከ 8ኛ ክፍል የሚያስተምሩ በግልና በመንግስት የሚተዳዱሩ ሁለት ትምህርት ቤቶች በጣቢያው ግቢ ውስጥ መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ተስፋዬ ከ8ኛ ክፍል በላይ ሲሆኑና ወደ ሮቤ ገርጀዳ ሲሄዱ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጡም አብራርተዋል። በተጨማሪም ከመደወላቡ ዩኒቨርስቲና ከበቆጂ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ሠራተኞችና የሠራተኛ ቤተሰቦች የሚማሩበትን ዕድል ተመቻችቷል ብለዋል። ጣቢያው የመምህራንን ማረፊያ፣ የመመላለሻ ትራንስፖርት፣ የመማሪያ ክፍል እና በኃይል ማመንጫ ቤቱና በማከፋፊያ ጣቢያው ተግባር ተኮር ትምህርት የሚማሩበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን ገልጸዋል። ሠራተኞች ወደ በቆጂና አዳባ ገበያ ሄደው የሚያስፈልጋቸውን ነገር እንዲሸምቱ በገበያ ቀናት ጣቢያው የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። የሠራተኛውን ጤና ለመጠበቅ ሙሉ ሕክምናና የላቦራቶሪ አገልግሎት የሚሰጥ ጤና ጣቢያ በጣቢያው መኖሩን ያስታወሱት አቶ ተስፋዬ ከክሊኒኩ አቅም በላይ ሲሆን አሰላ ከሚገኘው ሮሆቦት ሆስፒታል ጋር ባለው ስምምነት መሰረት ሠራተኛውን ሄዶ በነጻ እንዲታከም የትራንስፓርት አገልግሎት መመቻቸቱን ተናግረዋል። ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት በጣቢያው ሠራተኞች መኖሪያ ግቢ ያለውን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍም በዋናው መ/ቤት በኩል በጀት ተይዞ እየተሰራ ነው ብለዋል። እነዚህ ተግባራት የጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ ተፈጥሮላቸው ተረጋግተው ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲያከናውኑ የሚያስችሉ መሆናቸውንም ገልጸዋል። በቀጣይም ለጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲኖር እና ሙያዊ አቅማቸው እንዲገነባ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። እያንዳንዳቸው 38 ነጥብ 25 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ተርባይኖች ያሉት የመልካ ዋከና የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 95 ቋሚና 37 ጊዜያዊ ሠራተኞች አሉት።    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ተሸንፏል ........///........ በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ዛሬ በተከናወነ የ6ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ ለባዶ ተረቷል። የንግድ ባንክን ብቸኛ የማሸነፊያ ጎል ብርቱካን ገ/ክርስቶስ በ27ኛው ደቂቃ አስቆጥራለች። በጨዋታ የበላይነት የነበረው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በርካታ ግብ ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን ቢያገኝም በሚያስቆጭ ሁኔታ ዕድሎቹን አምክኗል። በአንፃሩ ንግድ ባንኮች ያገኘውን ብቸኛ ዕድል ወደ ጎል በመቀየር ማሸነፍ ችሏል። በ7ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከነማ ጋር ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም ይጫወታል።    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት .........///....... ቅዳሜ ህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም በአንፎ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በዓለምባንክ፣ በአንፎ፣ በቤቴል፣ በአሸዋሜዳ፣ በዲያስፖራ ሰፈር፣ በፊሊዶሮ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ይቆያል። በተመሳሳይ  እሁድ ህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በቆቃ - አዳማ 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 12፡00 እስከ 1፡00 ሰዓት ድረስ በአዳማ እና በአዋሽ ከተማ ኤሌክትሪክ ይቋረጣል። በተጨማሪም እሁድ ህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኮተቤ የኃይል ማስተላለፊያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በኮተቤ ብረታብረት ፣ በኪዳነምህረት፣ በአንቆርጫ እና አካባቢው ፣ በላምበረት መናኸሪያ፣ በእስራኤል ኤምባሲ ፣ በቤተመንግስት ፣ በዑራኤል፣ በጃንሜዳ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ ስለሆነ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ስርቆትን ለመከላከል ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ ሊሰራ ይገባል ........///........ በአፋር ክልል በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል ህብረተሰቡን ባሰተፈ መልኩ እንደሚሰሩ ከክልሉ፣ ከአውሲ ረሱ ዞንና ከተለያዩ ወረዳዎች ከተውጣጡ አመራሮች፣ የፀጥታ አካላት እና የጎሳ መሪዎች ጋር በተካሄደው ውይይት ላይ የተሳተፉ የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ቢልኤ አህመድ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው የስርቆት ወንጀል የብሄራዊ ደህንነት ስጋት እየሆነ መጥቷል። ከዚህ በፊት በስርቆት የወደመውን ንብረት መመለስ ባይቻልም ውድመቱ እንዳይቀጥል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መግባባት ላይ ተደርሶ እየተሰራ እንደሆነ አመልክተዋል። "ስርቆትን መከላከልና የሀገርን ሀብት መጠበቅ ፖሊስ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ማህበረሰብ ኃላፊነት አለበት" ያሉት ኮሚሽነሩ ለዚህም ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት። የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን መሃመድ በበኩላቸው በመሰረተ ልማቶቹ ላይ እየተፈፀመ የሚገኘውን የስርቆት ወንጀል ለማስቆም በየደረጃው ከሚገኙ የተለያዩ የፀጥታ አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል። ለመሠረተ ልማት ስርቆት ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት እንደ ክልል ቁርጥራጭ ብረቶቹን የሚገዙ ነጋዴዎች በክልሉ እንዳይሰማሩ የሚያደርግ አሰራር መዘርጋቱንም ተናግረዋል። በክልሉ የሚፈጠሩ የስርቆት ችግሮችን ለመፍታት የፀጥታ አካላት ኃላፊነት ወስደው እንደሚሰሩ ገልፀው ይህ ውጤታማ እንዲሆን ማህበረሰቡና ተቋሙ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር ተቀራርቦ መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሙሳ አብዶ እንደተናገሩት የክልሉ ማህበረሰብ አኗኗር የተበታተነ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መሠረተ ልማቱን በቅርበት ለመጠበቅ አስቸጋሪ ሊያደርገው ይችላል። ይሁንና ማህበረሰቡ በኃላፊነት ጥበቃ ማድረግ በሚችልበት ሁኔታ ላይ አመራሩ የግንዛቤ ማስጨመጫዎችን በስፋት መስጠት ይጠበቅበታል ብለዋል። የአውሲ ረሱ ዞን ብልፅግና ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ናስር ሃመዱ በበኩላቸው ማህበረሰቡ መሠረተ ልማቱን በኃላፊነት እንዲጠብቅ፣ ስርቆቱ በሀገር ኢኮኖሚ እና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በሚከናወነው ሥራ ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅዕኖ በማስገንዘብ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። ለህብረተሰቡ አገልግሎት በሚሰጡ የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከላከል ከአማራ ክልል የአጎራባች ወረዳዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም አስረድተዋል። የአጎራባች አካባቢዎችም ከዞኑ ማህበረሰብ ጋር ተቀናጅተው በመስራት የስርቆት ወንጀሎችን በትብብር እንዲከላከሉ አቶ ናስር ጥሪ አቅርበዋል። የስርቆት ድርጊቱ የክልሉ መገለጫ እንዳይሆን የፀጥታ ኃይሉ ህብረተሰቡን በማንቃት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ እና ማህበረሰቡም ከፀጥታ ኃይሉ ጎን እንዲቆም ኃላፊዎቹ አሳስበዋል። እንደ ሥራ ኃላፊዎቹ ገለፃ ውይይቱ ለስርቆት ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎችን በመለየት ጥበቃ የሚደረግበትን አግባብ እና የመረጃ ልውውጡ የሚካሄድበትን ሥርዓት ለመዘርጋት ዕድል ይፈጥራል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አቻ ተለያይቷል .........///....... ድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ባለው የኢትዮጵያ የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከነማ ጋር ነጥብ ተጋርቷል። ትናንት ምሽት አንድ ሰዓት የተከናወነው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ያለምንም ግብ ተጠናቋል። ግብ የሚሆኑ ኳሶችን በተደጋጋሚ ሙከራ በማድረግ ድሬዳዋ ከነማ የተሻለ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአንፃሩ በመልሶ ማጥቃት ጎል ለማግኘት ጥረት ሲያደርግ ተስተውሏል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ ኢድሪሱ አብዱላሂ በርካታ ጎል ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን በማዳን ክለቡን ታድጓል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ14 ነጥብ መቻልን ተከትሎ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በጊዜያዊነት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በ10ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ከስሁል ሽረ ጋር የሚጫወት ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋረጠው ኃይል መልሶ ተገናኝቷል …….///……. ለሦስት ዞኖችና ለጋምቤላ ክልል ኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆነውን የበደሌ መቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የመጠገን ሥራ በስኬት ተጠናቋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት ዛሬ ከረፋዱ 4፡50 ጀምሮ ለሦስት ሰዓት ከ30 ደቂቃ ተቋርጦ የነበረውን መስመር ከበደሌ ከተማ የተንቀሳቀሰው የጥገና ባለሙያዎች ቡድን ወደነበረበት እንዲመለስ አድርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም

በሦስት ዞኖችና ጋምቤላ ክልል ኃይል ተቋርጧል …….///……. ከበደሌ መቱ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት ዛሬ ከረፋዱ 4፡50 ጀምሮ በኢሉባቦር ዞን ያዩ በተባለ አካባቢ ኮንዳክተር ተበጥሷል፡፡ በዚህ የተነሳ በኢሉ አባቦር ዞን፣ በሸካ ዞን እና በቄለም ወለጋ ዞን እንዲሁም በጋምቤላ ክልል ኃይል መቋረጡን ገልፀዋል፡፡ የተበጠሰውን መስመር ለመጠገን ከበደሌ ከተማ የጥገኛ ባለሙያዎች ወደ ሥፍራው መንቀሳቀሳቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመው ችግሩ እስኪፈታ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በክልሉ የመሰረተ ልማት ስርቆትን ለማስቆም ሁሉም በቅንጅት እንዲሰራ ተጠየቀ ........///........ በአፋር ክልል እየተፈፀመ ያለውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ለማስቆም ሁሉም በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአፋር ክልል የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አሳሰቡ። በክልሉ እየተፈፀመ ያለውን የኃይል መሰረተ ስርቆት ለመከላከል ከክልሉ፣ ከአውሲ ረሱ ዞን፣ ከዱብቲ፣ ሚሌና አዳአር ወረዳዎች፣ ከሰመራና ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከተውጣጡ አመራሮችና የፀጥታ አካላት እንዲሁም ከጎሳ መሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአፋር ክልል የመልካም አስተዳደር ክላስተር  አስተባባሪ አቶ አህመድ ሁሴን እንደተናገሩት የኤሌክትሪክ ኃይል ለክልሉ ማህበረሰብ ለልማት ብቻ ሳይሆን ለእስትንፋሱም ፋይዳው የጎላ ነው። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት በማህበረሰቡ የአኗኗር ዘይቤ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ መጥቷል ብለዋል። በኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል በየደረጃው ያለው የክልሉ አመራር፣ የፀጥታ አካላት እና ማህበረሰቡ በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡም አሳስበዋል። የአፋር ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን በበኩላቸው ኤሌክትሪክ ለክልሉ ማህበረሰብ የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ በመሆኑ አመራሩ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከላከል ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ ነው ብለዋል። በክልሉ ማህበረሰብ እንደ መጤ ባህል የሚቆጠረው የስርቆት  ድርጊት እንዳይስፋፋ ሁሉም ችግሩ ከመከሰቱ በፊት ሊታገለው እንደሚገባ ተናግረዋል። የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሙሳ አብዶ እንደገለፁት የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል በአቀባይና ተቀባይ መካከል ያለውን ሰንሰለት መበጠስ ያስፈልጋል። ለዚሁ ደግሞ የሁሉምን ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው ያስረዱት። በስርቆት የተጠረጠሩ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ቀን ጀምሮ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጉዳዩን በቅርበት በመከታተል ከሚመለከተው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የአውሲ ረሱ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ናስር ሃመዱ መድረኩ ችግሩን በተናበበ መልኩ ለመከላከል ዕድል እንደሚፈጥር ጠቅሰው እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል በዞን ደረጃ አመራር ተሰጥቶበት እየተሰራ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ  ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት ተቋሙ በክልሉ ያለውን የኃይል ተደራሽነት ለማስፋፋት ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ ነው። ይሁን እንጂ በሀገር አቀፍ ደረጃ በመሠረተ ልማቶቹ ላይ እየተፈፀሙ ያሉ ስርቆቶች ተቋሙ የኃይል መሠረተ ልማቱን ለማስፋፋት በሚያከናውነው ሥራ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል ብለዋል። ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የኃይል መሰረተ ልማት ስርቆትን ለማስቀረት የተለያዩ ሥራዎችን ቢያከናውንም መፍትሔ እንዳልመጣ ነው የተናገሩት። በዚህም ተቋሙ በክልል በየደረጃው ከሚገኙ አመራርሮች ጋር ተቀራርቦ በመስራት ችግሩን ቀድሞ ለመከላከል በሁሉም አካባቢዎች ውይይቶችን እያካሄደ እንደሆነ እና መሠረተ ልማቱን የሚከታተልና ከክልሎች ጋር ተቀናጅቶ የሚሰራ ክፍል ማዋቀሩንም አስታውቀዋል። በክልሉ የሚስተዋሉ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል በውይይቱ ላይ የተሳተፉ አመራሮች ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን በመስጠት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። በተቋሙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ በሀገሪቱ እየተስፋፋ የመጣውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆትን ለመከላከል በየደረጃው ያለው አመራር  መሰረተ ልማቶችን የመጠበቅ ግዴታ እንዳለበት ተገንዝቦ መስራት ይኖርበታል ብለዋል። ከቅድመ መከላከል ሥራው ጎን ለጎን የፍትህና የፀጥታ አካላት በመሠረተ ልማት ስርቆት የተሳተፉ ወንጀለኞች ላይ አስተማሪ ቅጣት እንዲወስዱም አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሃ ጌታቸው እንደተናገሩት የአፋር ክልል የኃይል መሠረተ ልማቱን ለመጠበቅ እየተከተለ ያለው አሰራርና እየወሰደ ያለው እርምጃ የሚበረታታና ለሌሎችም ተሞክሮ የሚሆን ነው። ሁሉም ለመሠረተ ልማቱ ደህንነት ዋስትና ሆኖ እንዲሰራ የእኔነት ስሜት ያለው ማህበረሰብ መፍጠር እንደሚጠይቅ እና የዳጉ ባህላዊ የመረጃ ልውውጥ ስርዓትን ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል። በተቋሙ የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሀሰን መሀመድ ስለ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃላይ ገፅታና ባለፈው አንድ አመት በሪጅኑ ስለተፈፀሙ የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ሞሰሶዎች ስርቆት መጠንና ስርቆቱ በየትኞቹ አካባቢዎች እንደሚስተዋል በውይይቱ ወቅት ገለፃ አድርገዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+9