HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 276
مشترکین
+524 ساعت
+117 روز
+3430 روز
آرشیو پست ها
ሰኔ ፭ /5/በዚችም ዕለት ደግሞ ቅዱስ ቢፋሞን ምስክር ሆነ። ይህ ቅዱስ ለዮሐንስ ዘሐራቅሊ የእናቱ ወንድም ልጅ ነበር ዮሐንስም ታሥሮ ሳለ ያገለግለው ነበር። ዮሐንስም ገድሉን በፈጸመ ጊዜ ሥጋውን ገነዘ በበድኑ ላይም እንዲህ ብሎ አለቀሰ ከእግዚአብሔር የተለየሁ ሁኜ ብቻዬን እንዴት ትተወኛለህ ከቅዱስ ዮሐንስ ሥጋም እንዲህ የሚል ቃል ወጣ ወዳጄ ቢፋሞን ከእኔ ጋራ መኖርን ከፈለግህ ፈጥነህ ወደ መኰንኑ ሒደህ ክብርይግባውና በክርስቶስ ታመን ነገም ወደ እኔ ትመጣለህ። ይህንንም ሰምቶ የዮሐንስን ሥጋውን ቀበረ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ሔደ ። ክብርይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እየታመነ የረከሱ ጣዖታቱን ሰደበ። መኰንኑም ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጠ የምስክርነትንም አክሊል ተቀበለ ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ዕለት ደግሞ የመርቆሬዎስና የመቃርስ የይስሐቅና የዕብሎን የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው። የአብላርዮስም የምስክርነቱ መታሰቢያ ነው ። እግዚአብሔርበጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን። በዚች ዕለት ደግሞ ቅዱስ መቃርስ ምስጋና ይግባውና በጌታችን ስም በባሕር ውስጥ በመስጠም አረፈ። በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
+++ ልበ አምላክ ዳዊት “ምህረኒ እግዚኦ ለገቢረ ፈቃድከ እስመ አምላኪየ አንተ ወመንፈስከ ቅዱስ ይምርሐኒ በምድረ ጽድቅ፤ አንተ አምላኬ ነህና ፈቃድህን ለማድረግ አስተምረኝ፣ ቅዱስ መንፈስህም በጽድቅ ምድር ይምራኝ በማለት የጸለየው ለዚህ ነው:: /መዝ ፻ ፵ ፪፥፲ እንዲሁም ይኸው አባታችን ዳዊት ከፍልስጥኤማውያን ጋር በነበረበት ውጊያ ወደ ጦርነት ከመሄዱ በፊት “ዳዊትም፦ ወደ ፍልስጥኤማውያን ልውጣን? በእጄስ አሳልፈህ ትሰጣቸዋለህን?” ብሎ እግዚአብሔርን ይጠይቅ ነበር:: እግዚአብሔርም ይመልስለት ነበር፡- “እግዚአብሔርም ዳዊትን፦ ፍልስጥኤማውያንን በእርግጥ በእጅህ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁና ውጣ አለው::'' /፪ ሳሙ ፭፥፲ ፱/ ዳዊት በጦርነት ጊዜ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ነገሩ እግዚአብሔርን ሳይጠይቅ አያደርግም ነበር:: “ከዚያም በኋላ ዳዊት፦ ከይሁዳ ከተሞች ወደ አንዲቱ ልውጣን? ብሎ እግዚአብሔርን ጠየቀ እግዚአብሔርም፦ ውጣ አለው:: ዳዊትም ወዴት ልውጣ? አለ እርሱም፦ ወደ ኬብሮን ውጣ አለው::” /፪ ሳሙ፪፥ ፩/
+++ እግዚአብሔር ፈቃዱን ለእኛ የሚገልጥበትን ጊዜና ሁኔታ (መንገድ)እርሱ በሚወድደውና በሚፈቅደው መንገድ እንዲያደርገው ለእርሱ ልንተውለት ይገባል እንጂ እኛ መወሰንና መምረጥ የለብንም፡፡ እኛ እንዲህ ቢሆን የምንለው መንገድ መኖሩ ስሕተት ነው ማለት ሳይሆን፤ የግድ በዚያ መንገድ ካልሆነ ማለት ግን ተገቢ አለመሆኑን መዘንጋት አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ለእኛ የሚገልጥልን ሕሊናችንና ዐቅማችን ያን ለመቀበል ዝግጁ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔርን በሕልም ወይም በራእይ ወይም እንዲህ ባለ ሁኔታ ፈቃድህን ግለጥልኝ ብሎ አስቀድሞ መወሰን አይገባም፡፡ በምን ዓይነት መንገድ ቢገልጥልን እንደሚጠቅመን እርሱ ስለሚያውቅ ለእርሱ ልንተውለት ይገባል፡፡
+++ ለነገሮች ጊዜ መስጠት አጅግ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ በጊዜ ሒደት ውስጥ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነውንና ያልሆነውን ፍንትው አድርጎ መለየት ይቻላል፡፡ አንድ ጉዳይ የሚያስጨንቀን ወይም ፈቃደ እግዚአብሔር መሆን አለመሆኑ ግራ አጋብቶን ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ ስንሆን ከስሜታዊነትና ወደፊት በጊዜ የሚገለጠውን ነገር አስቀድመን ማወቅ ካለመቻላችን የተነሣ እንጨነቃለን፡፡ እየቆየ ሲሄድ ግን አእምሯችን የተሻለ እየተገነዘበው፣ እውነታው ፍንትው ብሎ እየተገለጠ ስለሚሄድ ጉዳዩን በአግባቡ መረዳትና መለየት በእጅጉ ቀላል እየሆነልን ይመጣል፡፡ እንዲሁም እግዚአብሔር ወዲያውኑ እውነቱን ቢነግረን አአምሯችን ሊቀበለው የሚከብደውን ነገር ቀስበቀስ ሲገልጥልን ለመቀበል የነበረው ክብደት ይቀንሳል፡፡ ውስጣችን እየተረዳውና እየተገነዘበው ይሔዳል፡፡ በዚህም መጀመሪያውኑ ብናውቀው ሊደርስብን ይችል ከነበረው ድንጋጤና የሕሊና መታወክ ያድነናል፡፡ እግዚአብሔር በሕይወታችን ውስጥ በሒደት የሚገጥሙንን ነገሮች
በአንድ ጊዜ የማይገልጥልን አንዱ ምክንያት ይኽ ነው፡፡ ስለዚህ እኛ ባልነው ጊዜ ሳይሆን ለእኛ በሚጠቅመን ሁኔታና ጊዜ ፈቃዱን እንዲያስታውቀን እግዚአብሔርን በትዕግሥትና በትሕትና ሆኖ መጠበቅ ተገቢ ነው፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
#ለምትወዱትና_እንድቀየርላችሁ_ለምትፈልጉት_ሰው_ሁሉ_ይኼንን_አድርሱ!! ሰይጣንና አጋንንት በቀኛችን ሲቆም የሚከሰተው ይኼ ነው!! የአቡና የአኬ መልስ ለጆርዲ! https://youtu.be/qcf0-8APBSw?si=RJ3r5LM4bMvmJOYR
ሰኔ ፬/4/በዚችም ቀን የአርቃድዮስ የእኅቱ የዲሙናስያ የግብጻውያኑ የአሞኒና የሚናስ የንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ጭፍሮችም የገድላቸው ፍጻሜ ሆነ። እሊህን ቅዱሳን በእሳት ምድጃ ውስጥ ከአባ ብሶይ ጋራ በጨመሩዋቸው ጊዜ የመላእክት አለቃ ገብርኤል መጥቶ ከነበልባሉ መካከል አወጣቸው። ወደ ንጉሡም ደርሰው ረገሙት እንዲህም አሉት የምስክርነት ሞት ፍጻሜያችንን የማትጽፍ ከዕለት ወደ ዕለት ለምን ትከፋለህ። ንጉሡም ሰምቶ ተቆጣ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡና ሥጋቸውን በእሳት እንዲያቃጥሉ አዘዘ እንደዚህም የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ፈጽመው የክብር አክሊልን ተቀበሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
#ግልጽ_በመሆናችሁ_በቻ_የተጎዳችሁ_ይኼንን_በደንብ_አዳምጡ! ባመኑት ሰዎች የሚጉዱ ሰዎች እንዲህ አይነት ናቸው! ንጹሕ ፍቅር እንዴት ይገለጻል? #ethiopia https://youtu.be/pF2cTOzNT_Y
#በሰዎች_ሕይወት_የምንቀናውና_ምቀኛ_የምንሆነው_በዚህ_ምክንያት_ነው!! በአጋንንት የባርነት ቀንበር ላለመያዝ ይሄንን አድርጉ! ዕድላችን በኮከብ ቆጠራ ሲወሰን! https://youtu.be/bJGGAGdZ6QE
+++ አንድ ሊቅ “ጸሎትና ጾም በሌለበት ሰው ውስጥ ሰይጣን አለ ብለን ማሰብ እንችላለንን?” ብሎ ይጠይቅና ሲመልስ “አዎ አጋንንት ወደ ሰው ውስጥ ሲገቡ መግባታቸውን በገሃድ አያሳውቁም፡ መግባታቸው እንዳይታወቅባቸው ለማድረግ ሲሉ ራሳቸውን ይደብቃሉ እንጂ፡ ሆኖም የገቡበትን ያን ሰጡክፉውን ነገር ሁሉ በስውር ከውስጥ ያስተምሩታል፡ መልካም የሆነውን ነገር ደግሞ ያስጠሉታል" ያ ሰው የሚፈጽመው የጠላትን ፈቃድ ሆኖ ሳለ እርሱ ግን እርሱ ራሱ እያደረገው እንደሆነ ያስባል'' ጠላት ትቶህ የሚወጣውና ሌላ መመለሻ አጋጣሚ እሰኪያገኝ ድረስ ከአንተ ርቆ የሚጠባበቀው ጸሎትና ጾምን ስትታጠቅ ብቻ ነው፡፡ ጸሎትና ጾም ከተተው ግን እንደገና ተመልሶ ይመጣል" ይላል፡፡
+++ ስለሆነም ጾምና ጸሎት በተተውበትና በሌለበት ሕይወት ዘንድ ኦርቶዶክሳዊነት ሽታውም አለ ማለት አይቻልም። ጾም የሌለበት ሰውነት የአጋንንት መሥሪያ ቤት እንጂ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አይሆንም፡፡ በተሐድሶዎችና በመሰሎቻቸው እያደረ “ዘመነኛ” ወይም “ሊበራል” በሚል ሽፋን ሰይጣንየሚሰብከውን “ጾም የለሽ” “ክርስትና” ወይም “እምነት” ልብ እንበል፡ እንወቅበትም! ኦርቶዶክሳዊነት በባሕርዩ ትህርምታዊ (Ascetic) ነው፡፡ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ሕዝቡንም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጠርቶ እንዲህ አላቸው፦ በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ" ያለው ለዚህ ነው፡፡ (ማር. 8፡34) ሆድን ወድዶ ጾምን ጠልቶ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር መሆን አይቻልም፡፡ እንዲህ ያሉት “ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ፣ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ፤ መጨረሻቸው ጥፋት ነው፣ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፣ ክብራቸው በነውራቸው ነው፣ አሳባቸው ምድራዊ ነው" የተባሉት ናቸው። (ፊል. 3፡18-19)
ከመድሎተ ጽድቅ መፅሃፍ የተወሰደ (በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተዘጋጄ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ሰኔ ፫ /3/በዚችም ቀን ደግሞ ኤላርዮስ የሚባል ኤጲስቆጶስ ሰማዕት ሆኖ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከሀዲውን ንጉሥ ዮላኪዮስን ጣዖታትን ስለማምለኩ ይገሥጸውና ይመክረው ነበር ንጉሥ ዮላኪዮስም አይሁድ የሰቀሉትን ባለማምለኬ አንተ ከሀዲ ትለኛለህ እነሆ አሁን እኔ አንተን ከሥቃይ ጽናት የተነሣ ያን የተሰቀለውን አምልኮቱን አስተውኻለሁ አለው። ከዚህ በኋላም ከመኳንንቶቹ ለአንዱ መኰንን ሰጥቶ ባለመራራት ያለማቋረጥ ሁልጊዜ እንዲአሠቃየው አዘዘው መኰንኑም ወስዶ በየራሱ በሆነ ሥቃይ አንዲት ቀን እንኳ ከቶ ሳያቋርጥ ሁልጊዜ እያሠቃየው አንድ ዓመት ሙሉ ኖረ። በዓመቱም ፍጻሜ በእሳት ውስጥ ጣሉት እርሱም ከእሳት መካከል ቆሞ እግዚአብሔርን ፈጽሞ እያመሰገነ ጸለየ ስለዚህችም ምልክት ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ብዙዎች አምነው በሰማዕትነት ሞቱ። ከዚህም በኋላ ከአታክልት መካከል እንደ ሚወጣ ሆኖ ከእሳት አወጡት። መኰንኑም ከማሠቃየት በደከመ ጊዜ በእርሱ ላይም የሚያደርገውን በእጣ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዝዞ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምሥጋና ይሁን እኛንም በዚህ ተጋዳይ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
በዓይነጥላ መንፈስ ባሕሪይ ውስጥ የአዳልሞቴ መንፈስ መገለጥና ምልክቶቹ! ነፍሳችንን ነጻ ለማውጣት አሁኑኑ ይኼንን እናድርግ!! ፍቅር ከስሜት በላይ ነውና አስተውሉ!! https://youtu.be/qOYT8HL0zf8?si=ArHpAv8iwG-0aLoR
መምህር ተስፋዬ ይህችን እናት እንዴት አስተምሮና መክሮ እንደቀየራት ተመልከቱ! Haile Gebriel Reacts19 #የቡና_ካዳሚዋ_እናት_የመናፍስት_ፈተና!! https://youtu.be/X25xtL7BkQY
ሰኔ ፪ /2/በዚች ቀን የመጥምቁ የቅዱስ ዮሐንስ ሥጋ የቀናተኛው ኤልያስ ደቀ መዝሙር ከሆነው ከነቢዩ ኤልሳዕ ሥጋ ጋር በአንድነት ተገኘ። ከሀዲው ንጉሥ ዑልያኖስ የጥጦስ ልጅ አስባስያኖስ ከአፈረሰው በኋላ በዘመኑ በኢየሩሳሌም የአይሁድ ምኵራባቸውን ሊሠራ ቢሞክርም ሦስት ጊዜ ፈረሰበት። አይሁድም እንዲህ አሉት የደጋግ ክርስቲያኖች ዐፅሞቻቸው በዚህ ቦታ ስለሚኖሩ ከዚህ ካላወጣሃቸውና ካላቃጠልኻቸው በዚህ ቦታ ምኵራብ አይሠራም። በዚያንም ጊዜ የቅዱሳንን ዐፅሞቻቸውን አውጥተው በእሳት እንዲአቃጥሉት አዘዘ በአፈለሱም ጊዜ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስንና የነቢዩ ኤልሳዕን ሥጋቸውን አግኝተው በእሳት ሊአቃጥሉ ፈለጉ ምእመናንም መጥተው ለወታደሮች ብዙ ገንዘብ ሰጡ ንጉሡም ሰምቶ እንዳያጠፋቸው በዚያች አገር እንዳያስቀሩ ከአማሏቸው በኋላ የቅዱሳንን ሥጋ ወደ እስክንድርያ ከአባ አትናቴዎስ አደረሱ። እሱም አክብሮ ተቀበላቸው። በአንዲት ዕለትም አባ አትናቴዎስ በአባቶቹ ቦታዎች ላይ ስለ ጸሐፊው ቴዎፍሎስም አብሮት ሳለ እግዚአብሔር መልካም ዘመን ቢሰጠኝ ሥጋቸውን በውስጧ አኖር ዘንድ ለቅዱሳን መጥምቁ ዮሐንስና ለነቢዩ ኤልሳዕ በስማቸው በዚህ ቦታ ቤተ ክርስቲያን እሠራለሁ አለ ቴዎፍሎስም ሰማው። አባ ቴዎፍሎስም በተሾመ ጊዜ አባ አትናቴዎስ የተናገረውን ያንን ቃል አስቦ ቤተ ክርስቲያን ሠራ። ከርሱ ጋራም ብዙዎች ካህናትንና የክርስቲያን ወገኖችን ይዞ የቅዱሳን የመጥምቁ ዮሐንስና የነቢዩ ኤልሳዕ ሥጋቸው ወዳለበት ሔደ በታላቅ ክብርም ተሸክመው አምጥተው ወደ ቤተ ክርስቲያን አስገቡ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የነገረን መደመጥ ያለበት አስገራሚው እውነት!! እባካችሁ ወላጆች ሴት ልጆቻችሁን ጠብቁ ተጠንቀቁም! ቤተ ክርስቲያን አልባው ክርስትና በዘመናችን! https://youtu.be/pwZ4_IJGYkw?si=x7xRCLihC3U0kcGt
ይድረስ ለዶ/ር ፍስሐና ለፓስተር ቢንያም ሽታዬ የሰዎች ከአጋንንት መፈታት ለሚያናድዳችሁ! መናፍስት ከማሕጸን ጀምሮ እንዴት ይወለዳል ላላችሁት! #ethiopia https://youtu.be/FCBHlLqPzaQ
«ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።» (1ኛ.ቆሮ.10፡13)
«ነገ (እሑድ) የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልደት [በዓለ ጰራቅሊጦስ] መንፈስ ቅዱስን ነው። ሰኞ ጾመ ሐዋርያት ይገባል። ረቡዕ ደግሞ ጾመ ድኅነት ይጀመራል።
በሰሞንኛ ጉዳይ ሳንጠመድ የነፍስ ስንቅ እንያዝ! እንበርታ!
ግንቦት ፴ /30/በዚችም ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሐዋርያ ቆሮስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ጌታችን በሚያስተምርበት ወራት ሦስት ዓመት አገልግሎታል ከዕርገቱ በኋላም ሐዋርያትን አገልግሏቸዋል ከእሳቸውም ጋራ መንፈስ ቅዱስን ተቀበለ። ከዚህም በኋላ ከሐዋርያ ጳውሎስ ጋራ በመሆን መልእክቶቹንም ወደ ብዙ አገሮች ተሸክሞ በመውሰድ አገለገለው። ከአይሁድና ከአሕዛብም ብዙዎቹን አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ከዚህ በኋላም በምሥራቅ ወዳሉ አገሮች ሔደ ከመኵራቦችም ብዙ መከራ ደርሶበት አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
በቁርባን ተጋበተው ያለቁርባን የሚኖሩ ሰዎች የሚገጥሟቸው ፈተናዎች!! የዘመኑ ጋብቻና ሥርዓት አልባ ጉዟችን! #hailegebrielreacts19
https://youtu.be/T05u1g28pkY?si=L4BCOkrwLxe5t4px
+9
🙏🙏🙏 ይድረስ የሰው መዳን ለማያስደስታቸሁ፣ ይድረስ ሰዎች ከአጋንንት ስላቀቁ ለምትናደዱ በሙሉ። አባታችን ቀሲስ ሄኖክ ወልደማሪያም ዛሬ አርብ JUN 6 በካናዳ ቶሮንቶ ኦንታርዮ ካምብሪጅ ከተማ የነበራቸው የትምህርተ ወንጌል፣ የቅብዓ ቅዱስ እና የጸበል ጥምቀት አገልግሎት በጥቂቱ ይሄንን ይመስላል።
አገልግሎቱ ነገ JUN 7, JUN 8 ቅዳሜ እና እሑድ ይቀጥላል!
ጠላት ይፈር፤ ይቃጠል!
የቁራ እንቁላል እንዲያቀርቡ በደብተራ የተጠየቁ ካዳሚዎችና መጨረሻቸው! የመናፍስቱን ሴራና ጥፋት እወቁበት! https://youtu.be/0WuBdKAUx10?si=0EmHtDS5rZ9uvj1d
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
