HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 280
مشترکین
-124 ساعت
+107 روز
+3530 روز
آرشیو پست ها
ተጠንቀቁ! ዘርን በቀን አምስት ጊዜ የሚያፈሱ ሰዎች || ግለወሲብና የአጋንንት ሴራ || እኛና የጸሎት ቤታችን || የቅዳሴ ሥርዓት || ግብረ አውናን 🚩💥🔥😭 https://youtu.be/QYXkN345h2A
«መሰልቸት»
◈ መሰልቸት ገጥሞህ ያውቃል? ዛሬስ ተሰምቶሃል? ካልሆነም አንድ ቀን ሊሰማህ ይችላልና እስቲ አዳምጥ፤ መሰልቸት ጊዜ ጉልበት፣ ዕድል እያለ ለመራመድ አለመፍቀድ ነው፤ መሰልቸት ከሞት በፊት መሞት ገዳይ ሳይመጣ ሞቶ መጠበቅ ሞትን መንገድ አጋምሶ መቀበል ነው፤ መሰልቸት ስለ ትላንት ማሰብ አይደለም በጣም ስለ ትላንት በማሰብ መሪውን ወይም በትሩን መጣል ነው፡፡
◈ መሰልቸት ስለ ነገ ማሰብም አይደለም ነገን ማየት አለመቻልና ለመኖር አለመፍቀድ ነው፤ መሰልቸት መናደድ ቢሆን በአንድ ነገር ይወጣ ይሆናል፤ መሰልቸት ግን የፍግ እሳት ሲሆን ውስጥ ውስጡን ባለቤቱን በልቶ የሚጨርሰው ነው፤ መሰልቸት ጭስ የማይታይበት ቃጠሎ ነው፤ አጠገባችን ያሉ ስንፍናችን፣ ልፍለፋችን፣ ማጉረምረማችን ያደከማቸው ሰዎች ይሰለቹናል፤ እኛን ሳይሆን ራሳቸውን እያራቁ ይመጣሉ፤ እናጠፋው ዘንድ ሁሉንም ነገር ይተዉልናል፡፡
◈ ያለማቋረጥ የሰዎች ኑሮ እንቅልፍ ሲነሣንና፣ የራሳችንን አስቀምጠን የሰው ወጥ ስናማስል ለጥቂት ጊዜያት ያደነቁን ሰዎች ይሰለቹናል፤ መሰልቸት ከጥጋብ በላይ በመሆኑ ሊያዩን ይሳናቸዋል መቼም ሰልችቻለሁ ወይስ አሰልችቻለሁ? ማለት ተገቢ ይመስላል፤ ምክንያቱም መሰልቸት ጠብ ስለሌለው መራራቅና መረሳሳት ያመጣል እግዚአብሔር ርእስ ያልሆነበት ማንኛውም ግንኙነት የሚደመደመው በመሰለቻቸት ነው፡፡
◈ መሰልቸት መቆጣት አይደለም፣ መቆጣት ገና ተስፋ ማድረግ አለው፤ መሰልቸት ግን ለነገሮች ትርጉም ማጣት ነው፤ መሰልቸት መጥገብ አይደለም፣ መጥገብ በትክክል የመመገብ ድንበር ነው፤ መሰልቸት የተዘረጋውን ገበታ በቃኝ ማለት ነው መሰልቸት ተደራራቢ ከሆኑ የሕይወት ፈተናዎች የሚመጣ ነው፤ ሰይጣን አንድን ዓይነት ፈተና በመደጋጋም ሲያመጣ መሰልቸት ይመጣል መሰልቸት ሞዛዛ ከሆኑ ከሰይጣን ፈተናዎች የሚመጣ ነው፤ ተደጋጋሚ በሽታ፣ ተደጋጋሚ ማጣቶች፣ ተደጋጋሚ ቤተሰባዊ ችግር፣ ተደጋጋሚ በሰዎች መከዳት ሲገጥም መሰልቸት ይመጣል፤ መሰልቸት ከጠላት ጋር ለመታረቅና ጊዜያዊ ሰላም ለማግኘትም የሚዳርግ ነው፤ መሰልቸት ግን ማልቀስ ቢሆን ይቀል ነበር፤ መሰልቸት ለማልቀስም አቅም ማጣት ነው፤ መሰልቸት በውስጡ ቁስለት፣ አልቻልም ባይነት፣ በቃኝ ብሎ መሸነፍ፣ ይህን ዓለም መጥላት፣ ተስፋ መቁረጥ አለው፡፡
◈ የምንፈልጋቸው ነገሮች አለመሆናቸው፣ ሰዎች ለራሳቸው ስሜት ብቻ መኖራቸው፣ የማንውጠው የማንተፋው ጉዳይ፣ በልቅሶም በሳቅም መግለጥ ያዳገተ መንቻካ ነገር ሲገጥም መሰልቸት ይመጣል፤ ዓይንን ከክርስቶስ ላይ ዘወር አድርጎ ሰዎች ላይ ማድረግ ሲጀመር መሰልቸት ይመጣል፤ ይህ ከባድ ውድቀት አለው፤ ፈተናው ገደል አፋፍ ላይ ሊያደርሰን ይችላል፤ መሰልቸት ግን ገደል ውስጥ ዘለን እንድንገባ ያደርገናል፤ መሰልቸት ፈተና ሳይሆን ለፈተናው ያለን የመጨረሻ ምላሽ ነው፡፡
◈ በኀዘን ላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ይውጣላቸው ተዉአቸው ይባላል፤ መሳቅ ከጀመሩ ግን ወዲያው ይይዟቸዋል ምክንያቱም ጉዳዩ ከኀዘን እያለፈ ነውና መሰልቸት ስሜታዊ መገለጫዎችን ከመጠቀም በላይ ነው፤ ማስረዳት አለመቻልና አለመፈለግ፣ ዋጋ የለውም ብሎ ጨርሶ መኖር፣ ግን ይህ ሁሉ ለምን ሆነ? የሚል ጥያቄ ነው፤ ሰይጣን እንድንሰለችና ከመስመር እንድንወጣ ተደጋጋሚ ፈተናዎችን ያመጣብናል፡፡
◈ የፉክክር ኑሮ ውስጥ መግባት አደገኛ የመሰልቸት መምጫ ነው፤ በቀላሉ የምናደርገውን ነገር ሰዎች እንዲያደርጉት መጠበቅ ከመሰልቸት ያደርሳል ሁሉንም እንደ አመጣጡ መመለስ አለመቻል፣ የውጊያ ሽሽት ወደ መሰልቸት ያደርሳል “ውኃ ቢወቅጡት እንቦጭ” ሲሆን መሰልቸት ይወለዳል፤ ሰዎችን ለማስደሰት መሞከር መሰልቸት ያመጣል፤ ሰዎች የሚከፉት እናስደስታችሁ ባልን ቁጥር ነው፤ ለእግዚአብሔር ደስታ ስንኖር እርሱን የሚያውቁ ይደሰቱብናል፡፡ የማይበስሉ ነገር ግን ማገዶ የሚፈጁ ሰዎች መሰልቸት ያመጣሉ ያልተማሩ የተማረውን መንቀፋቸው ብቻ ሳይሆን የተማረው ባልተማሩት ተስፋ መቁረጡ የአገራችን ትልቅ ችግር ነው፤ አዎ መሰልቸትን የምንከላከለው በአንድ መንገድ ብቻ ነው፤ እግዚአብሔር በማየት፡፡
◈ ከሁሉም ነገር መጠበቅ ያለብን የልኩን ነው፤ ከአበባ ጊዜያዊ ውበትን፣ ከእንስሳ ጊዜያዊ ወዳጅነትን ከሰዎች መለዋወጥን መጠበቅ አለብን የልኩን ያህል የኖረ ሰው ዛሬ እኛን ለማስደሰት ከልኩ በላይ አይሆንም የሚመጥነንን ባንሰማም የሚመጥናቸውን እንደ ተናገሩ፣ የሚመጥነንን ባንቀበልም የሚመጥናቸውን ያህል እንደ ወረወሩ መገንዘብ አለብን እግዚአብሔር ግን የልኩን ያህል ይገለጣል፤ ለሰማያዊ ሕይወት ብቻ ሳይሆን ለምድራዊ ኑሮም እግዚአብሔርን ማየት ያስፈልገናል፡፡
◈ መሰልቸት የሚወዱትን ያስጠላል እየመጣ ያለውን ደስታም ይገፋል፤ የጸሎት መልሱንም አይፈልግም፤ በልጅ ሕመም፣ በኑሮ ችግር፣ በትዳር ውጣ ውረድ፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት ውስጥ ሆናችሁ መሰልቸት የገጠማችሁ፣ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ መስቀልን፣ ለእርሱ የማይገባውን መከራ የተሸከመውን ጌታ አስቡ፤ አካባቢያችሁን ስታዩና ስታዳምጡ ትሰለቻላችሁ፡፡ የጠራችሁን ጌታ ስታዩ እንደ ጴጥሮስ ውኃውን እንደ ዓለት ትረግጣላችሁ፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
የጴንጤዎች ጉድ! ሰይጣን የሚመለክበት ቃል || ሰይጣንን አመልካለሁ! || ገድላትና መጽሐፍ ቅዱስ || ከሚያጭበረብሩ አጋንንት ተጠበቁ #ethiopia 😭💥🔥 https://youtu.be/a7W-LD4eqUQ
"ወደ መሬት ወድቀን ስንሰግድ ሀጢአት እንዴት ወደታች ጎትታ እንደጣለችን እናስታውሳለን። ዳግመኛም ከወደቅንበት ስንነሳ የእግዚአብሔር ጸጋና ምህረት እንዴት ከመሬት እንዳነሳንና የሰማዩን ርስት እንደሰጠን እንመሰክራለን።" (ቅዱስ ባስሊዮስ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
«ክርስትናን በተግባር የኖሩ ድንቅ አባት!»
◈ ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ “ዓይንህ ብታሰናክልህ ከአንተ አውጥተህ ጣላት ሁለት ዓይን እያለህ ሲዖል ከምትገባ ይልቅ አንድ ዓይና ሆነህ መንግሥተ ሠማያት ብትገባ ይቀልሃል” ብሎ የተናገረውን አምላከዊ ቃል የተገበረ ቅዱስ ሰው ነው።
◈ በአንድ ወቅት ልታሰናክለው የመጣችን ሴት ዓይቶ በየዋህነት አንድ ዓይናውን በወስፌ በማውጣት የጌታን ቃል ተግብሯል፡፡ ይህ ቅዱስ አባት በነበረበት ዘመን የነበሩ አይሁዳውያን ክርስቲያኖችን ይፈታተኑ የነበረበት ዘመን ስለነበር አዲስ ኪዳንን እየመረመሩ በክርስትና ሃይማኖት ላይ ይሳለቁ ነበር፡፡
◈ በዚህም “እምነት ቢኖራችሁ ይህንን ተራራ ከዚህ ተነቅለህ ወዲያ ተተከል ብትሉት ይታዘዝላችኋል” የሚለውን ቃል በመያዝ እስኪ እነዚህ ክርስቲያኖች ይህን ቃል በተግባር ያሳዩን እንደሆን እኛም ቤተ አይሁድን ለቀን ወደ ክርስትናው እንመለሳለን ካልሆነ ግን የክርስትና ሃይማኖት እራሱ በሐሰት ላይ የተመሠረተ ነው በማለት አልሙዔዝ በተሰኘው ግብጻዊ ገዢ ፊት ጳጳሳቱን ጠየቋቸው፡፡
◈ ጳጳሳቱም አርጅተው የነበሩ ገዳማትን እናድስ ዘንድ ፍቀድልን ብለው አልሙዔዝን ጠይቀውት ስለነበር እንግዲያውስ ይህን የአይሁዳውያኑን ጥያቄ መልሱና ገዳማቶቻችሁን ታድሳላችሁ እምነታችሁንም በምድረ ግብፅ ማስፋፋት ትችላላችሁ ይህን ማድረግ ባትችሉ ግን እምነታችሁም ከንቱ ነው እነዚህ አይሁዳውያን በእናንተ ላይ ይሰለጥናሉ አላቸው።
◈ ጳጳሳቱም በፍጽም እምነት መላ ምእመኑን ለሦስት ቀናት ሱባዔ በማወጅ በጸሎት ተጉ፡፡ በሦስተኛውም ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለፓትርያርኩ ተገልጣ ቅዱስ ስምዖን የተባለ ጻድቅ ሰው እንዳለና እርሱን ይዘው አምካታም ወደ ሚባለው ተራራ እንዲሄዱ አዘዘቻቸው፡፡ ቅዱስ ስምዖንም በቦታው በመገኘት የአምካታም ተራራን በማንቀሳቀስ ወደ ምስራቅ ግብፅ ተነሥቶ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡
በዚህ ተዓምርም ክርስትና ድንቅ ሃይማኖት መሆኗ ተመሰከረ፣ ፈሪሳውያኑም አፈሩ፡፡
◈ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንም በቅዱስ ስምዖን ጫማ ሰፊው አማካኝነት የአምካታም ተራራ በተዓምር የተንቀሳቀሰበትን ቀን በማሰብ ቅዱሱን ሲታከብረው ትኖራለች።
የጻድቁ አባታችን በረከት ይደርብን፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ያሰብኩት ይጠፋል፥ የሰራሁት አይባረክም፥ ያቀድኩት አይሳካም || የሰው ልጅ እንዴት ዳነ? || ክርስቶስ ለምን ሰው ሆነ? #ethiopia #eotc 🚩💥🔥😭 https://youtu.be/mEwNGVDiePQ
«ስለ መድኃኔዓለም መታሰቢያ»
◈ በአንድ ወቅት በገነት ያሉ ቅዱሳን፤ ቅዱስ መብዓ ጽዮን በሰማያት የተሰጠውን ክብር ተመለከቱና መድኃኔ ዓለምን "ለመብዓ ጽዮን ጻድቅ የሰጠኽው ይህ ሁሉ ክብር እና ሥጦታ ከምን የተነሣ ነው?" ብለው ጠየቁት። ክብር ይግባውና መድኃኔ ዓለም እንዲህ ሲል መለሰላቸው "እርሱ ግን ብዙ ወደደኝ የሞቴንም መታሰቢያም አደረገ፤ ለደቀ መዛሙርቴ የሞቴን መታሰቢያ አድርጉ ብዬ እንደነገርኳቸው" አላቸው። (ገድለ መብዓ ጽዮን ዘእሑድ)
◈ አምላካችን በወንጌል ያስተማረውን፤ ቅዱሳን በሕይወት ኖረው የሰበኩትን ክርስቲያናዊ ሕይወት እየኖረ (በንስሓ እና በመልካም መንፈሳዊ ምግባራት እየተመላለሰ)፤ የመድኃኔ ዓለምን መታሰቢያ የሚያደርግ ክርስቲያን ይህ ቃልኪዳን ተገብቶለታል። የሚያከብረውና መታሰቢያውን የሚያደርግ ግን መድኃኒታችንን የተቀበሉት የዮሴፍ እና ኒቆዲሞስ ጓደኛቸው ይሆናል። => ወዘሰ ያከብር እንዘ ይገብር ተዝካሮ፤ ሱታፌሆሙ ለኒቆዲሞስ ወዮሴፍ እለ ተወክፍዎ ለመድኃኒነ። የመድኃኔ ዓለምን መታሰቢያ ያደረገ ግን በመንግሥተ ሰማያት ባለሟልነትን ያገኛል፤ በየወሩም አምስት ሺህ ነፍሳትን ከደይን ያወጣል፤ በየሳምንቱ ዓርብ ዓርብም ስለ ስቅለቱ ሦስት መቶ አርባ ነፍሳት ይሰጠዋል፤ የዕንቊ የወርቅ አክሊል የብርሃን ልብስ ይሠጠዋል።
◈ "ዘገብረሰ ተዝካረ መድኅን ይረክብ ሞገሰ በመንግሥተ ሰማያት፤ ወአሥራተሂ ለለወርኁ ፶፻ ነፍሳተ ያወጽእ እምደይን ወበዕለተ ዓርብሂ ፫፻ወ፵ ይትወሀቦ በእንተ ስቅለቱ አክሊለ ዕንቊ ወወርቅ ወልብሰ ብርሃን ያሠረግዎ። (ገድለ መብዓ ጽዮን ዘሰኑይ) => የመድኃኔ ዓለምን መታሰቢያ አድርጉ መታሰቢያውን የሚያደርግ ክብሩ ብዙ ነውና።" (ተአምረ መድኃኔ ዓለም)
◈ "ለኅጡአ ምግባር ገብርከ ዘርቱዕ ሃይማኖቱ፤ ምስለ ቅዱሳን ይኩን ማኅደረ ቤቱ፤ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ አድኅነኒ እሞተ ከንቱ ፤ ኲሉ ከንቱ ከንቱ ንብረቱ፤ እስመ ኲሉ ኃላፊ ውእቱ። => መልካም ምግባር ለሌለው ሃይማኖቱ ግን ለቀናው ባሪያህ፤ ማደሪያውን መኖሪያውን ከቅዱሳን ጋር አድርግ፤ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ ከከንቱ ሞት አድነኝ፤ ዓለምም በዓለም ውስጥ ያለውም ከንቱ ነው፤ ሁሉም ኃላፊ ነውና።" (መልክዓ መድኃኔ ዓለም)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
በሰው እጅ የወደቀ ትውልድ | በልጆች የምትቸገሩ አድምጡ | ባልጸለይን ሰዓት የተወለዱ ልጆች | ስለ አጋንንት ብቻ ማውራት | ዘፈንን መላቀቅ ላቃታችሁ 🔥💥🚩😭 https://youtu.be/-1qbidmxmB8
«የምክር ስንቅ»
◈ "አንድ ወጣኒ መናኝ አንድን ታላቅ አባት ጥሩ ሰው የሚባለው ምን የሚያደርግ ነው ብሎ ጠየቃቸው፤ ይህ ትልቅ አባትም መልሰው ዘወትር ለኃጢያቱ የሚጨነቅና ይቅርታ የሚጠይቅ ዘወትር በሥራና በትጋት የተጠመደ ከመናገር ዝምታን ገንዘብ የሚያደርግ ትእዛዛቱን የሚጠብቅ እራሱን ዝቅ የሚያደርግ ነው በማለት መለሱለት።"
◈ "አንድ አባት ዓለምን ትቶ ወደገዳም ገብቶ ያለውን ሸጦ ለነደያን ስጥ ግን ጥቂት ገንዘብ ለችግር ይሆነኛል ብሎ ወደ ገዳም ይዞት ገባ ከዚያም ለአንዱ ታላቅ አባት ያደረገውን ሁሉ ነገራቸው ይህ አባትም አሁን አንድ ነገር አዝሃለሁ ወደ መንደር ሂድና ሥጋ ከሚሸጥበት ቦታ ሥጋ ገዝተህ ልብስህን አውልቀህ እርቃንህን ሁነህ በገዛሃው ሥጋ እርቃንህን ሁነህ ወደዚህና ብለው መከሩት እንደተባለው አድርጎ ሲመለስ ያን የያዘውን ሥጋ በማየት ውሾችና ቁራወች በዙሪያው ከበው ሥጋውን ስለፈለጉ ሰውነቱን አቆሳሰሉት ተመልሶ አባቴ እንዳሉኝ እድርጌ ስመለስ ውሻዎች እና ቁራዎች ሰውነቴን እንደዚህ አድርገው አቆሳሰሉኝ አላቸው ይህ አባትም ዓለምን የተወ ግን ትንሽ ገንዘብ ለሌላ ቀን ያስቀመጡትንም መናንያን አንተ ሥጋ ይዘህ ባዩህ ጊዜ ውሾች እና ቁራወች እንደከበቡህ አጋንንት ይከቡታል ስለዙህ ጥሪትህን ፈጽመህ ሳታስቀር ስጥ አሉት እሱም ምክራቸውን በምሳሌ ስላስራማሩት ተቀብሎ ህይወቱ ቀጠለ።"
◈ "ቅዱስ አባ ጳውሊ በአቢይ ጾም ሰሌን እየታታ የሚታታው ሰሌን ቢያልቅበት የታታውን መልሶ ተርትሮ እንደገና መስራት የጀመረው ሥራ ከመፍታት የተነሳ ጥፋት ሊመጣ እንደሚችል የሚያስተምር ነው።" በረከታቸው ይደርብን!
◈ "ዓሳ ከውሃ ወጥቶ ከቆየ ወዲያው እንደሚሞት ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ህይወቱ ከወጣ እንደዚሁ ይሞታል ዓሳም ተመልሶ ወደ ውሃው ሲገባ እንደሚድን ሰውም በንስሐ ሲመለስ እግዚአብሔር የይቅርታውን በር ይከፍትለታል ስለዚህ ንስሐን እንደቀላል ነገር አትቁጠረው።"
◈ "በቤተክርስቲያን አንዱ ጋር ሳታስበው ጭቅጭቅ ቢገጥምህ ስለ ቤተክርስቲያን አልሰማም አትበል እራስህን ትጎዳለህ ዶሮን ተመልከት እንቁላሏን ከማሞቅ ብታቋርጥ እንቁላሉ ይበላሻል አንተም አንደ እንቁላሉ እንዳትበላሽ ተመለስ።"
◈ "ክፋን የሚሰራ ምህረትንና ይቅርታን አያውቅምና ከክፋ ተጠበቁ በተቻለህ መጠን ባልሰራሀው ሥራ ስትከሰስ አዎ ሰርቻለሁ ግን ይቅርታ ለማለት ሞክር አንድ አባት በገዳም ሲኖሩ በገዳም አብረዋቸው የሚኖሩ ግዴለሽ መነኩሴ ሁልጊዜ ባልሰሩት ሲከሷቸው ይቅርታ ሲጠይቁ መጨረሻ ግን ሙት እስከማስነሳት በቁ ይህም ለአበምኔቱ ተገለጸላቸው አንተም ከዚህ አባት ተማር ዋጋ የሚገኘው ባልሰራህው ስትታማ ነው እንጂ በሰራህውማ ያው ስራህ ነው የሚነገርህ ያው የምታውቀው ማለቴ ነው።"
◈ "እውነተኛ ምስክር ነፍስን ከክፉ ያድናልና የሀሰት አቀጣጣይ አትሁን የእግዚአብሔር ትእዛዝ የህይወት ምንጭ ነውና ትእዛዛቱን ጠብቅ ቀናተኛ ሰው የአጥንት ነቀዝ ነውና ከቀናተኛ ጋር አትዋል። ድሃን የሚንቅ ፈጣሪውን ያሰቆጣል የሚያከብረው ግን ምህረት ያገኛልና ድሃን አትናቅ። አመጽና የክፉዎች መስዋዕት በእግዚአብሔር ዘነድ የረከሰ ነውና በክፉ ሥራ አትጓዝ።"
◈ "እግዚአብሔርን ባለመፍራት ከሚገኝ ብዙ ባለጸግነት እግዚአብሔርን በመፍራት የሚገኝ ጥቂት ሀብት ይሻላልና በፈሪሃ እግዚአብሔር ተመላለስ። ከተሰወረ ፍቅር የተገለጠ ዘለፋ ከጠላት መልካም ሃሳብ የወዳጅ ክፉ ምክር ከራቀ ወንድም የቀረበ ወዳጅ ሳይሻል እንደማይቀር አትዘንጋ። መልካም ሞት የመልካም ኑሮ ውጤት ነው፤ እንደ በረሃ ሸበቆ ነፋስ በነፈሰበት ሁሉ አትወዛወዝ። በድምጽ ብልጫ የወደዱህ መልሰው በድምጽ ብልጫ እንደሚጠሉህ እወቅ።"
◈ "ላያልፍ የመጣ ክፉ ነገር የለምና እስኪያልፍ ታገስ። ከጠላት ብቻ ሳይሆን ከወዳጅህም ተጠንቀቅ በወዳጅህ ተወግተህ አትድንምና። በሰዎች ስትገፋ ለምን አትበል ቅቤም ተገፍቶ ነው ከሰው ራስ ላይ የምትወጣው።"
◈ "አንደበተ ትልቅ ውስጥ ቀላል እንዳትሆን ተጠንቀቅ። በእግዚአብሔር እንጅ በደጋፊዎች አትተማን በደጋፊዎች ከተማመንክ ከሰባራ ወንበር ላይ እንደተቀመጥ ቁጠረው። የሰይጣን ደህና ባይኖረውም ብቻውን ካለ ሰይጣን ይልቅ በሰው ላይ ካለ ሰይጣን ተጠንቀቅ። ሰዎች በአንተ ላይ ምንም እንዳያወሩ ስልጣን የለህምና የሚሉህን እየሰማህ ስህተትህን አስተካክል።"
የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
"መምህር ከሆንክ ጸልይ፤ ከጸለይክ ደግሞ መምህር ነህ ማለት ነው።" (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ) => ጸሎት ሸክም የሌለው መሳሪያ ነው (ብጹዕ አቡነ እንዲሪያስ) 🙏🙏🙏
"ያለ ጸሎት ከሚያገለግል ሰው ይልቅ፤ ያለ አገልግሎት የምጸልይ ሰው ይሻላል።" ጸሎት ማቋረጥ የውድቀት መጀምሪያ ነው! (ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ)
የመናፍቅ መንፈስ ልዩ ባህሪያቶች || መምህር ግርማን ለምን ይቃወማሉ? || ሰይጣንና የንስሐ መንገድ || መምህር ተስፋዬ አበራ | ግርማ ወንድሙ #eotc 🚩🔥 https://youtu.be/4A7hVtyLD3Q
የመምህር ግርማ ትምህርት ለምን ልዩ ሆነ? ለአጋንንት የሚመች ኑሮ || የመምህር ተስፋዬ ልጆች ይናገራሉ! የዲያብሎስን ውጊያ አልተማርንም #ethiopia 🚩😭💥 https://youtu.be/llH8QIOdfgo
በእውቀቱ ምን ነካው! አባቶችን መንቀፍ እስከመቼ ደብተራዎችን መቃወም ለምን አቃተን? | ለከሳሾች የቀረበ ጥሪ ቀሲስ ሄኖክ መምህር ተስፋዬ አበራ 🔥🚩
https://youtu.be/mrq8io1GTVE
የታመሙ ልጆች ያሏችሁ ወላጆች አድምጡ! | የቀሲስ ሄኖክ መልዕክት | ይቅር የማይል ሰው ሃይማኖት የለውም | መምህር ተስፋዬ አበራ አባ ገብረኪዳን ግርማ 😭💥🚩
https://youtu.be/orOCSD1n0o4
🚩እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 21 በደብረ ምጥማቅ እንደተገለጸለች ከእመቤታችን ከ33 በዓላት አንዱ ነው። በግብጽ ካይሮ በምትገኘው ዘይቱን ማርያም በመባል በምትታወቀው በእመቤታችን ስም በታነጸች ቤተ ክርስቲያን ላይ ከግንቦት 21-25
+ የብርሃን እናቱ የባህርያችን መመኪያ
+ የመላእክት እህት
+ የነቢያት ትንቢት
+ የሐዋርያት ስብከት
+ የጻድቃን እመቤት
+ የሰማዕታት አክሊል
ንጽሕት ጽንዕት ክብርት ቅድስት ድንግል ማርያም በግልጥ ተገልጣ ክርስቲያኖችም አረማውያን ይመለከቷት ነበር፤ በቦታውም ድንኳን ተክለው ለ 5 ቀናት በዚያው ቆይተዋል።
ይህም የመገለጧ መታሰቢያ በዓል በግንቦት 21 በድምቀት ይከበራል።
አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ስለመገለጧ እንዲህ አሉ። አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ሐምሰ ዕለታተ፤ ትዕምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ፤ ሚመጠነ ማርያም ታስተፌሥሒ ትፍስሕተ፤ ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ፤ ብፁዕ ዘርዕየኪ በሕልሙ ሌሊተ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ጸልዩ ስገዱ ቁረቡ የምሉ ጠንቋዮች የድብርትና የጭንቀት መንፈሶች ማሠር እንጂ የማይፈቱ አገልጋዮች || የከመርናቸው የኃጢአት ሸክሞች #eotc 🚩💥😭🔥
https://youtu.be/giMrUq6z2Zo?si=bzrgpN9ZMx_LF_kh
የካህኑ የጠቋር አጋንንት ፈተና አገልጋይ ነኝ ዲያብሎስ አይነካኝም የውርስ የዛር መንፈሶች ጥቅት መንበርከኪያ ጊዜ ጸሎታችን አምጣ ብቻ 💥🔥😭
https://youtu.be/eR0NgFy9klM?si=1O7A5goUNH4YzSST
