fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 280
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+117 روز
+3830 روز
آرشیو پست ها
«ልብ ብለው ያንብቡት!» => ዛሬ የገድለ-ዲያብሎስ የዝና ታሪክ፣ የኃጢአትና የሞት ዜና መረጃ በበዛበት ዓለም ውስጥ እንገኛለን፡፡ ኃጢአት፤ ለዚህ ዘመን ሰው የመጀመሪያው ዕውቀትና የሥነ-ምግባሩ መግለጫ በመሆን፤ ጸሎት ጽድቅንና እውነትን የባርነት መንገድ አድርጎ እንዲያይ፤ የትውልዱ የውድቀት ጉዳይ ፈጻሚ የመሆን ዕጣ ድርሻውን ከዲያብሎስ ተምሯል፡፡ ‹‹በጎ እያደረጋችሁ፣ የማያውቁትን ሞኞች ዝም ታሰኙ ዘንድ እንዲህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና፤ አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ፡፡›› (1ጴጥ 2÷15-16) ክፉ መናፍስት፤ በሕይወታችንና በኑሯችን ውስጥ፤ ሥፍራና ቦታ አግኝተው፤ በውድቀት አዙሪት ውስጥ እንድንኖር ሊያደርጉ የቻሉበት አንዱና ዓብይ ምክንያት፤ ለአምላካችን የቅድስና አምልኮትና ለእግዚአብሔር ጸሎት ባለማድረሳችን ነው፡፡   => ከዲያብሎስ መሠረታዊ ሥልት አንዱ፤ በዓለማዊው መድረኮች ላይ ለመንፈሳዊ ሕይወት ቦታ እንዳይሰጥ፤ በተለይም ጸሎት ወደ እግዚአብሔር እንዳይደርግ ማዘናጋት ነው፡፡ ጸሎት አለማድረግ ደግሞ፤ ከእግዚአብሔር የሚያለያየን ዋንኛ መንገድ ነው፡፡ ዛሬ በዚህ ጎዳና ላይ እኛም እየተጓዝንበት እንገኛለን፡፡ ከአምላክህ ጋር ከተለያየህ ደግሞ፤ የምታዳብረው ጠባይ፤ ክፋትን፣ ተንኮልን፣ ፌዘኝነትና ደንታ ቢስነትን ወዘተ…ነው፡፡   => በዚህ መንገድ ከተጓዝን ደግሞ፤ ጸሎት የለም፡፡ ምናልባት የምንሰማውና የምናየው የአንድና የሁለት ደቂቃ የሕሊና ጸሎት የሚባለውን ነው፡፡ የሚገርመው ግን፤ ይህ የሕሊና ጸሎት ለማን እንደሆነ፣ ምን ተብሎ እንደተጸለየና ማን እንደሰማው አለመታወቁ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነቱ ጸሎት፤ ዘመናዊው ሰው ምንጊዜም አቅጣጫውን ሲለውጥ፣ እምነቱን ሲጥል፣ የማንነት ጉዳዩን ከመናቅም በላይ፤ አዲስ ነገርና የፈጠራ ሃሳብ መሞከሪያ ሲሆን፤ እራሱን እያዘናጋ በሕይወት ተምሳሌቱና ከጊዜው እይታ ጋር ሲወዳደር፤ ለየግል ፍላጎቱ ከሥራ ጋር ሲባዝንና ሲሯሯጥ፤ በመሐል ሃይማኖቱንና እምነቱን በመዘንጋት፤ ለከባድ መቅሰፍት እንዲጋለጥ የሚያደርግ ነው፡፡   => ክርስቲያን ወገኖችም፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን ሁሉ በሚገባ በመከተል፤ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በአምልኮት በመንበርከክ፣ በቅዱስ ቁርባን፣ በንስሐ፣ በጸበል፣ ወዘተ… በመቀደስ፤ የእግዚአብሔር ሰው ለመሆን እስካልቻልን ድረስ፤ የዲያብሎስ  መጫወቻ ሆነን ብንቀር የሚያሳዝንና የሚያሰቆጭ አይሆንም፡፡ ብዙ ሰው ስለ ክፉው መንፈስ ያለው አመለካከትና  ግምት፤  በእኔ ላይ መተት አይሠራም፤ እግዚአብሔርን አምናለሁ፤ እንዳቅሜ ጸሎት አደርሳለሁ፤ እመጸውታለሁ፣ አንዳንዴ እጾማለሁ ሲመቸኝ ቤተክርስቲያን እሄዳለሁ፤ ሰንበቴና የጽዋ ማሕበር እጠጣለሁ፣ የቄስ ዘርና የቅዱሳን ዘር ነኝ፤ አያቴ ዳዊት ደጋሚና ቤተክርስቲያን ተካይ መነኮሴ ገዳማዊ ነበሩ፤ መናኝ ባሕታዊ ዘመድ ነበረኝ እያልን፤ ራሳችንን በትልቅነት ደረጃ ውስጥ አስገብተን እንመካለን፤ ብዙ እናወራለን፤ የሚገርመው ግን፤ ከእግዚአብሔር ልጆች የዲያብሎስ ልጆች የተንኮልና የግፍ አሠራሩ ላይ፤ ከማንም በላይ የሰለጠኑና የጥቃት ሥልታቸው የረቀቀ፤ ሂደቱን በእያንዳንዱ በኋላው ታሪክ በሚመጻደቅ ትውልድ ላይ ሁሉ፤ የመንፈሱ ጥቃት በምስጢራዊ ሁኔታ ተከናውኖ መገኘቱ ነው፡፡   => ሌላው ቀርቶ የዓይነ-ጥላ አብሮን የመወለዱን ጉዳይ እንኳን ገና በግልጽ አልተረዳንም፡፡ ይህም የቱን ያህል ከማለዳ የመያ’ዝ ጉዳይ ጋር የተወሳሰበ እንደሆነ ያስረዳናል:: በመንፈሳዊ የሕይወት ጅማሬ ውስጥ፤ ለዕውቀት ሲባል የሚወሰዱ ዕፅ-ፋርሶችና በሰውነት ውስጥ የሚቀበሩ ከመንፈሱ ጋር በዕፆች አማካኝነት የሚገቡና በሰውነት ውስጥ ተመሳስለውና ተዋህደው የሚኖሩ የመንፈሶች አደጋዎች፤ በስፋት ያጠቁት ወገን ብዙ ነው፡፡   => በዚህ ዓይነት መንፈስ ተጠምደው ቤተ እግዚአብሔርንና ለምዕመናን፤ ከአነጋገር እስከ ተግባር ድረስ  መሰናከል ሆኖ የሚኖረው የአገልጋዮች ችግር፤ ከዚህ የልማድ አምልኮት ጋር የተያያዘ እንደሆነ፤ ብዙ በቤቱ የሚመላለሱ ሰዎችና በርካታ ምዕመናን ገና አልገባቸውም፡፡ ነገር ግን በተግባር የሚታየው ሁሉ የክፉው መንፈስ የውክልና ሥራ በቃል ክፉ በመናገር በልብ በመመቅኘት፣ ተንኮል፣ ቅናትና አስማታዊ አሠራር መግለጫ ነው፡፡ በሰውነት ውስጥ ተዋህዶ በመኖሩ ምክንያት የአገልግሎት ዘመኑን ሁሉ ለዓለማዊ ጥቅም ብቻ እንዲሰለፍ፤ በጥቅሙ የሚመጣበትን ሁሉ በማንኛውም የክፋት መንገድ በመበቀል፤ የመዋጋቱ ጉዳይ፤ ለመንፈሳዊ እምነቱ ከሚሰጠው ቦታ በላይ፤ ተንኮሉ የበለጠ ነው፡፡   => ከእውቀቱ ዘርፍ፤ ክፉ መናፍስት ዕውቀትን ሰጭ አካል አድርጎ ከጀመረ መንፈሳዊ አገልግሎቱ ውስጥ፤ ብዙም መልካም ነገር ባይጠበቅ የሚገርም አይሆንም፡፡ ምክንያቱም፤ ክፉው ዲያብሎስ ሥልቱም ተፈጥሮውም ሃይማኖታዊ ጉዞን የሚያመጣውን ጸጋ፣ ሞገስና የእምነት ኃይሉን ተመሳስሎ ማዳከም ስለሆነ፤ ይሄው ግቡ ዛሬ ብዙ የተሳካለት መሆኑን  በየቤተክርስቲያን ያለው የመለያየት ችግር ማሳያ ነው፡፡   => በመንፈሳዊ ግንዛቤያቸው የተሻሉ ሰዎች ግን፤ ሕብረተሰቡ ውስጥ ያለውን የክፉ መንፈስ ውስብስብ ፈተና የኑሮ፣ የእምነትና የአእምሮ መቃወስ፣ የጤና ማጣት አደጋ ይገነዘባሉ፡፡ የዚያኑ ያህል በተቃራኒው፤ ሳይቀደሱ የሚባርኩ፣ ሳያመልኩ የሚያገለግሉና የሚገለገሉ፣ የያዙትን ወንበር የሚያመልኩ፣ ለሌላው ጥፋትና ክህደት ምሳሌ የሚሆኑ ለአሰተዳደራዊ በደል መፍትሔ የማይሰጡ፣ የተዘበራረቀ አመለካከት ያላቸው፣ በጥቅምና በባለጸጋ የሚታለሉ፣ ሃይማኖታዊ አደራቸውን የዘነጉና ለሕዝብ ደህንነት ራእይ የሌላቸው፣ ችግሩን የማያዩና የማይሰሙ፣ በምትሐተኞች እጅ የተያዙና በቤተ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ኃይል መኖር ያቃታቸው አገልጋዮች ጥቂቶች አይደሉም፡፡       => በአጠቃላይ በእግዚአብሔር ቤት የምንገኝ አገልጋዮች፣ ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች ሁሉ፤ የክፉ መናፈስቱን የውጊያ ሥልቶችና ጥበቦች፣ የመጠጊያ፣ የመግቢያና የማጥቂያ አቅጣጫዎቻቸውን፣ ረቂቅ ጠባያቸውንና ሥሌታቸውን በመገንዘብ፤ ከርኩሳን መናፍስት ተገዢነት ነጻ ወጥተን፤ እውነተኛውን የእግዚአብሔርን የጽድቅ መንገድ መከተል እንችል ዘንድ፤ ኃያሉና ልዑሉ አምላካችን እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን፡፡ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

=> በእግዚአብሔር ጥላ ሥር የሌለ ትውልድ፤ ከመንፈስ ጠላቶቹ ጋር ይኖራል። የስኬት መንገድ በጠላት ተዘግቷል ኑሮው የእርሱ አይደለም። መድሐኒትና የሰው እጅ ላይ ውድቋል። ይሠራል፣ ይለፋል፣ ይማራል፣
=> በእግዚአብሔር ጥላ ሥር የሌለ ትውልድ፤ ከመንፈስ ጠላቶቹ ጋር ይኖራል። የስኬት መንገድ በጠላት ተዘግቷል ኑሮው የእርሱ አይደለም። መድሐኒትና የሰው እጅ ላይ ውድቋል። ይሠራል፣ ይለፋል፣ ይማራል፣ ይደክማል። ነገር ግን ጎተራው፣ ኪሱና እጁ ጭንቅላቱ ባዶ ነው። በረከቱ በመንፈሱ ተወስዷል። በገሃዱ ዓለም በግልፅ የማያያቸው ክፉ መንፈሶች ያሳድዱታል። በአጠቃላይ እነዚህ ከዓይኑ የተሰወረ ጠላቶቹ ይፋለሙታል። እርሱ ግን ጠላቶቹን ለመፋለም አቅም ያንሰዋል። ምክንያቱም፤ ለአምልኮትና ለጸሎት ጊዜ ስለሌለው፤ ሰማይ አልከፈት ብሏል። ስለዚህ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር የለም። እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን፣ ይጠብቀንም! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ» => ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ ይህንን የተናገረው ክቡር ዳዊት በመዝሙር 19፡12 ላይ የምናገኘው ነው፡፡ ‹‹ከተሰወረ ኃጢአት አንጻኝ። የድፍረት ኃጢአት እንዳይገዛኝ ባሪያህን ጠብቅ፤ የዚያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ፥ ከታላቁም ኃጢአት እነጻለሁ።›› በማለት ይናገርና ማብቅያው ‹‹አቤቱ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።›› በሚል ይደመድማል => ብዙ ጊዜ ብዙ የስዉር ህይወት ጎዳና ውስጥ ብዙ ጥፋቶች ይመጣሉ፡፡ ብዙ ነገሮች ይከሰታሉ፡፡ ለብዙ ዘመናት የቆየ የክፉ መናፍስት አሰራር ውርስ ውስጥ እንደገባን እንኳን አሁን አሁን ጥቂት መባነን ጀምረናል፡፡ ብዙዎቹ እንኳን አሁንም ሊባንኑ ያልቻሉ በዚሁ በክፉ አሰራር ስዉር መንገድ ውስጣዊው ህይወታቸው አቅጣጫ የጠፋቸው፣ የህይወት መንገድን ያጡ፣ ሠላማዊ የሆነ በረከት የራቃቸው ብዙ ናቸው፡፡ ያንን እንደ ልማድ ይዘዉት፣ እንደ ጸጋም ቆጥረዉት በተምታታና በረከት አልባ በሆነ ህይወት ራሳቸዉን መርተው ትውልዳቸው ኪሳራ ውስጥ ጥለው የሚያልፉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ስለዚህ ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ ሁላችንም ልንል ይገባናል፡፡ => እና ዛሬ ብዙ ሰው ከበረከትና ከእግዚአብሔር አምላክ ጸጋና ተስፋ በመራቅ በዲያብሎስ በኩል የሚኖረዉን ኑሮ እንደ ጣፋጭ የህይወት አካል አድርጎ ይዞታል፡፡ ከዚሁም ውስጥ አንዱ በግሉ ለመናፈስት መገበር ነው፡፡ በግሉ ለመናፍስት መገበር ማለት በተሰወረ ሐጥያት በኩል መናፍስቶቹን እንደ ሥራ ባህሪ ማሰማራት ነው፡፡ ከነዚህም ውስጥ አንዳንዱ ሰውነትን ለክፉ መናፍስት አሰራር መስጠት ነው፡፡ በዚህ ዘመን፣ በዚህ ግዜ፣ በዚህ በእውቀት፣ በዚህ በቴክኖሎጂ ዘመን ውስጥ ሰዎች የተሰወረ ስዉር የሆነ የሐጥያት አሰራር ውስጥ ይገባሉ፡፡ ከዚህም ውስጥ አንዱ መናፍስቱን የሚፈልጉትን ነገሮች ያሟላሉ፡፡ => ከሚጠይቅዋቸው ነገሮች አንዱ በፈርስ፣ በእንስሳት ደም፣ በሌሎች የደም አይነቶች መታጠብ፡፡ ሰውነትን፣ ገላን እነዚህ እነዚህን የመሳሰሉት ነገሮች በመናፍስት ግብር ውስጥ ሰውነትን ማሳለፍ ማለት ነው፡፡ በፈርስና በደም መታጠብ በዘመናችን በጣም ትልልቆቹ ወይዘራዝርትና ልዩ ሆኑ የሚባሉ ሰዎች ሁሉ ጭምር ለተሰሚነት፣ ለግርማ ሞጎስ አንዳንድ ነገሮችን ፍፃሜ እንዲመጣላቸው ወይም በመናፍስት እንዲጠበቁ አልያም በመናፍስት አሰራር ውስጥ ገበያው እንዲቃጠል፣ የሃብት ኃይሉ እንዲጨምር እነዚህ የመሳሰሉ ነገሮች በዚህ በተሰወረው የሐጥያት ኃይል ውስጥ የሚከናወን ነው፡፡ ለዚህ ነው ክቡር ዳዊት ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ በማለት ይህንን የጸሎት ኃይል ሲገልፅ የምናገኘው፡፡ => ዛሬ በዚህ አይነት የተጠላለፉና በዚህ በመናፍስት ጎዳና ውስጥም ዘግጠው የገቡ እንደ አንዱ ራሱን የቻለ ኑሮ አድርገው የያዙት ብዙዎች ናቸው፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ክብር ቢጠሩ እንኳን የማድመጥም፣ የመስራትም፣ የመለወጥም ፍቃድ የላቸዉም፡፡ ለምን? በተሰወረ ኃጢያት በኩል ልቦናቸው የሚያውቀዉና በአኗኗራቸው ውስጥ የክፉዉን አሰራር በህይወታቸው ዙርያ የለመዱት ነገር ሆኖው ስለሚገኙ፡፡ => ኃጢያት በራሱ ከመናፍስት ውጪ ተሰዉሮ የሚኖር ጉዳትም ጭምር ነው፡፡ አሁን ይህንን በዝርዝር ለመመልከት እስቲ በመጀመርያ ስዉር ሐጥያት ሲባል ምንድነው? የሚለዉን ነገር ላይ ትኩረት ለመስጠት እንሞክር፡፡ የተሰወረ ኃጢያት የሚነሳው ከልብ፣ ሕሊናና ከአዕምሮ ውስጥ ነው፡፡ ከሕሊናና ከአዕምሮ ውስጥ ከመሰወሩ ባሻገር ደግሞ የመናፍስት ግፊቶች ከነዚህ ካሉት ሦስት ቦታዎች ላይ መነሳት ሲጀምር የተጠናከረ የክፉ አሰራር ኃይል ወደ ዉጪ እንዲወጣ ያደርገዋል፡፡ ያ በሐሳብ፣ በዕቅድ፣ በፕሮግራም፣ በአነጋገርና በአፈፃፀም የሚገለጥ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ በማለት ክቡር ዳዊት ይህንን ወደ ሰማይ አምላክ ኃይልና ወደ ሰማይ አምላክ መንፈሳዊ ተስፋ እንዲገባ ራሱን አዘጋጅቶ እናገኘዋለን፡፡ => የተሰወረ ኃጢያት ምንጩ በምኞት ውስጥ የተካተተ ነው፡፡ የሰው ኑሮን መመልከት፣ የሰው ህይወትን ማየት፡፡ የሰው ህይወትን አይቶ ደግሞ በክፉ መከጀል፣ በክፉ ነገር ላይ ማሰብ፣ ተንኮል መፈፀም፣ ግፍ መስራት፣ በምቀኝነት ማየት፣ ኪሳራዉን መመኘት፣ ውድቀቱን መመኘት እና ደግሞ ከዛም በተግባር አልፎ ተርፎ በምትሐት ዓለም መሄድ የተሰወረ ሐጥያት ክፍል ነው፡፡ => ኃጢያት በራሱ ከመናፍስት ተሰዉሮ የቱን ያህል ጊዜ ፣ ዘመን፣ ወቅትን እንደሚጎዳ ለማረጋገጥ አሁን ብዙ አትቸገሩም፡፡ ከቁጥር 1 ጀምሮ እስከ ቁጥር 54 ድረስ ያሉትን። ቪሲዲ ( VCD )የሚታዩትን በሰው ህይወት ውስጥ ያሉትን የጉዳት መንገዶችን መገንዘብ አያስቸግረንም፡፡ ስለዚህ ይሄ የተሰወረ አሰራር ነው፡፡ የመናፍስት አሰራር ነው፡፡ ዓለማችን ይህንን በግልፅም በስዉርም የመሄጃ መንገድና የመኖርያም አካል አድርጎት እየተገነዘብን ነው ያለነው፡፡ ስለዚህ የመጀመርያው ኃጢያት ለክፉ መንፈስ ከመዳረግ በፊት ክፉዉን ሐሳብ በህይወታችን ውስጥ እንደ አንድ ራሱን የቻለ ጊዜ፣ ዘመን፣ ወቅትን ማምለጫ አድርገን ከተጠቀምንበት የተሰወረ ኃጢያት ከውስጣችን ጀምረዋል ማለት ነው፡፡ => ከመንፈሳዊ እስከ ዓለማዊ ድረስ ያለዉ ውድቀት ተጠናክሮ አንዱ ላንዱ የጠላትነት ስሜትን በፍቅር ምትክ ጠብን፣ በሠላም ምትክ ጦርነትን፣ በቦጎነትን ምትክ አረመኔነትን ለሰው ልጅ እየሰጠን ያለን ፍጡሮች ሆነናል፡፡ ስለዚህ‹‹ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ። የድፍረት ኃጢያት እንዳይገዛኝ ባሪያህን ጠብቅ፤ የዚያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ፥ ከታላቁም ኃጢአት እነጻለሁ። አቤቱ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።›› በእውነት እንዲህ እያልን ልንጸልይ ያስፈልጋል፡፡ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

=> "ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ" የሚሉ፥ የውጊያውን ዓለም በግልጽ የሚያስተምሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላትን በመዘንጋት፥ የተዋጊዎቹን ስምና ሥራ አታንሱ፤ የውጊያ ጥበባቸውን አታጋልጡ፤ ጽድቅ ጽድቁን ብቻ አውጉ ማለት እየኖርነው ያለው ክፋትና ሁለገብ ዓመፅ እየጋሸበ እንዲሄድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል፤ አድርጓልም:: (ዘጸ.15፥3) ፤ (መዝ.23፥1) ፤ (2ኛ ዜና.20፥15) ፤ (ኤፌ.6፥12) ፤ (ያዕ.4፥7) => ምንም እንኳ ይህንን ብልም፥ ወዲህም አንድ ነገር ይረ'ዳኛል:: ይኸውም ክፉው መንፈስ በመጀመሪያ ወደ ሰው ልጆች ለጥፋት የመጣበትን ጊዜ ያሳስበኛል:: መጽሐፈ ሄኖክ "ጋርድኤል" እያለ የሚጠራው መንፈስ፥ ወደ አዳምና ሔዋን ሲሄድ ማንነቱን በጣም በተዋበች የእባብ አካል ውስጥ ደብቆ እንደነበረ በብዙዎቻችን ይታወቃል:: ይሄም ከዕውቅና ውጪ ተሸሽጎ የመንቀሳቀሱ ነገር ከቀድሞውም ጀምሮ የነበረ መሠረታዊ ስልቱ እንደሆነ ያስረዳል:: በእርግጥስ ሔዋን እያነጋገራት ያለው በጥላቻና በቅናት የተሞላ ፍጡር መሆኑን ብታውቅ ኖሮ የሚለውን ለማድመጥ ዕድል ትሰጠዋለችን? => አሁንም ይኸው ነገር ነው ያለው:: በሥጋ ሕዋስ አለመታወቁና አለመለየቱን ተጠቅሞ እያጠፋ ያለው የዲያቢሎስ ሠራዊት፥ ስለ እርሱ የሚታወቅበትን መንፈሳዊ ትምህርት በተለያየ ዓይነት ጫና መከላከሉ የሚጠበቅ ነው:: ተከላካዮቹ የእግዚአብሔርን ቃል የሚጠቅሱና መልካም አድርገው የሚናገሩ ቢሆኑ አይደንቅም:: ምክንያቱም ይህንንስ ነገር ከመድኃኒታችን የምድረ በዳ ፈተና ተሞክሮ ልንወስድ ይገባናልና ነው:: (ማቴ. 4፥1-7) => ለመሆኑ "ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል" የምትለው ዝነኛ ጥቅስ ስለ የትኛው ዕውቀት ነው የምታነሣው? ስለ ቅዱስ ቅዱሱ ብቻ ያልናት የአስተምህሮ መንገድማ ውጤቱ ይኸው "የሕዝብ" መጥፋት ሆኖ ተደመደመደ እኮ:: መንፈሳዊ ትምህርቶች መሰጠት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ እሰከ ዛሬ ድረስ ቃሉ ያለማቋረጥ ይሰበካል:: ብዙ ዓይነት መምህራንና መጽሐፍት ሕዝቡ ላይ ይፈራረቁበታል:: ካልንስ እንደዚህ ዘመን ቃለ እግዚአብሔር ተስፋፍቶ የተላለፈበት ጊዜም የለ:: ሁለንተናዊ ጥፋቱ ግን ከመቀነስ ይልቅ ሲጨመር ነው የሚስተዋለው:: ምንድነው? => ልድገመው:: እግዚአብሔር ባወቀ ስለ ክፉዎቹ መናፍስት ነገር ንቁ የሚባለው ስለ ዲያቢሎስ የማውራት ሱስ ኖሮብን አይደለም:: ይልቁኑ ሕይወትን እስከማሳጣት የሚደረሰው ይህ የአስተምህሮ መንገድ፥ ከስድብ አሊያ ነቀፋ ውጪ ለሥጋ የሚያስቀረው ትርፍ የለውምና ስለ ዝናም ስንል አይደለም:: ክፉዎቹ እጅግ ጨካኝና ሰላም የለሽ ከመሆናቸው የተነሣ፥ ስለነርሱ ባይነሣ በወደድን ነበር:: አሰቃቂ ፍላጎትና ድርጊታቸው ለተፈጥሮአችን የማይመች ከመሆኑ አንጻር ብቻ ስለነሱ መረጃ ባለመለዋወጥ የሚሸሹን ቢሆን ምንኛ ደግ ነበር? => ግና ባላጋራዎቻችን ግትሮች ናቸው:: ሳልሳዊ አቡነ ሺኖዳ ዲያቢሎስን "መንቻካ" ሲሉ በመጽሐፋቸው ይጠሩታል:: (የዲያቢሎስ ውጊያዎች) እኛ ስለነሱ ስለማናወራ እነርሱ እኛን መፈታተናቸውን አያቆሙም:: አስታወስነውም አላስታወስነውም ሰይጣን ጠላቱ ስለመሆናችን [ለሰኮንድ] አይዘነጋውም:: አውቅነውም አላውቅነውም እኛን ከማጥፋት ከቶውኑ ወደኋላ አይልም:: ክርስቶስን ስንኳ ለመጣል የተነሣሣ ደፋር ልቡ በእኛ ቀኑን ሁሉ ለበጎ ነገር ልል ዘሊል ሆነን በምንውለው ላይማ እንዴት አይበረታታ? => በመሆኑ ወደድንም ጠላንም ክፉ ሥራውን እናስቆም ዘንድ፣ የሚጠንስሳቸው ተንኮሎቹን እንረዳ ዘንድ፣ ለመጣል የሚጠቀማቸውን ስልቶች እናውቅ ዘንድ፣ ለሕዋሳቶቻችን የሚያጋራውን ሁሉ እንለይ ዘንድ፣ ኃጢአት የሚስብበትንና የሚመራበትን መንገድ እንርቅ ዘንድ፣ በእግዚአብሔር ለመታመንና ለመደገፍ እንጥር ዘንድ፣ የቅዱሳኑን ሕይወት አብነትና ልምድ እናደርግ ዘንድ፣ ክፉውን ባለማወቅ በክፉው አንጠፋ ዘንድ የዲያቢሎስን ውጊያ እንማማራለን:: (የኤፌሶኑ መልእክት "መጋደላችን" ብሎ የሚጀምረው አንቀጽ ማለት "ገድል" ማለት ነው:: የቅዱሳን ገድል የሚተርከው ስለሌላ ስለምንም ሳይሆን ከክፋት ጋር ስላደረጉት መንፈሳዊ መጋደል ነው) => እንዲህ ሲባል ስለ መናፍስቱ ብቻ ስናመላልስ እንከርማለን ማለት አይደለም:: እንዲህ የሚያደርጉም ሲኖሩ ሊታረሙ ይገባል:: ባይሆን የውጊያው ትምህርት፥ ቅድስናን እንዲሠራ ርኩሰትን እንዲገራ ተደርጎ መሰጠት አለበት:: ብቻም ሳይሆን ያልበረቱ ምእመናን ትምህርቱን ለሥጋ ጥቅምና መድረሻ እንዳይገለገሉት በጥንቃቄ መተላለፍ አለበት:: ሰልፉ የእግዚአብሔር ነው ከተባለ፥ ድሉም የእግዚአብሔር እንደሆነ በአብክሮ ማሳወቅ ይገባልና:: #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ጥያቄ 6፡ ቤተ ክርስቲያን ደረቅ ሐዲስ እያለች የምታስተምረው የብሉይ ኪዳን ክፍል የሆነ መጽሐፍ የቱ ነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 5፡ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ከመጀመራችን በፍት ማድረግ የሚገባን ነገር የቱ ነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 4፡ የኦሪት መጻሕፍት በየት ሀገር ተጽፈዋል ተብሎ ይነገራል?
Anonymous voting

ጥያቄ 3፡ የነብዩ ኤርምያስ ኢትዮጵያዊው ደቀመዝሙር ማን ይባላል?
Anonymous voting

ጥያቄ 2: ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የሚመሰለው በምንድነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 1፡ ዘጸዓት ማለት ምን ማለት ነው?
Anonymous voting

ዕድሏንና ውበቷን በመናፍስት የተቀማች እናት! || አጋንንትን የሚያስገቡ እንጂ የማያስወጡ አገልጋዮች || የራሔሎ መንፈስ ድብቁ ሴራ #ethiopia #ebstv https://youtu.be/9jGPvsxxG40

መናፍስት የእምነት ኃይላችንን ለማዳከም ሦስት ቦታ ላይ ያደባሉ የእምነት ኃይላችን በአጋንንት ስፈተን የእምነት ኃይል ምንድነው? #ethiopia 😭😱🔥 https://youtu.be/BjgcRrvt8m0

በጸሎታችን ውስጥ ልካተቱ የሚገቡ ነገሮች | ጸሎታችን ልማዳዊ እንዳይሆን ይሄንን እናድርግ | በጸሎት ሰዓት ተመስጦ እንድኖረን | ጸሎትና የአጋንንቱ ፈተና 😱😭 https://youtu.be/ho2BJSK-Y8s

ጉድ! ለሀብት ብሎ ልጁን ለአጋንንት የሰዋ አባት! || ለገንዘብ ሲባል ራስን ለሰይጣን አሳልፎ መስጠት || የዘር የተዋርሶ መንፈሶች ፈተና #ethiopia 😱😱 https://youtu.be/CRw4c1GiiXI

=> አስተውሉ! ዘመን ዘመንን እየተካ የዓለም ጊዜ ወደፊት ወደ ማብቂያው ሰዓት በሚሄድበት የተፈጥሮ ዑደት፤ የሰው ልጆች ለክፉው ነገር አንድ ሆነው በመተባበር የሚገነቡት ቅድስናን የሚነካ ግንብ እንዲህ የሚለው አሳዛኝ ቃል ሁላችን ላይ እንዲታይ አሰገድዶአል፡፡ "ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል" (ወደ ሮሜ ሰዎች 3፥11) 'ሰማይ ጠቀስ' የሆኑ ፎቆችን፤ እስከ 'ሰማይ ደመና የሚደርሱ' በራሪ ቁሶችን፤ 'ሰማይን አልፈው የሚሄዱ" መንኮራኩሮችን በአንድ የቴክሎኖጂ ስምምነት የገነባው የኛ ዘመን፤ አንድ ወቅት ላይ "ከጠፈር ከፍታ ሆነን ወደ እግዚአብሔር ድንጋይ እንወርውር" ያለበትን የትዕቢት ርዝመት ስናስተውል በሰናዖር ሊቆም የነበረው 'እስከ ሰማይ የሚደርስ' ግንብ መልኩንና ቅርጹን ለውጦ መገንባቱ እንደቀጠለ ያስረዳናል፡፡ => "ኑ፥ ጡብ እንሥራ" አይደለም ያሉት? ወደ ትውልዳችን ሁኔታ መለስ ብለን ስናስብ፤ "ኑ፥ ጸሎት እናድርስ፣ ኑ፥ ለፈጣሪያችን እንሰግድ፣ ኑ፥ ሥጋና ደሙን እንቀበል፣ ኑ፥ ወገኖቻችንን እናግዝ" የተባባልንበት የቅድስና አንድነት የለም፡፡ ይልቅ በአንጻሩ "ኑ፥ እንጠጣ፣ ኑ፥ እንጫጫስ፣ ኑ፥ እንዘሙት፣ ኑ፥ በዘር እንከፋፈል፣ ኑ፥ ሰውን እናሳድድ፣ ኑ፥ የብሔር ስማችንን እናስጠራ" ብለን ክፉውን ለመገንባት የተሰባሰብንበት ዘመን፤ ክፉ መንፈሶች ጀምረውት የነበረው በሰው እጅ ክፉን የመገንባት ውጥን በይበልጡን ቀጥሎ፤ "ዓለሙ በመላው በክፋት እንደተያዘ እናውቃለን" ያሉት የብርሃን ሐዋሪያት የጸዳል-ቃል በጨለማ ገመድ (በመናፍስት መናበብ) የተሳሰርንበትን ጥቁር ክፋት የሚገለጥ ሊሆን ተጽፎአል፡፡ እንንቃ! => አገልግሎታችን እንደቀጠለ ነው! የፊታችን እሁድ ጥቅምት /17/2017 ዓ.ም በሰሚት ዋሻ መካነ ሕይወት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከቅዳሴ በኃላ አገልግሎቱ ይቀጥላል! => የቤተክርስቲያኑ አድራሻ፤ ሳሚት ኮንዶሚኒየም 2ተኛ በር ወረድ ብሎ ከኢትዮ ቻይና ት/ቤት እንደ ሁለተኛ መንገድ አማራጭ ሰሚት ጤና ጣቢያ መግቢያ መሆኑን እየገለጽን ሼር በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ይድረስ ለቢንያም ሽታዬና መሰሎቹ! || አጋንንትን አውጡ እንጂ አስገቡ አልተባልንም! || ለአጋንንት ጥብቅና የሚቆሙ አገልጋዮች #ethiopia #ebstv 😭😱 https://youtu.be/dbW-VE13UfM

ከክፉ መናፍስት እስራት ለመፈታት ይሄንን አድርጉ! || ዕድላችንና ዕውቀታችን በመናፍስት ሲወሰድ መንቃት አልቻልንም || ባዶነትና ጭንቀት የመናፍስቱ ዓለም 😭😱 https://youtu.be/Ye21FCQPSTk

«ሜምፈቦስቴ፡ አሳዳጊ የጣለው ልጅ!» => አስተውሉ! ዛሬ ልጆች ከቤተሰብ ጋር ከሚያሳልፉት ጊዜያት ይልቅ ትምህርት ቤት የሚያሳልፉት ጊዜ ሰፊ ነው። ስለዚህ ልጁ አባታችን ሆይ! የሚለውን ቃል ከቤተሰ
«ሜምፈቦስቴ፡ አሳዳጊ የጣለው ልጅ!» => አስተውሉ! ዛሬ ልጆች ከቤተሰብ ጋር ከሚያሳልፉት ጊዜያት ይልቅ ትምህርት ቤት የሚያሳልፉት ጊዜ ሰፊ ነው። ስለዚህ ልጁ አባታችን ሆይ! የሚለውን ቃል ከቤተሰብ ጋር አልመደም። እግዚአብሔር ሆይ! ብሎ የሚጸልይበት ጊዜና አቅም የለውም። የክፋትና የተንኮል ተጋቦት፡ በሕይወቴ እንዳይኖር ከልክልልኝ ብሎ፡ እግዚአብሔርን የተማጸነበት ጊዜ የለውም። ወላጆች ልጆቻቸው መንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ አልፈው፡ በመንፈስ ቅዱስ እንዲባረኩ ያደረጉት ጥረት የሚፈለገውን ያህል ባለመሆኑ ትውልዱ ዛሬ አደጋ ላይ ነው። => በመጀመሪያ ደረጃ፡ የወላጆች የራሳቸው መንፈሳዊ ጉዞ ላማዳዊና ራዕይ የሌለው ነው። ዞር ብለን የመንፈሳዊውን በረከት ስናይ ግን፡ በአዲስ ኪዳን በክርስቶስ ሥጋና ደም በቅድስና መሠረቶች ላይ ቆመን ዘመናትን ለማለፍና ትውልዶቻችንን መንፈሳዊ በረከት ለማስጨበጥ ትኩረት የሰጠንባቸው ጊዜዎች በጭራሽ የሉንም። ከዚህ የተነሳ ትውልዳችን በተለያየ ዓይነት መንገድ ለክፉ መንፈስ አደጋ ተጋልጦ ሲሰቃይ አልተረዳንም፣ አላገዝነውም! ጭራሽ ገፊዎቹም እኛው ሆነን ቁጭ! => ይህም የኃጢአት መንገድ መንገድ የምናስተውልበትን ዓይን እንደጋረደንና የሰው አስተሳሰብ እጅ ላይ እንደጣለን መገንዘብና መረዳት ይኖርብናል። ስለዚህ የሜምፈቦስቴን ሕይወት በሚመልስ ኑሮ ውስጥ የመገኘቱን ጉዳይ ለማስተዋል ጊዜ መስጠት አለብን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239