cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

✿✟ የ҈ ዳ҈ ዊ҈ ት҈ ዜ҈ ማ҈ ✟✿

╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮╭━─━─━─ ገና እንዘምራለን የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት @Zemaryan ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯╰━─━─━─ ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት ጥያቄ> creator ለማግኝት @kidanemiherat_bot @yita21 @Binyam https://youtu.be/Fz4JARE6-DI

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
15 498
مشترکین
-624 ساعت
-397 روز
-17230 روز
آرشیو پست ها
#አረገ_በስብሐት አረገ በስብሐት አረገ በእልልታ በስብሐት በእልልታ አረገ በስብሐት በእልልታ/2/ ሞትን ድል አድርጎ የሠራዊት ጌታ አረገ በስብሐት በእልልታ/2/ እንኳዋን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለእርገት ባዓል በሰላም አደረሳቹሁ አሜን ፫
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ በጸጥታ አካላት ተይዘው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ውስጥ ይገኛሉ። የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ም/ኃላፊ የሆኑት መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ ዛሬ  ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም ከቤታቸው ወደ ሥራ ብለው ከወጡ በኋላ ሥልካቸው የተዘጋ እና መገኘት ያልቻሉ ሲሆን ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በኋላ ግን በጸጥታ አካላት ተይዘው ወደ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መወሰዳቸውን የዝግጅት ክፍላችን ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ችሏል። በተመሳሳይ መ/ር ተሾመ በየነ ገላን አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል።
نمایش همه...
ስለ ዘፈን መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?? አብዛኛውን ጊዜ ለሰው እውነቱ ሲነገረው ከመቀበል ይልቅ በአካኪ ዘራፍ አግበስብሶ ማለፉ ልማዱ ነው። ስጋዊ ህይወትና ስጋዊ አስተሳስብ ስለሚያሸንፈው ማድመጥም ሆነ መቀበልም ይቀፈዋል። #ቅዱስ #ኤፍሬም #ሶሪያዊዉ የስጋዊ ህይወት ማሸነፍ ላቃታቸው ማለትም ስጋዊህ ህይወት ላሸነፋቸው እና መግደል ላቃታቸው  መፍትሔውን ሲናገር እንዲህ ይላል፦ የስጋዊው ህይወት ማሸነፍ ምትችሉት የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት በእናንተ ውስጥ በሙላት መኖር ሲጀምር ያኔ እናንተ የስጋዊ ሕይወት ትጠየፋላችው እያለ ይናገራል። ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ በቆላ 3:16 ላይ  «የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችው» እንዳለ የእግዚአብሔር ቃል እኛ ላይ በሙላት መኖር ሲጀምርብን አብዝተን ስንጸልይ አብዝተን ስንሰግድ አብዝተን ስንፆም  የስጋዊ ህይወታችንን እንጠየፋለን ማለት ነው። አብዛኛውን ጊዜ ዘፈን መልክ መልኩን እየቀየረ መጥቷል እያየነውም ነው። ይኼን ያነሳንበት ምክኒያት እንዳንዶቹ ስለፍቅር መዝፈን ስለሀገር መዝፈን ሀጢያት ነው ወይ የሚል ጥያቄ እያነሱ ስለምናያቸው ነው። አንድ ምሳሌ ይባላል። ምሳሌውም፦ #አዘለም_አቀፈም_ያው_ተሸከመ_ነው ይባላል። እና #ዘፈንም መልኩን ቢቀያይርና ርዕሱን ቢለዋውጥ ዘፈን ያው ዘፈን ነው። በአንድ ወቅት መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየው በriot(ርዮት) ፕሮግራም ቃለ መጠየቅ ላይ ቀርበው ስለዘፈን የሰርግ ሰፈን የሐገር ዘፈን እንዲኹም ሌሎች ሌሎችም በቤተክርስቲያን እንዴት ያዩታል ተብለው ሲጠየቁ እርሳቸውም ቤተክርስቲያንን አጥር እንዳጠረች በዚህ ጉዳይ ላይ እንደማትደራደርና ዘፈን ሀጢያት መሆኑን አስረግጠው አልፈዋል። ዘፈን ማለት በአጭሩ የአጋንንት ግብር ነው። በአንጻሩ ስለ ሰይጣንና የግብራበሮቹ የክፋት መናፍስት ግብር ነብየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ ሲናገር፦ በዚያም የምድረ በዳ አራዊት ያርፋሉ ጕጕቶችም በቤቶቻቸው ይሞላሉ ሰጐኖችም በዚያ ይኖራሉ በዚያም አጋንንት #ይዘፍናሉ ይላል። (ኢሳ 13:21) ለሰራዊት ጌታ ለቅዱስ እግዚአብሔር የሚቀርበውን ዝማሬና ምስጋና  የሚፈፀየፉ የአጋንንትን ግብር ማድረግ ይባስ ብሎ የአጋንንት ማህበርተኛ አንድም በክፉ ስራቸው የምንተባበር መሆን ነው። «ከአጋንንትም ጋር ማህበርተኞች እንድትሆኑ አልወድም»(1ኛ ቆሮ 10:20) #ዘፈን የስጋ ስራ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረን የሐጢያት ዋና ዋናዎች አርዕስተ ሀጢያት ብሎ እንደ ዘረዘረልን እናነባለን። ከእነዚህ ከ16ቱ ድርጊቶቹ ውስጥ አንዱ ዘፈን ወይንም ደግሞ ዘፋኝነት ነው። «የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው ርሱም #ዝሙት #ርኵሰት #መዳራት #ጣዖትን_ማምለክ #ሟርት #ጥል #ክርክር #ቅንአት #ቍጣ #ዐድመኛነት #መለያየት #መናፍቅነት #ምቀኝነት #መግደል #ስካር #ዘፋኝነት ይህንም የሚመስል ነው አስቀድሜም እንዳልኹ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።»(ገላ 5፥19-21 1ኛጴጥ 4:3) ዘፋኝነት በግልጽ መንግስተ ሰማያትን አያወርስም እያለ እንዴት ነው ሰው ወደዘፋኝነት የሚገባው። ዘፈን የዝሙት ማቀንቀኛ ነው። በየመልኩ ሊመሰገን የሚገባው ሁሉን ያስገኘ ሁሉን የፈጠረ እግዚአብሔር ነው። ነገር ግን ፈጣሪው ሳይሆን ፍጡሩን ገዢውን ሳይሆን ተገዢውን ማወደስ ማለት ትልቅ አስፀያፊ ተገባር ነው። አንዳንድ ሰው በጣም ነው ግርም የሚለው እግዚአብሔር ዘፈንን የሚፈቅድ ይመስል "ከእግዚአብሔር ጋር ዘፈን ጨርሻለሁ አሁን ይለቀቃል ከእግዚአብሔር ጋር" ሲሉ ይሰማሉ እግዚአብሔር ከሰይጣን ጋር ተባባሪ አደረጉት እኮ ይገርማል  ይህንን እንኳ ማሰብ ተስኗቸዋል እስከዚህም ድረስ ነው አስተሳሰባችን። እንደውም አለምን የፈጠረ አምላክ እንደየክብሩ ማወደስ ሲገባን በዘፈን አንድሰውን አይኑ ጥርሱ አፍንጫው እያለን ከንቱ ውዳሴ እንናገራለን። ከስልኩ እንኳ ዘፈን ለማጥፋት ያቃተው ትውልድ እኮ ነው ያለን በእውነቱ ስለዚህ ከእነዚህ አይነት ተግባር መራቅና መሸሽ ተገቢ ነው። አንዳንድ ሰዎች ያስደንቃሉ  እኛ እኮ ለመደሰት ነው የምንዘፍነው የምንጨፍረው በማለት ሲናገሩ እናያቸዋለን። ለእነዚህ አይነት ሰዎች መጽሐፋችን እንዲህ ይለናል፦ ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር ርሱ ይጸልይ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር ርሱ ይዘምር።(ያዕ 5፥13) ስለዚህ ማናችንም ብንሆን ስንደሰት መዘመር ስናዝን ደግሞ መጸለይ እንዳለብን መጽሐፉ ነግሮናል። ዳግም የመጋቢ ሐዲስ እሸቱን አነጋገር እንጠቀም እና እናብቃ።  መጋቢ ሐዲስ ምን አሉ ዘፈን እነ ሰርጸ እነ ማህሙድ አህመድ ሲይዙት ጽድቅ ነው። መጽሐፍ ቅዱሱ ግን ሲይዘው ሀጢያት ነው በማለት አስረግጠው አስቀምጠዋል። ይኼ ነው እውነቱ ሀጢያት ነው ለሰይጣን የምናቀርበው ግብር ነው ስለዚህ እግዚአብሔር የሰጠንን አንድበት እናመስግንበት ክፉ አናውራበት መድኃኔዓለም የሰጠንን እግር ወደጭፈራ ቤት ወደ ኃጢያት አናምራበት። ቤተክርስቲያን ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድበት ኪዳኑን ሰዓታቱን ማሕሌቱን እንቁምበት በዚህ ስፍራ ያላችሁ ሁሉ ይህንን አንብባችሁ ትምህርት እንደምትወስዱበት አልጠራጠርም። እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን ይቆየን!! ሼር በማድረግ በእንደዚህ አይነት ስፍራ ያሉትን ግንዛቤ እናስጨብጣቸው!!! ╔═★══════════📄══╗ ⛓         @Zemaryan          ⛓ ⛓         @Zemaryan          ⛓ ⛓         @Zemaryan          ⛓ ╚══📃══════════★═╝
نمایش همه...
❤አልረሳውም ያንን ዕለት❤ አልረሳውም ያንን ዕለት አልዘነጋው ያን ደግነት እናቴ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት እምዬ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት ስላለኝ ነው ምክንያት/፪/ ለሠው ተናግሬ ያልተረዳኝ ሰው ዕንባዬ በምሬት ከዓይኔ የሚፈሰው የቤቴን ገመና ሁሉን ስነግርሽ አዛኝት ነሽና እራራልኝ ልብሽ አረሳው መቼም የአንቺን ደግነት/፪/ ውለታ አለብኝ ኪዳነ ምሕረት አዝ ልቤ በሐዘን ጠቁሮ ውስጤ እየደማ መቅረዜ ሲጨልም ስጓዝ በጨለማ በራፌን ዘግቼ ዝምብዬ አለቅሳለሁ አይኔን አቀርቅሬ እናቴ እልሻለሁ ዘንበል አልሽልኝ ሠምተሽ ፆሎቴን/፪/ አልተጸየፍሽም ብቸኝነቴን አዝ እናት የለኝ ብዬ ከቶም አልከፋ እኔስ አይቻለሁ ስትሞይኝ በተስፋ ምድራዋዊ እናቴ ለጊዜው ነው ፍቅሯ ያንቺስ ግን ልዩ ነው እረ ስንቱን ላውራ ማርያም ማርያም ብል አልሠለችሽ/፪/ በልቤ ጽላት ስለ ታተምሽ አዝ___ ሲረበኝ መጥተሻል ሲጠመኝ ደርሰሻል ለጎደለው ቤቴ በረከት ሆነሻል ጭንቄም ቀለለልኝ ሐዘኔም ራቀ ያስጨነቀኝ ጠላት ራሱ ተጨነቀ መድሀኒት ወልደሽ ዳንኩኝ ከህመሜ/፪/ ይኸው ዘመርኩኝ በምልጃሽ ቆሜ 💖❤️💖❤️💖❤️💖❤️💖
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
በኪዳንሽ ለተማጸንን ሞት አለፈ ሕይወት ሆነልን የእርቃችን ሰነድ ነሽና ልጅሽ ሠራን እንደገና። እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቃል ኪዳኗ ንግሥት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወርኃ ግንቦት መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን። የእናታችን የከበረ ቃል ኪዳኗ፣ ምልጃ ጸሎቷ አይለየን፤ ልጇ ወዳጇ ረድኤት በረከቷን ያሳድርብን። የወር ሰው ይበለን። አሜን።
نمایش همه...
ያንደበቴ ጣፋጭ ውዳሴ ========///======== ያንደበቴ ጣፋጭ ውዳሴ ምፅናናብሽ ታዛለ ነፍሴ ከመቅደስሽ ፍቅር ተምሬ ማርያም ማርያም ይላል ከንፈሬ ልመናዬን ሰምተሻል በረድኤት ቀርበሻል በፍቅርሽ ተሸልሜ አረፍኩኝ ከሸክሜ{፪} ቃሌ ነው በተሰማ ተማፅኖዬን ሳሰማ በዙፋኑ ቀኝ ሆነሽ ድንግል ታስምሪናለሽ {፪} ማግኝት ማጣት አይደለም ልመናዬ በአለም አድይኝ ማስተዋሉን እንድረዳው መስቀሉን {፪} አይመራኝም በትሬ ድንግል ቆመሽ ከበሬ ምርኩዜ ብዬሻለው አንቺን እደገፋለው {፪}
نمایش همه...
ጊዜ አጠቃቀምና ክርስትና ◦ ክርስትና ቀልድ አይደለም ◦ ለቃለ እግዚአብሔር ጊዜ እንስጥ ◦ ለመንፈሳዊነት ጊዜ ይኑረን ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ 🔹▪️🔹▪️🔹▪️🔹▪️
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ውሎው ችግር ባለባቸውና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት ፱ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ ውሳኔ አሳለፈ። ምንጭ: EOTC TV
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም በጸጥታ ኃይሎች ለጥያቄ እንፈልግሃለን ተብለው ተወስደው የነበሩት መምህር ብርሃኑ አድማስ ከስር ተለቀው ወደ ሥራ ቦታቸው መመለሳቸውን የዝግጅት ክፍላችን አረጋግጧል።
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
#ሰበር_ዜና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት መምህር ብርሃኑ አድማስ ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓም በፀጥታ ኀይሎች ከቢሯቸው ተወስደዋል። መምህር ብርሃኑ ለጥያቄ እንፈልግሃለን ተብለው በፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ውስጥ እንደሚገኙ የዝግጅት ክፍላችን አረጋግጧል
نمایش همه...
#መከራ_መካሪ_ነው አዎ አንዳንድ ሰዎች እንደታመሙ እንጂ ለምን እንደታመሙ አያውቁም አንዳንድ ሰዎች በመከራ ውስጥ እንዳለፉ እንጁ ለምን በመከራ ውስጥ እንዳለፉ አያውቁም
نمایش همه...
#ቅዱስ_ሚካኤል ቅዱስ ሚካኤል(፫) ነፍሴ ሲጨነቅ ሲዝል ስጋዬ ፈጥነህ ተራዳኝ ዋስ ጠበቃዬ አንተ ስለሆንክ - - - ሚካኤል የአምላክ ባለሟል - - - ሚካኤል ልመናህ ፈጥኖ - - - ሚካኤል ከአምላክ ያቀርባል - - - ሚካኤል የዋህ መልአክ ነህ አዛኝ ለሰው(፪) ምልጃህ ፈጣን ነው ለምናምነው (፪) #አዝ ደዌ የጸናበት - - - ሚካኤል ባንተ ይድናል - - - -ሚካኤል በአደባባይህ - - - ሚካኤል ምስክር ሆኗል - - - ሚካኤል ከቤትህ መጥቶ የተማፀነ(፪) በቃል ኪዳንህ ህይወቱ ዳነ (፪) #አዝ ከአምላክ ተሰጥቶህ - - - ሚካኤል ክብርህ ያበራል - - - ሚካኤል ለጎስቋላው ሰው - - - ሚካኤል መጠጊያ ሆኗል - - - ሚካኤል ትንሽ ትልቁ ደሀው ሀብታሙ(፪) ለምኖ አግኝቷል ከአምላክ በስሙ(፪) #አዝ በብሉይ ኪዳን - - - ሚካኤል ከአምላክ ተልከህ - - - ሚካኤል ሕዝበ እስራኤልን - - - ሚካኤል ነጻ ያወጣህ - - - ሚካኤል በአዲስ ኪዳንም ድንቅ ስራ አለህ(፪) በተአምራትህ ትፈውሳለህ(፪) ሊቀ መዘምራን ዲ.ን.ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
نمایش همه...
እንዴት አደራችሁ
نمایش همه...
የጌታችን እና የመድሀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዓበይት በዐላት ስንት ናቸው እነማናቸው ?
نمایش همه...
ጥያቄ ልጠይቃችሁ
نمایش همه...
እንዴት አመሻችሁ
نمایش همه...
​​በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚገኙ እንግዳ ቃላት እና ትርጉማቸው ፡- በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡ ኪርያላይሶን፦ ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን»ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል አለበት፡፡ ትርጉሙ «አቤቱ ማረን»ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ«ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡ ናይናን፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡ እብኖዲ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው ታኦስ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡ ማስያስ፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው ትስቡጣ፦ «ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው አምነስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡ አምንስቲቲ ሙዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ -ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡ አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡ #ሼር @zemaryan @zemaryan
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
''እኔ የተዋሕዶ ድምፅ ነኝ እናንተስ'' 4ኛ ዙር ጉባኤ እና ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር መጋቢት 24/2015 ዓ.ም ተዘጋጅቷል:: እሑድ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥንና ዩቱዩብ በቀጥታ ስርጭት ይከታተሉ። አገልግሎቱን ለመደገፍ ጎ ፈንድ ሚ ማስፈንጠሪያ https://www.gofundme.com/f/gtbbd?utm_source=customer... ወገን ፈንድ Www.wegenfund.com/mk01 የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች **** ንግድ ባንክ 1000010822657 (BETH.TEW.SENBET.TBET MAHIB.KID +++++++++++++++++++++++++ ወጋገን ባንክ 0039595010103 +++++++++++++++++++++++++ አቢሲንያ ባንክ 4753388 +++++++++++++++++++++++++ ዳሸን ባንክ 0088872166011 +++++++++++++++++++++++++ አዋሽ ባንክ 01304800017700 ±++++++++++++++++++++++ አሐዱ ባንክ 0003488710101 +++++++++++++++++++++ አማራ ባንክ 9900017695658 +++++++++++++++++++++ ኦሮምያ ኅብረት ስራ ባንክ 1033100028173
نمایش همه...
በቅርቡ በተቋቋመው በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር ውስጥ በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፤ በአገልጋዮቿ እና በምእመናን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ እና በደል አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተሰጠ መግለጫ። ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ በተለያየ ዘመን በተነሱ ቅዱሳን ክርስትና እንዲሰበክ በማድረግ ለሺህ ዓመታት የሀገሪቱ የሃይማኖት፣ የታሪክ እና የሞራል ምንጭ ሆና ኖራለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን ራሷ የሆነው ክርስቶስን በመስበክ ያላመኑትን ከማሳመን፣ ያመኑትን ከማፅናት እና የፀኑትን ከመቀደስ ውጪ ሌላ ምድራዊ ዓላማ ሳይኖራት ነገስታቱንም ሆነ ምዕመኑን እኩል ንስሀ አባት መድባ አና ንስሀ አቀብላ፣ ቀድሳ አቁርባ እና ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩም ለሁሉም እኩል ፍትሃት አድርጋ የምትሸኝ ሰውን በፆታው፣ በቋንቋው፣ በነገዱ እና በማንነቱ አድሎ ሳታደርግ የኖረች ናት። ሆኖም ግን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራችን ውስጥ ያለአንዳች ማስረጃ የተፈጠሩ የሀሰት ትርክቶች እና እነዚህን ትርክቶች መሠረት ተደርገው በሰፊው ሲነዙ የነበሩ ሀሰተኛ መረጃዎች ቤተ ክርስቲያንን ዋጋ እያስከፈላት ይገኛል፡፡ አሁን አሁን የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች እና ምእመናን በሃይማኖታቸው ብቻ ተለይተው በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ባሉ አካላት ካህናት አባቶቻችን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ስጋና ደሙን ቀድሰውና አክብረው ለሰዎች ድህነት ይሆኑ ዘንድ በተሰጣቸው ስልጣነ ክህነት ምእመናን ለርስት መንግሥተ ሰማያት የሚያበቁ ሁነው ሳለ በተለያዩ ጊዜ ለሞት እና ለእንግልት እንዲሁም ለስደት እና ለእስራት ሲዳረጉ ማዬት የእለት ተእለት ተግባር ከሆነ ሰንበትበት ብሏል፡፡ በአዲሱ መንግስታዊ መዋቅራዊ አደረጃጀት በአዲስ አበባ ዙርያ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሸገር ከተማ በሜጢ ሆርሲሳ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህን የነበሩት ቄስ አባይ መለሰ በመጋቢት ፲ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ከቅዳሴ ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲሄዱ ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች በተፈጸመባቸው ድብደባ ሕይወታቸው ሊያልፍ መቻሉን ተረድተናል፡፡ መንግሥት የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ደኅንነት የማስጠበቅ እና ዋስትና የመስጠት እንዲሁም ጭካኔ እና አረመኔያዊ ከሆኑ ጥቃቶች የመጠበቅ መንግሥታዊ ኃላፊነት ሊኖርበት ይህንን ባለመወጣቱ ምክንያት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች እና ዜጎች በሕይወት የመኖር መብት በየእለቱ እየተሸረሸረ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሀገረ ስብከታችን በቀሲስ አብይ መለስ ሞት የተሰማንን መሪር ኃዘን እየገለጽን የሚመለከተው የፌዴራል፤ የአዲስ አበባ ከተማ እና የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ እና የፍትህ አካል ጉዳዩን ልዩ ትኩረት በመስጠት ተገቢውን ምርምራ በማድረግ ይህንን አስነዋሪ እና ጭካኔ የተሞላበትን የግድያ ወንጀል የፈጸሙ ወንጀለኞችን ለፍርድ እንዲያቀርብ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ስር የሚተዳደሩ ቁጥራቸው ከዐሥራ ሦስት በላይ የሆኑ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በአዲሱ የከተማ ድንበር ማካለል ወደ ኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ክልል ውስጥ የተካለሉ ቢሆኑም ለዓመታት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገንብተው መንፈሳዊ አገልግሎት ሲሰጡ ከቆዩ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ፩ የኤርቱ ሞጀ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ አብያተ ክርስቲያናትን ለማፍረስ ተሞክሮ ከእነዚህ ውስጥ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በመሉ በአፍራሽ ግብረ ሀይል እንዲፈርስ ከመደረጉም በላይ የፈረሰውን ቤተ ክርስቲያን በውስጡ ከሚገኙ ንዋያተ ቅድሳት ጋር በሙሉ እንዲቃጠሉ እና እንዲወድሙ ተደርጓል፡፡ ፪. በኤርቱ ሞጆ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያንን አጥሩን ማፍረስ ተጀምሮ ምእመናን እና የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች ባደረጉት ርብርብ የማፍረስ : ሒደቱ ለጊዜው ቢቆምም አሁንም ይህን ቤተ ክርስቲያንም ሆነ በሸገር ከተማ ውስጥ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት በከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ስለሆነም ለሀገር ባለውለታ የሆነችን ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በማሳደድ እና በማውደም ታሪካዊ መሠረቷን ለመናድ እና ከሌሎች ቤተ እምነቶች በመነጠል በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እየተፈጸመ ያለው አድሏዊ እና ኢ-ሕገ መንግስታዊ የሆነው ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም እንዲደረግ እያሳሰብን የፌዴራል እና የክልሉ መንግሥትም የድርጊቱን ፈጻሚ አካላት ላይ ተገቢውን እርምት እንዲወስድ ስንል እንጠይቃለን፤ በመጨረሻም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የሚመለከተው ባለስልጣን አካል በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተፈጸመውን እና ሕገ ወጥ ተግባርን በተመለከተ የድርጊቱን ፈጻሚ አካላትን በ፭ ቀናት ጊዜ ውስጥ ተለይተው በሕግ ተጠያቂ በማድረግ ለሕዝብ እንዲያሳጡት ጥሪ ያስተላለፈች ቢሆንም ይህ መግለጫ  አስከሚሰጥ ድረስ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላት ተለይተው ተጠያቂ አለመሆናቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥት ቤተ ክርስቲያን ያቀረበችውን ጥያቄ ምላሽ ሊሰጥ ያልቻለ በመሆኑ የድርጊቱን መነሻ ምክንያት የደረሰውን ጉዳት እና የድርጊቱን ፈጻሚዎች ለይቶ ለሕዝብ ይፋ የሚያደርግ የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ በማዋቀር ወደሥራ የተገባ መሆኑን እያሳወቅን ኮሚቴው የደረሰበትን ጥቅል መረጃ በአጭር ቀናት ጊዜ ውስጥ ለሕዝብ ሪፖርቱን የሚያቀርብ እና የድርጊቱ ፈጻሚዎች ቤተ ክርስቲያንን በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቁ እና አጥፊዎችም ለድርጊታቸው ተገቢውን ሕጋዊ ቅጣት እንዲያገኙ እየሠራን መሆኑን እናሳውቃለን። በመሆኑም፡ ፩. መንግሥት የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ በመሆናቸው ምክንያት በአሰቃቂ ሁኔታ በመንገድ ላይ ተደብድበው ሕይወታቸው እንዲያልፍ የተደረጉት የቄስ ዐብይ መለሰ ገዳዮችን ተከታትሎ ለፍርድ እንዲያቀርብ እና ችግሩን ከሥር ከመሠረቱ በመፍታት የአገልጋዮችንና የምእመናን መብት እንዲያስከብር ፪. በሸገር ከተማ አስተዳደር እየተፈፀመ ያለው አብያተ ክርስቲያናትን የማፍረስ ድርጊት በአስቸኴይ እንዲቆም እንዲደረግ፣ ፫. የፈረሱትን አብያተ ክርስቲያናት ቦታ ተመላሽ እንዲያደርግ እና የፈረሰውን ቤተ ክርስቲያንም በራሱ ወጪ እንዲያሠራ እንዲደረግ እንጠይቃለን። የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናን እና ምእመናት እንዲሁም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ አባቶች ዘመነ ቤተ ክርስቲያንን በጉልበታችን፤ በዕውቀታችን እና በገንዘባችን የምናገለግልበት ብቻ ሳይሆን በአካላችን፣ በጤናችን እና በሕይወታችንም መስዋዕትነትን የምንከፍልበት የሰማዕትነት ዘመን ነው፡፡ ይህ የሰማዕትነት መከራም በሀገራችንና በየቤታችን እየመጣ ያለ የመከራ ዘመን በመሆኑ አብዝቶ ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ፤ ሥጋችንን በጾም እና በስግደት በመግራት ከአባቶቻችሁ አባታዊ መመሪያ በመቀበል በሃይማኖታችሁ ጸንታችሁ እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ እግዚአብሔር ሀገራችንን እና ሕዝቦቿን ይባርክ። መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
نمایش همه...
በአዲስ አበባ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ቀሲስ ዐባይ መለሰ የተባሉ ካህን ቅዳሴ ጨርሰው ወደ ቤታቸው በመሄድላይ እንዳሉ በድንጋይ ተወግረው ሕይወታቸው ማለፉን የዐይን እማኞች ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለፁ። የሆርሲሳ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ቀሲስ ዐባይ መለሰ ሕይወታቸው ሲያልፍ ችግሩ ታወቀ እንጂ አስቀድሞ በአካባቢው አገልጋዮች ላይ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ይደርስ እንደነበር መረጃ ሰጭዎቻችን በቦታው ለተገኘው ዘጋቢያችን ገልፀዋል። ካህኑ በድንጋይ ተደብድበው እያሉ ምስልና ቪዲዮ ለማስረጃ ለመያዝ ቢሞክሩም በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ሞባይል እየተሰበሰበ መሰረዙንም ነግረውናል።
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
#ሰበር_ዜና  ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) አረፉ። ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ የሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት  መካከል አንዱ የሆኑት በቀድሞ ስማቸው አባ ኃይለማርያም መለሰ (ዶ/ር) በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪ እና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ  ተለይተዋል። በረከታቸው ይደርብን!!
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
Mahibere Kidusan - አፈናን የመታገል አካል ነው! በኦርቶዶክስ ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ሚዲያ እንዳይዘግበው ተደርጎ ከርሟል። ይህን ተከትሎ አማራጭ ድምፆች ከመቸውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ ሆኗል። ኦርቶዶክስ ድሞፅ እንድታገኝ ዘንድም ሚዲያዎችን ማጠናከር ይገባል። ከስር ባለው መልኩ ዘመቻ ተጀምሯል። አፈናን የመቃወም፣ የመታገል አንዱ መንገድ ነው። *********** "እኔ ተዋሕዶ ድምፅ ነኝ! እናንተስ?" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ጉባኤ በተያዘው መርሐ ግብር መሠረት 10፡00 ሰዓት ላይ ጀምሯል፡፡ ጉባኤውን በአካል መገኘት ስለማትችሉ በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቭዥን እና በዩቱዩብ ቻናሎች ይከታተሉ፡፡ ጎ ፈንድ ሚ ማስፈንጠሪያ https://www.gofundme.com/f/gtbbd?utm_source=customer... ወገን ፈንድ ማስፈንጠሪያ https://www.wegenfund.com/.../enee-yatawaahhedo-demetse.../ የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች **** ንግድ ባንክ 1000010822657 (BETH.TEW.SENBET.TBET MAHIB.KID +++++++++++++++++++++++++ ወጋገን ባንክ 39595010103 +++++++++++++++++++++++++ አቢሲንያ ባንክ 4753388 +++++++++++++++++++++++++ ዳሸን ባንክ 0088872166011 +++++++++++++++++++++++++ አዋሽ ባንክ 01304800017700 ±++++++++++++++++++++++ አሐዱ ባንክ 0003488710101 +++++++++++++++++++++ አማራ ባንክ 9900017695658 +++++++++++++++++++++ ኦሮምያ ኅብረት ስራ ባንክ 1033100028173
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
#የዜና_ጥቆማ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቴሌቪዥን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ለኦሲኤን ቴሌቪዥን ለአሐዱ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ለባላገሩ ቴሌቪዥን ለናሁ ቴሌቪዥን ለአሻም ቴሌቪዥን ለኢቢኤስ ቴሌቪዥን ለሀገሬ ቴሌቪዥን ለተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ለET ART ሚዲያ ለንቁ ሚዲያ ባላችሁበት ጉዳዩ፡- የዜና ሽፋንን ይመለከታል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር ተያይዞ በዛሬው ዕለት የካቲት 24 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ላይ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት መግለጫ የሚሰጥ በመሆኑ ከላይ የተጠቀሳችሁ ሚዲያዎች ብቻ በሰዓቱ ተገኝታችሁ መግለጫውን በመቅረጽና በመዘገብ የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡ የተጋበዛችሁ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እንኳን ለ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመትዎ በሰላም አደረስዎ!
نمایش همه...
የኢትዮጵያ ገበዝ የኢትዮጵያ ጠባቂ የቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦት ላይ መንግስት ተኩስ ከፍቷል! ምዕመኑ በዓሉን ማክበር ታቦቱን ማንገስ አልቻሉም። ተዋግቶ ኢትዮጵያን ላስከበራት ለቅዱስ ጊዮርጊስ መሳርያ ይገባዋል???‼️
نمایش همه...
Watch "ተዋሕድዋ - የአድዋ ድል እና ተዋሕዷዊ ገድል" on YouTube https://youtu.be/7_6A_kMAvSs
نمایش همه...
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መቐለ አሉላ ኣባነጋ ዓለም አቀፍ አየር ማረፍያ በሰላም ገብተዋል። በአየር ማረፊያው ሲደርሱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የቤተ ክህነት ሠራተኞች እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እና ምእመናን አቀባበል አድርገውላቸዋል።
نمایش همه...
በወለጋ ነቀምቴ ከተማ መንበረ ጵጵስናው በሚገኝበት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ውጥረት ተከስቷል። የብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሀገረ ስብከት በሆነው በነቀምቴ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስን ትእዛዝ በሚቀበሉ ኦርቶዶክሳውያን እና ሕገወጡን ተሿሚ እንቀበላለን በሚሉ ከሌላ አካባቢ በመኪና ለሁከት እንዲመጡ በተደረጉ ሰዎች መካከል ውጥረት መከሰቱ ተገልጿል። ጉዳዩ የተከሰተው ነገ የሚታሰበውን ወርኃዊ የቅዱስ ገብርኤል በዓል ምክንያት በማድረግ ሕገወጥ ተሿሚ የሆነውና ደጋፊዎች ነን የሚሉ ወደ ገዳሙ እንገባለን በማለታቸው እና በሰንበት ተማሪዎች፣ ኦርቶዶዶክሳውያን ወጣቶችና የአካባቢው ምእመናን ቅዱስ ሲኖዶስ የተወገዘ አካል በገዳሙ አይገባም በማለታቸው ነው። ውጥረቱን ለማርገብ የመከላከያ ሠራዊት የተገኘ ሲሆን የከተማው ከንቲባና የከተማው ፖሊስ አዛዥ ጉዳዩን ለመረዳት ከመሞከር ይልቅ ከብሔርና ፖለቲካ ጋር በማገናኘት መፍትሔ ሳይሰጡ በማባባስ ላይ እንደሚገኙ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በአሁኑ ሰዓት የአካባቢው ምእመናን፣ ወጣቶችና የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በቅዱስ ገብርኤል ገዳም ቅጥር ግቢ ውስጥ በመሆን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እየጠበቁ ይገኛሉ። ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በሕገ ወጥ መንገድ በወሊሶ የተሾሙ 25 "ኤጲስ ቆጶሳት" በቅዱስ ሲኖዶስ መወገዛቸው እንዲሁም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ ማገዱ ይታወሳል።
نمایش همه...
ከኃጢያታችን የበለጠ እግዚአብሔርን እጅግ የሚያሳዝነው ይቅር አይለንም ብለን ማሰባችን ነው። @zemaryan
نمایش همه...
1. ዘወረደ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡ #OrthodoxTewahdo #ኦርቶዶክስ #profile #timline #post #story On Telegram👇 • t.me/winagfx2t.me/winaedit2 Share 🙏 https://t.me/joinchat/V2t-Wam1Ovdhi6op
نمایش همه...