HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 270
مشترکین
-424 ساعت
+127 روز
+2630 روز
آرشیو پست ها
ሰዎችን መበቀል ከፈለጋችሁ ይኼንን በደንብ አዳምጡና ተግብሩ!! ሸዋፈራው ደሳለኝ የገጠመው ጉድ ምንድነው?? ኦርቶዶክስ ክርስቶስን አትሰብክም የምትሉ አዳምጡ!! https://youtu.be/A22w1KAHsNc
+3
- የሁሉንም ባሕል የማትንቀው ይልቁንስ አስማምታ የምታከብረን ሰብሳቢያችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን!
- ሃይማኖት ከእነትውፊትና ስርዓቱ ሲከወን ይህንን ይመስላል!
- እንደጎደለብን እንዳይሰማን አድርገው ይህን ዘመንን አስበው ሥርዓትን በልካችን ሰፍተው ለሰጡን አባቶቻችን ክብር ይሁን!
ነሐሴ ፲፰ /18/በዚች ቀን ቁጥሩ ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ እለእስክንድሮስ አረፈ። ይህም አባት ከአርዮስ ወገኖች ብዙ ችግር ደርሶበታል። በታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘመን በኒቅያ ሦስት መቶ ዐሥራ ስምን አባቶች ሊቃውንት አርዮስን በጉባኤ አውግዘው ከቤተ ክርስቲያን ለይተው በአሳደዱት ጊዜ። በእለእስክንድሮስና በአትናቴዎስ ላይ ነገር ይሰራ ዘንድ አስቦ ወደ ንጉሱ ሔዶ ከዉግዘቱ እንዲመልሱት እንደሚፈልግ ነገረው። ንጉሱም እለእስክንድሮስን በጠየቀዉ ጊዜ ስለ እግዚአብሔር ወልድ አምላክነት እንዲመሰክር ጠየቀው አርዮስም በሐሰት ማለ። ከዚያም ሱባዔ በኋላ አርዮስ መልካም ልብስን ለበሰ ወደ ቤተ ክርስቲያንም ገብቶ በመሠዊያው ፊት ከካህናቱ ጋራ ተቀመጠ። ከዚህም በኋላ አባ እለእስክንድሮስ እያዘነና እየተከዘ ከአርዮስ ጋራ ወደ ቅዳሴ ገባ ከኀዘኑም ብዛት የተነሣ የሚሠራውን አላወቀም የቅዳሴውንም ሥርዓት ሊጀምር ቆመ ። ያን ጊዜ የአርዮስ ሆዱ ተበጠበጠና ወጥቼ ልመለስ አለ ይህንንም ብሎ ወደ መጸዳጃ ቦታ ወጣ ። ሊጸዳዳም በተቀመጠ ጊዜ አንጀቱና የሆድ ዕቃው ሁሉ ወጣ በዚያውም ላይ ሞተ። በዘገየም ጊዜ ሊፈልጉት ወጡ በመጸዳጃውም ቦታ ሬሳውን ወድቆ አገኙት። ለዚህም አባት ለእለእስክንድሮስ ነገሩት እርሱም አደነቀ የከበረች ቤተ ክርስቲያኑን ያልጣላት ምስጉን የሆነ ክርስቶስንም አመሰገነው። ንጉሡም በሰማ ጊዜ አደነቀ ከሀዲ አርዮስም በሐሰት እንደማለና በሽንገላ እንደጻፈ አወቀ። ይህም አባት በበጎ ሥራ ጸንቶ ኖረ ለምለም ወደ ሆነ እርጅናም ደርሶ ወደ ወደደው ክርስቶስ ሔደ የሕይወት አክሊልንም አገኘ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239
መምህር ተስፋዬ ላይቪ ይገኛል በCMC ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ሁላችሁም ሸር ላይክ እያደረጋችሁ። https://www.youtube.com/live/hFsML8BkCQ4?si=4tuKKkjIMSJCsbxp
The 3 BIG Christological Debates Explained: Ethiopian Orthodox View #ethiopia #orthodoxy #oriental https://youtu.be/YkNNCC-xFC0
በቅዳሴ ወቅት የተፈጠረ አስገራሚው ተዓምርና ሰሚነሽ ኪዳነ ምህረት የሆነው ምንድነው?? ልጆቼን እንድታሳድግልኝ በመተት እሷን አረብ ሀገር ላኳት!! #ጸሎት https://youtu.be/PFKLoaY3PYI
ይኼንን ጉድ ሰምታችሁ ቤተሰቦቼ እራሳችሁን በጥንቃቄ ፈትሹ!! የእመቤታችን የእርገቷ ነገርና ማወቅ ያለብን ምስጥር! በምትጸልዩበት ጊዜ ይኼንን አስተውሉ! #ንቁ https://youtu.be/5r_0MptvjR0
🙏 በመላው ዓለም ያላችሁ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገቷ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
+ "ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ፣ ወማኅደሩ በጽድቅ ዘገብራ ከሃሊ፣ ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ፣ በመሰንቆሁ እንዘ የሐሊ፣ ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ።
+ ትርጕም፦እግዚአብሔር በእውነት ማደሪያው ያደረጋት፣ የጳውሎስ ፍጽምት ድንኳን እመቤታችን፣ የልጇ አገልጋይ ዳዊት በመሰንቆው እየዘመረ ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም ዐረገች"
ቅዱስ ያሬድ
+ አምላካችን እግዚአብሔር በአማላጅነቷ ለዓለማችን ሰላሙን፣ ፍቅሩን፣ ምሕረቱን ይላክልን። የእመቤታችን አማላጅነቷ አይለየን አሜን!!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
በጸሎት ሰዓት የመናፍስትን ወጥመድና ሴራ ለማክሸፍ ይኼንን እናድርግ!! ብዙዎቻችን ያላወቅነው የአዕምሮ መተትና የሚገጥሙን ፈተናዎች! #ዛር #አጋንንት #መተት https://youtu.be/rWHySEwxpWU
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ»
(የማቴዎስ ወንጌል 10፡1-15)
«አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ፥ እንዲያወጡአቸው በርኩሳን መናፍስት ላይ ደዌንና ሕማምንም ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው። የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም ይህ ነው፤ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን ወንድሙ እንድርያስም፥ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብም ወንድሙ ዮሐንስም፥ ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥ ቶማስም ቀራጩ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥ ቀነናዊውም ስምዖን ደግሞም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ። እነዚህን አሥራ ሁለቱን ኢየሱስ ላካቸው፥ አዘዛቸውም፥ እንዲህም አለ። በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ፥ ወደ ሳምራውያንም ከተማ አትግቡ፤ ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ። ሄዳችሁም። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች ብላችሁ ስበኩ። ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ። ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ፥ ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ፤ ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና። በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ። ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ፤ ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት፤ ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ። ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ። እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
ከጸሎታችን በኋላ ይኼንን ማድረጋችንን በጭራሽ እንዳንረሳ!! የማሕጸን መተትና ያልተረዳነው የአጋንንት ፈተናዎች! ዲያቆን ሄኖክ ስለ ስግደት ያስተማረን! #ጸሎት https://youtu.be/QIP5kZ7JQ8c
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ»
(የማቴዎስ ወንጌል 17፡14-24)
«ወደ ሕዝቡም ሲደርሱ አንድ ሰው ወደ እርሱ ቀረበና ተንበርክኮ። ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤ ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና። ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው አለው። ኢየሱስም መልሶ። የማታምን ጠማማ ትውልድ ሆይ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ ወደ እኔ አምጡት አለ። ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ። ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና። እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት። ኢየሱስም። ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ። ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም። ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው። በገሊላም ሲመላለሱ ኢየሱስ። የሰው ልጅ በሰዎች እጅ አልፎ ይሰጥ ዘንድ አለው፥ ይገድሉትማል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል አላቸው። እጅግም አዘኑ። ወደ ቅፍርናሆምም በመጡ ጊዜ ግብር የሚቀበሉ ሰዎች ወደ ጴጥሮስ ቀረቡና። መምህራችሁ ሁለቱን ዲናር አይገብርምን? አሉት።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ምክንያት ማብዛቱን አቁሙና አሁኑኑ እባካችሁ ይኼንን አድርጉ!! በቡዳ የመበላላታችንና የመያዛችን ምልክቶቹ እነዚህ ናቸው!! #oriental #orthodoxy https://youtu.be/j7--EKSAvmI
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ» እንኳን ለደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ!
(የሉቃስ ወንጌል 9፡28-40)
«ከዚህም ቃል በኋላ ስምንት ቀን ያህል ቈይቶ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ያዕቆብንም ይዞ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ። ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሁለት ሰዎች እነርሱም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር፤ በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር። ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ። ከእርሱም ሲለዩ ጴጥሮስ ኢየሱስን። አቤቱ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነውና አንድ ለአንተ አንድም ለሙሴ አንድም ለኤልያስ ሦስት ዳሶች እንሥራ አለው፤ የሚለውንም አያውቅም ነበር። ይህንም ሲናገር ደመና መጣና ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ። ከደመናውም። የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ። ድምፁም ከመጣ በኋላ ኢየሱስ ብቻውን ሆኖ ተገኘ። እነርሱም ዝም አሉ ካዩትም ነገር በዚያ ወራት ምንም ለማንም አላወሩም። በነገውም ከተራራ ሲወርዱ ብዙ ሕዝብ ተገናኙት። እነሆም፥ ከሕዝቡ አንድ ሰው እንዲህ እያለ ጮኸ። መምህር ሆይ፥ ለእኔ አንድ ልጅ ነውና ልጄን እንድታይልኝ እለምንሃለሁ። እነሆም፥ ጋኔን ይይዘዋል፥ ድንገትም ይጮኻል አረፋም እያስደፈቀው ያንፈራግጠዋል፥ እየቀጠቀጠም በጭንቅ ይለቀዋል፤ ደቀ መዛሙርትህንም እንዲያወጡት ለመንሁ፥ አልቻሉምም። ኢየሱስም መልሶ። እናንተ የማታምን ጠማማ ትውልድ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ልጅህን ወደዚህ አምጣው አለ። ሲቀርብም ጋኔኑ ጣለውና አንፈራገጠው፤ ኢየሱስ ግን ርኵሱን መንፈስ ገሥጾ ብላቴናውን ፈወሰው ለአባቱም መለሰው። ሁሉም ከእግዚአብሔር ታላቅነት የተነሣ ተገረሙ።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የካህኑን ልጅ በዝሙት ያሰቃዬ የሳጥናኤል አጋንንትና ክፋቱ!! ጸሎት ያቆመ ሰው እግዚአብሔርን የረሳና የተወ ነው!! ዘመናዊነት በአባቶች አንደበት ስገለጽ!! https://youtu.be/3pPCEUpxQ9g
ነሐሴ ፲፪አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የከበረ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። በዚች ቀን እግዚአብሔር ወደ ዕሌኒ ልጅ ወደ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ልኮታልና ለእርሱም ጠላቶቹን እስከ አሸነፋቸው መንግሥቱም እስከ ጸናች ድረስ ኃይልን ሰጠው የጣዖታትንም ቤት አፍርሶ አብያተ ክርስቲያናትን ሠራ። በጌጥም ሁሉ አስጌጣቸው። ስለዚህም አባቶቻችን የቤተ ክርስቲያን መምህራን የከበረ የመላእክት አለቃ የሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ በየወሩ በዐሥራ ሁለተኛው ቀን እናደርግ ዘንድ አዘዙን። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
የእግዚአብሔርን ጦር ዕቃ ይዘን ዲያብሎስን መዋጋትና ማሸነፍ ለምን አቃተን? የጸሎትና የስግደት ኃይልን ማወቅና መረዳት! https://youtu.be/krXT0AA3Pqo?si=VNIUfPoTuaVb7uyP
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ»
(የሉቃስ ወንጌል 16፡9-19)
«እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ። ከሁሉ በሚያንስ የታመነ በብዙ ደግሞ የታመነ ነው፥ ከሁሉ በሚያንስም የሚያምፅ በብዙ ደግሞ ዓመፀኛ ነው። እንግዲያስ በዓመፃ ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ እውነተኛውን ገንዘብ ማን አደራ ይሰጣችኋል? በሌላ ሰው ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ የእናንተን ማን ይሰጣችኋል? ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል። ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር። እንዲህም አላቸው። ራሳችሁን በሰው ፊት የምታጸድቁ እናንተ ናችሁ፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ልባችሁን ያውቃል፤ በሰው ዘንድ የከበረ በእግዚአብሔር ፊት ርኵሰት ነውና። ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ነበሩ፤ ከዚያ ጀምሮ የእግዚአብሔር መንግሥት ይሰበካል፤ ሁሉም ወደ እርስዋ በኃይል ይገቡባታል። ነገር ግን ከሕግ አንዲት ነጥብ ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ሊያልፍ ይቀላል። ሚስቱንም የሚፈታ ሁሉ ሌላይቱንም የሚያገባ ያመነዝራል፥ ከባልዋም የተፈታችውን የሚያገባ ያመነዝራል። ቀይ ልብስና ቀጭን የተልባ እግር የለበሰ አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥ ዕለት ዕለትም እየተመቸው በደስታ ይኖር ነበር።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ዮኒ ማኞ ትዝታው ሳሙኤልን አስጠነቀቀው!! በፓንቷ መተት አስርተው እንዳታገባና ልጅ እንዳትወልድ ዘጋጉባት!! መምህር ተስፋዬ የነገረን ወሳኝ መልዕክት!! የጋብቻ መሠረታዊ ምክንያቱን ምን ያህል ያውቃሉ! https://www.youtube.com/watch?v=LqQWQeaEb4c
ቤተሰቦቼ ለስንዴ እርዳታ ብለው የመስዋዕት በግ አደረጉኝ እያለችን ነው!! ጸሎተ ቅዳሴ ከጊዜና ከቦታ ውጭ ነው የሚያደርገን! #አጋንንት #ጸሎት #ስግደት #ንቁ https://youtu.be/CpQzZiueHII
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
