HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 277
Suscriptores
+224 horas
+97 días
+3830 días
Archivo de publicaciones
«መናፍስት እኛን የግለወሲብ ጥገኛ ለማድረግ የሚጠቀሙት ስልቶች»
፩/ ግለ ወሲብ ኃጢአት እንዳልሆነ በማሳሰብ
አይነጥላ ከማህፀን ሲቆራኝ ግለ ወሲብን ገና በለጋ እድሜ ያለማምዳል። መናፍስቶች ገና በማለዳዉ ሲቆራኙ ነገሮችን ከመልካምና ከክፋት አንፃር ለይተን እድናመዛዝን አይፈቅዱም፤ እዛዉ ክፋታቸዉ ዉስጥ ቆልፈዉ በማስቀመጥ ኃጢአትን መልካም እንደሆነ እየመከሩ የመዳኛ ጊዜ እስኪያልፍ ጥንቃቄ በተሞላ ስልታቸዉ ይስራሉ እንጂ። የአይነጥላ መንፈስም ግለ ወሲብ ሲያለማምድ ስለዚህ ተግባር ክፋቱንና አስከፊነቱን ምንም መረጃ እንዳይኖር በማሸሽ (መንገድ ይዘጋጋል) ግለ ወሲብ ኃጢአት እንዳልሆነ ኃጢአት የሚሆነዉ ከትዳር ዉጪ የሚደረግ ግንኙነት እንደሆነ ተቃራኒ ፆታ ብትቀርቡ በዚህ ኃጢአት ልትወድቁ እንደምትችሉ እያሳሰበ ትዳርም እንዳትይዙ የትዳር ጥላቻ እያሳደረ ራሱ ባለማመደዉ የኃጢአት አዘቅጥ ዉስጥ አስቀምጦ አዕምሮን አደንዝዞ በመያዝ ኃጢአት ይሁን አይሁን እስካልታወቀ ድረስ ከተቃራኒ ፆታ እያሸሸ የግለ ወሲብ ጥገኛ አድርጎ የሚያስቀምጥ ሴረኛ ነዉ።
ስለዚሁም ነዉ! አንዳንድ ሰዎች በዚህ መንገድ ካለፉ በኋላ ይሄ ጸያፍ ተግባር ኃጢአት እንደሆነ ባለመረዳት ጥያቄ የሚያነሱት ይሄ ጥያቄያቸዉ የሚያሳየዉ መንፈሱ እነዚህ ሰዎች ምን ያህል አደንዝዞ እንደያዛቸዉና በራሱ የክፋት ዓለም ዉስጥ አስቀምጧቸዉ እንደነበረ የሚያመላክት ነገር ነዉ። ግለ ወሲብ ኃጢአት ከመሆኑም አልፎ በእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስቀስፍ ኃጢአት ነዉ!
እግዚአብሔር በአንድያ ልጁ በምህረት ኪዳን ባይጎበኘን ኖሮ ስንቶቻችን የሞት ቅስፈት በመጣብን ነበረ። ግብረ አዉናን እግዚአብሔር የማይወደዉና የሚጸየፈዉ ትልቅ ኃጢአት ነዉ! በዘፍጥረት ክታብ ላይ አዉናን ዘሩን በምድር ላይ በማፍሰሱ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀስፏል (ዘፍ፤38፤9:10) ዛሬም ዲያቢሎስ ይሄንን የሚያስቀስፈዉን ኃጢአት ነዉ እንግዲህ መልካም እንደሆነ በማሳየት ከመልካም መንገድ የሚያስፈነግጠዉ።
ሌላዉ በተክሊል ለማግባት የሚያስቡም አሉ እርኩሱ መንፈስ ለእነዚህ ሰዎች ድንግልናቸዉ እንዳልተነካ ስለሚያሳስባቸዉ ጥያቄዉን ያነሳሉ። የጠላት ሴራ እንዲህ ነዉ፥ በኃጢአት ላይ ኃጢአት በማደራረብ ከእግዚአብሔር ጋር ማጋጨት የሥራ ድርሻዉ ነዉ። ግለ ወሲብ የፈጸመ ሰዉ የድንግልና ሕጉን በጠላት ምሪት ስለሚያፈርስ በተክሊል ማግባት አይችልም።
፪/ በተቃራኒ ፆታ ዘንድ እንዳትወደዱ በማድረግ
መናፍስቶች ሰዉ ለማጥፋት ሲሆን እጅና ጓንት ሆነዉ በመረዳዳት ክፉ ስራቸዉን ይሰራሉ። ይሄ ሴረኛ ጠላት ተቃራኒ ፆታ እንዲቀርብ ስለማይፈልግ ግንባር ላይ ተቀምጦ ብቸኝነት እስኪሰማችሁ ድረስ ተቃራኒ ፆታን እያባረረ ከሰዉ እንድትርቁ ያደርጋል። ማንም እንደማይወዳችሁ፣ መልከ ጥፉ እንደሆናችሁ፣ ብትለብሱም ብታጌጡም የማታምሩ ፍጥረት እንደሆናችሁ፣ መስታወት ፊት አቁሞ በማሳየት ራሳችሁን እንድትጠሉና ከሰዉ ርቃችሁ የብቸኝነት ሕይወት እንድትመሩ ይመክራል።
ከዚህ በኋላ ተስፋ ቆርጣችሁ በዚህ ጉዳይ ከማንም ጋር ላለማዉራት ወስናችሁ ሕይወታችሁን መምራት ስትጀምሩ የዝሙት መንፈሱ በተራዉ ይመጣና ሥራዉን ይጀምራል። ወደ ተቃራኒ ፆታ በዝሙት ዓይን እያስመለከተ በፍትወት እንድትቃጠሉ እያደረገ ያያችሁትን ሁሉ ለፍትወት እንድትመኙ ገፋፎቶ ወደዚህ ሕይወት ያሰማራል አንዴ በወጥመዱ ዉስጥ ከገባችሁ በኋላ በዚህ ጸያፍ ተግባር ተጠምዳችሁ እንድትኖሩ ያደርጋል።
፫/ በትዳር ሕይወታችሁ ደስተኛ እንደማትሆኑ በማሳሰብ
መናፍስቶች ከኃጢአት አዘቅጥ ዉስጥ እንዳንወጣ ስለሚፈልጉ አሳማኝ በሆነ ምክንያት አስረዉ ያስቀምጣሉ። አይነጥላ ይሄንን ሀሳብ አዕምሮ ዉስጥ ለመቅረጽና ነገሩን በእርግጠኝነት አምናችሁ እንድትቀበሉ ከሌሎች መናፍስት ጋር መናብብ ይፈጥራል። መናብብ ማለት ቅዱሳን ሆኑ እርኩሳን መናፍስት በእኛ ገሐዳዊ ዓለም እርስ በእርስ የሚያደርጉት መግባባት ማለት ነዉ።
እርኩሳን መናፍስት በማይገመት መልኩ አዕምሮን በክፉ ሀሳባቸዉ ይመርዛሉ። ይሄ ኩፉና ሴረኛ መንፈስ ከሌሎች መናፍስት ጋር በመናበብ ስለ ትዳር አስከፊነት ከልዩ ልዩ ባለትዳሮች እንድትሰሙና በተለይ በሩካቤ ጊዜ ያለዉን ችግር ግልጥ በሆነ መንገድ በተገኘዉ አጋጣሚ ሰዎች እንዲያወሩላችሁ እያደረገ በእናንተ ልብ ዉስጥ ፍርሀት ጨምሮ በአዕምሮ ዉስጥ የራሱን ምስል በመቅረጽ ገና ትዳርን ሳታዉቁት እንድትፈሩ ያደርጋል። በዚሁ በረከሰ ሕይወት ደስተኛ ሆናችሁ መኖር እንደምትችሉ በማሳሰብ የግለ ወሲብ ጥገኛ የሚያደርግ ሴረኛ የሆነ ጠላት ነዉ። ስለዚህም ነዉ በቤታችሁ ዉስጥ የጸሎት ቦታ አዘጋጅታችሁ የመንበርከኪያ ጊዜ ይኑራችሁ ጠላት ዲያቢሎስ ላይ ንቁ የሚባለዉ።
፬/ ዓይነ አፋር በማድረግ
መናፍስቶች ሥራቸዉን የሚሰሩት በዕቅድና በዓላማ ነዉ። አይነጥላ ወንዱንም ሴቷንም ዓይናፋር በማድረግ ከሰዉ እያሸሻቸዉ የብቸኝነት ሕይወትን ያለማምዳቸዋል። አይነጥላ ዓይናፋር የሚያደርጋቸዉ ሰዎች ከሰዎች ጋር ሕብረት ማድረግ የማይችሉ ከቤተሰብ ጋር እንኳን ሳይቀር ለመግባባት የሚቸገሩ ዝምም ያሉ ፍጡሮች ስለሚሆኑ ተግባቦታቸዉና ግንኙነታቸዉ ከቴክኖሎጂ ጋር ብቻ ይሆናል።
አብዛኛዉ ድህረገጾች የዲያቢሎስን ሴራ የሚስፋፋበት በመሆኑ መንፈሱ ለእነዚህ ሰዎች የኃጢአት መንገድ ለማሳየት አይቸገርም። በእርግጥ የቴክኖሎጂ መስፋፋት ጥቅም ቢያሰጠንም የብዙሃኑን ሕይወት እያቃወሰ በቁም እየገደለ ያለዉ የቴክኖሎጂ መስፋፋት ነዉ። መንፈሱ ሲታዩ ቀላል በሚመስሉ ሰዉነትን ሲዋሃዱ ግን ከመርዝ በላይ ገዳይ በሆነ ሴራዎቹ ሕይወት መጠልሸት ይጀምራል፤ በተንቀሳቃሽ ስልኮች በሚታዩ የወሲብ ፊልሞችና በልበ ወለድ መፅሐፍቶች ዉስጥ ለዝሙት የሚጋብዙ ቃላት፤ ሀገርኛ ፊልሞቻችን ላይ በሚታዩ አላስፈላጊ ተግባራት መሰረት በማድረግ [አጋጣሚዎችን በመጠቀም] እነዚህን ክፉ ምግባራት በማሳየትና በማስነበብ የሰዉ ልጆችን ሕይወት ማበላሸት ይጀምራል።
የአይነጥላ መንፈስ የኃጢአት መንገዶችን ለማለማመድ አንድ ሰከንድ ከበቂዉ በላይ ነዉ። የወሲብ ስሜት ቀስቃሽ የሆነዉን ምስል ወይም ፅሑፍ አዕምሮ ዉስጥ በመቅረፅ በትዉስታ መልክ እያመጣ ግለ ወሲብ ያለማምዳል። ከዚህ በኋላ እራሱ አጥፊ እራሱ ወቃሽ ሆኖ ቁጭ ይልና ኃጢአተኛ ነህ እግዚአብሔር ጠልቶሃል፣ እንዴት እንዲህ ታደርጋለህ ወዘተረፈ… የሚሉ ወቀሳዎችን እያስከተለ የግለ ወሲብን ፍላጎት ከፍ በማድረግ ከበፊቱ በበለጠ መንገድ ሚስጥራዊና ባይተዋር እያደረገ ጥንቃቄ በተሞላ መልኩ የፖርኖ ግራፊ ፊልምና የግለ ወሲብ ጥገኛ ያደርጋል።
፭/ ለስንፈተ ወሲብ በመዳረግ
የዲያቢሎስ ትልቅ ዓላማ ዓለምን በአንድ (globalization) ስር ጠቅልሎ መያዝ ስለሆነ በማንኛዉም መንገድ የኃጢአት መንገዶችን ያስፋፋል። አብዛኞቻችን በሕይወታችን ዉስጥ ለገጠመን ችግር መፍትሔ ፍለጋ ወደ ዓለም እንጂ ቅድሚያ ወደ እግዚአብሔር አናመለክትም።
ሕክምናዉም የተሳካ የሚሆነዉ የእግዚአብሔር ፍቃድና እርዳታ ሲጨመርበት እንደሆነ ግንዛቤዉም የለንም ቢኖረንም አናደርገዉም። የእምነት ኃይላችን የተዳከመ ስለሆነ ይሄ ተግባራችን ለመናፍስቱ ሴራ አመቺ ሆኗል። ምክንያቱም ሐኪሙን እንደ መሳሪያ ተጠቅሞ ኃጢአትን ያለማምዳሉና።
አይነጥላ፤ ዛር፤ የዝሙት መንፈስና ሌሎችም መናፍስቶች ጭምር የወንዶች ሀፍረተ ሥጋ ላይ በመቀመጥ ለስንፈተ ወሲብ ይዳርጋሉ መፍትሔ ፍለጋ ወደ ሐኪም በሚሄዱበት ጊዜም ወሲብ ቀስቃሽ የሆኑ ፅሑፎችን እንዲያነቡና ፖርኖግሪ ፊልሞችን እንዲመለከቱ ከባለሞያዉ ጥቆማ ስለሚያገኙ ወደዚህ ሕይወት በቀላሉ ይገባሉ። ከጊዜ በኋላ የ
መናፍስት እኛን የግለ ወሲብ ጥገኛ ለማድረግ የሚጠቀሙት ስልቶች ግለ ወሲብና በተክሊል ማግባት ግለ ወሲብ ወይም ሴጋ ምንድነው? #ethiopia 😱😭💥😱
https://youtu.be/5sPwT1Mij8M
«ልብ ብለው ያንብቡት!»
=> ዛሬ የገድለ-ዲያብሎስ የዝና ታሪክ፣ የኃጢአትና የሞት ዜና መረጃ በበዛበት ዓለም ውስጥ እንገኛለን፡፡ ኃጢአት፤ ለዚህ ዘመን ሰው የመጀመሪያው ዕውቀትና የሥነ-ምግባሩ መግለጫ በመሆን፤ ጸሎት ጽድቅንና እውነትን የባርነት መንገድ አድርጎ እንዲያይ፤ የትውልዱ የውድቀት ጉዳይ ፈጻሚ የመሆን ዕጣ ድርሻውን ከዲያብሎስ ተምሯል፡፡ ‹‹በጎ እያደረጋችሁ፣ የማያውቁትን ሞኞች ዝም ታሰኙ ዘንድ እንዲህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና፤ አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ፡፡›› (1ጴጥ 2÷15-16) ክፉ መናፍስት፤ በሕይወታችንና በኑሯችን ውስጥ፤ ሥፍራና ቦታ አግኝተው፤ በውድቀት አዙሪት ውስጥ እንድንኖር ሊያደርጉ የቻሉበት አንዱና ዓብይ ምክንያት፤ ለአምላካችን የቅድስና አምልኮትና ለእግዚአብሔር ጸሎት ባለማድረሳችን ነው፡፡
=> ከዲያብሎስ መሠረታዊ ሥልት አንዱ፤ በዓለማዊው መድረኮች ላይ ለመንፈሳዊ ሕይወት ቦታ እንዳይሰጥ፤ በተለይም ጸሎት ወደ እግዚአብሔር እንዳይደርግ ማዘናጋት ነው፡፡ ጸሎት አለማድረግ ደግሞ፤ ከእግዚአብሔር የሚያለያየን ዋንኛ መንገድ ነው፡፡ ዛሬ በዚህ ጎዳና ላይ እኛም እየተጓዝንበት እንገኛለን፡፡ ከአምላክህ ጋር ከተለያየህ ደግሞ፤ የምታዳብረው ጠባይ፤ ክፋትን፣ ተንኮልን፣ ፌዘኝነትና ደንታ ቢስነትን ወዘተ…ነው፡፡
=> በዚህ መንገድ ከተጓዝን ደግሞ፤ ጸሎት የለም፡፡ ምናልባት የምንሰማውና የምናየው የአንድና የሁለት ደቂቃ የሕሊና ጸሎት የሚባለውን ነው፡፡ የሚገርመው ግን፤ ይህ የሕሊና ጸሎት ለማን እንደሆነ፣ ምን ተብሎ እንደተጸለየና ማን እንደሰማው አለመታወቁ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነቱ ጸሎት፤ ዘመናዊው ሰው ምንጊዜም አቅጣጫውን ሲለውጥ፣ እምነቱን ሲጥል፣ የማንነት ጉዳዩን ከመናቅም በላይ፤ አዲስ ነገርና የፈጠራ ሃሳብ መሞከሪያ ሲሆን፤ እራሱን እያዘናጋ በሕይወት ተምሳሌቱና ከጊዜው እይታ ጋር ሲወዳደር፤ ለየግል ፍላጎቱ ከሥራ ጋር ሲባዝንና ሲሯሯጥ፤ በመሐል ሃይማኖቱንና እምነቱን በመዘንጋት፤ ለከባድ መቅሰፍት እንዲጋለጥ የሚያደርግ ነው፡፡
=> ክርስቲያን ወገኖችም፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን ሁሉ በሚገባ በመከተል፤ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በአምልኮት በመንበርከክ፣ በቅዱስ ቁርባን፣ በንስሐ፣ በጸበል፣ ወዘተ… በመቀደስ፤ የእግዚአብሔር ሰው ለመሆን እስካልቻልን ድረስ፤ የዲያብሎስ መጫወቻ ሆነን ብንቀር የሚያሳዝንና የሚያሰቆጭ አይሆንም፡፡ ብዙ ሰው ስለ ክፉው መንፈስ ያለው አመለካከትና ግምት፤ በእኔ ላይ መተት አይሠራም፤ እግዚአብሔርን አምናለሁ፤ እንዳቅሜ ጸሎት አደርሳለሁ፤ እመጸውታለሁ፣ አንዳንዴ እጾማለሁ ሲመቸኝ ቤተክርስቲያን እሄዳለሁ፤ ሰንበቴና የጽዋ ማሕበር እጠጣለሁ፣ የቄስ ዘርና የቅዱሳን ዘር ነኝ፤ አያቴ ዳዊት ደጋሚና ቤተክርስቲያን ተካይ መነኮሴ ገዳማዊ ነበሩ፤ መናኝ ባሕታዊ ዘመድ ነበረኝ እያልን፤ ራሳችንን በትልቅነት ደረጃ ውስጥ አስገብተን እንመካለን፤ ብዙ እናወራለን፤ የሚገርመው ግን፤ ከእግዚአብሔር ልጆች የዲያብሎስ ልጆች የተንኮልና የግፍ አሠራሩ ላይ፤ ከማንም በላይ የሰለጠኑና የጥቃት ሥልታቸው የረቀቀ፤ ሂደቱን በእያንዳንዱ በኋላው ታሪክ በሚመጻደቅ ትውልድ ላይ ሁሉ፤ የመንፈሱ ጥቃት በምስጢራዊ ሁኔታ ተከናውኖ መገኘቱ ነው፡፡
=> ሌላው ቀርቶ የዓይነ-ጥላ አብሮን የመወለዱን ጉዳይ እንኳን ገና በግልጽ አልተረዳንም፡፡ ይህም የቱን ያህል ከማለዳ የመያ’ዝ ጉዳይ ጋር የተወሳሰበ እንደሆነ ያስረዳናል:: በመንፈሳዊ የሕይወት ጅማሬ ውስጥ፤ ለዕውቀት ሲባል የሚወሰዱ ዕፅ-ፋርሶችና በሰውነት ውስጥ የሚቀበሩ ከመንፈሱ ጋር በዕፆች አማካኝነት የሚገቡና በሰውነት ውስጥ ተመሳስለውና ተዋህደው የሚኖሩ የመንፈሶች አደጋዎች፤ በስፋት ያጠቁት ወገን ብዙ ነው፡፡
=> በዚህ ዓይነት መንፈስ ተጠምደው ቤተ እግዚአብሔርንና ለምዕመናን፤ ከአነጋገር እስከ ተግባር ድረስ መሰናከል ሆኖ የሚኖረው የአገልጋዮች ችግር፤ ከዚህ የልማድ አምልኮት ጋር የተያያዘ እንደሆነ፤ ብዙ በቤቱ የሚመላለሱ ሰዎችና በርካታ ምዕመናን ገና አልገባቸውም፡፡ ነገር ግን በተግባር የሚታየው ሁሉ የክፉው መንፈስ የውክልና ሥራ በቃል ክፉ በመናገር በልብ በመመቅኘት፣ ተንኮል፣ ቅናትና አስማታዊ አሠራር መግለጫ ነው፡፡ በሰውነት ውስጥ ተዋህዶ በመኖሩ ምክንያት የአገልግሎት ዘመኑን ሁሉ ለዓለማዊ ጥቅም ብቻ እንዲሰለፍ፤ በጥቅሙ የሚመጣበትን ሁሉ በማንኛውም የክፋት መንገድ በመበቀል፤ የመዋጋቱ ጉዳይ፤ ለመንፈሳዊ እምነቱ ከሚሰጠው ቦታ በላይ፤ ተንኮሉ የበለጠ ነው፡፡
=> ከእውቀቱ ዘርፍ፤ ክፉ መናፍስት ዕውቀትን ሰጭ አካል አድርጎ ከጀመረ መንፈሳዊ አገልግሎቱ ውስጥ፤ ብዙም መልካም ነገር ባይጠበቅ የሚገርም አይሆንም፡፡ ምክንያቱም፤ ክፉው ዲያብሎስ ሥልቱም ተፈጥሮውም ሃይማኖታዊ ጉዞን የሚያመጣውን ጸጋ፣ ሞገስና የእምነት ኃይሉን ተመሳስሎ ማዳከም ስለሆነ፤ ይሄው ግቡ ዛሬ ብዙ የተሳካለት መሆኑን በየቤተክርስቲያን ያለው የመለያየት ችግር ማሳያ ነው፡፡
=> በመንፈሳዊ ግንዛቤያቸው የተሻሉ ሰዎች ግን፤ ሕብረተሰቡ ውስጥ ያለውን የክፉ መንፈስ ውስብስብ ፈተና የኑሮ፣ የእምነትና የአእምሮ መቃወስ፣ የጤና ማጣት አደጋ ይገነዘባሉ፡፡ የዚያኑ ያህል በተቃራኒው፤ ሳይቀደሱ የሚባርኩ፣ ሳያመልኩ የሚያገለግሉና የሚገለገሉ፣ የያዙትን ወንበር የሚያመልኩ፣ ለሌላው ጥፋትና ክህደት ምሳሌ የሚሆኑ ለአሰተዳደራዊ በደል መፍትሔ የማይሰጡ፣ የተዘበራረቀ አመለካከት ያላቸው፣ በጥቅምና በባለጸጋ የሚታለሉ፣ ሃይማኖታዊ አደራቸውን የዘነጉና ለሕዝብ ደህንነት ራእይ የሌላቸው፣ ችግሩን የማያዩና የማይሰሙ፣ በምትሐተኞች እጅ የተያዙና በቤተ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ኃይል መኖር ያቃታቸው አገልጋዮች ጥቂቶች አይደሉም፡፡
=> በአጠቃላይ በእግዚአብሔር ቤት የምንገኝ አገልጋዮች፣ ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች ሁሉ፤ የክፉ መናፈስቱን የውጊያ ሥልቶችና ጥበቦች፣ የመጠጊያ፣ የመግቢያና የማጥቂያ አቅጣጫዎቻቸውን፣ ረቂቅ ጠባያቸውንና ሥሌታቸውን በመገንዘብ፤ ከርኩሳን መናፍስት ተገዢነት ነጻ ወጥተን፤ እውነተኛውን የእግዚአብሔርን የጽድቅ መንገድ መከተል እንችል ዘንድ፤ ኃያሉና ልዑሉ አምላካችን እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
=> በእግዚአብሔር ጥላ ሥር የሌለ ትውልድ፤ ከመንፈስ ጠላቶቹ ጋር ይኖራል። የስኬት መንገድ በጠላት ተዘግቷል ኑሮው የእርሱ አይደለም። መድሐኒትና የሰው እጅ ላይ ውድቋል። ይሠራል፣ ይለፋል፣ ይማራል፣ ይደክማል። ነገር ግን ጎተራው፣ ኪሱና እጁ ጭንቅላቱ ባዶ ነው። በረከቱ በመንፈሱ ተወስዷል። በገሃዱ ዓለም በግልፅ የማያያቸው ክፉ መንፈሶች ያሳድዱታል። በአጠቃላይ እነዚህ ከዓይኑ የተሰወረ ጠላቶቹ ይፋለሙታል። እርሱ ግን ጠላቶቹን ለመፋለም አቅም ያንሰዋል። ምክንያቱም፤ ለአምልኮትና ለጸሎት ጊዜ ስለሌለው፤ ሰማይ አልከፈት ብሏል። ስለዚህ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር የለም። እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን፣ ይጠብቀንም!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ»
=> ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ ይህንን የተናገረው ክቡር ዳዊት በመዝሙር 19፡12 ላይ የምናገኘው ነው፡፡ ‹‹ከተሰወረ ኃጢአት አንጻኝ። የድፍረት ኃጢአት እንዳይገዛኝ ባሪያህን ጠብቅ፤ የዚያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ፥ ከታላቁም ኃጢአት እነጻለሁ።›› በማለት ይናገርና ማብቅያው ‹‹አቤቱ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።›› በሚል ይደመድማል
=> ብዙ ጊዜ ብዙ የስዉር ህይወት ጎዳና ውስጥ ብዙ ጥፋቶች ይመጣሉ፡፡ ብዙ ነገሮች ይከሰታሉ፡፡ ለብዙ ዘመናት የቆየ የክፉ መናፍስት አሰራር ውርስ ውስጥ እንደገባን እንኳን አሁን አሁን ጥቂት መባነን ጀምረናል፡፡ ብዙዎቹ እንኳን አሁንም ሊባንኑ ያልቻሉ በዚሁ በክፉ አሰራር ስዉር መንገድ ውስጣዊው ህይወታቸው አቅጣጫ የጠፋቸው፣ የህይወት መንገድን ያጡ፣ ሠላማዊ የሆነ በረከት የራቃቸው ብዙ ናቸው፡፡ ያንን እንደ ልማድ ይዘዉት፣ እንደ ጸጋም ቆጥረዉት በተምታታና በረከት አልባ በሆነ ህይወት ራሳቸዉን መርተው ትውልዳቸው ኪሳራ ውስጥ ጥለው የሚያልፉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ስለዚህ ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ ሁላችንም ልንል ይገባናል፡፡
=> እና ዛሬ ብዙ ሰው ከበረከትና ከእግዚአብሔር አምላክ ጸጋና ተስፋ በመራቅ በዲያብሎስ በኩል የሚኖረዉን ኑሮ እንደ ጣፋጭ የህይወት አካል አድርጎ ይዞታል፡፡ ከዚሁም ውስጥ አንዱ በግሉ ለመናፈስት መገበር ነው፡፡ በግሉ ለመናፍስት መገበር ማለት በተሰወረ ሐጥያት በኩል መናፍስቶቹን እንደ ሥራ ባህሪ ማሰማራት ነው፡፡ ከነዚህም ውስጥ አንዳንዱ ሰውነትን ለክፉ መናፍስት አሰራር መስጠት ነው፡፡ በዚህ ዘመን፣ በዚህ ግዜ፣ በዚህ በእውቀት፣ በዚህ በቴክኖሎጂ ዘመን ውስጥ ሰዎች የተሰወረ ስዉር የሆነ የሐጥያት አሰራር ውስጥ ይገባሉ፡፡ ከዚህም ውስጥ አንዱ መናፍስቱን የሚፈልጉትን ነገሮች ያሟላሉ፡፡
=> ከሚጠይቅዋቸው ነገሮች አንዱ በፈርስ፣ በእንስሳት ደም፣ በሌሎች የደም አይነቶች መታጠብ፡፡ ሰውነትን፣ ገላን እነዚህ እነዚህን የመሳሰሉት ነገሮች በመናፍስት ግብር ውስጥ ሰውነትን ማሳለፍ ማለት ነው፡፡ በፈርስና በደም መታጠብ በዘመናችን በጣም ትልልቆቹ ወይዘራዝርትና ልዩ ሆኑ የሚባሉ ሰዎች ሁሉ ጭምር ለተሰሚነት፣ ለግርማ ሞጎስ አንዳንድ ነገሮችን ፍፃሜ እንዲመጣላቸው ወይም በመናፍስት እንዲጠበቁ አልያም በመናፍስት አሰራር ውስጥ ገበያው እንዲቃጠል፣ የሃብት ኃይሉ እንዲጨምር እነዚህ የመሳሰሉ ነገሮች በዚህ በተሰወረው የሐጥያት ኃይል ውስጥ የሚከናወን ነው፡፡ ለዚህ ነው ክቡር ዳዊት ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ በማለት ይህንን የጸሎት ኃይል ሲገልፅ የምናገኘው፡፡
=> ዛሬ በዚህ አይነት የተጠላለፉና በዚህ በመናፍስት ጎዳና ውስጥም ዘግጠው የገቡ እንደ አንዱ ራሱን የቻለ ኑሮ አድርገው የያዙት ብዙዎች ናቸው፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ክብር ቢጠሩ እንኳን የማድመጥም፣ የመስራትም፣ የመለወጥም ፍቃድ የላቸዉም፡፡ ለምን? በተሰወረ ኃጢያት በኩል ልቦናቸው የሚያውቀዉና በአኗኗራቸው ውስጥ የክፉዉን አሰራር በህይወታቸው ዙርያ የለመዱት ነገር ሆኖው ስለሚገኙ፡፡
=> ኃጢያት በራሱ ከመናፍስት ውጪ ተሰዉሮ የሚኖር ጉዳትም ጭምር ነው፡፡ አሁን ይህንን በዝርዝር ለመመልከት እስቲ በመጀመርያ ስዉር ሐጥያት ሲባል ምንድነው? የሚለዉን ነገር ላይ ትኩረት ለመስጠት እንሞክር፡፡ የተሰወረ ኃጢያት የሚነሳው ከልብ፣ ሕሊናና ከአዕምሮ ውስጥ ነው፡፡ ከሕሊናና ከአዕምሮ ውስጥ ከመሰወሩ ባሻገር ደግሞ የመናፍስት ግፊቶች ከነዚህ ካሉት ሦስት ቦታዎች ላይ መነሳት ሲጀምር የተጠናከረ የክፉ አሰራር ኃይል ወደ ዉጪ እንዲወጣ ያደርገዋል፡፡ ያ በሐሳብ፣ በዕቅድ፣ በፕሮግራም፣ በአነጋገርና በአፈፃፀም የሚገለጥ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ በማለት ክቡር ዳዊት ይህንን ወደ ሰማይ አምላክ ኃይልና ወደ ሰማይ አምላክ መንፈሳዊ ተስፋ እንዲገባ ራሱን አዘጋጅቶ እናገኘዋለን፡፡
=> የተሰወረ ኃጢያት ምንጩ በምኞት ውስጥ የተካተተ ነው፡፡ የሰው ኑሮን መመልከት፣ የሰው ህይወትን ማየት፡፡ የሰው ህይወትን አይቶ ደግሞ በክፉ መከጀል፣ በክፉ ነገር ላይ ማሰብ፣ ተንኮል መፈፀም፣ ግፍ መስራት፣ በምቀኝነት ማየት፣ ኪሳራዉን መመኘት፣ ውድቀቱን መመኘት እና ደግሞ ከዛም በተግባር አልፎ ተርፎ በምትሐት ዓለም መሄድ የተሰወረ ሐጥያት ክፍል ነው፡፡
=> ኃጢያት በራሱ ከመናፍስት ተሰዉሮ የቱን ያህል ጊዜ ፣ ዘመን፣ ወቅትን እንደሚጎዳ ለማረጋገጥ አሁን ብዙ አትቸገሩም፡፡ ከቁጥር 1 ጀምሮ እስከ ቁጥር 54 ድረስ ያሉትን። ቪሲዲ ( VCD )የሚታዩትን በሰው ህይወት ውስጥ ያሉትን የጉዳት መንገዶችን መገንዘብ አያስቸግረንም፡፡ ስለዚህ ይሄ የተሰወረ አሰራር ነው፡፡ የመናፍስት አሰራር ነው፡፡ ዓለማችን ይህንን በግልፅም በስዉርም የመሄጃ መንገድና የመኖርያም አካል አድርጎት እየተገነዘብን ነው ያለነው፡፡ ስለዚህ የመጀመርያው ኃጢያት ለክፉ መንፈስ ከመዳረግ በፊት ክፉዉን ሐሳብ በህይወታችን ውስጥ እንደ አንድ ራሱን የቻለ ጊዜ፣ ዘመን፣ ወቅትን ማምለጫ አድርገን ከተጠቀምንበት የተሰወረ ኃጢያት ከውስጣችን ጀምረዋል ማለት ነው፡፡
=> ከመንፈሳዊ እስከ ዓለማዊ ድረስ ያለዉ ውድቀት ተጠናክሮ አንዱ ላንዱ የጠላትነት ስሜትን በፍቅር ምትክ ጠብን፣ በሠላም ምትክ ጦርነትን፣ በቦጎነትን ምትክ አረመኔነትን ለሰው ልጅ እየሰጠን ያለን ፍጡሮች ሆነናል፡፡ ስለዚህ‹‹ከተሰወረ ኃጢያት አንጻኝ። የድፍረት ኃጢያት እንዳይገዛኝ ባሪያህን ጠብቅ፤ የዚያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ፥ ከታላቁም ኃጢአት እነጻለሁ። አቤቱ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።›› በእውነት እንዲህ እያልን ልንጸልይ ያስፈልጋል፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
=> "ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ" የሚሉ፥ የውጊያውን ዓለም በግልጽ የሚያስተምሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላትን በመዘንጋት፥ የተዋጊዎቹን ስምና ሥራ አታንሱ፤ የውጊያ ጥበባቸውን አታጋልጡ፤ ጽድቅ ጽድቁን ብቻ አውጉ ማለት እየኖርነው ያለው ክፋትና ሁለገብ ዓመፅ እየጋሸበ እንዲሄድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል፤ አድርጓልም:: (ዘጸ.15፥3) ፤ (መዝ.23፥1) ፤ (2ኛ ዜና.20፥15) ፤ (ኤፌ.6፥12) ፤ (ያዕ.4፥7)
=> ምንም እንኳ ይህንን ብልም፥ ወዲህም አንድ ነገር ይረ'ዳኛል:: ይኸውም ክፉው መንፈስ በመጀመሪያ ወደ ሰው ልጆች ለጥፋት የመጣበትን ጊዜ ያሳስበኛል:: መጽሐፈ ሄኖክ "ጋርድኤል" እያለ የሚጠራው መንፈስ፥ ወደ አዳምና ሔዋን ሲሄድ ማንነቱን በጣም በተዋበች የእባብ አካል ውስጥ ደብቆ እንደነበረ በብዙዎቻችን ይታወቃል:: ይሄም ከዕውቅና ውጪ ተሸሽጎ የመንቀሳቀሱ ነገር ከቀድሞውም ጀምሮ የነበረ መሠረታዊ ስልቱ እንደሆነ ያስረዳል:: በእርግጥስ ሔዋን እያነጋገራት ያለው በጥላቻና በቅናት የተሞላ ፍጡር መሆኑን ብታውቅ ኖሮ የሚለውን ለማድመጥ ዕድል ትሰጠዋለችን?
=> አሁንም ይኸው ነገር ነው ያለው:: በሥጋ ሕዋስ አለመታወቁና አለመለየቱን ተጠቅሞ እያጠፋ ያለው የዲያቢሎስ ሠራዊት፥ ስለ እርሱ የሚታወቅበትን መንፈሳዊ ትምህርት በተለያየ ዓይነት ጫና መከላከሉ የሚጠበቅ ነው:: ተከላካዮቹ የእግዚአብሔርን ቃል የሚጠቅሱና መልካም አድርገው የሚናገሩ ቢሆኑ አይደንቅም:: ምክንያቱም ይህንንስ ነገር ከመድኃኒታችን የምድረ በዳ ፈተና ተሞክሮ ልንወስድ ይገባናልና ነው:: (ማቴ. 4፥1-7)
=> ለመሆኑ "ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል" የምትለው ዝነኛ ጥቅስ ስለ የትኛው ዕውቀት ነው የምታነሣው? ስለ ቅዱስ ቅዱሱ ብቻ ያልናት የአስተምህሮ መንገድማ ውጤቱ ይኸው "የሕዝብ" መጥፋት ሆኖ ተደመደመደ እኮ:: መንፈሳዊ ትምህርቶች መሰጠት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ እሰከ ዛሬ ድረስ ቃሉ ያለማቋረጥ ይሰበካል:: ብዙ ዓይነት መምህራንና መጽሐፍት ሕዝቡ ላይ ይፈራረቁበታል:: ካልንስ እንደዚህ ዘመን ቃለ እግዚአብሔር ተስፋፍቶ የተላለፈበት ጊዜም የለ:: ሁለንተናዊ ጥፋቱ ግን ከመቀነስ ይልቅ ሲጨመር ነው የሚስተዋለው:: ምንድነው?
=> ልድገመው:: እግዚአብሔር ባወቀ ስለ ክፉዎቹ መናፍስት ነገር ንቁ የሚባለው ስለ ዲያቢሎስ የማውራት ሱስ ኖሮብን አይደለም:: ይልቁኑ ሕይወትን እስከማሳጣት የሚደረሰው ይህ የአስተምህሮ መንገድ፥ ከስድብ አሊያ ነቀፋ ውጪ ለሥጋ የሚያስቀረው ትርፍ የለውምና ስለ ዝናም ስንል አይደለም:: ክፉዎቹ እጅግ ጨካኝና ሰላም የለሽ ከመሆናቸው የተነሣ፥ ስለነርሱ ባይነሣ በወደድን ነበር:: አሰቃቂ ፍላጎትና ድርጊታቸው ለተፈጥሮአችን የማይመች ከመሆኑ አንጻር ብቻ ስለነሱ መረጃ ባለመለዋወጥ የሚሸሹን ቢሆን ምንኛ ደግ ነበር?
=> ግና ባላጋራዎቻችን ግትሮች ናቸው:: ሳልሳዊ አቡነ ሺኖዳ ዲያቢሎስን "መንቻካ" ሲሉ በመጽሐፋቸው ይጠሩታል:: (የዲያቢሎስ ውጊያዎች) እኛ ስለነሱ ስለማናወራ እነርሱ እኛን መፈታተናቸውን አያቆሙም:: አስታወስነውም አላስታወስነውም ሰይጣን ጠላቱ ስለመሆናችን [ለሰኮንድ] አይዘነጋውም:: አውቅነውም አላውቅነውም እኛን ከማጥፋት ከቶውኑ ወደኋላ አይልም:: ክርስቶስን ስንኳ ለመጣል የተነሣሣ ደፋር ልቡ በእኛ ቀኑን ሁሉ ለበጎ ነገር ልል ዘሊል ሆነን በምንውለው ላይማ እንዴት አይበረታታ?
=> በመሆኑ ወደድንም ጠላንም ክፉ ሥራውን እናስቆም ዘንድ፣ የሚጠንስሳቸው ተንኮሎቹን እንረዳ ዘንድ፣ ለመጣል የሚጠቀማቸውን ስልቶች እናውቅ ዘንድ፣ ለሕዋሳቶቻችን የሚያጋራውን ሁሉ እንለይ ዘንድ፣ ኃጢአት የሚስብበትንና የሚመራበትን መንገድ እንርቅ ዘንድ፣ በእግዚአብሔር ለመታመንና ለመደገፍ እንጥር ዘንድ፣ የቅዱሳኑን ሕይወት አብነትና ልምድ እናደርግ ዘንድ፣ ክፉውን ባለማወቅ በክፉው አንጠፋ ዘንድ የዲያቢሎስን ውጊያ እንማማራለን:: (የኤፌሶኑ መልእክት "መጋደላችን" ብሎ የሚጀምረው አንቀጽ ማለት "ገድል" ማለት ነው:: የቅዱሳን ገድል የሚተርከው ስለሌላ ስለምንም ሳይሆን ከክፋት ጋር ስላደረጉት መንፈሳዊ መጋደል ነው)
=> እንዲህ ሲባል ስለ መናፍስቱ ብቻ ስናመላልስ እንከርማለን ማለት አይደለም:: እንዲህ የሚያደርጉም ሲኖሩ ሊታረሙ ይገባል:: ባይሆን የውጊያው ትምህርት፥ ቅድስናን እንዲሠራ ርኩሰትን እንዲገራ ተደርጎ መሰጠት አለበት:: ብቻም ሳይሆን ያልበረቱ ምእመናን ትምህርቱን ለሥጋ ጥቅምና መድረሻ እንዳይገለገሉት በጥንቃቄ መተላለፍ አለበት:: ሰልፉ የእግዚአብሔር ነው ከተባለ፥ ድሉም የእግዚአብሔር እንደሆነ በአብክሮ ማሳወቅ ይገባልና::
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ጥያቄ 6፡ ቤተ ክርስቲያን ደረቅ ሐዲስ እያለች የምታስተምረው የብሉይ ኪዳን ክፍል የሆነ መጽሐፍ የቱ ነው?
ዕድሏንና ውበቷን በመናፍስት የተቀማች እናት! || አጋንንትን የሚያስገቡ እንጂ የማያስወጡ አገልጋዮች || የራሔሎ መንፈስ ድብቁ ሴራ #ethiopia #ebstv https://youtu.be/9jGPvsxxG40
መናፍስት የእምነት ኃይላችንን ለማዳከም ሦስት ቦታ ላይ ያደባሉ የእምነት ኃይላችን በአጋንንት ስፈተን የእምነት ኃይል ምንድነው? #ethiopia 😭😱🔥
https://youtu.be/BjgcRrvt8m0
በጸሎታችን ውስጥ ልካተቱ የሚገቡ ነገሮች | ጸሎታችን ልማዳዊ እንዳይሆን ይሄንን እናድርግ | በጸሎት ሰዓት ተመስጦ እንድኖረን | ጸሎትና የአጋንንቱ ፈተና 😱😭
https://youtu.be/ho2BJSK-Y8s
ጉድ! ለሀብት ብሎ ልጁን ለአጋንንት የሰዋ አባት! || ለገንዘብ ሲባል ራስን ለሰይጣን አሳልፎ መስጠት || የዘር የተዋርሶ መንፈሶች ፈተና #ethiopia 😱😱 https://youtu.be/CRw4c1GiiXI
=> አስተውሉ! ዘመን ዘመንን እየተካ የዓለም ጊዜ ወደፊት ወደ ማብቂያው ሰዓት በሚሄድበት የተፈጥሮ ዑደት፤ የሰው ልጆች ለክፉው ነገር አንድ ሆነው በመተባበር የሚገነቡት ቅድስናን የሚነካ ግንብ እንዲህ የሚለው አሳዛኝ ቃል ሁላችን ላይ እንዲታይ አሰገድዶአል፡፡ "ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል" (ወደ ሮሜ ሰዎች 3፥11) 'ሰማይ ጠቀስ' የሆኑ ፎቆችን፤ እስከ 'ሰማይ ደመና የሚደርሱ' በራሪ ቁሶችን፤ 'ሰማይን አልፈው የሚሄዱ" መንኮራኩሮችን በአንድ የቴክሎኖጂ ስምምነት የገነባው የኛ ዘመን፤ አንድ ወቅት ላይ "ከጠፈር ከፍታ ሆነን ወደ እግዚአብሔር ድንጋይ እንወርውር" ያለበትን የትዕቢት ርዝመት ስናስተውል በሰናዖር ሊቆም የነበረው 'እስከ ሰማይ የሚደርስ' ግንብ መልኩንና ቅርጹን ለውጦ መገንባቱ እንደቀጠለ ያስረዳናል፡፡
=> "ኑ፥ ጡብ እንሥራ" አይደለም ያሉት? ወደ ትውልዳችን ሁኔታ መለስ ብለን ስናስብ፤ "ኑ፥ ጸሎት እናድርስ፣ ኑ፥ ለፈጣሪያችን እንሰግድ፣ ኑ፥ ሥጋና ደሙን እንቀበል፣ ኑ፥ ወገኖቻችንን እናግዝ" የተባባልንበት የቅድስና አንድነት የለም፡፡ ይልቅ በአንጻሩ "ኑ፥ እንጠጣ፣ ኑ፥ እንጫጫስ፣ ኑ፥ እንዘሙት፣ ኑ፥ በዘር እንከፋፈል፣ ኑ፥ ሰውን እናሳድድ፣ ኑ፥ የብሔር ስማችንን እናስጠራ" ብለን ክፉውን ለመገንባት የተሰባሰብንበት ዘመን፤ ክፉ መንፈሶች ጀምረውት የነበረው በሰው እጅ ክፉን የመገንባት ውጥን በይበልጡን ቀጥሎ፤ "ዓለሙ በመላው በክፋት እንደተያዘ እናውቃለን" ያሉት የብርሃን ሐዋሪያት የጸዳል-ቃል በጨለማ ገመድ (በመናፍስት መናበብ) የተሳሰርንበትን ጥቁር ክፋት የሚገለጥ ሊሆን ተጽፎአል፡፡ እንንቃ!
=> አገልግሎታችን እንደቀጠለ ነው! የፊታችን እሁድ ጥቅምት /17/2017 ዓ.ም በሰሚት ዋሻ መካነ ሕይወት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከቅዳሴ በኃላ አገልግሎቱ ይቀጥላል!
=> የቤተክርስቲያኑ አድራሻ፤ ሳሚት ኮንዶሚኒየም 2ተኛ በር ወረድ ብሎ ከኢትዮ ቻይና ት/ቤት እንደ ሁለተኛ መንገድ አማራጭ ሰሚት ጤና ጣቢያ መግቢያ መሆኑን እየገለጽን ሼር በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
