fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 267
مشترکین
+124 ساعت
+57 روز
+2230 روز
آرشیو پست ها
ጉድ! በመገናኛ በድብቅ ሰው የሚገበርበት ትልቁ ሕንጻና አስከፊ ምስጥሮቹ!! መተት አይነካኝም እያልኩ ስኩራራ ይኼው ጉድ ሆንኩኝ!! መቁጠሪያ ያጋለጠው ምስጥር! https://youtu.be/Ymdod1QaM_o

ማንያዘዋል እሸቱ የመተት ጉዳይ ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ እያለን ነው ወገን!! ጡቷን በመተት ከተፈጥሮና ከተለመደው ውጭ አደረጉት እጅግ ያሳዝናል!! https://youtu.be/llgw5Ge81rw

እግዚአብሔር ከፍ ሊያደርጋችሁ ሲል የሚታዩ 5 አስገራሚ ህልሞችና ትርጉማቸው!! ይኼንን ነገር በህልም ካያችሁ እባካችሁ ተጠንቀቁ!! #ህልም #ሕልሞች #ጸሎት https://youtu.be/a95iFM7fMlQ

ወለተ ሰንበትና ገብረ ኪዳን ለቅዱስ ሩፋኤል 1100 ብር አስገብተዋል! እግዚአብሔር ይስጥልኝ። በወጣ ይተካ በርቱልኝ ቤተሰቦቼ። ሌሎቻችሁም ከላይ በተጠቀሰው አካውንት ማስገባታችሁን እንዳትረሱ። የቅዱ
ወለተ ሰንበትና ገብረ ኪዳን ለቅዱስ ሩፋኤል 1100 ብር አስገብተዋል! እግዚአብሔር ይስጥልኝ። በወጣ ይተካ በርቱልኝ ቤተሰቦቼ። ሌሎቻችሁም ከላይ በተጠቀሰው አካውንት ማስገባታችሁን እንዳትረሱ። የቅዱስ ሩፋኤል ረድኤት በረከቱ በሁላችን ላይ ይሁን።

"ዳግም ትንሣኤ" ስላልን ክርስቶስ ዳግም ተነሣ አያሰኝም። ለሁለተኛ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ መገለጡን መናገር ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤ ዕለት ሐዋርያት ባሉበት በዝግ ቤት ገብቶ በመካከላቸው ተገኝቶ <<ሰላም ለሁላችሁ ይሁን>> በማለት ትንሣኤውን ገልጾላቸዋል። <<አስታረቅኋችሁ>> ሲል ነው። ቅዱሳን ሐዋርያት የትንሣኤውን የምሥራች ለቅዱስ ቶማስ ሲነግሩት አላመነም ነበር። "ትንሣኤ ሙታን የለም" ከሚሉ ከሰዱቃውያን ወገን ስለነበር ነው። <<በእርግጥም እናንተ ትንሣኤውን 'ዐየን' ብላችሁ ስትሰብኩ እኔ ግን 'ሰምቻለሁ' ብዬ ልመስክር ላስተምር ነውን?>> ብሎ <<ካላየሁ አላምንም"µ>> አለ። ይልቊንም <<የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ዳስሼ ካላየሁ፥ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ላይ ካላገባሁ እጄንም በጐኑ ካላገባሁ፤>> አላምንም አላቸው። ከስምንት ቀን በኋላ (በሳምንቱ) ደቀ መዛሙርቱ በድጋሜ በዝግ ቤት ውስጥ ነበሩ። ቶማስም ከእነርሱ ጋር ነበር። (ዮሐ ፳፥፳፮) ደጁ ተዘግቶ ሳለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መጣ። ማንም ሳይከፍትለት ገብቶ በመካከላቸውም ቆመና <<ሰላም ለእናንተ ይሁን>> አላቸው። ጌታችንም ሐዋርያ ቶማስን <<ጣትህን በጎንህ አስገባው ያመንህ እንጂ ተጠራጣሪ አትሁን>> ብሎም ገሠፀው። ቶማስም እጆቹን ከሰደደ በኋላ <<እግዚእየ ወአምላኪየ - ጌታዬና አምላኬ>> ብሎ መለሰ። መለኮት ነውና ቢዳስሰው እጁ ከእሳት እንደገባ ጅማት እርር ኩምትር አለ። መዳሰሱን ሲያይ <<እግዚእየ>> ማቃጠሉን ሲያይ <<አምላኪየ>> አለ። ይህንንም ሊቁ <<አንተ ዘቀዳሚ ወአንተ ዘይእዜ>> ብሎ ተርጐሞታል። የሚገርመው ነገር መለኮትን የዳሰሰች የቅዱስ ቶማስ እጅ በሕያውነት ትኖራለች። በሕንድ ሀገር ከመንበር ላይ ከታቦቱ ጋር የሚያኖሯት ሲሆን በዓመት አንድ ቀን (የአስተርእዮ ማርያም) እየወጣች የሚሾመውን አገልጋይ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች። አንድ ዓመት አገልግሎ ያርፋል። በዓመቱ ወጥታ ከሚተካው አገልጋይ እጅ ላይ ታርፍና ተተኪውን ተሿሚ ታመላክታለች። እንዲህ እያለች ግብረ መንፈስ ቅዱስን እየገለጠች ትኖራለች። ከበዓሉ ረድኤት ይክፈለን።

✈️ ወደ አሜሪካ ጉዟችንን ጀምረናል 🇺🇸 በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት እና በአካባቢው የሚገኙ ማህበረ ምዕመናን ባደረጉት መንፈሳዊ አገልግሎት ጥሪ መሠረት፣ ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 13 (April 19th – April 21st) ከጠዋቱ 10:00 እስከ 5:30 ድረስ መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ጉዟችንን በእግዚአብሔር ጸጋ ጀምረናል። እግዚአብሔር በዚህ ጉዞ ብዙዎችን ይባርክ፣ ከመናፍስት እስራት ያውጣ፣ ይፈውስ፣ ይመልስ። አሜን!

=> የእህታችን ጥያቄ (አስራለሁ በመቁጠሪያ እቀጠቅጣለሁ በንስሀ እመላለሳለሁ ግን ሂወቴ በጭንቅ ውስጥ ነው። ቤተሰቤ አልቀዋል ብቻየን እየተንገዳገድኩ ነው። 4 አመቴን ይዣለሁ ወደናንተ ት/ት ከገባሁ እየሆነ ያለው ለዕይምሮ ይከብዳል ይህኛውን በጭንቅ አለፈ ተመስገን ስል ከዛ የሚበልጥ ይተካል በቃ አሁን ለመድኩት መሰል ከቅዱስ ሰጋው እና ደሙ ካላራቀኝ ዝም ብየማየት ጀመርኩ። ምን ላድርግ ወንድሜ ምከረኝ።) => እህታችን ሰላመ እግዚአብሔር ይድረስሽ። የምታልፊበት የፈተና እሳት እጅግ ከባድ እንደሆነ ቢሰማኝም፣ በቃላትሽ ውስጥ ግን ከአልማዝ የጠነከረ እምነት አያለሁና። በተለይም "ከሥጋ ወደሙ ካላራቀኝ ዝም ብዬ ማየት ጀመርኩ" ያልሽው ቃል በሰማያውያን መላእክት ዘንድ ትልቅ ክብር ያለው የጽናት ምስክርነት ነው። => ፈተናሽ የጥንካሬሽ እንጂ የኃጢአትሽ መለኪያ አይደለም፡ በቤተክርስቲያን ትምህርት፣ ሰይጣን ብርቱ ጾም፣ ጸሎትና ንስሐ ያለበትን ሰው በከፋ መንገድ ይፈታተነዋል። ቅዱስ እንጦንስ እንደሚለው "ፈተና ባይኖር ማንም አይድንም ነበር"። ቤተሰብሽን ማጣትሽና ብቻሽን መሆንሽ ጌታችን በመስቀል ላይ የነበረውን ብቸኝነት ያስታውሰናል። ስለዚህ "እግዚአብሔር ጥሎኛል" ብለሽ በፍጹም እንዳታስቢ፤ ይልቁንም በፈተናው እሳት ውስጥ አብሮሽ አለ። => ከውጊያ ወደ መታመን ተሻገሪ፡ አንዳንዴ በጭንቅ ውስጥ ሆነን በመቁጠሪያ ስንቀጠቀጥና ስናስር፣ ውጊያችንን በራሳችን ጉልበት ለማሸነፍ እየሞከርን ሊሆን ይችላል። ይህም ድካምንና ጭንቅን ይጨምራል። አሁን "ዝም ብዬ ማየት ጀመርኩ" ያልሽው ትክክለኛው የመንፈሳዊነት ደረጃ ነው። እንደ ኢዮብ "እግዚአብሔር ሰጠ፣ እግዚአብሔር ነሣ፣ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን" ብሎ ራስን ለእግዚአብሔር ፈቃድ አሳልፎ መስጠት ሰይጣንን የሚያሸንፍ ትልቅ መሣሪያ ነው። => ቅዱስ ቁርባን የሕይወትሽ መልሕቅ ነው፡ ከምንም በላይ የያዝሽውን የቁርባን ሕይወት አጥብቀሽ ያዢ። ሥጋ ወደሙን የምትቀበዪው ለደስታ ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ አንቺ ላለ በጭንቅና በሐዘን ለደከመ ነፍስ መድኃኒት እንዲሆን ነው። በቁርባን ውስጥ ክርስቶስ በአንቺ ውስጥ ስላለ፣ የሚመጣው ፈተና ሁሉ የሚጋጠመው ከአንቺ ጋር ሳይሆን በአንቺ ውስጥ ካለው ከክርስቶስ ጋር ነው። => የደረሰብሽን የቤተሰብ መጥፋትና የሥነ-ልቦና ጫና ለንስሐ አባትሽ በዝርዝር አስረጅ። አንዳንዴ በጭንቅ ሰዓት የጸሎት ሕጋችንን (ለምሳሌ የመቁጠሪያ ብዛቱን) አባቶች ቀለል እንዲያደርጉልን ማድረግ ይገባል፤ ትኩረትሽ በብዛት ላይ ሳይሆን በውስጣዊ ሰላም ላይ እንዲሆን። አርማም (ዝምታ) በቀን ውስጥ ጥቂት ደቂቃዎችን "ጌታ ሆይ! አንተ እንደወደድክ አድርግ" በማለት በዝምታ እግዚአብሔርን የመጠበቅ ልምምድ አድርጊ። እህቴ ሆይ! አራት ዓመት ሙሉ በጽናት መቆምሽ ራሱ ትልቅ ተአምር ነው። ከዚህ በኋላ የሚመጣው ፈተና ቢበልጥም፣ በአንቺ ውስጥ ያለው ጸጋ ደግሞ ከዚያ በላይ ይበልጣል። የደረሰብሽን መራራ ሐዘን እግዚአብሔር በሰማያዊ መጽናናት ይተካሽ። ከሥጋ ወደሙ አትራቂ፤ እርሱ የመጨረሻው ድልሽ ነው። ድል ለምትታገስ ነፍስ ናትና በርቺ!

ቅዱስ ሩፋኤል ይስጥልን በወጣ ይተካ!! ለቅዱስ ሩፋኤል ቤተሰቦቼ ብዙዎቻችሁ እየተሳተፋችሁ ነው። አሁንም የቻላችሁትን አስገቡ በርቱልኝ።
ቅዱስ ሩፋኤል ይስጥልን በወጣ ይተካ!! ለቅዱስ ሩፋኤል ቤተሰቦቼ ብዙዎቻችሁ እየተሳተፋችሁ ነው። አሁንም የቻላችሁትን አስገቡ በርቱልኝ።

እኛ ለትውልዳችን መንበርከክ ሲያቅተን ማንኛውም የጥፋት መንፈስ ያንበረክከዋል!! ሚስቶች ዛሬ ልመርቃችሁ እንደዚህ አይነት ደጄን የሆነ ባል ይስጣችሁ!! #ጸሎት https://youtu.be/S97b7hIgCIg

=> የእህታችን ጥያቄ "የግድ ቆራቢ ማግባት አለብኝ ወይ?" ሰላም እህታችን በቅዱስ ቁርባን ሕይወት ውስጥ ሆነሽ ትዳርን ማሰብሽ የሚበረታታና የሚቀደስ ሐሳብ ነው። ለጠየቅሽው ጥያቄ አጭርና ቀጥተኛ ምላሾችን እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡ => የግድ ቆራቢ ማግባት አለብኝ ወይ ላልሽው? አዎ፣ በቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ቆራቢ ክርስቲያን የሚመርጠው የሕይወት አጋር ቆራቢ ቢሆን ይመረጣል። ምክንያቱም ጋብቻ "አንድ ሥጋ" የሚኮንበት ምስጢር ስለሆነ፣ ሁለቱም በአንድ መንፈሳዊ ደረጃ (በቁርባን) ቢጓዙ የቤተሰቡ መንፈሳዊ መሠረት ጠንካራ ይሆናል። ሥርዓተ ተክሊል ለመፈጸምም ሁለቱም ተዘጋጅተው መቁረብ ይኖርባቸዋል። ሆኖም፣ አጋርሽ ለመቁረብ ፈቃደኛና ዝግጁ የሆነ አማኝ ከሆነ፣ አብሮ በመዘጋጀት ወደ ቁርባን ሕይወት መግባት ይቻላል። => በአለማዊ ሥራ ውስጥ ሆኖ እንዴት ይገኛል ላልሽው ደግሞ? ሥራሽ ከብዙ ሰዎች ጋር የሚያገናኝሽ መሆኑ አጋር ለማግኘት እንቅፋት ሳይሆን "ዕድል" ሊሆን ይችላል። ነገር ግን መስፈርቶችሽ ግልጽ ሊሆኑ ይገባል፦ በሥራ ቦታሽ ክርስቲያናዊ ማንነትሽን (ጠባይሽን፣ አለባበስሽንና ንግግርሽን) ጠብቂ። ይህም ለአንቺ የሚመጥን "እግዚአብሔርን የሚፈራ" ሰው እንዲቀርብሽ ያደርጋል። ሰውየው የግድ በሥራ ቦታሽ የሚገኝ ላይሆን ይችላል፤ ነገር ግን በሥራ ቦታሽ የምታሳዪው ቅንነትና መልካም ሥነ-ምግባር ለሌሎች መልካም ምስክርነት ይሆንልሻል። => ከሱባኤ ውጭ ምን ዓይነት እንቅስቃሴ ያስፈልጋል? "እምነት ያለ ሥራ የሞተ ነው" እንደሚለው መጽሐፍ፣ ከጸሎት ጎን ለጎን የሚከተሉትን እንቅስቃሴዎች አድርጊ፦ ለንስሐ አባትሽ መንገር ትዳር እንደምትፈልጊ ለንስሐ አባትሽ ንገሪያቸው። አባቶች ብዙ መንፈሳዊ ልጆችን ስለሚያውቁ፣ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ጠንካራ የሆነና ለአንቺ የሚመጥን ሰው ሲኖር ሊጠቁሙሽ ወይም ሊያስተዋውቁሽ ይችላሉ። በመንፈሳዊ ማኅበራት መሳተፍ በሰንበት ትምህርት ቤት ወይም በበጎ አድራጎት ማኅበራት ውስጥ በንቃት መሳተፍ፣ ካንቺ ጋር ተመሳሳይ መንፈሳዊ ዓላማ ያላቸውን ሰዎች ለማግኘት ትልቁ መንገድ ነው። ዝግጁ መሆን አንድ ሰው ሲቀርብሽ "ለመቁረብ ፈቃደኛ ነው ወይ? ሃይማኖቱን ይወዳል ወይ? ሥነ-ምግባሩስ?" የሚሉትን ነጥቦች በውይይት ለማወቅ ጥረት አድርጊ። ባጭሩ፦ ጸሎትሽ እንዳለ ሆኖ፣ በቤተክርስቲያን አካባቢ ባለሽ ተሳትፎና ለንስሐ አባትሽ ባለሽ ግልጽነት እግዚአብሔር መንገዱን ያቀናልሻል። ዋናው ነገር በሐሳብሽ "መቁረብን" ቅድመ ሁኔታ አድርገሽ መነሳትሽ ትክክለኛ መንገድ ነው። እግዚአብሔር እንደ ልብሽ መሻት ቅዱስ ጋብቻን ይፍቀድልሽ!

=> በኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ የጋብቻና ትዳር ጉዳዮች (ነገረ ጋብቻ) ላይ ጥያቄ ካላችሁ ውድ ቤተሰቦቼ መጠየቅ መወያየት እንችላለን። ነጻ ሆናችሁ #ያገባችሁም #ያላገባችሁም አሁን በዝግጅት ላይ ያላችሁ ሁላችሁም መሳተፍና መጠየቅና ማወቅ ያለባችሁን ነገር በግልጽ በውስጥ መስመር ጻፉልኝ። ጠይቁ እንቀያይ። https://t.me/haile_gebriel_tube_bot

"ኢየሱስ ጌታ ነው!" ማለት ፉከራ እና መመጻደቂያ ወይም መበሻሸቂያ አይደለም። አስተውሉ! "ጌታ እና አምላክ እኛ ነን" በሚሉ ነገስታት ፊት በድፍረት ተነግሮ የሚያስገድል ብዙ ክርስትያኖችም ሰማዕት
"ኢየሱስ ጌታ ነው!" ማለት ፉከራ እና መመጻደቂያ ወይም መበሻሸቂያ አይደለም። አስተውሉ! "ጌታ እና አምላክ እኛ ነን" በሚሉ ነገስታት ፊት በድፍረት ተነግሮ የሚያስገድል ብዙ ክርስትያኖችም ሰማዕት የሆኑበት ትልቅ ምስክርነት ነው! ስለዚህ አታርክሱት ከሚያረክሱትም ሰዎች ራቁ።

የመናፍስትን ሴራ ከልጅነቴ ጀምሮ ባለማወቀ ይኼንን ሁሉ መከራና ፈተና አስተናግጃለሁ!! የእህታችን አስገራሚ ምስክርነት ስለ መምህር ግርማ አገልግሎት!! #ጸሎት https://youtu.be/Ran3YA_pmMo

ዘፈን ኀጢአት ነው። የሀገር፣ የባንዲራ፣ የባሕል ዘፈን.... አያስኮንንም የሚል የሞኝ ትምህርት ነው። ሁሉም ዘፈን ስሜት ቀስቃሽ አጋንንትን አንጋሽ ነው። አታሽሞንሙኑት። የቤታችን ሰዎች ከመዝሙሩም ከዘፈኑም ባትሆኑብን ደስ ይለናል። በእርግጥ እንዲህ ብለን ስለተናገርን ብቻ "ጻድቃን" የሚል የምጸት ማዕረግ ይሰጠናል። ብናስተውልስ?!

“ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ስናቆም፤ ጭንቀቶቻችን እኛን ማናገር ይጀምራሉ” (አባ ጴሜን ቭላድ)
“ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ስናቆም፤ ጭንቀቶቻችን እኛን ማናገር ይጀምራሉ” (አባ ጴሜን ቭላድ)

ስለ ክርሰትና ያልተመለሱ ከባባድ ጥያቄዎች! | ከዲያቆን ዘላለም ታዬ ጋር https://youtu.be/GDizojJkYus