Condominuim Market in Addis Ababa
رفتن به کانال در Telegram
በዚህ የቴሌግራም Chanel ከ10,000 ተከታይ በላይ ባለው facebook page በቀን እስከ 500 ሰው ጎብኚ ብለው condoaddis.etsecurities.com በማስታወቂያ ክፍያ ቤትዎን እና መኪናዎን መሸጥ ፣ ማከራየት ይችላሉ ኮሚሽን መክፈል ለማይፈልጉ buy ads here https://telega.io/c/condoaddis 0913587955 መረጃ ለመላክና ለጥያቄ @antget1
نمایش بیشتر3 600
مشترکین
+124 ساعت
-137 روز
-1130 روز
آرشیو پست ها
ከ2019 ጀምሮ የቤት ኪራይ ዋጋ በአዲስ መተመኛ ሊወሰን ነው
በአዲስ አበባ ከተማ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን ፍትሃዊ፣ ሳይንሳዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ለመወሰን የተዘጋጀ የዋጋ መተመኛ ጥናት ዛሬ ቀርቦ በባለድርሻ አካላት ፊት ውይይት ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ የኑሮ ጫናን ለመቀነስ እና በቤት ኪራይ ገበያ ውስጥ የተስፋፉ ሕገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን ለመግታት በተከታታይ እየሰራ ነው።
እንደ ኃላፊዋ ገለጻ፣ በ2016 ዓ.ም. የተከናወነው ሰፊ የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ በዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ አሁን የቀረበው የኪራይ ዋጋ መተመኛ ጥናትም የውል ማደስ ሂደትን ፍትሃዊና ግልጽ ለማድረግ ያግዛል።
ጥናቱ የአከራዮችን ተገቢ ገቢ ከወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ጋር በማጣጣም የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ተከራዮችም ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ እንዲከፍሉ እና የተረጋጋ የኢኮኖሚ ኑሮ እንዲመሩ እንደሚያስችል ተገልጿል።
እንዲሁም ጥናቱ የቤት ኪራይ ገበያውን ጤናማና ሊተነበይ በሚችል መልኩ በማደራጀት፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን የእምነት ክፍተት ለመቀነስ እንዲሁም የሕገ-ወጥ ደላሎችን ጣልቃ ገብነት ለመግታት እንደሚረዳ ተጠቁሟል።
ጥናቱ በአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፣ በ2019 በጀት ዓመት በተግባር እንደሚውል ተገልጿል።
በሚኪሊላንድ ኮንዶሚኒየም የተደቀነው አደጋ!😡
#maeda : በአዲስ አበባ ፣አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 የሚገኘው የሚኪሊላንድ (ብርጭቆ) ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ካለፈው ዓመት የክረምት ወራት ጀምሮ በሚኖሩበት የኮንዶሚኒየም ግቢ ውስጥ ባጋጠመ የመሬት መንሸራተትና መሰነጣጠቅ ሳቢያ ለከፍተኛ ስጋት መጋለጣቸውን ገለጹ።
ችግሩ ከተከሰተ አስር ወራት ቢቆጠሩም፣ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ለጉዳዩ አፋጣኝ ምላሽ ባለመስጠታቸው ነዋሪዎቹ አሁንም ለሞትና ለንብረት ውድመት አደጋ ተጋልጠው እንደሚገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
እንደ ነዋሪዎቹ ገለጻ፣ የመሬት መሰነጣጠቁ የጀመረው በ2017 ዓ.ም ክረምት መውጪያው ላይ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ጥልቀቱ እስከ ሦስት ሜትር የሚደርስ ጉድጓድ ፈጥሯል።
ይህ አደጋ የመኖሪያ ህንጻዎችን ግድግዳ ከማላቀቁ ባለፈ በአቅራቢያው በሚገኘው የሚኪ ሌላንድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይም ጉዳት አድርሷል።
ስጋቱን አስመልክቶ ያነጋገርናቸው አንድ ነዋሪ “መሬቱ እየተንሸራተተና እየተሰነጠቀ መጣ፤ አስፋልቱም ወደ ታች ወረደ አሁን ወደ ሦስት ሜትር ያክል ወደታች ወርዷል በጥልቅ ወደ ታች ጉድጓድ ይታያል” በማለት የሁኔታውን አሳሳቢነት ገልጸዋል።
አደጋው በተከሰተበት ወቅት የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ኮሚሽን እንዲሁም የአዲስ አበባ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ሃላፊ ኢ/ር ወንዱሙ ሴታ ቦታው ድረስ በመገኘት የተመለከቱ ሲሆን ችግሩ እስከሚስተካከል ለደህንነታቸው ሲባል ነዋሪዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ እና በሌሎች አካባቢዎች ተጠልለው እንዲቆዩ ምክረሃሳብ ማስቀመጣቸውን አስታውሰዋል።
በሁለት ብሎክ 58 አባውራ በችግሩ ምክንያት ለአደጋ ተጋልጠው የነበረ ቢሆንም የበለጠ የሚያሰጋቸው 29 አባውራ መኖሪያዎች በወቅቱ እንዲታሸጉ እና ለደህንነታቸው ሲባል ለቀው እንዲወጡ ተደርጎ ነበር።
ይሁን እንጂ ለተፈናቀሉት 29 አባወራዎች ዘላቂ የመኖሪያ መፍትሄ ባለመሰጠቱና የቤት ኪራይ ዋጋ በመናሩ፣ ነዋሪዎቹም አቅም የሌላቸው በመሆኑ ስጋት ወዳለበት መኖሪያ ቤቶቻቸው ለመመለስ መገደዳቸውን ገልጸዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ጉዳዩን ሲያስረዱ “ ወጥቶ የመከራየት አቅም ስለሌለው [ነዋሪው] ተመልሶ ገብቷል።ጥቂት ሰው ቢቀር ነው እንጂ ሁሉም ገብቷል፤ አሁን ደግሞ ክረምት ሲመጣ ቦታው በጣም ያሰጋል ” ብለውናል።
ነዋሪዎቹ መፍትሄ ፍለጋ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ጀምሮ እስከ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ድረስ ደጋግመው ቢመላለሱም፣ እስካሁን ያገኙት ምላሽ “ይሰራል” የሚል የተስፋ ቃል ብቻ መሆኑን ይገልጻሉ።
በተለይም የመንግስት መስሪያ ቤቶቹ ሃላፊነቱን አንዱ ወደ ሌላው በመግፋት መፍትሄውን እንዳዘገዩት ነዋሪዎቹ ይናገራሉ።
“ከማዘጋጃ ወደ መንገዶች ደብዳቤ ተልኳል ይሉናል፤ መንገዶች ስንሄድ ደግሞ መልሰው ወደዚህ ይልኩናል። ስራውን አስጀምረው ኦፊሻሊ እንኳን ኑሩበት የሚባል መልስ የለም፤ በእንጥልጥል ላይ ነው ያለነው” ሲሉ በቢሮክራሲው መጉላላታቸውን ነዋሪው ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የክረምቱ ወቅት መቃረቡ ስጋቱን እጥፍ ድርብ አድርጎታል ብለውናል።
በህንጻው ውስጥ የሚኖሩ ህጻናትና አረጋውያን ህንጻው ላይ በሚፈጠር ንቅናቄና ንዝረት ሳቢያ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ ነግረውናል።
ነዋሪዎቹ “ሰው በስጋት ነው፤ ኃይለኛ ዝናብ ሲጥል ሁሉም ወደ ውጭ ነው የሚወጣው ቢያንስ መንገዱ ባይሰራ እንኳ ህንጻው እንዳይናድ ማጠናከሪያ ስራ እንዲሰራ ነው ጥያቄያችን” በማለት የሚመለከተው አካል ከመዘናጋት ወጥቶ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ይመለከታቸዋል የተባሉት እና በቦታውም ተገኝተው ተመልከተው ለነበሩት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ወንዱሙ ሴታ ተደጋጋሚ የስልክ ሙከራ ቢያደርግም ስልክ ሊነሳለት አልቻለም።
መረጃው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ነው
Tiktok.com/@condoaddis
https://m.youtube.com/@condoaddis
T.me/condoaddis
Linkedin.com/company/condoaddis
Facebook.com/condoadis
በአያት፣ በአራብሳ እና ጀሞን በመሳሰሉ ሰፋፊ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚገኙባቸው አከባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ መታየቱ ተሰምቷል፡፡
የቤት ኪራይ ጭማሪው በተለይም ከሁለት ወራት ወዲህ በከፍተኛ መጠን ማሻቀቡን ነው ለማወቅ የተቻለው፡፡
በአያት ኮንዶሚኒየም ከ20 እስከ 22 ሺሕ ብር ኪራይ ይከፈልበት የነበረው ባለ ሁለት ክፍል መኝታ ቤት ወደ 30 ሺሕ ብርና ከዚያ በላይ ያሻቀበ ሲኾን፣ እስከ 15 ሺሕ ብር ይከፈልበት የነበረው ባለ አንድ ክፍል መኝታ ቤት ደሞ እስከ 25 ሺሕ ብር መድረሱን እንዲሁም 'ስቱዲዮ' ተብሎ የሚጠራው አንድ ወጥ የመኖሪያ ክፍል ከ10 ሺሕ ብር ወደ 16 ሺሕ ብር ገደማ ማሻቀቡን የዋዜማ ሬዲዮ ዘገባ ጠቁሟል፡፡
በገላን፣ ቦሌ አራብሳ እና ጀሞ በሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ በተመሳሳይ አከራዮች ከፍተኛ የኪራይ ጭማሪ ማድረጋቸውም ተሰምቷል።
የከተማዋ አሥተዳድር በበኩሉ የቤት ኪራይ ጭማሪ እንዳይደረግ አከራዮችን ቀደም ሲል ውል ማስገባቱ አይዘነጋም።
ሆኖም በአዲስ አበባ ከተማ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የቤት ኪራይ ቁጥጥር ውል ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜ መቅረቱን ተከትሎ በከተማዋ የመኖሪያ ቤቶች ላይ ከ50 እስከ 100 በመቶ የሚደርስ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ እየተደረገ ስለመሆኑ ከቀናት በፊት የወጡ ዘገባዎች አመላክተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበኩሉ ያለፉት ሁለት ዓመታት የቤት ኪራይ ውል በመጪው ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የሚያበቃ መሆኑን ተከትሎ ጥናት እያስጠና እንዳለ ገልፆ በጥናቱ ውጤት መሠረት አሁን በስራ ላይ ያለው የኪራይ ዋጋ ባለበት የሚቀጥል፣ የሚጨምር ወይም የሚቀንስ ከሆነ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ተናግሯል።
🔍 ቤት እየፈለጉ ነው?
🏠 ቤት እያከራዩ ነው?
💼 ወኪል (ደላላ) ነዎት?
KIRAYE ለአዲስ አበባ ተከራዮች እና አከራዮች ፍፁም መፍትሄ ይዞ መጥቷል! 🇪🇹
በየቀኑ ከሚሰማው የቤት ኪራይ ማጭበርበር እና ውክቢያ ራስዎን የሚጠብቁበት የመጀመሪያው ታማኝ መድረክ፦
✅ Verified Profiles — ሁሉም ተጠቃሚ በማንነት መታወቂያ የተረጋገጠ ነው
⭐️ Trust Score— ከማን ጋር እንደሚስማሙ ከፊርማ በፊት አስቀድመው ይወቁ
📄 Digital Agreement — ህጋዊ የኪራይ ውል በስልክዎ በሰከንዶች ውስጥ ያዘጋጁ
🔒 Secure Deals — ከአሰልቺ ሩጫ እና ከማጭበርበር ሙሉ በሙሉ ይገላገሉ
👉 kiraye-xy6c.vercel.app
ፍጹም ነፃ ነው — ዛሬውኑ ይመዝገቡ!
💡 ቤት ለሚፈልግ ወይም ለሚያከራይ ወዳጅዎ ሼር በማድረግ ከማጭበርበር ይታደጓቸው!
🙋♀ ሰላም ቤተሰብ 👉የሚሸጥ ቤት አለን።
ሳይት፦ ቦሌ አራብሳ ኮንደሚኒየም 🏢🔑
-ለትራንስፖርት 💡ምቹ
-ስፋት ፦72
-ደረጃ 4ኛ
አሰራር : ሙሉ ሴራሚክቆንጆ ቦርድ አለዉ
ወርሀዊ ገቢ25,000 የሚከራይ
-አምስት አመት የሞላው
📍ለካሽ 5.2ድርድርአለዉ
📍ለባንክ5.2ድርድር አለዉ
ገዥ ከሆኑ ብቻ ይደውሉልን🤙
☎️☎️☎️☎️☎️☎️
🔍 ቤት እየፈለጉ ነው?
🏠 ቤት እያከራዩ ነው?
💼 ወኪል (ደላላ) ነዎት?
KIRAYE ለአዲስ አበባ ተከራዮች እና አከራዮች ፍፁም መፍትሄ ይዞ መጥቷል! 🇪🇹
በየቀኑ ከሚሰማው የቤት ኪራይ ማጭበርበር እና ውክቢያ ራስዎን የሚጠብቁበት የመጀመሪያው ታማኝ መድረክ፦
✅ Verified Profiles — ሁሉም ተጠቃሚ በማንነት መታወቂያ የተረጋገጠ ነው
⭐️ Trust Score— ከማን ጋር እንደሚስማሙ ከፊርማ በፊት አስቀድመው ይወቁ
📄 Digital Agreement — ህጋዊ የኪራይ ውል በስልክዎ በሰከንዶች ውስጥ ያዘጋጁ
🔒 Secure Deals — ከአሰልቺ ሩጫ እና ከማጭበርበር ሙሉ በሙሉ ይገላገሉ
👉 kiraye-xy6c.vercel.app
ፍጹም ነፃ ነው — ዛሬውኑ ይመዝገቡ!
💡 ቤት ለሚፈልግ ወይም ለሚያከራይ ወዳጅዎ ሼር በማድረግ ከማጭበርበር ይታደጓቸው!
የሽያጭ ውል ጊዜ ገደብ የተራዘመ መሆኑን ለማሳወቅ የቀረበ ማስታወቂያ
ተቋማችን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ያስገነባቸው የጋራ መኖሪያ ህንጻ ስር የሚገኙ ንግድ ቤቶችን እና በካፒታል ፕሮጀክት የተገነቡ ንግድ ቤቶችን በጨረታ ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ 8ኛ ዙር እና 2ኛ ዙር ግልጽ ጨረታ በተመሳሳይ ቀን በአንድ የጨረታ ሰነድ ማውጣቱ እና የጨረታው 1ኛ ደረጃ አሸናፊዎች ግንቦት 05 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት (ቅዳሜን ሙሉ ቀን ጨምሮ) እስከ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሽያጭ ውል ስናከናውን መቆየታችን ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ ከሲስተም መቆራረጥ እና ተጫራቾች ካነሱት ከባንክ የገንዘብ ዝውውር መዘግየት አንፃር የባከኑ የስራ ቀናትን ታሳቢ በማድረግ ለተጨማሪ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከግንቦት 25 እስከ ሰኔ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ በመሆኑ ቀደም ሲል በተገለፀላችሁ የመዋዋያ ቦታ በአካል ወይም በህጋዊ ወኪሎቻችሁ በኩል የሚጠበቅባችሁን ቅድመ ሁኔታ በማሟላት በተገለጸው የሽያጭ ውል ጊዜ ገደብ ውስጥ ውል መፈጸም እንድትችሉ ጥሪ የቀረበላችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
https://bit.ly/4nL0s4x
የጋራ መኖርያ ቤቶችን በሚያስተዳድሩ ማህበራት ላይ አስገዳጅ የዲጂታል ክፍያ ስርዐት እየዘረጋ ያለው 'እፎይ ፕላስ' የተባለው የግል ድርጅት ውዝግብ አስነሳ
አሰራሩ አዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ኮንዶሚኒየሞች እና አፓርትመንቶች ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የታቀደ ሲሆን የጋራ መኖርያ ማህበራት ይህንን አሰራር ካልተቀበሉ የባንክ ሂሳባቸው እንደሚታገድ ክፍለ ከተሞች እያስጠነቀቁ ይገኛሉ
https://bit.ly/4nL0s4x
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
