HAMLE 19 NO. 2 P/P/Primary and Middle SCHOOL
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
352
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+47 روز
+1530 روز
آرشیو پست ها
የ6ኛ ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና መስጫ መርሀ ግብር
(ታህሳስ 30/2017 ዓ.ም)
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
ለትምህርት ቤታችን መምህራን ና አሰተዳደር ሰራተኞች በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ!!! /Baga Geessan!!!! 🎄🎄🌲🌲🌲🌲🌲🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🌲🌲🌲🌲🌲
መልካም በዓል!!!Ayyaana Gaarii!!
በቀን 28/04/2017ዓ.ም በሐምሌ 19 ቁ.2 ቅ/አ/መ/ደ/ት/ቤት የገና በአልን ምክንያት በማድረግ አቅም ለሌላቸው የተማሪ ወላጆች ለባዕል መዋያ የሚሆን ስጦታ ተበረከተ።
✍የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተናን ይመለከታል
✅የ2017 ዓ.ም የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና መረጃ ለ6ኛ ና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
1️⃣ የ6ኛ ክፍል በተመለከተ
በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
👉አማርኛ
👉እንግሊዘኛ
👉ሒሳብ
👉አካ/ሳይንስ እና
👉ግብረ ገብ ሲሆኑ
✍️ የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና የሚዘጋጀው ከ6ኛ ክፋል first semester (5ኛ ክፍልን first semester ይጨምራል)
2⃣የ8ኛ ክፍል በተመለከተ
✅ የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና የሚዘጋጀው ከ8ኛ ክፍል first semester (ከ7ኛ ክፋልን first semester ይጨምራል)
በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
👉Eng
👉አማርኛ
👉ሒሳብ
👉ሶሻል ሳይንስ
👉አጠ/ሳይንስ
👉የዜግነት ት/ት
👉በመሆኑም የፈተና ወቅት እየተቃረበ በመሆኑ ተማሪዎች በዚህ መረጃ መሰረት በአግባቡ ማጥናት ይጠበቅባቸዋል::
👉በዚህ መረጃ መሠረት ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+3
እድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ለሆኑ ሴት ተማሪዎች ከታህሳስ 21 ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት በትምህርት ተቋማት የማህጸን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት እንደሚሰጥ ተገለጸ።
(ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም) የክትባቱን ሂደት በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ከከተማ አስተዳደሩ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ ጋር በመሆን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል።
የማህጸን በር ካንሰር ክትባት እድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ሆኖ ከዚህ በፊት ክትባቱን ላልወሰዱ ታዳጊ ሴት ልጆች እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ ገልጸው ዘንድሮ በከተማ አስተዳደሩ ክትባቱን እንዲወስዱ በዕቅድ ከተያዙ 177,000 በላይ ታዳጊ ሴቶች ውስጥ 90% የሚሆኑት በትምህርት ተቋማት እንደመገኘታቸው በትምህርት ቤት ለሚሰጠው ክትባት ከፍተኛ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል።
የማህጸን በር ካንሰር በሀገራችን ኢትዮጵያ ከጡት ካንሰር ቀጥሎ በገዳይነቱ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ በሽታ እንደሆነ በተለያዩ ጥናቶች መረጋገጡን ዶክተር ዮሀንስ ጫላ ጠቁመው ክትባቱ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ መቆየቱን በመጥቀስ የዘንድሮ መርሀግብር ስኬታማ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ የትምህርት ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፈዋል።
Repost from HAMLE 19 NO. 2 P/P/Primary and Middle SCHOOL
11/04/2017 ዓ.ም
ለሐምሌ 19 ቁ 2 ቅድመ አንደኛ፤አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች በሙሉ በ2017 የተጀመረው የሰኞ ማለዳ የእውቀት ሽግግር መርሐ ግብር ሰኞ 14/04/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 የሚካሄድ ስለሆነ በሰዓቱ ICT ክፍል እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
04/04/2017 ዓ.ም
ለሐምሌ 19 ቁ 2 ቅድመ አንደኛ፤አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች በሙሉ በ2017 የተጀመረው የሰኞ ማለዳ የእቀት ሽግግር መርሐ ግብር ሰኞ 07/04/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 የሚካሄድ ስለሆነ በሰዓቱ ICT ክፍል እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
