fa
Feedback
EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

رفتن به کانال در Telegram

This is official telegram chanel of Ethiopian football federation refereeing department.

نمایش بیشتر
1 668
مشترکین
+324 ساعت
+47 روز
-1130 روز
آرشیو پست ها
የሀዘን መግለጫ ! የጨዋታ ታዛቢ (ኮሚሽነር) አበራ ቡፌቦ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ኮሚሽነር አበራ ቡፌቦ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሚያዘጋጃቸው የተለያዩ ውድድሮች በጨዋታ አመራርነት እ
የሀዘን መግለጫ ! የጨዋታ ታዛቢ (ኮሚሽነር) አበራ ቡፌቦ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ኮሚሽነር አበራ ቡፌቦ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሚያዘጋጃቸው የተለያዩ ውድድሮች በጨዋታ አመራርነት እና ኮሚሽነርነት ለረጅም ጊዜያት በማገልገል አሳልፈዋል። የኮሚሽነር አበራ ቡፌቦ ሥርዓተ ቀብር በነገው እለት ሰኔ 10 በሺንሺቾ ከተማ ቃለ ህይወት ቤተ-ክርስቲያን ከቀኑ 7፡00 ይፈፀማል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኮሚሸነር አበራ ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰብ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለእግር ኳስ ቤተሰብ እና ለሙያ ባልደረቦች መፅናናትን ይመኛል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል - አድሃ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ ! ኢድ ሙባረክ ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል - አድሃ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ ! ኢድ ሙባረክ ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የሀዘን መግለጫ ! የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች፣ ዓለም አቀፍ ዳኛ እና አመራር የነበሩት አንጋፋው የእግር ኳስ ሰው ጌታቸው ገብረማርያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ጌታቸው ገብረማርያ
የሀዘን መግለጫ ! የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች፣ ዓለም አቀፍ ዳኛ እና አመራር የነበሩት አንጋፋው የእግር ኳስ ሰው ጌታቸው ገብረማርያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ጌታቸው ገብረማርያም በተጫዋችነት ለኦሜድላ እና ጥጥ ማኅበር እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫውተው ያሳለፉ ሲሆን በመቀጠል ለረጅም ዘመናት በዓለም አቀፍ ዳኝነት ጭምር በሚታወቁበት የዳኝነት ሙያ አገልግለዋል። ከዳኝነት ከተገለሉ በኋላም በኮምሽነርነት፣ በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትነት እንዲሁም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች በጥቅሉ ከ60 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ላይ በማገልገል አሳልፈዋል። የአቶ ጌታቸው ገብረማርያም ሥርዓተ ቀብር በነገው ዕለት በአማኑኤል ቤተ-ክርስቲያን ከቀኑ 9፡00 ይፈፀማል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በእኚህ ታላቅ የእግር ኳስ ሰው ጌታቸው ገብረማርያም ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰብ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለእግር ኳስ ቤተሰብ እና ለሙያ ባልደረቦች መፅናናትን ይመኛል።

ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ85ኛው የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልካም በዓል !
ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ85ኛው የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልካም በዓል !

ለU20 ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ አመራሮች የተስተካከለ ⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️ የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይ ጨዋታ ለመምራት የአካል ብቃት ፈተና ወስዳችሁ ማለፍ ያልቻላችሁ እና በተለያየ ጊዜ የፌዴራል ዳኝነት ስልጠና ወስዳችሁ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሊጎች ያልተቀላቀላችሁ ዳኞች የአካል ብቃት ፈተና የሚሰጠው 19/08/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም በመሆኑ የጤና የምርመራ ውጤት ይዛችሁ በመምጣት ለባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን ከ1፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና ስለሚሰጥ በተገለፀው አግባብ ራሳችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትገኙ እናሳውቃለን። ማስታወሻ - የፈተናው አይነትYOYO intermittent, RSA እንዲሁም CODA መሆኑን እንገልፃለን። ለአዲስ ፌደራል ዳኞች እድሜ አንዱ መመዘኛ ነው። 👇👇👇👇👇 “ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

ለወንዶች ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ አመራሮች ⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️ የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይ ጨዋታ ለመምራት የአካል ብቃት ፈተና ወስዳችሁ ማለፍ ያልቻላችሁ እና በተለያየ ጊዜ የፌዴራል ዳኝነት ስልጠና ወስዳችሁ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሊጎች ያልተቀላቀላችሁ ዳኞች የአካል ብቃት ፈተና የሚሰጠው 19/08/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም በመሆኑ የጤና የምርመራ ውጤት ይዛችሁ በመምጣት ለባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን ከ1፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና ስለሚሰጥ በተገለፀው አግባብ ራሳችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትገኙ እናሳውቃለን። ማስታወሻ - የፈተናው አይነትYOYO intermittent, RSA እንዲሁም CODA መሆኑን እንገልፃለን 👇👇👇👇👇 “ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! መልካም በዓል ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! መልካም በዓል ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የሀዘን መግለጫ ! በኢትዮጵያ እግር ኳስ ለረጅም ጊዜያት በዳኝነት እንዲሁም በአሁኑ ወቅት በሴቶች ፕሪምየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ውድድሮች ላይ በጨዋታ ታዛቢነት ሲያገለገሉ የቆዩት በቀለ ወልደ
የሀዘን መግለጫ ! በኢትዮጵያ እግር ኳስ ለረጅም ጊዜያት በዳኝነት እንዲሁም በአሁኑ ወቅት በሴቶች ፕሪምየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ውድድሮች ላይ በጨዋታ ታዛቢነት ሲያገለገሉ የቆዩት በቀለ ወልደጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በጨዋታ ታዛቢ በቀለ ወልደጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰብ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለእግር ኳስ ቤተሰብ እና ለሙያ ባልደረቦች መፅናናትን ይመኛል።

ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! ኢድ ሙባረክ ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! ኢድ ሙባረክ ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የአካል ብቃት ምዘና ጥሪን ይመለከታል ⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️ የወንዶች እና ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ፥ ወንዶች እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ እንዲሁም የሊግ አንድ የጨዋታ አመራሮች ሁናችሁ ከዚህ በፊት የተሰጠውን ሁለተኛ ዙር ፈተና ማለፍ ያልቻላችሁ እና በተለያዬ ምክንያት ለፈተና መምጣት ያልቻላችሁ ብቻ በድጋሚ ምዘና የሚሰጠው ሐሙስ በ24/07/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም ሁለተኛ ዙር ምዝና ጊዜ ያልተገኛችሁ የጤና የምርመራ ውጤት ይዛችሁ በመምጣት ለባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን 1፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና ለመውሰድ ራሳችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትገኙ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያለፈተናው የሚመጡትን የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 “አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለታላቁ የዓድዋ ድል 130ኛ ዓመት ክብረ በዓል አደረሳችሁ ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለመላው ኢትዮጵያውያን መልካም በዓል ይመኛል።
ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለታላቁ የዓድዋ ድል 130ኛ ዓመት ክብረ በዓል አደረሳችሁ ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለመላው ኢትዮጵያውያን መልካም በዓል ይመኛል።

የሀዘን መግለጫ ! በኢትዮጵያ እግር ኳስ በዳኝነት ለረጅም ጊዜያት ያገለገለው አፈወርቅ አድማሱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ከ25 ዓመታት በላይ በፌዴራል ዳኝነት ያገለገለው አፈወርቅ አድማሱ ሥርዓተ
የሀዘን መግለጫ ! በኢትዮጵያ እግር ኳስ በዳኝነት ለረጅም ጊዜያት ያገለገለው አፈወርቅ አድማሱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ከ25 ዓመታት በላይ በፌዴራል ዳኝነት ያገለገለው አፈወርቅ አድማሱ ሥርዓተ ቀብር በዛሬው እለት በሀዋሳ ሥላሴ ቤተ-ክርስቲያን ከቀኑ 9፡00 ላይ ይፈፀማል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በእግር ኳስ ዳኛ አፈወርቅ አድማሱ ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰብ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለእግር ኳስ ቤተሰብ እና ለሙያ ባልደረቦቹ መፅናናትን ይመኛል።

የስልጠና ጥሪን ይመለከታል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጋር በመተባበር ተተኪዎችን ለማብቃት ያለመ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል። በመሆኑም ስማችሁ በዝርዝሩ የተጠቀ
የስልጠና ጥሪን ይመለከታል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጋር በመተባበር ተተኪዎችን ለማብቃት ያለመ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል። በመሆኑም ስማችሁ በዝርዝሩ የተጠቀሰ የጨዋታ አመራሮች ከሰኞ የካቲት 16 እስከ 20/2018 ዓ/ም ለሚሰጠው ስልጠና የተመረጣችሁ ስለሆነ በመጭው እሁድ ማለትም የካቲት 15/2018 ዓ/ም አዲስ አበባ በመምጣት ካዛንቺስ በሚገኘው ጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል ከቀኑ 10:00 ላይ ተገኝታችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን። ለስልጠናው ስትመጡ አስፈላጊ የዳኝነት ቁሳቁሶችን ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኃል። "ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች እንዲፈጠሩ እንሰራለን"

What Mr. Pierluigi Collina is says about referees mistakes is so far interesting........

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሽልማት በተለያዩ ምክንያቶች ሳይከናወን ዘግይቶ የነበረው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ሽልማት የ2017 የውድድር ዓመት ምርጦችን ዕውቅና የመስጠት መርሐ ግብር ማክሰኞ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሽልማት በተለያዩ ምክንያቶች ሳይከናወን ዘግይቶ የነበረው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ሽልማት የ2017 የውድድር ዓመት ምርጦችን ዕውቅና የመስጠት መርሐ ግብር ማክሰኞ የካቲት 17/2018 እንዲካሄድ ተወስኗል። በሐርመኒ ሆቴል በሚካሄደው የሽልማት መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ፣ የወንዶች ከፍተኛ ሊግ፣ የሴቶች ከፍተኛ ሊግ፣ የሊግ አንድ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ ኮከብ ተጫዋች፣ ኮከብ አሰልጣኝ፣ ኮከብ ግብጠባቂ፣ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ እንዲሁም ምስጉን ዳኛ እና ረዳት ዳኛ ሽልማት የሚበረከትላቸው ይሆናል።