Defence Construction Enterprise
رفتن به کانال در Telegram
Defense Construction Enterprise (DCE) is one of the leading construction companies in Ethiopia. We are different from other companies as we work in the most remote and difficult areas of the country. We are dedicated and devoted to build the country.
نمایش بیشتر1 681
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
-1730 روز
آرشیو پست ها
+3
ታሪካዊው የራስ ኃይሉ ዓለም-አቀፍ መዋኛ ገንዳ በዛሬው እለት ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል ተደረገ
ሚያዝያ 17/2018ዓ.ም
መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የሚገኘውን የራስ ኃይሉ ዘመናዊ መዋኛ ግንባታ ፕሮጀክት በስኬት አጠናቆ ለአገልግሎት እንዲውል አደረገ።
ኢንተርፕራይዙ የግንባታ ሥራውን ቀደም ብሎ አጠናቆ የርክክብ ሂደቱ የዘገየ ቢሆንም በዛሬው ቀን ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል የመክፈቻ ዝግጅት ተካሄደ።
የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደረጄ ኃ/ገብርኤል እንደገለጹት፤ ግንባታ ፕሮጀክቱ በዋናነት 4,100 ሜትር ኪዩብ ውሃ የሚይዝ (50x25ሜትር) ዓለም-አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዋኛ ገንዳ ፣ የሕፃናት መዋኛ ገንዳ ፣ የመዝናኛ ክበብ ፣ የልብስ መቀየሪያ ፣ ሱቆች እና የፓምፕ ቤት ያካተተ ነው፡፡
ለመዋኛ ገንዳው አገልግሎት የሚሆን እጅግ ዘመናዊ የሙቀት መቆጣጠሪያ (Heating System)፦ የውሃውን ሙቀት እንደ አስፈላጊነቱ በማስተካከል ለውድድርና ለልምምድ ምቹ የሚያደርግ ቴክኖሎጂ ያለው ሲሆን ውሃው በፊዚካላዊ፣ ኬሚካላዊ እና ባዮሎጂካዊ መንገዶች ውሃ ታክሞና ተጣርቶ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል የሚያስችል ዘመናዊ አሠራር ያለው ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት ማዕከሉ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ያደረጉ ሲሆን፤ ይህም ለከተማዋ ስፖርታዊ እንቅስቃሴና ለመዝናኛ ዘርፍ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ይታመናል።
መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በታታሪ የሥራ መሪዎቹና ባልደረቦቹ ሕይወት ማለፍ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል!
በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የምስራቅ ቀጠና ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ላይ በኃላፊነትና በባለሙያነት ሲያገለግሉ የነበሩት፡-
1. ሌ/ኮሎኔል ኢንጂነር አዲሱ ጎአ (የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ)
2. አቶ ሳሙኤል ማሞ (የፕሮጀክቱ ሾፌር)
3. ኢንጂነር በረከት ቁጣ (ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የፕሮጀክቱ አማካሪና ተቆጣጣሪ መሐንዲስ)
ባጋጠማቸው ድንገተኛ የመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ስንገልጽ በታላቅ ሀዘን ነው።
እነዚህ ውድ የሥራ ባልደረቦቻችን፣ ተቋማዊና ሀገራዊ ግዳጃቸውን በላቀ ዲስፕሊንና በትጋት ሲወጡ የነበሩ የሥራ መሪዎችና ባለሙያዎች ነበሩ። የነበራቸው ሙያዊ ብቃት፣ የሥራ ወዳድነትና ለተቋማችን ስኬት በነበራቸው ቁርጠኝነት ዘወትር ሲታወሱ ይኖራሉ።
ተቋማችን መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሟች ቤተሰቦች፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለሥራ ባልደረቦቻቸው በሙሉ መፅናናትንና ብርታትን ይመኛል።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልን!
Repost from FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በ986 ሚሊዮን ብር የህንጻ ግንባታ ፕሮጀክት ጀመረ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሦስት የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት የሚውል የ986 ሚሊዮን ብር ግዙፍ የህንጻ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ወደ ሥራ አስገብቷል።
ለፌዴራል ዋና ኦዲተር፣ ለኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን እና ለኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በጋራ አገልግሎት የሚሰጠው ይህ ፕሮጀክት፤ ሦስት ቤዝመንት እና ግራውንድ ጨምሮ ባለ ሦስት ፎቅ ዘመናዊ ሕንጻ፣ የ200 መኪኖች ማቆሚያ እና የቅጥር ግቢ ማስዋብ ሥራዎችን ያካተተ ነው።
ኢንተርፕራይዙ የገባውን ውል መሠረት በማድረግ፣ ዲዛይኑን ጨምሮ አጠቃላይ ግንባታውን በ7 ወራት አጭር ጊዜ ውስጥ በጥራት አጠናቆ ለማስረከብ የሰው ኃይልና ማሽነሪዎቹን ወደ ሳይት በማሰማራት ሥራውን በቁርጠኝነት ጀምሯል።
የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር እንዳልካቸው በዛብህ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የሆኑት የሳይት ዝግጅት፣ የወሰን ማካለል እና የአፈር ምርመራ ሥራዎች በተሳካ ሁኔታ በመከናወን ላይ ይገኛሉ።
ግንባታው ከመሬት በታች ሦስት ቤዝመንቶች ያሉት በመሆኑ፣ በዙሪያው ባሉ ይዞታዎችና መሠረተ ልማቶች ላይ ምንም ዓይነት አደጋ እንዳይደርስ የቁፋሮ ድጋፍ ግንባታ በልዩ ጥንቃቄ እየተከናወነ መሆኑን ኢንጂነር እንዳልካቸው ገልጸዋል።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የተጣለበትን አገራዊ ኃላፊነት ለመወጣትና ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በውል ስምምነቱ መሠረት በጥራትና በፈጣን አፈጻጸም ለማጠናቀቅ በከፍተኛ ትጋት እየሠራ ይገኛል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ ጥላሁን ደስታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.officialኀ
Repost from FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
በመጠናቀቅ ላይ ያለው የድሬዳዋ ምስራቅ ቀጠና ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማዕከል ፕሮጀክት ሂደት፦
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገነባቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በጥራትና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ገንብቶ ለግንባታው ባለቤት እያስረከበ ይገኛል።
ከነዚህም መካከል በድሬዳዋ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ምስራቅ ቀጠና ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማዕከል ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ግንባታው 97% ደርሷል።
የህንጻው ባለቤት የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የሆነው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከ972 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፤ ግንባታው በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ለታለመለት አገልግሎት እንዲውል በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተሰራ ይገኛል።
የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ሌተናል ኮሎኔል ኢንጂነር አዲሱ ጎአ እንደገለጹት፤ ግንባታው ነሐሴ 2015 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፣ በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እና በፌዴራል ፖሊስ መካከል ባለው ጠንካራ ቅንጅትና መደጋገፍ ስራው ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል።
ኢንተርፕራይዙ አስቸጋሪ ቦታዎችን ጭምር በመግንባት፣ ዘመናዊ ማሽነሪዎችን እና የሰለጠነ የሰው ኃይል በመጠቀም ግንባታዎችን የማጠናቀቅ ብቃቱን በዚህ ፕሮጀክትም ዳግም አስመስክሯል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ለታለመለት ዓላማ እንደሚውል ይጠበቃል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ መሳይ ያደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.officialኀ
ለመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ሠራተኞች የጅምር እሳት አደጋ መከላከል ሥልጠና ተሰጠ
መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር፣ ለዋና መሥሪያ ቤትና በከተማው ዙሪያ ለሚገኙ የፕሮጀክት ሠራተኞች በተግባር የተደገፈ የመሠረታዊ እሳት አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ሥልጠና ሰጥቷል። የሥልጠናው ዋነኛ ግብ በአደጋ ምክንያት የሚደርሰውን የሰው ሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት ማስቀረት እንዲሁም የንብረት ውድመትን በቅድመ-መከላከል ተግባራት መቀነስ መሆኑን የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የሙያ ምክርና ቴክኒክ ድጋፍ ባለሙያ አቶ አጉማስ አለምመጣሁ ገልጸዋል።
ሠልጣኞቹ በቆይታቸው ስለ እሳት ኬሚስትሪ፣ አፈጣጠርና የማጥፊያ ዘዴዎች ማለትም ስለ ማስራብ፣ ማቀዝቀዝ እና ማፈን ጥልቅ ግንዛቤ ማግኘት ችለዋል። በተጨማሪም አደጋ ከመከሰቱ በፊት ሊወሰዱ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች (Prevention)፣ አደጋ ሲከሰት የሚጠቀሙባቸው መሣሪያዎችና ዘዴዎች (Protection) እንዲሁም አስቸኳይ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ የሚከተሏቸው የአደጋ ጊዜ መውጫ መመሪያዎች (Procedure) ላይ በንድፈ-ሐሳብና በተግባር ልምምድ አድርገዋል።
አቶ አጉማስ በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢንተርፕራይዙ በርካታ የንብረት ክምችት ወይም ስቶሮች ያሉበት ተቋም በመሆኑ፣ 70 በመቶው ትኩረት በቅድመ-መከላከል ሥራ ላይ መዋል እንዳለበት ተናግረዋል። ሠልጣኞችም ወደ ሥራ ገበታቸው ሲመለሱ የተቋሙን የዝግጁነት ደረጃ በየጊዜው እንዲገመግሙ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ሥልጠናው በተግባር የተደገፈ በመሆኑ አደጋ ሲያጋጥም በእውቀት ላይ የተመሠረተ ምላሽ ለመስጠት አቅም እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።
አመራሩ በዲሲፕሊን፣ በሥነ ምግባር በሥራ አመራር ለበታቾቹ አርአያ መሆን እንዳለበት ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በሥራ አፈጻጸማቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡና የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በሚገባ ለተወጡ የሠራዊት አባላት የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል።
በዕለቱ የኢንተርፕራይዙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ሰጠኝ ሊኪሳ፤ የማዕረግ ዕድገት በዘፈቀደ የሚሠጥ ሳይሆን የተቋሙን ራዕይ ለማሳካት በታየ ተጨባጭ የሥራ ውጤት ላይ ተመስርቶ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለማዕረግ ተሿሚዎቹ ለቀጣይ ሥራቸው መመሪያ ሲሰጡ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል፦
✅ ኃላፊነት፡- ማዕረግ መጨመር ተጨማሪ ኃላፊነትን መሸከም በመሆኑ፣ እያንዳንዱ አመራር ከማዕረጉ ጋር የሚመጥን አስተሳሰብና ክህሎት ሊኖረው ይገባል።
✅ አርአያነት፡- አመራሩ በዲሲፕሊን፣ በአለባበስ፣ በአነጋገርና በሥራ አመራር ረገድ ለበታች ሠራተኞችና ለሥራ ባልደረቦቹ ምሳሌ መሆን አለበት።
✅ ዝግጁነት፡- የሥራ መሪዎች በሙያቸውም ሆነ በወታደራዊ ሳይንስ ራሳቸውን በማብቃት ለማንኛውም ሀገራዊ ጥሪ ምንጊዜም ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ መሳይ ያደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.officialኀ
Repost from FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
አመራሩ በዲሲፕሊን፣ በሥነ ምግባር በሥራ አመራር ለበታቾቹ አርአያ መሆን እንዳለበት ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በሥራ አፈጻጸማቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡና የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በሚገባ ለተወጡ የሠራዊት አባላት የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል።
በዕለቱ የኢንተርፕራይዙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ሰጠኝ ሊኪሳ፤ የማዕረግ ዕድገት በዘፈቀደ የሚሠጥ ሳይሆን የተቋሙን ራዕይ ለማሳካት በታየ ተጨባጭ የሥራ ውጤት ላይ ተመስርቶ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለማዕረግ ተሿሚዎቹ ለቀጣይ ሥራቸው መመሪያ ሲሰጡ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል፦
✅ ኃላፊነት፡- ማዕረግ መጨመር ተጨማሪ ኃላፊነትን መሸከም በመሆኑ፣ እያንዳንዱ አመራር ከማዕረጉ ጋር የሚመጥን አስተሳሰብና ክህሎት ሊኖረው ይገባል።
✅ አርአያነት፡- አመራሩ በዲሲፕሊን፣ በአለባበስ፣ በአነጋገርና በሥራ አመራር ረገድ ለበታች ሠራተኞችና ለሥራ ባልደረቦቹ ምሳሌ መሆን አለበት።
✅ ዝግጁነት፡- የሥራ መሪዎች በሙያቸውም ሆነ በወታደራዊ ሳይንስ ራሳቸውን በማብቃት ለማንኛውም ሀገራዊ ጥሪ ምንጊዜም ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ መሳይ ያደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.officialኀ
Repost from FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
የመከላከያ ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የመስክ ምልከታ አደረገ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም
ከመከላከያ ሚኒስቴር የተለያዩ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ የከፍተኛ መኮንኖች ቡድን የኢንተርፕራይዙን የእቅድ አፈጻጸም፣ የንብረት አያያዝ፣ የፕሮጀክቶች ጥራትና የክትትል ሥርዓት ተመልክተዋል።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ኢንጂነር ሰጠኝ ሊኪሳ፣ ኢንተርፕራይዙ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው፣ ምልከታው ያሉ ክፍተቶችን በሚገባ ያሳየና መከላከያ ኢንተርፕራይዙን ለማገዝ የሚያደርገውን ድጋፍ ያመላከተ መሆኑን ተናግረዋል።
ተቋሙ ከሪፎርም በኋላ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በማፈላለግና የሥራ አድማሱን በማስፋት ረገድ አበረታች ለውጦች እያሳየ እንደሚገኝ የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው ስራን ቆጥሮ ከመረከብ ባለፈ ውጤትን መለካትና ማረጋገጥ ከተቻለ የግንባታ ሥራዎቹ የተቋሙን እውነተኛ አቅም የሚያሳዩ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ኢንተርፕራይዙ በግንባታው ዘርፍ ብቁ፣ ቀልጣፋና በጥራት ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥል፤ በምልከታ ወቅት የታዩ ክፍተቶችና የቴክኒክ ጉድለቶች በአፋጣኝ ታርመው ወደ ሥራ መገባት እንዳለባቸው ቡድኑ አስገንዝቧል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ መሪ ኮሎኔል ፈይሳ ታደሰ በበኩላቸው፤ ኢንተርፕራይዙ ለመከላከያ ሚኒስቴር ያለውን ስትራቴጂካዊ ፋይዳ ከግምት በማስገባት መሰል የክትትል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ መሳይ ያደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.officialኀ
የመከላከያ ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የመስክ ምልከታ አደረገ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም
ከመከላከያ ሚኒስቴር የተለያዩ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ የከፍተኛ መኮንኖች ቡድን የኢንተርፕራይዙን የእቅድ አፈጻጸም፣ የንብረት አያያዝ፣ የፕሮጀክቶች ጥራትና የክትትል ሥርዓት ተመልክተዋል።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ኢንጂነር ሰጠኝ ሊኪሳ፣ ኢንተርፕራይዙ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው፣ ምልከታው ያሉ ክፍተቶችን በሚገባ ያሳየና መከላከያ ኢንተርፕራይዙን ለማገዝ የሚያደርገውን ድጋፍ ያመላከተ መሆኑን ተናግረዋል።
ተቋሙ ከሪፎርም በኋላ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በማፈላለግና የሥራ አድማሱን በማስፋት ረገድ አበረታች ለውጦች እያሳየ እንደሚገኝ የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው ስራን ቆጥሮ ከመረከብ ባለፈ ውጤትን መለካትና ማረጋገጥ ከተቻለ የግንባታ ሥራዎቹ የተቋሙን እውነተኛ አቅም የሚያሳዩ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ኢንተርፕራይዙ በግንባታው ዘርፍ ብቁ፣ ቀልጣፋና በጥራት ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥል፤ በምልከታ ወቅት የታዩ ክፍተቶችና የቴክኒክ ጉድለቶች በአፋጣኝ ታርመው ወደ ሥራ መገባት እንዳለባቸው ቡድኑ አስገንዝቧል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ መሪ ኮሎኔል ፈይሳ ታደሰ በበኩላቸው፤ ኢንተርፕራይዙ ለመከላከያ ሚኒስቴር ያለውን ስትራቴጂካዊ ፋይዳ ከግምት በማስገባት መሰል የክትትል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ መሳይ ያደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.officialኀ
Repost from FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
የመከላከያ ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የመስክ ምልከታ አደረገ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም
ከመከላከያ ሚኒስቴር የተለያዩ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ የከፍተኛ መኮንኖች ቡድን የኢንተርፕራይዙን የእቅድ አፈጻጸም፣ የንብረት አያያዝ፣ የፕሮጀክቶች ጥራትና የክትትል ሥርዓት ተመልክተዋል።
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ኢንጂነር ሰጠኝ ሊኪሳ፣ ኢንተርፕራይዙ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው፣ ምልከታው ያሉ ክፍተቶችን በሚገባ ያሳየና መከላከያ ኢንተርፕራይዙን ለማገዝ የሚያደርገውን ድጋፍ ያመላከተ መሆኑን ተናግረዋል።
ተቋሙ ከሪፎርም በኋላ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በማፈላለግና የሥራ አድማሱን በማስፋት ረገድ አበረታች ለውጦች እያሳየ እንደሚገኝ የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው ስራን ቆጥሮ ከመረከብ ባለፈ ውጤትን መለካትና ማረጋገጥ ከተቻለ የግንባታ ሥራዎቹ የተቋሙን እውነተኛ አቅም የሚያሳዩ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ኢንተርፕራይዙ በግንባታው ዘርፍ ብቁ፣ ቀልጣፋና በጥራት ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥል፤ በምልከታ ወቅት የታዩ ክፍተቶችና የቴክኒክ ጉድለቶች በአፋጣኝ ታርመው ወደ ሥራ መገባት እንዳለባቸው ቡድኑ አስገንዝቧል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ መሪ ኮሎኔል ፈይሳ ታደሰ በበኩላቸው፤ ኢንተርፕራይዙ ለመከላከያ ሚኒስቴር ያለውን ስትራቴጂካዊ ፋይዳ ከግምት በማስገባት መሰል የክትትል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ መሳይ ያደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.officialኀ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
