HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
前往频道在 Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
显示更多2 278
订阅者
+324 小时
+137 天
+3830 天
帖子存档
#ከወንድም_ከሴትም_ጋር_እተኛለሁ_የዘመኑ_ሰዎች_አሳፋሪ_ንግግር! የሉሲፈር መንፈስ የአያያዝ ስልቱና ጥፋቱ! መተት በጸጉራችን ሲደረግ ይኼንን ምልክት ታያላችሁ!
https://youtu.be/b_wXcMJCtew?si=jVknpCOOxw4CjN6I
ሰኔ ፰ /8/በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው። እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው። ይህም እንዲህ ነው ለጻድቁ ዮሴፍ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ተገልጾለት ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ አገር ሒድ አለው። ዮሴፍም ነቅቶ ተነሣ ክብር ይግባውና ሕፃኑን ጌታችንን እናቱንና እኅቷ ሰሎሜን ይዞ ወደ ግብጽ አገር ሔዱ በዚያም በውስጧ ባሉ በብዙ አገሮች እየዞሩ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ኖሩ። ሄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሁለተኛ ተገለጠለት ወደ እስራኤልም አገር ሕፃኑንና እናቱን ይዞ እንዲመለስ አዘዘው። በሚመለሱም ጊዜ ወደ መዓልቃ ደረሱ ከዚያም ወደ መጣርያ አገር ደረሱ ይቺም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውኃ ያፈለቀባትና የመታጠቢያ ቦታ የሆነች ናት እርሷም እስከ ዛሬ አለች ሰዎችም ከአገሩ ሁሉ ከየነገዱ ሁሉ መጥተው አምላክን ወደ ወለደችና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ይለምናሉ ከተባረከውም የውኃ ምንጭ ታጥበው ከደዌያቸው ሁሉ ይድናሉ በዛሬዪቱ ቀን ከከበረች ቤተ ክርስቲያንም ይባረካሉ። እርሷን እመቤታችንን ለመረጣትና ለወደዳት በሥጋም እናቱ ላደረጋት ስለርሷም ዘመድ ለሆነንና ወደርሱ ላቀረበን ወራሾቹም ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
አሳፋሪው የቢንያም ሽታዬ ንግግርና ዳግም ቁልቁል የመውረድ ጉዳይ!!
https://youtu.be/c8eawHLq8is?si=T27YnVCtA-Aw8Y2o
#ቤታችን_በአጋንንት_የመያዙና_የመጠቃቱ_ምልክቶችና_መፍትሔዎቹ!! ቤታችን ጸሎትና ስግደት ማድረግ ለምን ከበደን? #hailegebrielreacts19 #ጸሎት https://youtu.be/K08lLCp4ZQM
ሰኔ ፯ /7/አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሰባት በዚች ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተከፈተችበትና የከበረችበት ነው። እርሷም ዌላ በሚባል አደባባይ ያለች ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ተዘግታ የኖረች ነበረች። ይኸውም በአንድ ሽህ ሃያ ዓመተ ሰማዕታት ነው። ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ሰው ለሆነ ሕይወትና መድኃኒት አድርጎ እርሷን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
በመዝሙረ ዳዊት ጸሎት በውሻ የተደገመባትን መተትና ክፉ መንፈስ ያሸነፈች ጀግና!! ከሰዎች ሥጦታ ስንቀበል ልናደርግ የሚገቡ ጥንቃቄዎች!! Haile Gebriel Reacts19 https://youtu.be/ROHsNWyRrNA?si=7AFVb2zfcYgc6cEo
#የሰውን_ልጅ_የክፋት_ጥግ_ተመልከቱ_ሕጻኗን_በመተት_አፍዝዘው_አደንግዘው_ቁራኛ_አደረጓት!! ፖርኖግራፊ በዓይን የሚገባ ርኩሰትና ክፋት! #የሮፍናን_ኮንሰርት! https://youtu.be/jq6tvRBnOO8
#የዕለቱ_ወንጌል_አንብቡት!
+++ አንተ ታናሽ መንጋ፥ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ። ያላችሁን ሽጡ ምጽዋትም ስጡ፤ ሌባ በማይቀርብበት ብልም በማያጠፋበት በሰማያት የማያልቅ መዝገብ የሚሆኑትን የማያረጁትንም ኮረጆዎች ለራሳችሁ አድርጉ፤ መዝገባችሁ ባለበት ልባችሁ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤ እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል። ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው። ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር። እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና። ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ምሳሌ ለእኛ ወይስ ደግሞ ለሁሉ ትናገራለህን? አለው። ጌታም አለ። እንኪያስ ምግባቸውን በጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው በቤተ ሰዎቹ ላይ የሚሾመው ታማኝና ልባም መጋቢ ማን ነው? ጌታው መጥቶ እንዲህ ሲያደርግ የሚያገኘው ያ ባሪያ ብፁዕ ነው። እውነት እላችኋለሁ፥ ባለው ሁሉ ላይ ይሾመዋል።
(የሉቃስ ወንጌል 12፡32-44)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«በመንገድ እየሄድህ ሳለ በድልድይ ስር ስታልፍ ድንገት ከላይ የሚንጠባጠብ የቆሸሸ ውኃ ቢነካህ ሁኔታው ሊያናድድህ ይችላል። ነገር ግን ያ ቦታ እንደሚያፈስ እያወቅህ ተመላልሰህበት ከበሰበስህ ግን ጥፋቱ የአንተ እንጂ የማንም አይደለም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው አንዳንዴ ልክ እንደዚያ ጠብታ ሰይጣን ወደ ኅሊናህ ሊያስገባ የሚሞክረው ነፍስህን የሚያቆሽሽ ክፉ ሐሳብ ይኖራል። አንዴ የነካህ ክፉ ሐሳብ ግን ተመላልሶ እንዲያቆሽሽህ ከፈቀድህ ተወቃሹ አንተ እንጂ ሰይጣን አይሆንም።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ሰኔ ፭ /5/በዚችም ዕለት ደግሞ ቅዱስ ቢፋሞን ምስክር ሆነ። ይህ ቅዱስ ለዮሐንስ ዘሐራቅሊ የእናቱ ወንድም ልጅ ነበር ዮሐንስም ታሥሮ ሳለ ያገለግለው ነበር። ዮሐንስም ገድሉን በፈጸመ ጊዜ ሥጋውን ገነዘ በበድኑ ላይም እንዲህ ብሎ አለቀሰ ከእግዚአብሔር የተለየሁ ሁኜ ብቻዬን እንዴት ትተወኛለህ ከቅዱስ ዮሐንስ ሥጋም እንዲህ የሚል ቃል ወጣ ወዳጄ ቢፋሞን ከእኔ ጋራ መኖርን ከፈለግህ ፈጥነህ ወደ መኰንኑ ሒደህ ክብርይግባውና በክርስቶስ ታመን ነገም ወደ እኔ ትመጣለህ። ይህንንም ሰምቶ የዮሐንስን ሥጋውን ቀበረ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ሔደ ። ክብርይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እየታመነ የረከሱ ጣዖታቱን ሰደበ። መኰንኑም ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጠ የምስክርነትንም አክሊል ተቀበለ ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ዕለት ደግሞ የመርቆሬዎስና የመቃርስ የይስሐቅና የዕብሎን የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው። የአብላርዮስም የምስክርነቱ መታሰቢያ ነው ። እግዚአብሔርበጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን። በዚች ዕለት ደግሞ ቅዱስ መቃርስ ምስጋና ይግባውና በጌታችን ስም በባሕር ውስጥ በመስጠም አረፈ። በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
+++ ልበ አምላክ ዳዊት “ምህረኒ እግዚኦ ለገቢረ ፈቃድከ እስመ አምላኪየ አንተ ወመንፈስከ ቅዱስ ይምርሐኒ በምድረ ጽድቅ፤ አንተ አምላኬ ነህና ፈቃድህን ለማድረግ አስተምረኝ፣ ቅዱስ መንፈስህም በጽድቅ ምድር ይምራኝ በማለት የጸለየው ለዚህ ነው:: /መዝ ፻ ፵ ፪፥፲ እንዲሁም ይኸው አባታችን ዳዊት ከፍልስጥኤማውያን ጋር በነበረበት ውጊያ ወደ ጦርነት ከመሄዱ በፊት “ዳዊትም፦ ወደ ፍልስጥኤማውያን ልውጣን? በእጄስ አሳልፈህ ትሰጣቸዋለህን?” ብሎ እግዚአብሔርን ይጠይቅ ነበር:: እግዚአብሔርም ይመልስለት ነበር፡- “እግዚአብሔርም ዳዊትን፦ ፍልስጥኤማውያንን በእርግጥ በእጅህ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁና ውጣ አለው::'' /፪ ሳሙ ፭፥፲ ፱/ ዳዊት በጦርነት ጊዜ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ነገሩ እግዚአብሔርን ሳይጠይቅ አያደርግም ነበር:: “ከዚያም በኋላ ዳዊት፦ ከይሁዳ ከተሞች ወደ አንዲቱ ልውጣን? ብሎ እግዚአብሔርን ጠየቀ እግዚአብሔርም፦ ውጣ አለው:: ዳዊትም ወዴት ልውጣ? አለ እርሱም፦ ወደ ኬብሮን ውጣ አለው::” /፪ ሳሙ፪፥ ፩/
+++ እግዚአብሔር ፈቃዱን ለእኛ የሚገልጥበትን ጊዜና ሁኔታ (መንገድ)እርሱ በሚወድደውና በሚፈቅደው መንገድ እንዲያደርገው ለእርሱ ልንተውለት ይገባል እንጂ እኛ መወሰንና መምረጥ የለብንም፡፡ እኛ እንዲህ ቢሆን የምንለው መንገድ መኖሩ ስሕተት ነው ማለት ሳይሆን፤ የግድ በዚያ መንገድ ካልሆነ ማለት ግን ተገቢ አለመሆኑን መዘንጋት አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ለእኛ የሚገልጥልን ሕሊናችንና ዐቅማችን ያን ለመቀበል ዝግጁ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔርን በሕልም ወይም በራእይ ወይም እንዲህ ባለ ሁኔታ ፈቃድህን ግለጥልኝ ብሎ አስቀድሞ መወሰን አይገባም፡፡ በምን ዓይነት መንገድ ቢገልጥልን እንደሚጠቅመን እርሱ ስለሚያውቅ ለእርሱ ልንተውለት ይገባል፡፡
+++ ለነገሮች ጊዜ መስጠት አጅግ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ በጊዜ ሒደት ውስጥ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነውንና ያልሆነውን ፍንትው አድርጎ መለየት ይቻላል፡፡ አንድ ጉዳይ የሚያስጨንቀን ወይም ፈቃደ እግዚአብሔር መሆን አለመሆኑ ግራ አጋብቶን ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ ስንሆን ከስሜታዊነትና ወደፊት በጊዜ የሚገለጠውን ነገር አስቀድመን ማወቅ ካለመቻላችን የተነሣ እንጨነቃለን፡፡ እየቆየ ሲሄድ ግን አእምሯችን የተሻለ እየተገነዘበው፣ እውነታው ፍንትው ብሎ እየተገለጠ ስለሚሄድ ጉዳዩን በአግባቡ መረዳትና መለየት በእጅጉ ቀላል እየሆነልን ይመጣል፡፡ እንዲሁም እግዚአብሔር ወዲያውኑ እውነቱን ቢነግረን አአምሯችን ሊቀበለው የሚከብደውን ነገር ቀስበቀስ ሲገልጥልን ለመቀበል የነበረው ክብደት ይቀንሳል፡፡ ውስጣችን እየተረዳውና እየተገነዘበው ይሔዳል፡፡ በዚህም መጀመሪያውኑ ብናውቀው ሊደርስብን ይችል ከነበረው ድንጋጤና የሕሊና መታወክ ያድነናል፡፡ እግዚአብሔር በሕይወታችን ውስጥ በሒደት የሚገጥሙንን ነገሮች
በአንድ ጊዜ የማይገልጥልን አንዱ ምክንያት ይኽ ነው፡፡ ስለዚህ እኛ ባልነው ጊዜ ሳይሆን ለእኛ በሚጠቅመን ሁኔታና ጊዜ ፈቃዱን እንዲያስታውቀን እግዚአብሔርን በትዕግሥትና በትሕትና ሆኖ መጠበቅ ተገቢ ነው፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
#ለምትወዱትና_እንድቀየርላችሁ_ለምትፈልጉት_ሰው_ሁሉ_ይኼንን_አድርሱ!! ሰይጣንና አጋንንት በቀኛችን ሲቆም የሚከሰተው ይኼ ነው!! የአቡና የአኬ መልስ ለጆርዲ! https://youtu.be/qcf0-8APBSw?si=RJ3r5LM4bMvmJOYR
ሰኔ ፬/4/በዚችም ቀን የአርቃድዮስ የእኅቱ የዲሙናስያ የግብጻውያኑ የአሞኒና የሚናስ የንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ጭፍሮችም የገድላቸው ፍጻሜ ሆነ። እሊህን ቅዱሳን በእሳት ምድጃ ውስጥ ከአባ ብሶይ ጋራ በጨመሩዋቸው ጊዜ የመላእክት አለቃ ገብርኤል መጥቶ ከነበልባሉ መካከል አወጣቸው። ወደ ንጉሡም ደርሰው ረገሙት እንዲህም አሉት የምስክርነት ሞት ፍጻሜያችንን የማትጽፍ ከዕለት ወደ ዕለት ለምን ትከፋለህ። ንጉሡም ሰምቶ ተቆጣ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡና ሥጋቸውን በእሳት እንዲያቃጥሉ አዘዘ እንደዚህም የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ፈጽመው የክብር አክሊልን ተቀበሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
#ግልጽ_በመሆናችሁ_በቻ_የተጎዳችሁ_ይኼንን_በደንብ_አዳምጡ! ባመኑት ሰዎች የሚጉዱ ሰዎች እንዲህ አይነት ናቸው! ንጹሕ ፍቅር እንዴት ይገለጻል? #ethiopia https://youtu.be/pF2cTOzNT_Y
#በሰዎች_ሕይወት_የምንቀናውና_ምቀኛ_የምንሆነው_በዚህ_ምክንያት_ነው!! በአጋንንት የባርነት ቀንበር ላለመያዝ ይሄንን አድርጉ! ዕድላችን በኮከብ ቆጠራ ሲወሰን! https://youtu.be/bJGGAGdZ6QE
+++ አንድ ሊቅ “ጸሎትና ጾም በሌለበት ሰው ውስጥ ሰይጣን አለ ብለን ማሰብ እንችላለንን?” ብሎ ይጠይቅና ሲመልስ “አዎ አጋንንት ወደ ሰው ውስጥ ሲገቡ መግባታቸውን በገሃድ አያሳውቁም፡ መግባታቸው እንዳይታወቅባቸው ለማድረግ ሲሉ ራሳቸውን ይደብቃሉ እንጂ፡ ሆኖም የገቡበትን ያን ሰጡክፉውን ነገር ሁሉ በስውር ከውስጥ ያስተምሩታል፡ መልካም የሆነውን ነገር ደግሞ ያስጠሉታል" ያ ሰው የሚፈጽመው የጠላትን ፈቃድ ሆኖ ሳለ እርሱ ግን እርሱ ራሱ እያደረገው እንደሆነ ያስባል'' ጠላት ትቶህ የሚወጣውና ሌላ መመለሻ አጋጣሚ እሰኪያገኝ ድረስ ከአንተ ርቆ የሚጠባበቀው ጸሎትና ጾምን ስትታጠቅ ብቻ ነው፡፡ ጸሎትና ጾም ከተተው ግን እንደገና ተመልሶ ይመጣል" ይላል፡፡
+++ ስለሆነም ጾምና ጸሎት በተተውበትና በሌለበት ሕይወት ዘንድ ኦርቶዶክሳዊነት ሽታውም አለ ማለት አይቻልም። ጾም የሌለበት ሰውነት የአጋንንት መሥሪያ ቤት እንጂ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አይሆንም፡፡ በተሐድሶዎችና በመሰሎቻቸው እያደረ “ዘመነኛ” ወይም “ሊበራል” በሚል ሽፋን ሰይጣንየሚሰብከውን “ጾም የለሽ” “ክርስትና” ወይም “እምነት” ልብ እንበል፡ እንወቅበትም! ኦርቶዶክሳዊነት በባሕርዩ ትህርምታዊ (Ascetic) ነው፡፡ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ሕዝቡንም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጠርቶ እንዲህ አላቸው፦ በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ" ያለው ለዚህ ነው፡፡ (ማር. 8፡34) ሆድን ወድዶ ጾምን ጠልቶ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር መሆን አይቻልም፡፡ እንዲህ ያሉት “ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ፣ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ፤ መጨረሻቸው ጥፋት ነው፣ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፣ ክብራቸው በነውራቸው ነው፣ አሳባቸው ምድራዊ ነው" የተባሉት ናቸው። (ፊል. 3፡18-19)
ከመድሎተ ጽድቅ መፅሃፍ የተወሰደ (በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተዘጋጄ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ሰኔ ፫ /3/በዚችም ቀን ደግሞ ኤላርዮስ የሚባል ኤጲስቆጶስ ሰማዕት ሆኖ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከሀዲውን ንጉሥ ዮላኪዮስን ጣዖታትን ስለማምለኩ ይገሥጸውና ይመክረው ነበር ንጉሥ ዮላኪዮስም አይሁድ የሰቀሉትን ባለማምለኬ አንተ ከሀዲ ትለኛለህ እነሆ አሁን እኔ አንተን ከሥቃይ ጽናት የተነሣ ያን የተሰቀለውን አምልኮቱን አስተውኻለሁ አለው። ከዚህ በኋላም ከመኳንንቶቹ ለአንዱ መኰንን ሰጥቶ ባለመራራት ያለማቋረጥ ሁልጊዜ እንዲአሠቃየው አዘዘው መኰንኑም ወስዶ በየራሱ በሆነ ሥቃይ አንዲት ቀን እንኳ ከቶ ሳያቋርጥ ሁልጊዜ እያሠቃየው አንድ ዓመት ሙሉ ኖረ። በዓመቱም ፍጻሜ በእሳት ውስጥ ጣሉት እርሱም ከእሳት መካከል ቆሞ እግዚአብሔርን ፈጽሞ እያመሰገነ ጸለየ ስለዚህችም ምልክት ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ብዙዎች አምነው በሰማዕትነት ሞቱ። ከዚህም በኋላ ከአታክልት መካከል እንደ ሚወጣ ሆኖ ከእሳት አወጡት። መኰንኑም ከማሠቃየት በደከመ ጊዜ በእርሱ ላይም የሚያደርገውን በእጣ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዝዞ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምሥጋና ይሁን እኛንም በዚህ ተጋዳይ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
በዓይነጥላ መንፈስ ባሕሪይ ውስጥ የአዳልሞቴ መንፈስ መገለጥና ምልክቶቹ! ነፍሳችንን ነጻ ለማውጣት አሁኑኑ ይኼንን እናድርግ!! ፍቅር ከስሜት በላይ ነውና አስተውሉ!! https://youtu.be/qOYT8HL0zf8?si=ArHpAv8iwG-0aLoR
መምህር ተስፋዬ ይህችን እናት እንዴት አስተምሮና መክሮ እንደቀየራት ተመልከቱ! Haile Gebriel Reacts19 #የቡና_ካዳሚዋ_እናት_የመናፍስት_ፈተና!! https://youtu.be/X25xtL7BkQY
