fa
Feedback
አቡ ዩስራ - ንጽጽራዊ አስተምህሮ

አቡ ዩስራ - ንጽጽራዊ አስተምህሮ

رفتن به کانال در Telegram

የአቡ ዩስራ ንጽጽራዊ ሀይማኖት ላይ ያተኮሩ የፁሁፍና የድምጽ ስራዎች ይቀርቡበታል።

نمایش بیشتر
4 063
مشترکین
+324 ساعت
+137 روز
+5530 روز
آرشیو پست ها
በወላይታ ሶዶ ከተማ "አቶ ሽኩር መሃመድ መጽሐፍ ቅዱስን ቀደው ለብስኩት መጠቅለያ ተጠቀሙ" ተብሎ የተሰራጨው ዜና እውነታውን ያላገናዘበ እና የአካባቢውን አናሳ ሙስሊም ከክርስትያኑ ጋር ለማጋጨት ሆን ተብሎ የተቀነባበረ "እኩይ ድራማ" ለመሆኑ ግልጽ ማሳያዎች አሉት። ከአካባቢው ሰዎች ስለ ጉዳዩ ከሰማሁት አንጻር የተወሰኑትን ነጥቦች ልዘርዝርላችሁና ከዚህ ጩኸት ጀርባ ያሉ አካላት ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ ምላሹን ለራሳችሁ ውሰዱት። መግቢያ እንዲሆናችሁ፣ አቶ ሽኩር የተባሉት ግለሰብ ተግባሩ ሲፈጸም ከነአካቴው ቦታው ላይ አልነበሩም፣ ኃላ ግርግሩ ከተፈጠረ በኃላ ተጠርተው ነው የመጡት። ይህ ተግባር ተፈጸመ በተባለበት ወቅት የነበሩት አስተናጋጅ ልጆች ገና በአስራዎቹ እድሜ የሚገኙና አማርኛ ቋንቋ ማንበብ አይደለም በስርኣቱ እንኳን መናገር የሚከብዳቸው ታዳጊዎች ናቸው። በተጨማሪም ልጆቹ በርግጥም ብስኩቱን ጠቅለውበታል ወይንስ ሰዎቹ ሆንብለው ከውጭ ይዘው መጥተዋል የሚለው ገና በህግ በኩል እየተጣራ የሚገኝ ነው። ይህንን ያዙና ከዚህ በታች ነጥቦቹን ላስቀምጥላችሁ፦ ፩/ በአሁኑ ሰዓት አንድ መጽሐፍ ቅዱስ በገበያ ላይ በሺዎች የሚቆጠር ብር ያወጣል። አንድ በክፍለ ሀገር ከተማ ውስጥ በሻይ ቤት ንግድ የሚተዳደር ሰው፣ በትንሽ ሳንቲም የሚገዛ መጠቅለያ ወረቀት እያለ፣ በመቶዎች የሚቆጠር ብር አውጥቶ መጽሐፍ ቅዱስን ለብስኩት መጠቅለያነት ይጠቀማል ማለት የጤናማ አእምሮ ውጤት አይደለም። ፪/ ልጆቹ ማንበብና መጻፍ የማይችሉ በመሆኑ ወረቀቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ገጽ ይሁን ወይም ሌላ ተራ ወረቀት የመለየት አቅም አይኖረውም። ፌስታል በመከልከሉ ምክንያት አሁን ላይ ያረጁ መጽሐፍትና ወረቀቶች ለተለያዩ ጥቅሞች በኪሎ ተሸጠው ለችርቻሮ ነጋዴዎች እጅ እንደሚገቡ ይታወቃል። ግለሰቡ ወረቀቱን ከወረቀት መሸጫ ገዝቶት ሊሆን እንደሚችል ግልጽ ሆኖ ሳለ፣ "ሆን ብሎ ሃይማኖት ለማናጋት" ተብሎ መፈረጁና በማህበራዊ ሚዲያ መጋጋሉ ሆን ተብሎ ግጭት የመፍጠር ዘመቻ ነው። ፫/ ወላይታ የፕሮቴስታንት (የጴንጤ) እምነት ተከታዮች በብዛት የሚገኙባት ከተማ እንደሆነች ይታወቃል። በእንደዚህ ዓይነት አካባቢ ላይ ያለ አንድ ሙስሊም ነጋዴ፣ ቤተሰቡንና ንግዱን አደጋ ላይ ጥሎ መጽሐፍ ቅዱስን ለብስኩት መጠቅለያነት እያወቀ ይጠቀማል ብሎ ማሰብ ፈጽሞ የማይመስል ነገር ነው። ግለሰቡ እንዲህ ዓይነት ድፍረት ቢኖረው እንኳ፣ ጥቃቅን ብስኩት ለመጠቅለል ሲል ራሱን ለሞት አሳልፎ አይሰጥም። ፬/ የሚያሳዝነው ፖሊስ ገና ምርመራው ሳይጠናቀቅ "እኩይ ተግባር"፣ "ለዘመናት የቆየውን እሴት ለማናጋት የታለመ" እያለ መግለጫ መስጠቱ፣ ገና ሳይፈረድበት ግለሰቡን ወንጀለኛ አድርጎ ለህዝብ ቁጣ አሳልፎ መስጠት ነው። ይህ ደግሞ ጉዳዩ ከግለሰቡ ጥፋት ይልቅ በስተጀርባው ሌላ የፖለቲካ ወይም የሃይማኖት ግጭት የመቆስቆስ አጀንዳ ያላቸው ሰዎች የህግ አካላትን ሳይቀር እያሳሳቱ መሆኑን የሚጠቁም ነው። ፭/ በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ መጻሕፍት ካረጁ በኋላ ለወረቀት ሻጮች ይሰጣሉ። እነዚህ ወረቀቶች በኪሎ ተመዝነው ለችርቻሮ ነጋዴዎች ይሸጣሉ። በተለይ አሁን ፌስታል ከመከልከሉ ጋር ዋነኛ መገልገያው ወረቀት ሁኗል። ነጋዴው የገዛው ወረቀት ውስጥ ምን እንዳለ ላያውቅ ይችላል። ጥፋቱ መጽሐፍ ቅዱሱን አርጅቷል ብሎ ለቆሻሻ ወረቀት ሻጭ በኪሎ በሸጠው ሰው ላይ እንጂ፣ ምንነቱን ሳያውቅ ለንግድ በተጠቀመው ምስኪን ነጋዴ ላይ መሆን የለበትም። ➺ ማጠቃለያ ልጆቹ ይህንን ተግባር አድርገውታል እንኳን ቢባል የሚሰጠው ትርጉም ባለማወቅ የሰሩትን ስህተት መነሻ በማድረግ፣ በአካባቢው ያለውን ሰላም ለማናጋት የሚፈልጉ አካላት ጉዳዩን ሆን ብለው እያጋጋሉት እንዳለ ነው። ፖሊስና ህዝቡ እንዲህ ዓይነት ጥቃቅንና ባለማወቅ የሚደረጉ ስህተቶችን ለትልቅ ግጭት መነሻ ከማድረግ ይልቅ፣ በእርጋታና በእውነት ላይ ተመስርተው ሊፈርዱ ይገባል። ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻ https://t.me/Yahyanuhe

ከአመታት በፊት በአሜሪካ ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ የሚማር አንድ ወንድማችን ለሒዳያ እስላማዊ ማዕከል አንድ አፕሊኬሽን በነፃ ሰርቶ አስረከበን። ስራው እጅግ የሚያምር ስለነበር ከልብ አመሰገንኩት። እሱ ግን በሰራው ስራ ብቻ ሳይረካ "ኡማውን የሚጠቅም ሌላ ምን ልስራ? ጠቁመኝ" አለኝ። በወቅቱ አንድ ሁሌም የሚረብሸኝ ጉዳይ ነበር። የቁርኣን አፕሊኬሽኖች ለአጠቃቀም ምቹ አለመሆናቸውና በተለይ ገፅታቸው (Interface) ከሌሎች ተመሳሳይ የሌላ እምነት አፖች አንፃር ሲታይ ማራኪ አለመሆኑ ያበሳጨኝ ነበር። "ለምን ለአጠቃቀም ቀላልና እጅግ ማራኪ የሆነ የቁርኣን አፕሊኬሽን አትሰራም? አኼራህ ላይ ትልቅ ሰደቀተል ጃሪያ ይሆንልሃል" አልኩት፤ ሌሎች ጥቂት ሀሳቦችንም ተወያየን። ከዚህች አጭር ውይይት በኋላ ዓመታት አለፉ። ስለ ጉዳዩም ምንም መረጃ አልነበረኝም። ነገር ግን ሰሞኑን፣ በእነዚህ በተባረኩ የረመዳን የመጨረሻ ቀናት ውስጥ... ፈጽሞ ያልጠበቅኩትን እጅግ አስደሳች ብስራት አበሰረኝ! ያኔ ያሰብነው ህልም እውን ሆኖ፣ በአማርኛ፣ በኦሮምኛ፣ በአፋርኛ እና በሌሎችም የሀገራችን ቋንቋዎች የተዘጋጀ፣ እጅግ ውብና ለመጠቀም ቀላል የሆነ የቁርኣን አፕሊኬሽን ሰርቶ መጨረሱን አበሰረኝ! አፕሊኬሽኑ ለአንድሮይድም ሆነ ለአይፎን ተጠቃሚዎች ዝግጁ የተደረገ ሲሆን ወንድማችን ይህንን ትልቅ ስራ የሰራው ያለውን ውድ ሰዓት እያጣበበ በትርፍ ጊዜው ነው። አላህ (ሱ.ወ) መልካም ምንዳውን ይክፈለው! ሁላችሁም ይህንን አፕሊኬሽን ከታች ባለው ሊንክ ዳውንሎድ አድርጋችሁ እንድትጠቀሙበት በደስታ እጋብዛችኋለሁ። ከተጠቀማችሁት በኋላ እንዲስተካከል ወይም እንዲጨመር የምትፈልጉትን ሀሳብ ኮመንት ላይ ብታካፍሉን ደግሞ ይበልጥ እናዳብረዋለን። ለዚህ ቀና ወንድማችን ከልብ የሆነ ዱዓ እናድርግለት! ፖስቱን ሼር በማድረግ በተጠቃሚው ልክ እርስዎም የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ። 🔗ለአንድሮይድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=dev.ridwan.quran 📎 ለአይፎን፦ https://apps.apple.com/us/app/nur-quran-app/id6759636756 ሁላችንም ሼር በማድረግ ተደራሽ እናድርገው።

አልሐምዱሊላህ ተጨማሪ አንድ ቀን አገኝን።

ረያን መስጂድ ግንባታ Reyan Mesjid Ginbata CBE: 1000752099147 ​«مَنْ بَنَى مَسْجِدًا لِلَّهِ بَنَى اللَّهُ لَهُ بَيْتًا فِي الْجَنَّةِ»

ሁላችሁም እንደምታውቁት በዚህ ገጽ ላይ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ንጽጽሮችንና ትምህርታዊ ጽሁፎችን ስናካፍል ቆይተናል። ሆኖም ግን፣ ቀድሞ ስጠቀምበት የነበረውና ከ100ሺ በላይ ተከታይ የነበረው ዋናው ገጽ
ሁላችሁም እንደምታውቁት በዚህ ገጽ ላይ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ንጽጽሮችንና ትምህርታዊ ጽሁፎችን ስናካፍል ቆይተናል። ሆኖም ግን፣ ቀድሞ ስጠቀምበት የነበረውና ከ100ሺ በላይ ተከታይ የነበረው ዋናው ገጽ (Page) በፌስቡክ ሕግጋት ምክንያት ለተወሰኑ ወራት ከእይታ ውጪ ሆኗል (ታግዷል)። በዚህ ሳቢያ ትምህርቱ ግን መቆም የለበትምና አዳዲስ የንጽጽር ጥናቶችን፣ ቪዲዮዎችንና ጽሁፎችን በቋሚነት የማጋራበት አዲስ ፔጅ አዘጋጅቻለሁ። ከእንግዲህ በስፋት የምንገናኘው እዚያኛው ገጽ ላይ ይሆናል። አዲሱን ፔጅ በዚህ ሊንክ ያገኙታል፦ https://www.facebook.com/share/1b3VE7KduG/ ትምህርቶቼ ጠቃሚ ናቸው ብላችሁ የምታምኑ ሁላችሁም ወደዚህ አዲስ ገጽ በመምጣት Follow እና See First በማድረግ ቤተሰብ እንድትሆኑና ትምህርቱን ለሌሎችም እንድታጋሩ በትህትና እጠይቃለሁ።

አላህ «ፍቅር» ነው ወይስ «አፍቃሪ»? ብዙ ጊዜክርስቲያን ወገኖች መጽሐፍ ቅዱስ "እግዚአብሔር ፍቅር ነው" (1ኛ ዮሐንስ 4:8) የሚለውን ጥቅስ በመጥቀስ፣ ሙስሊሞችን "አላህ ፍቅር ነውን?" ብለው ይጠይቃሉ። ለእዚህ ጥያቄ እስላማዊ ምላሹ አጭርና ግልጽ ነው፡- አላህ «ፍቅር» አይደለም፤ ነገር ግን እርሱ «እጅግ አፍቃሪ» (አል-ወዱድ ) ነው። (ቁርኣን 85፡14) አምላክ የባህሪ ባለቤት እንጂ ባህሪው ራሱ አይደለም አምላክ ፍቅርነው" ማለት በቋንቋም ሆነ በሥነ-መለኮት ትክክለኛ ትርጉም አይሰጥም። ምክንያቱም ፍቅር ስሜት ወይም ባህሪ ሲሆን፣ አምላክደግሞ ያንን ባህሪ የሚገልጽ "ባለቤት" ነው።ይህንን በሌሎችየአምላክ ባህሪያት ስናነጻጽረው ይበልጥ ግልጽ ይሆናል፦·     አምላክ "ምሕረት" አይደለም፤ እርሱ እጅግመሐሪ(አር-ራህማን) ነው። አምላክ "ፍትሕ" አይደለም፤ እርሱ እጅግፍትሐዊ(አል-ዐድል) ነው። አምላክ "እንክብካቤ" አይደለም፤ እርሱ ተንከባካቢ(አል-ሙሀይሚን) ነው። አምላክ "ኃይል" አይደለም፤ እርሱ ሁሉንቻይ(ኃያል) (አል-ቀዊይ) ነው።

"ሙስሊሞች ማታ ከሚስቶቻቸው ጋር ግንኙነት ስለሚያደርጉ ጾማቸው ጾም አይባልም" የሚል ትችት ብዙ ጊዜ ከኦርቶዶክሶች እንሰማለን። የዚህ ትችት ዋነኛ ችግር የራስን ሚዛን ለሌላው የመጠቀም ችግር ነው። በክርስትና (በተለይ በኦርቶዶክስ) ሥርዓት ጾም ወቅትን ያማከለ ሕግ ነው። ለምሳሌ የዐቢይ ጾም 55 ቀናት ሲጾም፣ በነዚህ ቀናት ውስጥ ሌሊትም ሆነ ቀን የትዳር ግንኙነት ማድረግ ክልክል ነው። በእስልምና ግን ጾም የ"ቀን"እንጂ የ"ሌሊት" ሕግ አይደለም! የሙስሊሙ ጾም የሚጀምረው ንጋት (ፈጅር) ላይ ሲሆን የሚያበቃው ፀሐይ ስትጠልቅ (መግሪብ) ላይ ነው። ፀሐይ ከጠለቀች በኋላ ጾም የለም፤ "የጾም ማብቂያ" (ኢፍጣር) ነው። ስለዚህ አንድ ሙስሊም ጾም በሌለበት ሰዓት (በሌሊት) የፈጸመው ሕጋዊ ድርጊት፣ በቀን የዋለውን ጾም እንዴት ሊያፈርስበት ይችላል? ሌላው መዘንጋት የሌለበት በእስልምና "በባለ ትዳሮች መካከል የሚደረግ ግንኙነት" ኃጢአት አይደለም። በአንዳንድ ሃይማኖታዊ ፍልስፍናዎች ውስጥ ሥጋዊ ግንኙነት (በትዳርም ውስጥ ቢሆን) እንደ "ርኩሰት" ወይም "ከመንፈሳዊነት የሚያርቅ" ተደርጎ ይታሰባል። እስልምና ግን ይህንን አይቀበልም። በትዳር ውስጥ የሚደረግ ግንኙነት አላህ የፈቀደው ጸጋ፣ እንዲያውም ምንዳ (አጅር) የሚያስገኝ "ሶደቃ" (ምጽዋት) ነው። በቀን ውስጥ ከሚስት መራቅ የተፈለገው ግንኙነቱ "ርኩስ" ስለሆነ ሳይሆን፣ ልክ ንጹህ ውሃ መጠጣትና ሐላል ምግቦችን መብላት በቀን ውስጥ እንደተከለከለው ሁሉ፣ አላህን ለመታዘዝና ራስን ለመቆጣጠር (ተቅዋ) ነው። አላህ የሰውን ልጅ ተፈጥሮ ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህም እንዲህ የሚል ግልጽ መለኮታዊ አዋጅ አውርዷል፦ "በጾም ሌሊት ወደ ሴቶቻችሁ መድረስ ለእናንተ ተፈቀደላችሁ፡፡ እነርሱ ለእናንተ ልብሶች ናቸው፤ እናንተም ለእነርሱ ልብሶች ናችሁ... አሁን ተገናኙዋቸው፤ አላህም ለእናንተ የጻፈላችሁን ነገር (ልጅ) ፈልጉ፡፡" (ሱረቱ አል-በቀራህ 2፡187) አምላክ (አላህ) ራሱ "በሌሊት ተፈቅዶላችኋል" ካለ፣ የሰው ልጅ በምን ስልጣኑ ነው "አይ፣ ስለተገናኛችሁ ጾማችሁ አይባልም" የሚለው? አምልኮ ማለት የሰውን ሎጂክ ሳይሆን የአምላክን ሕግ መከተል ነው። እስልምና የ"ራህባኒያህ" (Monasticism / ምንኩስና) ሥርዓትን አያበረታታም። የረመዳን ጾም አላማ የሰውን ልጅ ስሜት ገድሎ ድንጋይ ማድረግ ሳይሆን፣ ስሜቱን ለተወሰነ ሰዓት በቁጥጥር ስር ማዋል ነው። አንድ ሰው ከንጋት እስከ ማታ የራሱ የሆነችውን ሕጋዊ ሚስቱን (በአላህ ትእዛዝ) መራቅ ከቻለ፣ ከረመዳን በኋላ አላህ እርም አድርጎ የከለከለውን ዚና (ዝሙት) በቀላሉ ይርቃል ማለት ነው። ትልቁ ስልጠና ይህ ነው! ማጠቃለያ አንድን ፈተና ማለፍ የሚለካው ፈታኙ ባወጣው መመሪያ እንጂ፣ ሌላ ተማሪ ባወጣው መመሪያ አይደለም። በእስልምና የጾም መመሪያ "በቀን መታቀብ፣ በሌሊት መፍታት" ነው። ስለዚህ ማታ ላይ ውሃ መጠጣት ጾምን እንደማያፈርሰው ሁሉ፣ በትዳር መገናኘትም (አላህ ስለፈቀደው) ጾምን አያፈርስም። ጾሙ ቀላል ነው ተብሎ የሚያስተችም አይደለም። ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻ https://t.me/Yahyanuhe

ድርብ መስፈርት "የየርኅራኄ መለኪያው "ሥቃዩ" ራሱ ሳይሆን የሥቃዩ ሰለባ "ማንነት" መሆኑን ነው። ​እናቱን ላጣች ዝንጀሮ የሚያለቅስ፣ ነገር ግን በፍርስራሽ ስር ሆኖ ለሚጮህ ሕፃን ዝምታን የሚመርጥ
+1
ድርብ መስፈርት "የየርኅራኄ መለኪያው "ሥቃዩ" ራሱ ሳይሆን የሥቃዩ ሰለባ "ማንነት" መሆኑን ነው። ​እናቱን ላጣች ዝንጀሮ የሚያለቅስ፣ ነገር ግን በፍርስራሽ ስር ሆኖ ለሚጮህ ሕፃን ዝምታን የሚመርጥ ዓለም፤ "ሥልጣኔ"፣ "ሰብአዊነት"፣ "ምሕረት" እና "ፍትሕ" በሚሉ ቃላት ተሸፍኖ የነበረውን እውነተኛ አውሬነቱን አጋልጧል።

እንኳን ለታላቁ የረመዷን ወር ፆም አላህ በሰላም በጤና አደረሳችሁ! ፆሙን አላህ የዱዓ፣ የቂርኣት፣ የዚክር፣ የመልካም ተግባራት ወር ያድርግልን ረመዷን ሙባረክ!!

​ወንድማችን ሳላህ ዘይን ነገ በሚያስመርቀው አዲስ መጽሐፉ፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጊዜ ሂደት 'ሰማዕት' የሆኑ ብራናዎችን ያስቃኘናል። ​ሁላችሁም በዕለቱ ተገኝታችሁ የዚህ ድንቅ ዝግጅት ተካፋይ እን
​ወንድማችን ሳላህ ዘይን ነገ በሚያስመርቀው አዲስ መጽሐፉ፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጊዜ ሂደት 'ሰማዕት' የሆኑ ብራናዎችን ያስቃኘናል። ​ሁላችሁም በዕለቱ ተገኝታችሁ የዚህ ድንቅ ዝግጅት ተካፋይ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል። ​ነገ እንገናኝ!

ቁርኣን የመጨረሻውና ብቸኛው መመሪያ ነው‼ ቁርኣን 5:19 يَآأَهۡلَ ٱلۡكِتَٰبِ قَدۡ جَآءَكُمۡ رَسُولُنَا يُبَيِّنُ لَكُمۡ عَلَىٰ فَتۡرَةࣲ مِّنَ ٱلرُّسُلِ أَن تَقُولُواْ مَا جَآءَنَا مِنۢ بَشِيرࣲ وَلَا نَذِيرࣲۖ فَقَدۡ جَآءَكُم بَشِيرࣱ وَنَذِيرࣱۗ وَٱللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيۡءࣲ قَدِيرࣱ [እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! «አብሳሪና አስፈራሪ አልመጣልንም» እንዳትሉ ከመልክተኞች በመቋረጥ ጊዜ ላይ ሲኾን (ሕጋችንን) የሚያብራራ ኾኖ መልክተኛችን በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ አብሳሪና አስፈራሪም በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው] ​ይህ የቁርኣን አንቀፅ ከነቢዩ ዒሳ (ዐ.ሰ) በኋላ እስከ ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ) መላክ ድረስ ባለው የሽግግር ወቅት (ፈትራ) ሌላ ነቢይ ስላልተላከ፣ የመጽሐፉ ሰዎች (አህሉል ኪታብ) ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ) ሲላኩ የመከተል ግዴታ እንዳለባቸው የሚያስገነዝብ ነው። ​አንቀጹ የሚያስጠነቅቀው በትንሳኤ ቀን፡- "ጌታችን ሆይ! እኛ እኮ በተሳሳተ መንገድ ላይ ነበርን፤ ትክክለኛውን መንገድ የሚያሳየንና የሚያስተምረን አብሳሪም ሆነ አስጠንቃቂ መልእክተኛ አልመጣልንም፤ ታዲያ ለምን ትቀጣናለህ?" የሚል የሀሰት ሙግት እንዳያቀርቡ ነው። አላህ ይህን ሰበብ አስቀድሞ በመዝጋት የመጨረሻውን ነቢይ ልኳል። ​ቁርኣን የመጨረሻውና ብቸኛው መመሪያ ነው፤ ከእሱ ውጪ ሌላን መንገድ መከተልም ዘላቂ ድነትን  አያስገኝም።

"ሃይማኖታዊ ጥላቻ እንጂ አመክንዮአዊ ትችት አይደለም" ብዙን ግዜ ክርስቲያኖች ነብያችሁ /ሰዐወ/ እንደ ሴት ቁጭ ብሎ ይሸናል በማለት ለመሳለቅ ይሞክራሉ ።ነገር ግን በምስሉላይ እንደምንመለከተው፣ የ
"ሃይማኖታዊ ጥላቻ እንጂ አመክንዮአዊ ትችት አይደለም" ብዙን ግዜ ክርስቲያኖች  ነብያችሁ /ሰዐወ/  እንደ ሴት ቁጭ ብሎ ይሸናል በማለት ለመሳለቅ ይሞክራሉ ።ነገር ግን በምስሉላይ እንደምንመለከተው፣ የብሉይ ኪዳን ካህናትም ሆኑ ኢየሱስ ይለብሱት የነበረው ልብስ ረጅም ቀሚስ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ካህናቱ ከበፍታ የተሠራ ረጅም ቀሚስና መጠምጠሚያ እንዲያደርጉ ያዛል። በተጨማሪም "እፍረተ ሥጋቸውን ይከድኑ ዘንድ ከወገባቸው እስከጭናቸው የሚደርስ የበፍታ ሱሪ አድርግላቸው" ይላል። [ዘጸአት 28:39-42] ኢየሱስም  ይለብስ የነበረው ቀሚስ "ያለ ስፌትከላይ እስከ ታች የተሸመነ" እንደነበር ይገልጻል።[ዮሐንስ 19:23] መፅሀፍ ቅዱስ ቆሞ መሸናትን ባያበረታታም የወንድ ልጅ ባህሪ ወይንም መገለጫ ተደርጎ የተወሰደባቸው በርካታ ጥቅሶች አሉ። "ግድግዳ ላይ የሚሸና" (pisseth against the wall) የሚለው ሐረግ ወንዶችን ለመግለጽ በብሉይ ኪዳን ጥቅም ላይ ውሏል። ★1ኛ ሳሙኤል25፡22 - "ከእርሱ ለሆኑት ሁሉ እስከ ጠዋት ድረስ ግድግዳ ላይ የሚሸናውን አንድ ወንድ ብተው..."(KJV: "any that pisseth against the wall"). ★1ኛ ነገሥት14:10, 21:21 -  "ግድግዳ ላይየሚሸናውን" (ወንዱን) ሁሉ እንደሚያጠፋ ይናገራል። ሌላኛው ነጥብ "እንደ ሴት " ቁጭ ብሎ ይሸናል ብሎ መናገር በራሱ ሴትን እንደ ነውር ወይንም ዝቅተኛ ፍጥረት መቁጥር ነው። ሴት ቁጭ ብላ የምትሸናው በተፈጥሮዋ ነው ይህ ደግሞ ነውር አይደለም። ጥያቄያችን ኢየሱስ እና ካህናቱ  ከላይ እንዳለው ምስል ከለበሱ እንዴት ነበር የሚሸኑት ? ንፅህናቸውን ለመጠበቅ ቁጭ ብለው ቢሸኑ እንደሴት ሆኑ ሊባሉ ነውን?

የኤፒስቲን ፋይልና የማይቀረው የሰማይ መዝገብ! ሰሞኑን ዓለምን እያነጋገረ ያለው የ ኤፒስቲን ፋይል በምድር ላይ ስልጣንና ገንዘብ ያላቸው ሰዎች በምስጢር የሰሩት ግፍና ወንጀል መጋለጥን ያሳያል። ይህ ክስተት ቁርኣን ከ1,400 ዓመታት በፊት ያስጠነቀቀንን ታላቅ እውነት ያስታውሰናል፡- "(ለሰው ሁሉ) መጽሐፉም ይቀርባል፡፡ ወዲያውም ከሓዲዎችን በውስጡ ካለው ነገር ፈሪዎች ኾነው ታያቸዋለህ፡፡ «ዋ ጥፋታችን! ለዚህ መጽሐፍ (ከሥራ) ትንሽንም ትልቅንም የቆጠራት ቢኾን እንጂ የማይተወው ምን አለው» ይላሉም፡፡ የሰሩትንም ነገር ሁሉ ቀራቢ ኾኖ ያገኙታል፡፡ ጌታህም አንድንም አይበድልም፡፡" አል-ካህፍ 18:49 ምን እንማር? ★ ምስጢር የሚባል ነገር የለም! በኤፒስቲን ደሴት ላይ በምስጢር የተሰሩ ግፎች ዛሬ ለዓለም ይፋ ሆኑ። በአላህ ዘንድ ደግሞ "ትንሽም ትልቅም" ስራ አይቀርም። በምድር ላይ የጠፋ ፋይል፣ የተገደለ ምስክርና የተደለዘ መረጃ ቢኖርም፣ የሰማዩ መዝገብ ግን ሁሉንም ይዟል። ★ ፍትህ አይጓደልም! በዱንያ ላይ ፍትህ በገንዘብ ሊገዛ ይችላል፤ ተበዳዮችም ድምጻቸው ታፍኖ ሊቀር ይችላል። ነገር ግን አላህ "ጌታህ አንድንም አይበድልም" ይላል። የሰራነውን ሁሉ "ቀራቢ ሆኖ" የምናገኝበት ቀን ይመጣል። ★የእኔና የእርስዎ ፋይልስ?   የሌሎችን ፋይል መጋለጥ በጉጉት እንደምናየው ሁሉ፣ የእኛም ፋይል በአላህ ፊት የሚዘረጋበት ቀን አለ። የሰው ስም ከመጥፋቱ በፊት፣ የእኛ ስራዎች በአላህ ዘንድ ሳይጋለጡ በፊት ዛሬውኑ በተውበት (በንሰሃ) እናጥፋቸው። በሰው ፊት ከመዋረዳችን በፊት አላህን እንፍራ፤ የተደበቀ ወንጀላችንን በአላህ ይቅርታ እንሸፍን።

"በእርግጥም አልገደሉትም.. " ብዙ ጊዜ የክርስትና ምሁራን "የኢየሱስ ስቅለት የታሪክ ሀቅ ነው" በሚል ይሞግታሉ። ነገር ግን "ታሪክ" ማለት በሰዎች እይታና ስሜት ላይ የተመሰረተ ዘገባ እንጂ ፍፁም እውነት ማለት አይደለም። 1. የሰው ልጅ ምስክርነት ፍፁም አለመሆኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች "አየን" ወይም "ሰማን" ስላሉ ብቻ ነገሩ እውነት ላይሆን ይችላል። የሰው ልጅ ስሜት (ማየትና መስማት) በአምላክ ፈቃድ ሊለወጥ ይችላል። ሰዎች ያዩትን ወይም የሰሙትን ታሪክ አድርገው ቢመዘግቡም፣ አምላክ ግንዛቤያቸውን ከሸፈነው ያ የታሪክ ዘገባ "የታሪክ ስህተት" ይሆናል። 2. መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ (2 ነገሥት 7:6-7) ይህንን ሀሳብ ለማረጋገጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘውን የሶርያ ሠራዊት ታሪክ እንደ ምሳሌ እንመለከት:– ♦ ሶርያውያን የእስራኤልን ከተማ ከበው ሳለ፣ አምላክ የሰረገላ፣ የፈረስና የታላቅ ጭፍራ ድምፅ እንዲሰሙ አደረገ። ሶርያውያንም "የኬጥያውያንና የግብፅ ነገሥታት መጡብን" ብለው በማመን ካምፓቸውን ጥለው ሸሹ። ♦ነግር ግን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን በወቅቱ ወደ ሶርያውያን ካምፕ የሄዱት አራት ለምጻሞች ብቻ ነበሩ። ምንም ዓይነት ሠራዊት አልነበረም። ♦ በዚያ ዕለት የነበረ አንድ የሶርያ ወታደር ታሪክ ቢጽፍ "በታላቅ የግብፅና የኬጥያውያን ሠራዊት ተሸነፍን" ብሎ ነበር የሚመዘግበው። የታሪክ ጸሐፊዎችም ይህንን ድርጊት "ታሪካዊ ሀቅ" አድርገው ይይዙት ነበር። ነገር ግን ታሪኩ የተመሰረተው በአምላክ በተለወጠ "የሰዎች ግንዛቤ" ላይ እንጂ በነባራዊ እውነታ ላይ አልነበረም። አይሁዶችና ሮማውያን "ኢየሱስን ሰቀልነው" ብለው ቢመዘግቡም፣ ያ ዘገባ የተመሰረተው በታየላቸው ምስል ላይ ነው። ቁርኣን እንዲህ ይላል፦ "አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፤ ነገር ግን ለእነሱ (የተሰቀለው ሰው በዒሳ) ተመሰለባቸው።" (4:157) ልክ የሶርያ ወታደሮች ያልነበረን ሠራዊት እንደሰሙት ሁሉ፣ የኢየሱስ ሰቃዮችም ያልነበረን ስቅለት እንዳዩ አድርገው አመኑ። ስናጠቃልለው "መለኮታዊ መግለጫ" ከሰዎች "የታሪክ ምስክርነት" በላይ እውነትን የመግለጥ አቅም አለው። የታሪክ ጸሐፊዎች የሚመዘግቡት ያዩትን/የሰሙትን ብቻ ነው። አምላክ በቁርኣን ግን የሚነግረን የሆነውን ነው። ስለዚህ የታሪክ መመዝገብ የአላህን ተአምር ሊያስተካክል አይችልም‼

" ነብይነት በክርስትና " አምላክ ነብያትን የሚልከው ትእዛዙን እንዲፈፅሙ ፣እንዲያከብሩ ነው።ነገር ግን ህግና ትእዛዝ ሰጥቶ የላካቸው ነብያት የታሰበለትን ዓላማ ካላሳኩ።  መጀመሪያውን "ክርስትና በነብያት ያምናል " ብሎ መናገር ምን ጥቅም አለው? ቀደም ብለው የነበሩ ሰዎች ህግን ሲያከብሩ ፣ትእዛዛትን ሲተገብሩ ነበር እንጂ "አምላክ" መስዋዕት ሊሆንልን ነው ብለው አልነበረም። ይህ እምነታቸው ከነበረ ነብይነት በክርስትናው አላስፈላጊ ነበር። "ሕጉ ምንም ፍጹም አላደረገምና፥ ስለዚህም የምትደክም የማትጠቅምም ስለሆነች የቀደመች ትእዛዝ ተሽራለች፥ ወደ እግዚአብሔርም የምንቀርብበት የሚሻል ተስፋ ገብቶአል"[ዕብ 7:18-19 ]

በነብዩ ﷺ ግዜ የነበሩ አይሁዶች ተውራትን በእብራይስጥ እያነበቡ ለሙስሊሞች ወደ አረብኛ ይተረጉሙ ነበር፣የአላህ መልእክተኛ ለሙስሊሞቹ እንዲህ አሏቸው።
የመጽሐፉን ሰዎች አትመኑአቸው፣ አታስተባብሏቸውምም። ነገር ግን እንዲህ በሉ፡ 'በአላህ አመንን፣ ወደ እኛ በተወረደውም፣ ወደ እናንተም በተወረደው (ሁሉ) አመንን።' ቡኻሪ 7362
ከዚህ ሐዲስ የምናገኛቸው ቁም ነገሮች: ① በጭፍን እንዳናምን፦ የቀድሞ መጻሕፍት በጊዜ ሂደት የሰው እጅ ስለገባባቸው (ሰለተበረዙ)፣ ከመፅሀፉ ሰዎች የሚነገረን መረጃ የተዛባ ወይም ስህተት የመሆን እድሉ ከፍተኛ ስለሆነ። ②በጭፍንም እንዳናስተባብል፦ የሚነገረን መረጃ ምናልባትም ከመጀመሪያው እውነተኛ መለኮታዊ ቃል ውስጥ አንዱ ሊሆን ይችላል። አስተባበልን ካልን የአላህን ቃል   እንደማስተባበል ሊቆጠርብን ይችላል። ③ነቢዩ (ﷺ) "አትመኑአቸውም አታስተባብሏቸውም" ያሉት፣ በመጻሕፍቱ ውስጥ እውነትም ስህተትም ተቀላቅሎ ሊኖር እንደሚችል ስላወቁ ሙስሊሞች በጥንቃቄ እንዲጓዙ ለማድረግ ነው። ④ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ) ይህንን ትዕዛዝ የሰጡት ሙስሊሞች በቁርአን ውስጥ በግልጽ ያልተረጋገጡ ወይም ያልተካዱ መረጃዎችን ከመጽሐፉ ሰዎች (አይሁዶች እና ክርስቲያኖች) ሲሰሙ እንዴት ማስተናገድ እንዳለባቸው ለማስተማር ነው። በቁርኣን በግልፅ ለመጡ ነገሮችን ግን ምንግዜም ቅደሚያ የሚሰጠው ቁርኣኑ መሆኑን ያስረዳል።

በማርቆስ 13፡32 መሰረት "ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን  ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም " በዚህጥቅስ መሰረት ሰለ ትንሳኤ ቀን መላእክት የማያውቁ ከሆነ ከመላእክት ጋር አብሮ የተጠቀሰው “ልጅ”  አያውቅም እያለ ያውቃል ማለት እንዴት ያስኬዳል ? ልጅም የሚያውቅ ከሆነ መላእክት የማያውቁበት ምክንያት ምንድ ነው ?