fa
Feedback
Condominuim Market in Addis Ababa

Condominuim Market in Addis Ababa

رفتن به کانال در Telegram

በዚህ የቴሌግራም Chanel ከ10,000 ተከታይ በላይ ባለው facebook page በቀን እስከ 500 ሰው ጎብኚ ብለው condoaddis.etsecurities.com በማስታወቂያ ክፍያ ቤትዎን እና መኪናዎን መሸጥ ፣ ማከራየት ይችላሉ ኮሚሽን መክፈል ለማይፈልጉ buy ads here https://telega.io/c/condoaddis 0913587955 መረጃ ለመላክና ለጥያቄ @antget1

نمایش بیشتر
Buy Ad
3 677
مشترکین
+124 ساعت
+147 روز
+8330 روز
آرشیو پست ها
የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀሩት ፤ ሳይረፍድብዎ ውልዎን ያድሱ ! ከሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባና እድሳት አገልግሎ
የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀሩት ፤ ሳይረፍድብዎ ውልዎን ያድሱ ! ከሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባና እድሳት አገልግሎት እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ የሚቆይ በመሆኑ ፣ የተሰጠው ጊዜ ሊጠናቀቅ አነስተኛ ቀናት ቀርተውታል። ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በመቅረብ  አከራዮችና ተከራዮች ውላቸውን እያደሱ ቢሆንም በመጨረሻዎቹ ቀናት ሊደርስ ከሚችል መጨናነቅ እንዲሁም ጊዜው ካለፈ በኋላ የሚያጋጥሙ የቅጣት ውሳኔዎችንና አላስፈላጊ የህግ መተላለፎችን ለማስቀረት ቀሪዎቹን ቀናት በአግባቡ መጠቀም አስፈላጊ ነው። ውል ማደስ የሚያስገኛቸው ዋና ዋና ጥቅሞች፦ ህጋዊ ከለላ ያገኛሉ፦ አከራይም ሆኑ ተከራይ መብትና ግዴታቸውን በህግ ጥላ ስር ያረጋግጣሉ። አላስፈላጊ አለመግባባቶችን ይቀርፋሉ፦ የኪራይ ተመንና የውል ዘመንን በግልጽ በመደንገግ ሰላማዊ አብሮነትን ይፈጥራሉ። ቅጣትን ያድናሉ፦ ሁለት ዓመት የሞላቸው ውሎች ሆነው በተቀመጠው ገደብ (ነሐሴ 30) ካለደሱ ለህጋዊና አስተዳደራዊ ተጠያቂነትና ለተጨማሪ ቅጣት ስለሚያጋልጡ ውል ማደስዎ ከነዚህ ቅጣቶች ያድናል። ትኩረት፦ የምዝገባ ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ ምንም አይነት ተጨማሪ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ፣ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በአቅራቢያዎ ወደሚገኘው የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመቅረብ ውልዎን እንዲያድሱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ሕጋዊ ውል — ለሰላማዊና ለተረጋጋ አኗኗር መሠረት ነው! ነሀሴ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት        ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aahdab

ለሽያጭ – 34 ካሬ የንግድ ሱቅ | ጀሞ 1 ጀሞ 1 ኮንዶሚኒየም ስፋት 34 ካሬ Ground Floor ከዋና መንገድ አጠገብ ወርሃዊ ኪራይ፦ 25,000 ብር ሙሉ ሰነድ ያለው መጠየቂያ ዋጋ፦ 4.2 ሚሊዮን ብር ለተጨማሪ መረጃና ለቦታው ለማየት፦ 📞 0934158917 ለቁም ነገር ገዢ ድርድር ይደረጋል።

📢 NEW LISTING 📌 Category: Real Estate 📝 Title: Yr 💰 Price: 853 👤 Contact: @Antget1

የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀሩት ፤ ሳይረፍድብዎ ውልዎን ያድሱ ! ከሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባና እድሳት አገልግሎ
የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀሩት ፤ ሳይረፍድብዎ ውልዎን ያድሱ ! ከሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባና እድሳት አገልግሎት እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ የሚቆይ በመሆኑ ፣ የተሰጠው ጊዜ ሊጠናቀቅ አነስተኛ ቀናት ቀርተውታል። ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በመቅረብ  አከራዮችና ተከራዮች ውላቸውን እያደሱ ቢሆንም በመጨረሻዎቹ ቀናት ሊደርስ ከሚችል መጨናነቅ እንዲሁም ጊዜው ካለፈ በኋላ የሚያጋጥሙ የቅጣት ውሳኔዎችንና አላስፈላጊ የህግ መተላለፎችን ለማስቀረት ቀሪዎቹን ቀናት በአግባቡ መጠቀም አስፈላጊ ነው። ውል ማደስ የሚያስገኛቸው ዋና ዋና ጥቅሞች፦ ህጋዊ ከለላ ያገኛሉ፦ አከራይም ሆኑ ተከራይ መብትና ግዴታቸውን በህግ ጥላ ስር ያረጋግጣሉ። አላስፈላጊ አለመግባባቶችን ይቀርፋሉ፦ የኪራይ ተመንና የውል ዘመንን በግልጽ በመደንገግ ሰላማዊ አብሮነትን ይፈጥራሉ። ቅጣትን ያድናሉ፦ ሁለት ዓመት የሞላቸው ውሎች ሆነው በተቀመጠው ገደብ (ነሐሴ 30) ካለደሱ ለህጋዊና አስተዳደራዊ ተጠያቂነትና ለተጨማሪ ቅጣት ስለሚያጋልጡ ውል ማደስዎ ከነዚህ ቅጣቶች ያድናል። ትኩረት፦ የምዝገባ ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ ምንም አይነት ተጨማሪ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ፣ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በአቅራቢያዎ ወደሚገኘው የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመቅረብ ውልዎን እንዲያድሱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ሕጋዊ ውል — ለሰላማዊና ለተረጋጋ አኗኗር መሠረት ነው! ነሀሴ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት        ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aahdab ይመልከቱ

ሸገር ቱሉ ዲምቱ ኮንዶሚኒየም ✔️ ስፋት : 86m2 ✔️ የተፈቀደለት አገልግሎት : ለመኖርያ ✔️ የሚገኝበት ወለል : 1ኛ ✔️ የቤቱ አይነት: G7 ✔️ ቦታው : ከዋናው የቱሉ ዲምቱ መንገድ 30 ሜ
ሸገር ቱሉ ዲምቱ ኮንዶሚኒየም ✔️ ስፋት : 86m2  ✔️ የተፈቀደለት አገልግሎት : ለመኖርያ ✔️ የሚገኝበት ወለል : 1ኛ ✔️ የቤቱ አይነት: G7 ✔️ ቦታው : ከዋናው የቱሉ ዲምቱ መንገድ 30 ሜትር የማይርቅ እና መስቀለኛ ላይ የሚገኝ ከስሩ ባንክ ያለው ✔️ የሸገር ዲጂታል ካርታ የጨረሰ፣ ስም መዞር የሚችል ✔️ 20,000 ብር ከተከራየ ሁለት ዓመት ሊሆነው ነው (እስከ 30,000 ብር የሚከራይ) ✔️ ውስጡ ፓርቲሽን የሌለው (ለንግድ የተከራየ) ✔️ የአቢሲኒያ ባንክ ብድር 3 ሚሊዮን ያለበት ✔️ ዋጋ: 6.3 ሚሊዮን 🔑ባለቤት በውስጥ መስመር ያገኛሉ

👉 ኮንዶሚኒየም የሚከራይ 👉 ቦታ ገላን ቃሊቲ በሐይወይው ባለው አስፖልት አጠገብ 👉 ባለ አንድ መኝታ 47 ካሬ 👉 አራተኛ ወለል 👉 የተሟላ የግቢ ጥበቃ ያለው 👉 ባለቤት ነኝ 👉የኪራይ ዋጋ
👉  ኮንዶሚኒየም የሚከራይ 👉  ቦታ ገላን ቃሊቲ በሐይወይው ባለው አስፖልት አጠገብ 👉  ባለ አንድ መኝታ 47 ካሬ 👉  አራተኛ ወለል 👉  የተሟላ የግቢ ጥበቃ ያለው 👉 ባለቤት ነኝ 👉የኪራይ ዋጋ 23,000 መከራየት የሚፈልግ በዚህ ስልክ መደወል ይችላል  0909259319።

የሚሸጥ አያት ኮንደሚኒየም 🏘✔️ ቦታ አያት ፀበል/ቁጥር 1 ከመቄዶንያ ጀርባ 🏘✔️ ደላላ የለውም፣ ባለቤት ነኝ። 🏘✔️ 1ኛ ፎቅ 🏘✔️ ባለ2 መኝታ ቤት 🏘 ✔️ 1መታጠቢያ ቤት 🏘 ✔️ ሙሉ
የሚሸጥ አያት ኮንደሚኒየም 🏘✔️  ቦታ አያት ፀበል/ቁጥር 1 ከመቄዶንያ ጀርባ 🏘✔️ ደላላ የለውም፣ ባለቤት ነኝ። 🏘✔️ 1ኛ ፎቅ 🏘✔️ ባለ2 መኝታ ቤት 🏘 ✔️ 1መታጠቢያ ቤት 🏘 ✔️ ሙሉ ጥንቅቅ ብሎ የተሰራ 🏘✔️ እዳ የዘጋ ዲጂታል ካርታ 🏘✔️ ኪችን ካብኔት የተገጠመለት  ና ቁም ሳጥን 🏘✔️ 59ካሬ ሜትር common area 69.45 🏘✔️6.5ሚ ፣ 🏘 ✔️ ለባንክም በካሽም ይሆናል፣ ደላላ የለውም፣ ባለቤት ነኝ:: 🏘  📞 ለበለጠ መረጃ 0911832437 ይደውሉ

የውጭ ዜጎች በአዲስ አበባ ቤት ለመግዛት 150 ሺህ ዶላር ያስፈልጋቸዋል አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2018 — ET Securities የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ሊሆኑ የሚችሉበትን የአፈጻጸም ማዕቀፍ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ በአዲስ አበባና ሸገር ከተሞች የሚገዙ የውጭ ዜጎች ቢያንስ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በሕጋዊ የባንክ መስመር ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ። የአዲሱ ማዕቀፍ መሠረት የሆነው የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤትነት መብት አዋጅ ቁጥር 1388/2025 ሲሆን፣ አዋጁ የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት እንዲገዙ የሚያስችል አዲስ የሕግ ማዕቀፍ ዘርግቷል። መመሪያው እንደሚያስቀምጠው የሚፈለገው የውጭ ምንዛሬ መጠን በአካባቢው የልማት ደረጃ መሠረት የሚለያይ ሲሆን፣ በአዲስ አበባና ሸገር 150 ሺህ ዶላር፣ በተለያዩ የክልል ከተሞች 120 ሺህ ዶላር፣ በአፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝና ጋምቤላ 100 ሺህ ዶላር የዝቅተኛ መጠን ገደብ እንደተቀመጠ ተገልጿል። ይህ ገደብ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፈቃድ ካላቸው የውጭ ባለሀብቶች የተለየ አተገባበር እንዳለውም ተመልክቷል። አዋጁ የውጭ ባለሀብቶችን ከመደበኛው የ150 ሺህ ዶላር መስፈርት የተለየ ሁኔታ ውስጥ ያስቀምጣል። አንድ ቤት ብቻ አዲሱ ማዕቀፍ የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ንብረት ባለቤትነትን በቁጥርም ይገድባል። በአጠቃላይ አንድ የውጭ ዜጋ አንድ የመኖሪያ ቤት ብቻ እንዲኖረው ተደንግጓል። የሚገዛው ንብረትም በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ መሠረት በሊዝ መሬት ላይ የተገነባ መኖሪያ ቤት መሆን አለበት፤ የመሬት ባለቤትነት ግን ለውጭ ዜጎች አይሰጥም። በተጨማሪም በመንግሥት ድጎማ የተገነቡ እና ለዜጎች ተብለው የተዘጋጁ የኮንዶሚኒየም ቤቶች በዚህ የባለቤትነት መብት ሊገዙ እንደማይችሉ ተቀምጧል። ከኢትዮጵያ ባንኮች ብድር አይፈቀድም የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ቤት ግዢን ለመፈጸም ከኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት ብድር መውሰድ አይችሉም። ይህም የግዢው ገንዘብ ከውጭ ምንዛሬ ምንጭ በሕጋዊ የባንክ ሥርዓት ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን የሚያረጋግጥ መስፈርትን ያጠናክራል። የቤቱን ንብረት ማከራየት ይቻላል የውጭ ባለቤቶች የገዙትን ቤት ለመኖሪያ ዓላማ ማከራየት ይችላሉ። ነገር ግን ንብረቱን እንደ ካፌ፣ ቢሮ ወይም ሌላ የንግድ ቦታ መጠቀም በዚህ ማዕቀፍ አይፈቀድም። ከዚህ በተጨማሪ ከንብረቱ ኪራይ ወይም ከሽያጭ የሚገኝ ገቢ በሕጋዊ የውጭ ምንዛሬ ሥርዓት መሠረት ወደ ውጭ አገር ሊተላለፍ ይችላል። የቪዛ እና የመኖሪያ ጥቅሞች በሕጋዊ መንገድ ቤት የገዙ የውጭ ዜጎች ከንብረት ባለቤትነቱ ጋር ተያይዞ የመኖሪያ ፈቃድ ወይም እስከ አምስት ዓመት የሚቆይ ብዙ ጊዜ መግቢያና መውጫ ቪዛ ሊያገኙ ይችላሉ። በተጨማሪም የባለቤትነት መብቱ በ“Principle of Reciprocity” መርህ የተመሠረተ ሲሆን፣ የውጭ ገዢው ዜግነት ያለበት አገር ለኢትዮጵያውያን ተመሳሳይ የመኖሪያ ንብረት ባለቤትነት መብት መፍቀዱ ከሚታዩ መስፈርቶች አንዱ ነው። አዲሱ ማዕቀፍ በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬ ፍሰትን ለማሳደግ እና የሪል እስቴት ዘርፉን ለውጭ ካፒታል ለማስፋት የታቀደ ሲሆን፣ በሌላ በኩል የውጭ ገዢዎች በሀገር ውስጥ ባንኮች ከሚሰጡ ብድሮች ይልቅ የውጭ ምንዛሬ እንዲያስገቡ በማስገደድ በውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ ተጨማሪ ፍሰት ለመፍጠር ያለመ ነው። የአዋጁ መሠረታዊ ማዕቀፍ ከጥቅምት 2 ቀን 2025 ጀምሮ ተፈጻሚ ሆኗል።

በአከራይ ተከራይ ውል እድሳት ፈፅሞ የተከለከሉ ጉዳዮች? ✍ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤ ✍ የውል እድሳት ምዝገባን አለመፈጸም በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት ከሐምሌ  1 ቀን ጀምሮ የተጀመረውን አዲስ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እድሳት ምዝገባ ሳያከናውን መቅረት ወይም መሸሽ አይቻልም።  ✍ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ዕድሳት አለማስመዝገብ፤ ✍ ሕገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ በከተማ አስተዳደሩ       ከተቀመጠው የ11.5% ዓመታዊ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ በላይ መጨመር ወይም በየምክንያቱ ዋጋ ማናር በጥብቅ የተከለከለ ነው። ✍ አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤ ✍ በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤ ✍ አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ       እንዲፈጸም ማስገደድ፤ ✍ በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የሆነ የኤሌክትሮኒክስ መንገድ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈጸም፤ ✍ ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት  እንዲቀመጥ ማድረግ፤ ✍  የመንደር ወይም የ«ልዩ» ውል ማሰር፦ በየደረጃው በሚገኙ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ፅህፈት ቤቶች ሳይመዘገብና ዕውቅና ሳይሰጠው፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ብቻ የሚደረግ ማናቸውም ዓይነት "የመንደር ውል" ወይም "የውስጥ ስምምነት" በሕግ ፊት ዋጋ የለውም፤ የተከለከለም ነው። ✍ በጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) አካባቢ የሚደረጉ ሕገ-ወጥ ውሎች በኮንዶሚኒየም መንደሮች ውስጥ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶችን  ያለ ቢሮው ዕውቅናና ምዝገባ በሕገ-ወጥ መንገድ ማከራየትና ውል መዋዋል የተከለከለ ነው። ከላይ የተጠቀሱ ክልከላዎችን የፈጸመ አስተዳደራዊ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡ " ሕጋዊ ምዝገባን ባለመፈጸም ራስዎን ለሕግ  ተጠያቂነትና   ለአላስፈላጊ ቅጣት አያጋልጡ!" Condoaddis.com

"የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ድሮ በነበረው ዋጋ ለማስረከብ እንቸገራለን"ከንቲባ አዳነች አቤቤ ​ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ተረካቢዎች ወቅቱን ያገናዘበና ምክንያታዊ የሆነ ዋጋ መክፈል ግድ እንደ
"የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ድሮ በነበረው ዋጋ ለማስረከብ እንቸገራለን"ከንቲባ አዳነች አቤቤ ​ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ተረካቢዎች ወቅቱን ያገናዘበና ምክንያታዊ የሆነ ዋጋ መክፈል ግድ እንደሚላቸው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ ትናንት በከተማው ምክር ቤት ተጠይቀው እንደተናገሩት፥ ቤቶቹን የዛሬ 20 ዓመት በነበረው የዋጋ ተመን ማስተላለፍ የማይቻል ቢሆንም፣ አሁንም ዋጋው ተመጣጣኝ (Affordable) እንዲሆን ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ማንበብ ይቀጥሉ👇 ​condoaddis.com