fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 380 مشترک است و جایگاه 5 573 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 194 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 380 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 06 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 32 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.44% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.50% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 449 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 461 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 20 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 07 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 380
مشترکین
-424 ساعت
-257 روز
+3230 روز
آرشیو پست ها
፠ ‹‹አርኅው ኆኀተ መኳንንት፤ (እናንተ መኳንንት፤ ደጃፎችን ክፈቱ)፡፡›› ወይትረኀዋ ኆኃት እለ እምፍጥረት፡፡ ‹‹መኑ ውእቱ ዝንቱ ንጉሠ ስብሐት፡፡›› (ክብር፥ ምስጋና የሚገባው ይህ ንጉሥ ማነው?
+1
፠ ‹‹አርኅው ኆኀተ መኳንንት፤ (እናንተ መኳንንት፤ ደጃፎችን ክፈቱ)፡፡›› ወይትረኀዋ ኆኃት እለ እምፍጥረት፡፡ ‹‹መኑ ውእቱ ዝንቱ ንጉሠ ስብሐት፡፡›› (ክብር፥ ምስጋና የሚገባው ይህ ንጉሥ ማነው?)›› ፠ ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ኃያላን ውእቱ ዝንቱ ንጉሥ ስብሐት (ክብር፥ ምስጋና የሚገባው ይህ ንጉሥ የኃያላን አምላክ እግዚአብሔር ነው፡፡)›› ‹‹ይባእ ንጉሠ ሰብሐት፥ ይባእ አምላከ ምሕረት፡፡ (የምስጋናው ንጉሥ ይግባ፤ የምሕረቱ አምላክ ይግባ፡፡›› /መዝሙረ ዳዊት ፳፫/

ሰላምሽ ዛሬ ነው ኢየሩሳሌም ወደ አንቺ መጥቷልና አምላክ ዘለዓለም/፪/ ሆሳዕና በአርያም እያሉ ዘመሩ ሕፃናት በኢየሩሳሌም አንቺ ቤተልሔም የዳዊት ከተማ የሕዝቦችሽ ብርሃን መጣልሽ በግርማ/፪/ ሆሳዕና እያሉ አመሰገኑት በኢየሩሳሌም አዕሩግ ሕፃናት/፪/ ኪሩቤል መንበሩን የሚሸከሙት መስቀል ተሸክሞ ሆነን መድኀኒት/፪/ የኢየሱስን ሕማም ደናግልም አይተው እያለቀሱለት ሄዱ ተከትለው/፪/ ሆሳዕና በአርያም እያሉ ዘመሩ ሕፃናት በኢየሩሳሌም ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

፠ በዐውደ ምሕረቱ ላይም አባቶች መዘምራን ጥንግ ድርብ ይዘው ቁጭ ይበሉ፤ ፠ ወጣቶችና ታዳጊ ዲያቆናት ጥንግ ድርብ ይዘውና መቋሚያ ይዘው ይቁሙ፡፡ ፠ ‹‹ተፂዕኖ ዲበ ዕዋል›› የሚለውን አባቶች እያወጡ ሕፃናትና ወጣቶች እየተቀበሉ 14 ምዕራፍ ያህል ይበሉ፡፡ ፠ በስተመጨረሻም ዘንባባው ተባርኮ ለሕዝቡ ለበረከት ይታደላል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ሥርዓተ_ቅዳሴ_ምንባባት_ምስባክ #ወሥርዐተ_ዑደት_ዘበዓለ_ሆሳዕና፡፡ (በድምፅ ከፈለጉ በቴሌግራም አድራሻችን (https://t.me/medihanaelem) ያገኛሉ፡፡ (ፎቶ ላይ የምትመለከቷቸው፤ በሃገራችን ደረጃ በዋናነት የተፂዕኖ ክብረ በዓል የሚበርባቸው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያምና፤ ርዕሰ አድባራት መንበረ ፀሐይ እንጦጦ ማርያም ላይ ሲከበር የሚያሳዩ ናቸው) #ሥርዓተ_ቅዳሴ_ዘበዓለ_ሆሳዕና (#ዘበዓለ_ተፂዕኖ) * ከሥርዓተ ማኅሌቱ በኋላ የቤተ ክርስቲያኑ የምዕራብ ደጃፍ እንደተዘጋ ከውጭ ፍሬ ሰሞነኛው ዲያቆን በመሶበ ወርቅ ያኖረውን የመሥዋዕቱን ኅብስተ አኰቴት በራሱ ላይ እንደተሸከመ÷ ሠራዒው ዲያቆንም የቊርባኑን የወይን ጽዋ እንደያዘ በመካከል ቆሞ በመዝሙረ ዳዊት ያለውን ‹‹አርኅው ኆኀተ መኳንንት፤ እናንተ መኳንንት! ደጃፎችን ክፈቱ!›› የሚለውን ቃል ከመዝሙራቱ ጠቅሶ በዕዝል ዜማ ለ ጊዜያት ያሰማል፡፡ ዋናው ቀዳሽ ካህን ከመቅደሱ ውስጥ ኾኖ ‹‹መኑ ውእቱ ዝንቱ ንጉሠ ስብሐት፥ መኑ ውእቱ ዝንቱ ንጉሠ ስብሐት፥ መኑ ውእቱ ዝንቱ ንጉሥ ስብሓት፡፡›› ማለትም ‹‹ክብር ምስጋና የሚገባው ይህ ንጉሥ ማነው›› እያለ በመጠየቅ ከዚያው ከመዝሙራቱ የሚጠቀሰውን ቃል በእዝል ዜማ ለ ጊዜያት እያሰማ ይመልስለታል፡፡ በኛው ጊዜ ዲያቆኑ በዚያው የዜማ ስልት ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ኃያላን ውእቱ ዝንቱ ንጉሥ ስብሐት›› ማለትም ‹‹ክብር ምስጋና የሚገባው ይህ ንጉሥ የኃያላን አምላክ እግዚአብሔር ነው!›› የሚለው ቃል ለ ጊዜያት በማሰማት ምላሹን ይሰጠዋል፡፡ በመጨረሻ ካህኑ በልዩ የወረብ ዜማ ‹‹ይባእ ንጉሠ ሰብሐት፥ ይባእ አምላከ ምሕረት፡፡›› ማለትም ‹‹የምስጋናው ንጉሥ ይግባ፤ የምሕረቱ አምላክ ይግባ፡፡›› እያለ የቤተ ክርስቲያኑን ደጃፍ ይከፍተዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ቀዳስያኑም÷ መዘምራኑም÷ ካህናቱም÷ ሕዝቡም ሁሉ መሥዋዕቱንና ቊርባኑን እንዳጀቡ በኅብረት ይህንኑ ዝማሬ እያሰሙ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይዘልቃሉ፤ ከመቅደሱ በር ሲደርሱም ቀዳስያኑ ወደ ቅድስተ ቅድሳን ይገባሉ፤ መዘምራኑም ወደ ቅኔ ማኅሌታቸው ይመለሳሉ፡፡ የሥርዓተ ቅዳሴው ጸሎት አልቆ ወደፍሬ ቅዳሴው ከመግባታቸው በፊት ለበዓሉ ከተመደቡት ከአዲስ ኪዳን መልእክታት ምንባቦች በኋላና ከምሥራቹ (ከወንጌሉ) የአዋጅ ቃል ንባብ አስቀድሞ ከብሉይ ኪዳን መዝሙራት መካከል ተጠቅሶ የሚዘመረው ምስባክ ‹‹ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ ባርክናክሙ እምቤተ እግዚአብሔር እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ፡፡›› ማለትም ‹‹በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፤ በእግዚአብሔር ቤት ኾነን መረቅናች፤ ጌታ እግዚአብሔር ለእኛ ተገለጠ፡፡›› የሚለው ነው፡፡ #ምንባባት፤ #ዘቅዳሴ፡፡ † ዕብ. ፱፥፲፩-፳፰ † ፩ኛ ጴጥ. ፬፥፩-፲፩ † የሐዋርያት ሥራ ፳፰÷፲፩-፴፩ ምስባክ፤ /መዝ. ፹፥፫/ ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ፤ በዕምርት ዕለት በዓልነ፤ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ፡፡ (ትርጕም፤ከሕጻናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋዘህ ስለጠላት፣ ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት፡፡) ወንጌል፤ ሉቃ. ፲፱፥፳፰-፵፰ ቅዳሴ፤ ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ፡፡ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ #ሥርዐተ_ዑደት_ዘበዓለ_ሆሳዕና፡፡ ቀጥሎም በቤተ መቅደሱና በቤተ ክርሰቲያኑ ዙሪያ ዑደት እያደረጉ መሪና ተመሪ በመሆን ሕዝቡም እየተቀባበለ የሚከተለውን ሥርዐት ያድርሱ፡፡ ፠ #በቤተ መቅደስ ምስባክ፤ /መዝ. ፻፲፯፥፳፮/ ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ ባረክናክሙ እምቤተ እግዚአብሔር፤ እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ፡፡ ወንጌል፤ ሉቃ. ፲፱፥፩-፲፩ አቡን፤ በ፪ (ሃሌ ሃሌ ሉያ) አርዕዩነ ፍኖቶ ወንሑር ቤቶ፤ እስመ አምጽዮን ይወጽእ ሕግ ወቃለ እግዚአብሔር እምኢየሩሳሌም፤ ንሳለማ ለመድኀኒትነ በትፍሥሕት ተቀበልዋ ለታቦት እስመ ዋካ ይእቲ ወብርሃን፡፡ ይ.ሕ.፤ አርዕነ ፍኖቶ... እስከ ተፍጻሜት ምልጣን፤ንሳለማ ለመድኀኒትነ በትፍሥሕት፤ ተቀበልዋ ለታቦት፤ እስመ ዋካ ይእቲ ወብርሃን፤ ዋካ ይእቲ ወብርሃን፡፡ ይ.ሕ.፤ እስመ ዋካ ይእቲ ወብርሃን፤ ዋካ ይእቲ ወብርሃን፡፡ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ፠ #በምዕራብ ምስባክ፤ /መዝ. ፻፳፩፥፩/ ተፈሣሕኩ እስመ ይቤሉኒ ቤተ እግዚአብሔር ነሐውር፤ ወቆማ እገሪነ ውስተ አዕፃድኪ ኢየሩሳሌም፤ ኢየሩሳሌምሰ ሕንጽት ከመ ሀገር፡፡ ዓዲ፤መዝ. ፱፥፲፩ ዘምሩ ለእግዚአብሔር ዘየኀድር ውስተ ጽዮን፤ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ እስመ ተዘከረ ዘይትሐሠሥ ደሞሙ፡፡ ወንጌል፤ ማቴ. ፳፩፥፩-፲፯ አቡን፤በ፮/ሃሌ ሉያ (፪)፥ሃሌ ሃሌ ሉያ(፫)/፤ ሰመያ አብርሃም፤ ወይቤላ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር፤ ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ በእምርት ዕለት በዓልነ ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን፡፡ ምልጣን፤ ንፍሑ ቀርነ….(መዝ. ፹፥፫) በል ይ.ሕ.፤ ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን፤ ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን፡፡ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ፠ #በደቡብ ምስባክ፤ /መዝ. ፷፥፪/ እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ በእንተ ጸላኢ፤ ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ፡፡ ወንጌል፤ ማር. ፲፩፥፩-፲፩ አቡን፤በ፮/ሃሌ ሉያ (፪)፥ ሃሌ ሃሌ ሉያ(፫)/፤ ወትቤ ጽዮን አርኅዉ ሊተ አናቅጸ፤ ይባዑ ሕዝብ ብዙኃን፤ ወያዕትቱ ዕብነ እምፍኖት ለንጉሥ ለወልደ ዳዊት፤ ንጉሦሙ ለ፳ኤል ውእቱ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፡፡ ምልጣን፤ ወያዕትቱ ዕብነ …. በል ይ.ሕ.፤ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፡፡ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፡፡ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ፠ #በምሥራቅ ምስባክ፤ /መዝ. ፵፱፥፩/ እምሥራቀ ፀሐይ እስከነዓረብ፤ ወእምጽዮን ሥነ ስብሐቲሁ፤ እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ፡፡ ወንጌል፤ ሉቃ. ፲፱፥፳፰-፵፰ አቡን፤ በ፮ (ሃሌ ሉያ /፪/፥ሃሌ ሃሌ ሉያ/፫/)፤ ባረኮ ያዕቆብ ለይሁዳ ወልዱ ወይቤሎ ሀሎ ንጉሥ ዘይወጽእ እምኔከ፤ ዘየሐጽብ በወይን ልብሶ ወበደመ አስካል ሰንዱኖ ንጉሦሙ ለእስራኤል ውእቱ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፡፡ ምልጣን፤ ዘየሐጽብ …. በል ይ.ሕ.፤ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፡፡ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፡፡ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ፠ #በሰሜን ምስባክ፤ /መዝ. ፻፵፯፥፩/ ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር፤ ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን፤ እስመ አጽንዐ መናሥግተ ኆኃትኪ፡፡ ዓዲ፤መዝ. ፹፥፫ ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ፤ በዕምርት ዕለት በዓልነ፤ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ፡፡ ወንጌል፤ ዮሐ. ፲፪፥፲፪-፲፱ አቡን፤ በ፪ (ሃሌ ሃሌ ሉያ)፤ ባኡ ውስተ ሀገር፤ ወበዊአክሙ ትረክቡ ዕዋለ አድግ ዕሡረ፤ ፍትሕዎ ወአምጽእዎ ሊተ፡፡ ምልጣን፤ ፍትሕዎ …. በል ይ.ሕ.፤ ፍትሕዎ ወአምጽእዎ ሊተ፡፡/፪/ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ፠ ካህናት ወደ ቤተ መቅደስ ከገቡ በኋላ፤ መዘምራኑ ቀጥሎ ያለውን ይበሉ፡፡ አቡን፤ በ፩ (ሃሌ ሉያ) አልጺቆ ኢየሱስ ኢየሩሳሌም ርእያ ለሀገር፤ ወይቤላ ሶበ ተአምሪ ጽዮን ነዋ ንጉሥኪ በጽሐ ብርሃንኪ ዮም ሰላምኪ፡፡ ምልጣን፤ ወይቤላ ሶበ ተአምሪ ጽዮን ነዋ ንጉሥኪ በጽሐ ብርሃንኪ ዮም ሰላምኪ፤ ተፈሥሒ በሕዝብኪ ዮም ሰላምኪ፤ ይትሐፈሩ ጸላእትኪ ዮም ሰላምኪ፤ ሰላምኪ ሰላምኪ ዮም ሰላምኪ፡፡ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ ꖴ

#ሆሣዕና (#በዓለ_ተፂዕኖ) (#የፀበርት_እሑድ) #ወሥርዐተ_ማኅሌት ፠ የሰሞነ ሕማማት የመጀመሪያው ቀን፤ የዐቢይ ጾም ስምንተኛውና የመጨረሻው ሳምንት ሆሣዕና ይባላል፤ ፠ በዕብራይስጡ ‹‹ሆሼዕናህ›› የሚል ሲሆን ትርጕሙም ‹‹እባክህ አሁን አድን፤ አንድም መድኀኒት›› ማለት ነው፡፡ በትንቢተ ዘካርያስ ላይ በአህያ ላይ ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ (በግእዙ ተፂዕኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ኢየሩሳሌም በክብር) ስለሚል በአብዛኛው የሃገራችን ክፍል ከጥንት ጀምሮ በዋነኛነት ‹‹የተፂዕኖ በዓል›› በመባል ይታወቃል፡፡ እንዲሁም ዘንባባ በግእዙ ፀበርት እየተባረከ ስለሚሰጥ ‹‹የፀበርት እሑድ›› ይባላል፡፡ ፠ በዚህ ዕለት ጌታችን የማዳን ሥራውን ወደሚፈጽምባት ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ ቤተ ፋጌ ሲደርስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ልኮ ‹‹ያስፈልጉኛልና የታሠሩትን አህያና ውርንጫ ይዛችሁልኝ ኑ፡፡›› ብሎ ላካቸው፡፡ በምስጢሩም የአዳምን ልጆች ከዲያብሎስ ቁራኝነት ሊፈታ እንደ መጣ ለማጠየቅ ነው፡፡ እነርሱም እንደታዘዙት አመጡ፤ እስከ ቤተ መቅደስ 16 ምዕራፍ ሲሆን 14ቱን በእግሩ፣ 2ቱን ምዕራፍ (ከደብረ ዘይት ተራራ አካባቢ አንስቶ እስከ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ) በአህያ ሄዶ፣ ቤተ መቅደሱን 3 ጊዜ በውርንጫላዋ ከዞረ በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ፡፡ #ለምን_ጌታችን_በአህያ_ውርንጫ_ተቀምጦ_ወደ_ቤተ_መቅደስ_ገባ * ቀድሞ በነቢያት ዘመን ጸብዕ (ጥል) በሆነ ጊዜ በፈረስ ተቀምጠው፥ የጦር ዕቃ ይዘው፥ ዘገር ነቅንቀው፥ ጦር ሰብቀው፥ (ነጋሪት እያጎሰሙ፥ መለከት እያስነፉ) ይታዩ ነበር፤ ዘመነ ሰላም፥ ዘመነ ምሕረት በሆነ ጊዜ ደግሞ በአህያ ተቀምጠው፥ መነሳንስ ይዘው ይታያሉ፤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በነቢያት ሥርዐት ‹‹ዘመነ ሰላም ይዤላችሁ›› መጣሁ፤ በ7ቱ መስተጻርራን /ተጣልጠው የነበሩ/ (በሰውና በእግዚአብሔር ፣ በሰውና በመላእክት፣ በሥጋና በነፍስ፣ በተገዘሩት በሕዝበ እሥራኤልና ቆላፍ በሆኑት በአሕዛብ መካከል) የነበረው ጠብ ማብቃቱን ለመግለጥ እንዲሁም በነቢያት የተተነበየውን ሊፈጽም፤ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ 117፥25-26 ‹‹በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፡፡›› ብሏል፤ ነቢዩ ዘካርያስም በትንቢቱ በአህያ እንደሚመጣ ተናግሮ ነበር ‹‹የጽዮን ልጅ ሆይ ደስ ይበልሽ ፣ ንጉሥሽ የዋህ ሆኖ በአህያና በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፡፡›› /ዘካ. 9፥9/፡፡ * ጌታችንም ኢየሩሳሌምን ሰላምሽ ዛሬ ነው ሰላሟን አውጆላታል፤ በሌላ አንቀጽም ከተማይቷን እየተመለከተ አልቅሶላታል፡፡(ስለ ሰላምሽ የሚሆነውን አንቺስ ብታውቂ … … ፡፡) /ሉቃ. 19፥24/፡፡ * የተዋረደች እንስሳ (አህያም) በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ሰማያዊ ንጉሥ ክርስቶስ በትሕትናው ዙፋኑ መቀመጫ አደረጋት፤ ሸክም ያቆሰላት፥ ዱላ የሰለቻት፥ ዕረፍት የናፈቃት ‹‹ቀንበሬ ልዝብ፥ ሸክሜ ቀላል ነው›› ያለ ንጉሥ ተቀመጠባት፡፡ #ለምን_የዘንባባ_ዝንጣፊ (ፀበርት)፤ (የቴምር ዛፍ ዝንጣፊና የወይራ ዛፍ ዝንጣፊ) ይዘው #ዘመሩ * በአህያ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባም ደቀ መዛሙርቱና በግራና በቀኝ የነበሩ ሕዝቦችም ‹‹እንኳን አንተ የተቀመጥክባትም አህያ መሬት መርገጥ አይገባትም›› እያሉ ግማሹ ልብሱን፥ ግማሹ የዘንባባ ዝንጣፊ አነጠፉለት፤ ክብሩንና መድኀኒትነቱን ገለጡ፡፡ * አብርሃም ይስሐቅን፣ ይስሐቅ ደግሞ ያዕቆብን በወለዱ ጊዜ፣ እስራኤል ከግብጽ በወጡ ጊዜ፣ ዮዲት ሃገሯን ሊወር የመጣውን ሆሎፎርኒስ የተባለ የአይሁድ ንጉሥ በገደለች ጊዜ ዘንባባ ይዘው አመስግነው ነበር፤ በዚያ ልማድ ጌታችንንም ዘንባባ ይዘው ‹‹ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ፥ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፥ ሆሣዕና በአርያም›› /መዝ. 8፥2፣ ሉቃ. 19፥38/ እያሉ አመሰገኑት፤ ዘመን የተቈጠረለት፥ ምሳሌ የተመሰለለት፥ ትንቢት የተተነበየለት፥ ምሥጢር የተመሠጠረለት የዳዊት ልጅ፤ አምላክ ወልደ አምላክ መሆኑን መሰከሩ፡፡ * አይሁድም ሕፃናት ሲያመሰግኑ ሰምተው በቅንአት በታወረ ልቦናቸው ‹‹ዝም አስብላቸው እንጂ›› አሉት፡፡ ጌታችንም ‹‹ከሕፃናትና ከሚጠቡ አፍ ምስጋና ለራስህ አዘጋጀህ›› /መዝ. 8፥2/ የሚለውን የመጽሐፍ ቃል ጠቅሶ አሳፍሯቸዋል፡፡ በሌላም አንቀጽ ዝም በሉ እያሉ ሊያስቆሙ ሲሞክሩ የቢታንያ ድንጋዮች አፍ አውጥተው አመስግነውታል፤ ይህንንም ተመልክተው አፍረዋል፡፡ * አንድም ዘንባባ እሾኻም ነው የኃይል የድል ምልክት አለህ ሲሉ፤ * አንድም ዘንባባ እሳት ለብልቦ ይተወዋል እንጂ አይበላውም አንተም ባሕርይህ አይመረመርም ሲሉ፤ * አንድም ዘንባባ ረጅም (ልዑል) ነው አንተም ባሕርይህ ልዑል ነው ሲሉ ዘንባባ አንጥፈው ተቀብለውታል፡፡ * አንድም ዘንባባ ደርቆ እንደገና ሕይወት ይዘራል፤ አንተም የደረቀ ሕይወታችንን የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ፤ * ዘንባባ የሰላም ምልክት ነው የሰላም አምልክ ነህ ሲሉ፤ * ዘንባባ የነፃነት ምልክት ነው ከባርነት ነፃ የምታወጣን አንተነህ ሲሉ፡፡ ፠ ከዚህ በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ በዚያ ይሸጡ ይለውጡ የነበሩትን ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት›› ብሎ በመቆጣት የለዋጮችን ገበታ እየገለበጠ አስወጣቸው፡፡ ፠ ይህ በዓል ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዓበይት በዓላት መካከል አንዱ ነው፡፡ እኛም የዕለቱን ክብረ በዓል ሥርዐተ ማኅሌት አቅርበንላችኋል፡፡ ፠ ታሪኩ በነቢያት መጻሕፍትና በአራቱም ወንጌላት ውስጥ ይገኛል፡፡ (ማቴ. 21÷1-17፣ ማር. 11÷ 1-10፣ ሉቃ. 19÷29-38፣ ዮሐ. 12÷12-15)፨ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (#ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን_)፤ #ክፍል፪_ #ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ (ሳኦል የአማሌቃውያንን ምርኮ ባገኘበት ወቅት፣ ሐናንያ ገንዘብ በእጁ በገባበት ወቅት ሰይጣን እንደፈተናቸው ልብ ይሏል /ሐናንያ ሆይ መንፈስ ቅዱስን ታታልል ዘንድ ከመሬቱ ሽያጭ ታስቀር ዘንድ ሰይጣን በልብህ ስለምን ሞላ?፡፡›› ሐዋ. ፭፥፫/ እኛንም እንዲሁ እንደ ዘመናችን ሁኔታ መልኩን እየለዋወጠ ይፈትነናል፡፡ እርሱ የ7511 ዓመታት የመፈተን የሥራ ልምድ ያለው ነውና!!፡፡ ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣውና መጽሐፍ ቅዱስም የተጻፈበት ዐቢይ ጉዳይ ሰይጣን በሰው ልጆች ላይ እያደረሰ ካለው ጉዳትና ጥፋት ለመታደግና ችግሩንም በዝርዝር ለማሳወቅና ሰዎችም የሰይጣንን ክፉ ሥራ ዐውቀው እንዲርቁ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡›› ፩ዮሐ. ፫፥፰/ ‹‹በእኔም የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፡፡›› ዮሐ. ፲፪፥፵፮ ***ነገር ግን ጌታችን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ፤ ሰው በመሆኑ ይህ የሕይወት ብርሃን ለዓለም ቢበራም፤ ሁሉም #ሰው ነፃ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከዲያብሎስ ሽንገላ ለመላቀቅ ፈቃደኛ አለመሆኑን ተመልክቶ /‹‹ወደ ሕይወት የሚወስደው በር የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚገቡትም ጥቂቶች ናቸው፡፡›› ብሏል ማቴ. ፯፥፲፬/ ጌታችን እንዲህ ያለው ሰዎች ነፃ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው የሰይጣንን ፈቃድ በመፈጸም በፈቃደ ሥጋቸው ስለሚመሩና የእርሱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ደስተኛና ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ለመግለጽ እንጂ ወደ ሕይወት የሚወስደው መንገድ የሚጠብ ሁኖ አይደለም፡፡ ይህ የሕይወት መንገድ የሚሰፋው የራስ ፈቃደኝነት ሲታከልበት ነው፡፡ #ለሰው ልጅ ወደ ሕይወት ለመግባት ወሳኙ ነገር ፈቃደኝነት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ቢሆንም የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ነጻ ፈቃድ ያለው አድርጎ ስለፈጠረው መልካሙን ነገር ሊያደርግ በሚፈልግበት ጊዜ ፈቃደኝነታቸው ይጠይቃል፡፡ /ድውያንን ሲፈውስ ልትድን ትወዳለህን እያለ የሚጠይቃቸውን ልብ ይሏል፡፡ ዮሐ. ፭፥፮/ #የራስ ፈቃደኝነት ካለ ትእዛዛትን መጠበቅ ቀላል ይሆናል፡፡ /የዘለዓለምን ሕይወት እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ ብሎ ለጠየቀው ሀብታም ጎልማሳ ‹‹ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ትእዛዛትን ጠብቅ … ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂደህ ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፤ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፡፡›› ነገር ግን ሀብታሙ ጎልማሳ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ታላቅ ሐዘን ተሰምቶታል፡፡ ማቴ. ፲፱፥፳፩/ #ጽድቅ፣ ቅድስናና ሰይጣንን ማሸነፍ የሚመጣው በራስ ፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ #አንድ_ሰው_በፍጹም_ትሕትና_ትእዛዛትን_ለመጠበቅ_የራስ_ፈቃደኝነት_ካለውና_ንስሐ_ከገባ__በቀላሉ_ሰይጣንን_የሚያሸንፍበት_ኀይል_ከእግዚአብሔር_ያገኛል፡፡ ሰይጣንም የብዙ ዘመን ልምድ ስላለው ይህን ሁኔታ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ሰዎች፤ ++ሰዎች ትእዛዛትን ለመጠበቅ የራስ ፈቃደኝነት እንዳይኖራቸው የተለያየ ምክንያት በመፍጠር አጥብቆ ይዋጋቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን ሊጠብቁና ንስሐ ሊገቡ ሲያስቡ በታላቅ ፍርሃትና ስጋት እንዲያዙ ያደርጋቸዋል፡፡ ++ሰዎችን ሕግና ትእዛዛትን መፈጸም ከባድና ጭንቅ፥ በሩም የጠበበ፥ ፈጽሞም የማያሳልፍ አድርጎ ያሳያቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን የሚጠብቁና በቁርጠኝነት ንስሐ የሚገቡ ከሆነ በዚህ ምድር ላይ መኖር እንደማይችሉና ታላቅ ጉዳት እንደሚደርስባቸው ደጋግሞ በማሳሰብና በማስፈራራት ያሳምናቸዋል፡፡ … ነገር ግን በፍጹም ትሕትናና በራስ ፈቃደኝነት ትእዛዙን በመጠበቅና ንስሐ በመግባት ከዚህ ሰይጣናዊ ውጊያ ነጻ ይወጣሉ፤ ነጻ ሲወጡም በሰይጣን አሳሳቢነትና ማስፈራርት ከባድ መስሎ ይታያቸው የነበረው ትእዛዛት ለእነርሱ የደስታና የሰላም ምንጭ ይሆንላቸዋል፡፡ /ይህንንም በሐዋርያትና በቅዱሳንና ቅዱሳት ሕይወት ታውቋል ማቴ. ፲፩፥፳፰/ ከእውነተኛ (መንፈሳዊ) ሕይወት ርቀው የሚኖሩ ሰዎች በጥቂት የፈተና ሰዐት ስንኳ መታገሥና መረጋጋትን፥ ሰላማዊነትንና አስተዋንትን አጥተውና ተስፋ ቆርጠው ለከፋ ችግር የሚጋለጡት አስቀድሞ የጠጠጋቸው ሰይጣናዊ መንፈስ ስለሚያስጨንቃቸውና ስለሚያስፈራራቸው ነው፡፡ #የሰው ልጅ በምድር ላይ እስካለ ድረስ በጥንተ ጠላቱ ሰይጣን በየጊዜው መፈተኑ አይቀሬ በመሆኑ /ዘፍ. ፫፥፲፭/ ውጊያውም ከደምና ከሥጋ ጋር ሳይሆን ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ ከአለቆችና ከሥልጣናት እንዲሁም ከረቂቃን ሰይጣናት ከዲያብሎስ ሠራዊት ጋር በመሆኑ፤ ፈተናውን ለማለፍ የሰይጣን መግቢያ የሆኑ ቀዳዳዎችን ለመድፈን እንዲያስችለው መንፈሳዊ ዝግጅት ማድረግ አለበት፡፡ ከኃጢአት ንጹሕ ሁኖ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ያደርግ ዘንድ ስለሰይጣን አስከፊነት በእጅጉ መማርና ማወቅ፥ መረዳትና ማስተዋል ይገባዋል፡፡ +‹‹ከሚመጣው ሁሉ መዳን ትችሉ ዘንድና በሰው ልጅ ፊትም ለመቆም እንድትችሉ ሁል ጊዜ በጸሎት ትጉ፡፡›› ሉቃ. ፳፩፥፮ +‹‹ለጸሎት ትተጉ ዘንድ … ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ፡፡›› ፩ቆሮ. ፯፥፭ +‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡›› ኤፌ. ፮፥፲፩ +‹‹በመጠን ኑሩ፥ ንቁም ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፡፡›› ፩ጴጥ. ፭፥፰ +‹‹በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፤ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት፡፡›› ኤፌ. ፬፥፳፯ #አንድ ሰው ካመነና ከተጠመቀ በኋላ ስለሰይጣን ክፋትና ተንኮል ጥልቅ እውቀት ከሌለውና በመንፈሳዊ ትሩፋት የማይተጋ ከሆነ በቀላሉ ተመልሶ በሰይጣን አገዛዝ ሥር ይወድቃል፡፡ ከዚያ በኋላም ሕይወቱ በእጅጉ የከፋ ይሆንበታል፡፡ /‹‹ርኩስ መንፈስ ከሰው ከወጣ በኋላ ዕረፍት ለማድረግ ፈልጎ ውኃ ወደሌለበት ምድረ በዳ ይዞራል፤ አያገኝም፡፡ ከዚህም በኋላ እንግዲህስ ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፡፡ በመጣም ጊዜ ባዶ ሁኖ ተጠርጎና ተጊጦ ያገኘዋል፤ ከዚህም በኋላ ይሄዳል፤ ከእርሱም የሚከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትን ያመጣል፤ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው የኋላ ኑሮው ከፊተኛው የከፋ ይሆናል፡፡›› ማቴ. ፲፪፥፵፫ ‹‹በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርሷ ተጠልፈው ከተሸነፉ ከፊተኛው ኑሯቸው ይልቅ የኋለኛው ኑሯቸው የባሰና የከፋ ይሆንባዋቸዋል፡፡›› ፪ጴጥ. ፪፥፳/፡፡ ሰዎች ዳግመኛ በሰይጣን ሽንገላ ተታለው በዓለም ርኵሰት እንዳይወድቁ የሚረዳ እውቀት ማግኛ የሚሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብና ማወቅ እንዲረዳ መምህረ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ፲፭፥፬ ላይ .. መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፏልና ብሎ እንደተናገረው፤ ርዕሰ ባሕታውያውን ቀሲስ ቅዱስ አባ ጳውሊ ከሰይጣን ጋር ያደረገውን ምልልስ ከብራና ገልብጠው ከግእዝ ወደ አማርኛ የሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም አሳተመው፡፡ #ቀሲስ_ጳውሊ_ወደ_ጭፈራ_ቤት_የሚሄዱትን_ሰዎች_የሚያስተውን_ሰይጣን_በዙ_ጥያቄዎችን_ሊጠይቀው_እንደገዘተው፤ #ሰይጣን_ሰዎችን_እንዴት_እንደሚፈትንና_ኃይል_እንዴት_እንደሚያገኝ_፤ #ክፍል_፫ _.… #ይቀጥላል_ይጠብቁን_/

#በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

#በየቀኑ_እስከ_በዓለ_ትንሣኤ_የሚቀርብ #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (#ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን_)፤ #ክፍል፪_ #ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ (ሳኦል የአማሌቃውያንን ምርኮ ባገኘበት ወቅት፣ ሐናንያ ገንዘብ በእጁ በገባበት ወቅት ሰይጣን እንደፈተናቸው ልብ ይሏል /ሐናንያ ሆይ መንፈስ ቅዱስን ታታልል ዘንድ ከመሬቱ ሽያጭ ታስቀር ዘንድ ሰይጣን በልብህ ስለምን ሞላ?፡፡›› ሐዋ. ፭፥፫/ እኛንም እንዲሁ እንደ ዘመናችን ሁኔታ መልኩን እየለዋወጠ ይፈትነናል፡፡ እርሱ የ7511 ዓመታት የመፈተን የሥራ ልምድ ያለው ነውና!!፡፡ ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣውና መጽሐፍ ቅዱስም የተጻፈበት ዐቢይ ጉዳይ ሰይጣን በሰው ልጆች ላይ እያደረሰ ካለው ጉዳትና ጥፋት ለመታደግና ችግሩንም በዝርዝር ለማሳወቅና ሰዎችም የሰይጣንን ክፉ ሥራ ዐውቀው እንዲርቁ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡›› ፩ዮሐ. ፫፥፰/ ‹‹በእኔም የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፡፡›› ዮሐ. ፲፪፥፵፮ ***ነገር ግን ጌታችን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ፤ ሰው በመሆኑ ይህ የሕይወት ብርሃን ለዓለም ቢበራም፤ ሁሉም #ሰው ነፃ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከዲያብሎስ ሽንገላ ለመላቀቅ ፈቃደኛ አለመሆኑን ተመልክቶ /‹‹ወደ ሕይወት የሚወስደው በር የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚገቡትም ጥቂቶች ናቸው፡፡›› ብሏል ማቴ. ፯፥፲፬/ ጌታችን እንዲህ ያለው ሰዎች ነፃ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው የሰይጣንን ፈቃድ በመፈጸም በፈቃደ ሥጋቸው ስለሚመሩና የእርሱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ደስተኛና ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ለመግለጽ እንጂ ወደ ሕይወት የሚወስደው መንገድ የሚጠብ ሁኖ አይደለም፡፡ ይህ የሕይወት መንገድ የሚሰፋው የራስ ፈቃደኝነት ሲታከልበት ነው፡፡ #ለሰው ልጅ ወደ ሕይወት ለመግባት ወሳኙ ነገር ፈቃደኝነት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ቢሆንም የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ነጻ ፈቃድ ያለው አድርጎ ስለፈጠረው መልካሙን ነገር ሊያደርግ በሚፈልግበት ጊዜ ፈቃደኝነታቸው ይጠይቃል፡፡ /ድውያንን ሲፈውስ ልትድን ትወዳለህን እያለ የሚጠይቃቸውን ልብ ይሏል፡፡ ዮሐ. ፭፥፮/ #የራስ ፈቃደኝነት ካለ ትእዛዛትን መጠበቅ ቀላል ይሆናል፡፡ /የዘለዓለምን ሕይወት እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ ብሎ ለጠየቀው ሀብታም ጎልማሳ ‹‹ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ትእዛዛትን ጠብቅ … ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂደህ ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፤ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፡፡›› ነገር ግን ሀብታሙ ጎልማሳ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ታላቅ ሐዘን ተሰምቶታል፡፡ ማቴ. ፲፱፥፳፩/ #ጽድቅ፣ ቅድስናና ሰይጣንን ማሸነፍ የሚመጣው በራስ ፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ #አንድ_ሰው_በፍጹም_ትሕትና_ትእዛዛትን_ለመጠበቅ_የራስ_ፈቃደኝነት_ካለውና_ንስሐ_ከገባ__በቀላሉ_ሰይጣንን_የሚያሸንፍበት_ኀይል_ከእግዚአብሔር_ያገኛል፡፡ ሰይጣንም የብዙ ዘመን ልምድ ስላለው ይህን ሁኔታ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ሰዎች፤ ++ሰዎች ትእዛዛትን ለመጠበቅ የራስ ፈቃደኝነት እንዳይኖራቸው የተለያየ ምክንያት በመፍጠር አጥብቆ ይዋጋቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን ሊጠብቁና ንስሐ ሊገቡ ሲያስቡ በታላቅ ፍርሃትና ስጋት እንዲያዙ ያደርጋቸዋል፡፡ ++ሰዎችን ሕግና ትእዛዛትን መፈጸም ከባድና ጭንቅ፥ በሩም የጠበበ፥ ፈጽሞም የማያሳልፍ አድርጎ ያሳያቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን የሚጠብቁና በቁርጠኝነት ንስሐ የሚገቡ ከሆነ በዚህ ምድር ላይ መኖር እንደማይችሉና ታላቅ ጉዳት እንደሚደርስባቸው ደጋግሞ በማሳሰብና በማስፈራራት ያሳምናቸዋል፡፡ … ነገር ግን በፍጹም ትሕትናና በራስ ፈቃደኝነት ትእዛዙን በመጠበቅና ንስሐ በመግባት ከዚህ ሰይጣናዊ ውጊያ ነጻ ይወጣሉ፤ ነጻ ሲወጡም በሰይጣን አሳሳቢነትና ማስፈራርት ከባድ መስሎ ይታያቸው የነበረው ትእዛዛት ለእነርሱ የደስታና የሰላም ምንጭ ይሆንላቸዋል፡፡ /ይህንንም በሐዋርያትና በቅዱሳንና ቅዱሳት ሕይወት ታውቋል ማቴ. ፲፩፥፳፰/ ከእውነተኛ (መንፈሳዊ) ሕይወት ርቀው የሚኖሩ ሰዎች በጥቂት የፈተና ሰዐት ስንኳ መታገሥና መረጋጋትን፥ ሰላማዊነትንና አስተዋንትን አጥተውና ተስፋ ቆርጠው ለከፋ ችግር የሚጋለጡት አስቀድሞ የጠጠጋቸው ሰይጣናዊ መንፈስ ስለሚያስጨንቃቸውና ስለሚያስፈራራቸው ነው፡፡ #የሰው ልጅ በምድር ላይ እስካለ ድረስ በጥንተ ጠላቱ ሰይጣን በየጊዜው መፈተኑ አይቀሬ በመሆኑ /ዘፍ. ፫፥፲፭/ ውጊያውም ከደምና ከሥጋ ጋር ሳይሆን ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ ከአለቆችና ከሥልጣናት እንዲሁም ከረቂቃን ሰይጣናት ከዲያብሎስ ሠራዊት ጋር በመሆኑ፤ ፈተናውን ለማለፍ የሰይጣን መግቢያ የሆኑ ቀዳዳዎችን ለመድፈን እንዲያስችለው መንፈሳዊ ዝግጅት ማድረግ አለበት፡፡ ከኃጢአት ንጹሕ ሁኖ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ያደርግ ዘንድ ስለሰይጣን አስከፊነት በእጅጉ መማርና ማወቅ፥ መረዳትና ማስተዋል ይገባዋል፡፡ +‹‹ከሚመጣው ሁሉ መዳን ትችሉ ዘንድና በሰው ልጅ ፊትም ለመቆም እንድትችሉ ሁል ጊዜ በጸሎት ትጉ፡፡›› ሉቃ. ፳፩፥፮ +‹‹ለጸሎት ትተጉ ዘንድ … ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ፡፡›› ፩ቆሮ. ፯፥፭ +‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡›› ኤፌ. ፮፥፲፩ +‹‹በመጠን ኑሩ፥ ንቁም ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፡፡›› ፩ጴጥ. ፭፥፰ +‹‹በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፤ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት፡፡›› ኤፌ. ፬፥፳፯ #አንድ ሰው ካመነና ከተጠመቀ በኋላ ስለሰይጣን ክፋትና ተንኮል ጥልቅ እውቀት ከሌለውና በመንፈሳዊ ትሩፋት የማይተጋ ከሆነ በቀላሉ ተመልሶ በሰይጣን አገዛዝ ሥር ይወድቃል፡፡ ከዚያ በኋላም ሕይወቱ በእጅጉ የከፋ ይሆንበታል፡፡ /‹‹ርኩስ መንፈስ ከሰው ከወጣ በኋላ ዕረፍት ለማድረግ ፈልጎ ውኃ ወደሌለበት ምድረ በዳ ይዞራል፤ አያገኝም፡፡ ከዚህም በኋላ እንግዲህስ ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፡፡ በመጣም ጊዜ ባዶ ሁኖ ተጠርጎና ተጊጦ ያገኘዋል፤ ከዚህም በኋላ ይሄዳል፤ ከእርሱም የሚከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትን ያመጣል፤ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው የኋላ ኑሮው ከፊተኛው የከፋ ይሆናል፡፡›› ማቴ. ፲፪፥፵፫ ‹‹በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርሷ ተጠልፈው ከተሸነፉ ከፊተኛው ኑሯቸው ይልቅ የኋለኛው ኑሯቸው የባሰና የከፋ ይሆንባዋቸዋል፡፡›› ፪ጴጥ. ፪፥፳/፡፡ ሰዎች ዳግመኛ በሰይጣን ሽንገላ ተታለው በዓለም ርኵሰት እንዳይወድቁ የሚረዳ እውቀት ማግኛ የሚሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብና ማወቅ እንዲረዳ መምህረ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ፲፭፥፬ ላይ .. መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፏልና ብሎ እንደተናገረው፤ ርዕሰ ባሕታውያውን ቀሲስ ቅዱስ አባ ጳውሊ ከሰይጣን ጋር ያደረገውን ምልልስ ከብራና ገልብጠው ከግእዝ ወደ አማርኛ የሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም አሳተመው፡፡ #ቀሲስ_ጳውሊ_ወደ_ጭፈራ_ቤት_የሚሄዱትን_ሰዎች_የሚያስተውን_ሰይጣን_በዙ_ጥያቄዎችን_ሊጠይቀው_እንደገዘተው፤ #ሰይጣን_ሰዎችን_እንዴት_እንደሚፈትንና_ኃይል_እንዴት_እንደሚያገኝ_፤ #ክፍል_፫ _.… #ይቀጥላል_ይጠብቁን_/

‹‹#መሐረነ_አብ (#የምሕላ_ጸሎት)፤ #በግእዝና_በአማርኛ፡፡ (በድምፅ ከፈለጋችሁ በቴሌግራምና (https://t.me/medihanaelem) በዩቲዩብ ገጻችን https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w ያገኛሉ፡፡ ፠ ‹‹ሳታቋርጡ ጸልዩ›› እንዳለ ቅዱ ጳውሎስ በ፩ኛ ተሰ. ፭፥፲፯ ጌታችንም ‹‹ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ›› ማቴ ፳፬፥፬ ብሎ አርአያ ሆኖ እንዳስተማረን፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ከምንገለገልባቸው ጸሎቶች አንዱና ዋነኛው ‹‹መሐረነ አብ›› ጸሎት ነው፡፡ ፠ መሐረነ አብ የሚወለውን ስያሜውን ያገኘው ጸሎቱ ሲጀምር ‹‹መሐረነ አብ፥ መሐረነ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ መሐሪ ተዘከረነ በሣህልከ፡፡›› (አብ ሆይ ማረን፥ ወልድ ሆይ ይቅር በለን፥ ይቅር ባይ መንፈስ ቅዱስ ሆይ በይቅርታህ አስበን) ብሎ ስለሚጀምር ነው፡፡ ፠ የመሐረነ አብ ጸሎትን ያዘጋጀው ከ40 መጻሕፍት በላይን የደረሰውና ካልዓይ ቅዱስ ያሬድ ፥ ካልዓይ ቄርሎስ የተባለው ቅዱሱ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ ነው፡፡ ሲያዘጋጀውም ከተለያዩ ቅዱሳት መጻሕፍትና እንደ ቅዱስ ያሬድ ካሉ ሊቃውንት ድርሰቶች ኀይለ ቃላት ያላቸውንና ለጸሎት ተስማሚ የሆኑ ቃላትን እንደ ንብ ቀስሞ ነው ያዘጋጀው፡፡ ፠ ቅዱሱ ያዘጋጀውም በመጽሐፈ ሰዐታት ድርሰቱ ላይ በስተመጨረሻ ከኪዳን በፊት እንዲደረስ አድርጎ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ከዓመት እስከ ዓመት በየዕለቱ ኪዳን በሚደርስባቸው ማንኛውም የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክንና ገዳማት ‹‹የመሐረነ አብ ጸሎት››ም ከኪዳን በፊት ይደርሳል፡፡ ፠ የመሐረነ አብ ጸሎት ከኪዳን በፊት ብቻ ሳይሆን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት በዋይዜማው የሚደርስ፣ ለግል ጸሎት፣ ረሃብ ጦርነት፥ አባር ቸነፈር፥ ተስሕቦና ወረረሽኝ በሽታ በመጣ ወቅት የሚደረስ ሲሆን ከእግዚኦታ ጋር አብሮ ስለሚባልም ‹‹የምሕላ ጸሎት›› በመባልም ይጠራል፡፡ ፠ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ በ14ኛው ክፍለ ዘመን ‹‹መሐረነ አብ››ን ከደረሰው በኋላ የተነሡ ቅዱሳንንና አባ ጊዮርጊስ ያላካተታቸውን በየጊዜው የተነሡ ሊቃውንት አካትተውታል፤ (ነገር ግን ሊቃውንቱ አሻሽለው ያዘጋጁት‹‹የመሐረነ አብ›› ጸሎት የሚደርሰው በታላላቅ ገዳማትና አድባራት ነው፡፡ ፠ የጸሎቱ አደራረስም በመሪና በተመሪ (በቀኝና በግራ) በተራ ስለሆነ በጋራ የሚጸለይና ዜማው የሚመስጥ፤ የቃሉ አሰዳደርም የሚያስደንቅ፤ የያዘው ኀይለ ቃል እንባን የሚያስነባ ነው፡፡ በተለይም በገዳም ያሉ አባቶች በጋራ(በማኅበር)ና በግል ጸሎት ዕለት ዕለት ያደርሱታል፡፡ ፠ በዓለማችን የተከሰተውን የ‹‹ኮሮና ቫይረስ›› የተስሕቦ በሽታ ከሃገራችንና ከዓለማችን እንዲያርቅልን የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ጕባኤ ለሃገራችን ለ1 ወር ያህል (ከመጋቢት 29 - ሚያዝያ 29) ድረስ ጸሎት እንዲደረግ ባስተላለፈው ጥሪ መሠረት፤ ቤተ ክርስቲያናችንም ዘወትር ማታ ከ3-4 ሰዐት የመሐረነ አብ ጸሎት እያደረሰች ትገኛለች፡፡ ፠እኛም በመደበኛ የሚጸለየውን ‹‹የመሐረነ አብ›› ጸሎት በግእዝና በአማርኛ አዘጋጅተንላችኋል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w